ch
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

前往频道在 Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

显示更多
2 926
订阅者
+3224 小时
+3727 天
+36630 天
帖子存档
#ዜና እስር ኦህዴድ መራሹ የእኩይ አህመድ አገዛዝ የብልጽግና ስብስብ በተለያዩ የአርማጭሆ ቀጠናወች የፋኖ ቤተሰብ ናቸው የሚላቸውን እና ከፋኖ ጋር ትደዋወላላችሁ በሚል በሬ ወለድ የሐሰት መረጃ ንጹሃ
+1
#ዜና እስር ኦህዴድ መራሹ የእኩይ አህመድ አገዛዝ የብልጽግና ስብስብ በተለያዩ የአርማጭሆ ቀጠናወች የፋኖ ቤተሰብ ናቸው የሚላቸውን እና ከፋኖ ጋር ትደዋወላላችሁ በሚል በሬ ወለድ የሐሰት መረጃ ንጹሃን ዜጎችን እያፈሰ ወደ ማጎሪያ ቤት እያስገባቸው መሆኑን ቀኘ መረጃውን አድርሶናል:: ማዕከላዊ አርማጭሆ ወረዳ ማሰሮ ደንብ ተሰግስጎ የሚገኘው እና በደስታው አለባቸው የሚመራው ዘራፊ ቡድን የህዝባች መሬት ከመዝረፉ በተጨማሪ ከፈጣሪ በታች የህዝባችን ሀኪም የሆነውን ዶ/ር በሪሁን አደራጀውን ጨምሮ በርካታ ሴት እና ወንዶችን ወደ ማጎሪያ ቤት ማስገባቱ ተሰምቷል:: ዶ/ር በሪሁን አደራጀው የአርበኛ መከታው አደራጀው ወንድም ሲሆን ያደገበትን ማህበረሰብ ለማገልገል ማሰሮ ደንብ ከተማ መለስተኛ ክሊኒክ ከፍቶ ያለ እረፍት ሌት ከቀን ህዝባችን እያከመ የሚገኝ እንቁ ዶ/ር ሲሆን ወንድምህ ፋኖ ነው በማለት ዛሬ ነሐሴ 12/2018 ዓ.ም ከምሽቱ 1:00 አካባቢ ከሚሰራበት ቦታ በአጥቦ አይለብሴው የብልጽግና ገረድ መኳንንት በሚባል ሚሊሻ ወደ ጣቢያ መወሰዱን የመረጃ ምንጮቻችን ነግረውናል:: የህዝባችን መድሃኒት ዶክተሩን ፍቱት! ፍትህ ለተገፋው ህዝባችን! ድል ለፋኖ ሀይላችን! ክብር ለሰማዕታት! ነሐሴ 12/2018 ዓ.ም መረጃወን ያደረሰን ፦ ዘመቻ ሰማዕታት

ሰበር ዜና! በዋግኽምራ ግንባር 14ኛ (ኃይሉ ከበደ) ክፍለጦር ጠላትን በመደምሰስ ብሬን እና በርካታ ክላሽ ማረከች! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) 1ኛ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር 14ኛ (ኃይሉ ከበደ) ክፍለጦር ፋኖዎች በሦስት አቅጣጫ ማለትም በዋግኽምራ ዞን የጠላት 38ኛ ክፍለ ጦር ከላልኪው፣ 39ኛ ክፍለ ጦር ከአስከተማ በዲውና እና ከአዚላ የመጣውን የብልፅግና መከላከያ ሰራዊት ዋልካው ከሚባል ቦታ ክንደ ነበልባሎቹ ድባቅ መትተውታል። በዚህ አዉደዉጊያ አንድ ብሬን፣ 26 ክላሽንኮቭ መሳሪያ፣ 5 ምርኮኛ፣ 15 ቦምብ፣ 12 ትጥቅ፣ 25 ካዝና፣ 9 ወታደራዊ ሻንጣ፣ 1100 የክላሽ ተተኳሽ፣ 1800 የብሬን ተተኳሽ በምርኮ የተገኘ ሲሆን እና ከ50 በላይ የጠላት ሀይል ተደምስሷል። ​የፋኖወች ምት መቋቋም ያቃተው የጠላት ኃይል መድፍ በዘፈቀደ በማስወንጨፍ በአካባቢው የንጹሃን አርሶ አደሮችን ንብረት ሲያወድም ሴቶችና ህፃናት ላይ ጥቃት ማድረሱና የህዝብ ንብረት ሲዘርፍ ዉሏል ሲል የ303ኛ አሳምነዉ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃዉን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን 1ኛ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ! ነሃሴ 13/2018 ዓ.ም

ሰበር የድል ዜና!! ጀብደኞቹ 206ኛ ኮር በጠዋቱ ተዓምር ሰርተዋል ነሐሴ 13/2018 ዓ.ም አፋብን ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ጀብደኞቹ 24ኛ ክ/ጦርና 14ኛ ክ/ጦር በመቀናጀት
+1
ሰበር የድል ዜና!! ጀብደኞቹ 206ኛ ኮር በጠዋቱ ተዓምር ሰርተዋል ነሐሴ 13/2018 ዓ.ም አፋብን ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ጀብደኞቹ 24ኛ ክ/ጦርና 14ኛ ክ/ጦር በመቀናጀት ከደብረማርቆስ በቅርብ ርቀት ላይ በምትገኘው አገዛዙ መሽጎባት ትገኝ ከነበረው ደብረዘይት ከተባለ ቦታ ላይ የአገዛዙን ዙፋን አስጠባቂ ቅጥረኛ ዘራፊ ኃይል ሙሉ በሙሉ በመደምሰስ የተለመደ ገድላቸውን በዛሬው ዕለት ደግመውታል። 24ኛ ክ/ጦር ስናን አባጅሜ ሻለቃ በፋኖ የትግል እንቅስቃሴ ከተበሰረበት ጊዜ ጀምሮ በተደጋጋሚ ወደ ስናን እና አካባቢው ቀጠና ያመራን ወራሪ ጠላት ሰልቅጣ በመብላት ና በመደምሰስ የምትታወቅ ምትሀተኛ ሻለቃ ስትሆን በዛሬው ዕለትም ከክንደ ነበልባሏ 14ኛ ክ/ጦር ጋር በመቀናጀት የተለመደ ጀብዷን ፈፅማለች።። አለ ነገር Dave Amhara

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ 1ኛ ምኒልክ ዕዝ ዋና ወታደራዊ አማካሪ ኮረኔል ሞገስ ዘገዬ፣ አሁን በሥልጣን ላይ ያለው የብልፅግና አገዛዝ ከቀደመው የደርግ ሥርዓት ጋር ፍጹም መመሳሰሉን ገልጸው፣ የአገዛዙን ፀረ-ሕዝብ አካሄድ ለመግታትና ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚደረገው ትግል ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቁ። ​ኮረኔል ሞገስ በወቅታዊ ሀገራዊ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ሁኔታዎች ዙሪያ ባሰፈሩት ጽሑፍ፣ በብሔር ስም የተደራጁ የፖለቲካ ሆድ-አደሮች ሕዝብን ለከፍተኛ መከራ ዳርገዋል ብለዋል። በተለይም በሁለቱ ሕዝቦች መካከል የጋራ ውይይትና ሰላማዊ የመፍትሔ በሮች እንዳይከፈቱ በማድረግ አገሪቱን ወደ አሰቃቂ ደም መፋሰስ መሪዎቿ ማድረጋቸውን ጠቁመዋል። ​የመከላከያ ሰራዊቱን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት፣ የስርዓቱ ዙፋን ጠባቂ የሆነው ሠራዊት ለድሃ ልጅ ደንታ በሌለው አገዛዝ እየተገፋፋ በየገደሉና በየጫካው ሲረግፍ፣ ይፋዊ የሕዝብ ወገንተኝነት ያለውና ያለ ደሞዝ ለነፃነት የሚታገለው የፋኖ ኃይል ግን የአገዛዙን ሰራዊት በማማረክና መዋቅሩን በመበታተን ላይ ይገኛል ብለዋል። ​በወታደራዊ ሳይንስ የታወቁትን አምስቱን የውጊያ ዓይነቶች (የመከላከል፣ የመመለስ፣ የማጥቃት፣ የደፈጣ እና የከተማ ውጊያ) ፋኖ በጥራትና በከፍተኛ ዲሲፕሊን በመተግበር ላይ መሆኑን አንስተው፤ በሽምቅ ውጊያ ስልቱ የአገዛዙን የጦር ማሽነሪ ኢላማ በማድረግ ከፍተኛ ድል እያናጸፈ መሆኑን አብራርተዋል። ​በሌላ በኩል በሀገሪቱ ከአስር በላይ የነፃነት ግንባሮች መፈጠራቸው አገዛዙ የደረሰበትን የፖለቲካ ከሰረና የመዋቅር መፈራረስ እንደሚያሳይ የገለጹት ኮረኔል ሞገስ፣ በጂኦ-ፖለቲካም አገዛዙ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በመቆራረጡ የተነጠለ መሆኑን ገልጸዋል። ​በአማራ ሕዝብ ላይ ከተፈጸመው ጅምላ ጭፍጨፋ አንጻር ይህንን አገዛዝ ታግሎ ከማሸነፍና ለፍርድ ከማቅረብ ውጭ ሌላ አማራጭ የሌለ መሆኑን የገለጹት ዋና ወታደራዊ አማካሪው፣ ፋሺስታዊው ሥርዓት ለፍርድ ቀርቦ የሕዝብ ሉዓላዊነት እስኪረጋገጥ ድረስ ትግሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አጽንኦት ሰጥተዋል።

አፋብን 1ኛ ምኒልክ ዕዝ 14ኛ እና15ኛ ኮር በደቡብ ወሎ ዞን በሁለት ግንባሮች ደማቅ ድልን ተጎናጽፈዋል!! ​የአፋብን 1ኛ ምኒልክ ዕዝ ስር 14 እና15ኛ ኮር የተቀናጁ አሃዶች በደቡብ ወሎ መቅደላ እና አልብኮ ወረዳዎች በተካሄዱ ውጊያዎች በጠላት ኃይል ላይ ከፍተኛ ሰብአዊ  እና ቁሳዊ ኪሳራ አድርሰዉበታል ። ​ነሐሴ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከንጋቱ 11፡30 ጀምሮ በመቅደላ ወረዳ ማሻ ከተማ በተካሄደው መብረቃዊ ጥቃት፣ የወገን ኃይል ከተማዋን እና ወታደራዊ ገዥ ቦታዎችን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር በማዋል በህዝብ ላይ ግፍ ሲፈፅሙ የነበሩ ሚሊሾችን ጨምሮ ከ45 በላይ የጠላት አባላት ሲደመሰሱ፣ በርካታ ቁስለኞች ወደ ጊባ እና ደሴ ይዘው እንዲፈረጥጡ ያደረጉት ሲሆን በዚህም ከ25 በላይ ክላሽንኮቭ፣ 15 F1 ቦምቦች እና በርካታ የክላሽና ብሬን ተተኳሾች መማረክ ችለዋል። ​በሌላ በኩል በአልብኮ ወረዳ ፉርሴ ተራራ ላይ መሽጎ በነበረው የጠላት አድማ ብተና ኃይል ላይ የ14ኛ ኮር 143ኛ ክፍለ ጦር አሃዶች በወሰዱት ቀጥታ የምሽግ ጥቃት፣ የሻምበል መሪውን እና የዘመቻ ኃላፊውን ጨምሮ 15 የጠላት አባላት ሲደመሰሱ ከ30 በላይ ቁስለኛ ማድረግ ተችሏል። ከደቂቃዎች በፊትም የምኒልክ ዕዝ 101ኛ ኮር በተንታ ወረዳ በመድፍና በድሮን ታገዞ የተንቀሳቀሰዉ የአገዛዙ ሰራዊት አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ድልን መጎናጸፋቸዉን ዘግበናል ።   መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን 1ኛ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን  መምሪያ! ነሃሴ 12/2018 ዓ.ም

🚨 ሰበር ዜና | በማሻና ተንታ ግንባር ከባድ እርምጃ በማሻና ተንታ ግንባር ከባድ እርምጃ የተወሰደበት የአገዛዙ ጦር በጃማ በኩል ፈርሶ ከነ ሙሉ ትጥቁ እጁን ለፋኖ መስጠቱ ታወቀ። በማሻና ተንታ ግ
+4
🚨 ሰበር ዜና | በማሻና ተንታ ግንባር ከባድ እርምጃ በማሻና ተንታ ግንባር ከባድ እርምጃ የተወሰደበት የአገዛዙ ጦር በጃማ በኩል ፈርሶ ከነ ሙሉ ትጥቁ እጁን ለፋኖ መስጠቱ ታወቀ። በማሻና ተንታ ግንባር በተደረገ ውጊያ የጠላት ብልፅግና መከላከያ ሠራዊት በፋኖ ከበባ ውስጥ ገብቶ ዳሽቆ መቅረቱን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል። ይሄንን ተከትሎ በዚኸው አከባቢ በጃማ ግንባር በግዳጅ ላይ ከሚገኘው የአገዛዙ ኃይል መካከል በርካታ ወታደሮች ከጥርናፌያቸው በመውጣት ከነሙሉ ትጥቃቸው በአፋብን 1ኛ ምኒልክ ዕዝ 15ኮር 152ኛ ክ/ጦርን ዛሬ ነሐሴ 12/2018 ዓ/ም ተቀላቅለዋል።

የፋሽስቱን የዱርየዎች ስብስብ ክላ ብለው ፋኖን የተቀላቀሉ ቆራጦች ናቸው። ህዝባቸውን አንጨፈጭፍም በማለት ከስህተታዊ ድርጊት ከደምና ወንጀሉ የታቀቡ ጀግኖች👏 #እናንተንና መሰሎቻችሁን እናከብራለን!
የፋሽስቱን የዱርየዎች ስብስብ ክላ ብለው ፋኖን የተቀላቀሉ ቆራጦች ናቸው። ህዝባቸውን አንጨፈጭፍም በማለት ከስህተታዊ ድርጊት ከደምና ወንጀሉ የታቀቡ ጀግኖች👏 #እናንተንና መሰሎቻችሁን እናከብራለን!!

አገዛዙ በዲማ ጊዮርጊስ ገዳም እና በከተማዋ የሚኖሩ ኖሪዎች ላይ ከፍተኛ ዝርፊያና ውድመት ፈፅሟል!! ነሀሴ10/2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 1:30 እስከ ምሽቱ 12:00 ሰዓት ባአካሄደው ውጊያ የፋኖን ክንድ መቋቋም ሲያቅተው የአብይ አህመድ ወንበር ጠባቂ ሰራዊት በዛሬው እለት ነሀሴ 11/2018 ዓ.ም በዲማ ከተማ የሚኖሩ ንፁሃን አርሶ አደሮችን ማዳበረያ፣ የነጋዴውን ሀብት ንብረት፣ በከተማዋ የሚገኙ ምግብ ቤት የሚገኝ መገልገልያ ዕቃዎችና በከተማዋ ኖሪዎች ላይ ከፍተኛ ዝርፊያ ፈፅሟል። በጄኔራል መሃመድ ተሰማ ለ4 ቀን ዲማ ከተማ የመሰንበት ግዳጅ የተቀበሉ ጄኔራሎች እና ኮለኔሮች በሜካናይዝድ፣ መድፍ፣ BM፣ ፔንፔ፣ ሞረተር፣ ዙ23፣ ድሽቃ፣ ብሬን፣ ስናይፐርና በርካታ የእግርኛ ሰራዊት ከደብርወረቅ፣ ከየዕድውሃ፣ ማህበሰብረሃን፣ ወይራ ጠልማ፣ ቢቸና፣ ደጀን፣ የትኖራ፣ ቁይ አሰንዳቦ እና በጎጃም የተለያዩ ቦታዎች የተሰባሰበው የአገዛዙ ሰራዊት ዲማ ከተማ ያቀና ቢሆንም እንደ ተርብ የሚናደፍት ጀግኖች የአባ ኮስትር በላይ ዘለቀ ልጆች ነሀሴ 10/2018 ዓ.ም ታላቁ ዲማ ጊዮረጊስን ላለማስደፈር በላያቸው ላይ የመድፍ፣ የBM እና ከባድ መሳሪያዎችን ሳይበግራቸው ከጠላትን ሰራዊት ጋር በመተናነቅ በቦንብ በማበራየት ከፍተኛ ጉዳት በማድርስ ሲዋጉ ውለዋል። ይሁንና አገዛዙ በአስወነጨፋቸው የመድፍ እና BM ቅንቡላዎች በታላቁ ዲማ ጊዮረጊስ ገዳም ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲደርስ በገዳሙ የሚገኙ መነኩሳት አገዛዙ በተኮሰው ሞርተር ቅንቡላ ፍንጣሪ ከባድ ቁስለኛ በመሆን ቢቸና የመጀመረያ ደረጃ ሆሲፒታል መግባታቸው ተረጋግጦል። የአርበኞች እና የቅዱሳን ምድር ታላቁ ዲማ ጊዮረጊስ ገዳምን ለማውደም ጠላት ያልተጠቀማቸው ከባድ መሳሪያ የለም የአገዛዙ ሀይል አለኝ የሚላቸውን መሳሪያዎችን ሁሉ ዲማ ጊዮረጊስ በማስወንጨፍ ከፍተኛ ዝሪፊያና ውድመት ፈፅሟል። አገዛዙ በታላቁ ዲማ ጊዮረጊስ የሰራቸውን ዝርፊያ፣ ውድመት በተመለከተ ሙሉ መረጃውን ይዘን የምንመለስ ይሆናል። አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት       ነሀሴ 12/2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያን የታሪክ አቅጣጫ በመቀየርና የነጻነት ተምሳሌትነቷን በመገንባት ረገድ እንደ አፄ ምኒልክ እና እቴጌ ጣይቱ ብጡል ዓይነት ጥምረት በታሪካችን ውስጥ አብሮ ታይቶ አይታወቅም።  መሪዎቻችን የተወለዱበትን ቀን ስናስብ፣ ታላቅነታቸውን ብቻ ሳይሆን የአመራር ጥበባችሁንና ለሀገር ያበረከቱትን የማይጠፋ ውርስ እናስታውሳለን። ​የአፄ ምኒልክ ገናናነትና ዘመናዊነት ​አፄ ምኒልክ የኢትዮጵያን አንድነት ከመመለስ አልፈው ሀገሪቱን ወደ ዘመናዊነት ጎዳና የመሩ አርቆ አዋቂ መሪ ነበሩ። ~የአደዋ ድል መሐንዲስ፦ የተቀናጀ የጦር አመራርና ሕዝብን የመቀስቀስ ጥበባቸው የዓለምን የኃይል ሚዛን ያናወጠውን የታላቁን የአደዋ ድል አስኝቷል። ~የዘመናዊነት መሠረት ጣይ፦ ስልክ፣ ባቡር፣ ትምህርት ቤት፣ ሆስፒታልና ዘመናዊ የገንዘብ ሥርዓትን በማስተዋወቅ ኢትዮጵያን ከዘመኑ ጋር አያይዘዋል። ~የእርቅና የአንድነት መሪ፦ በጥበብና በትዕግሥት የተሞላው አመራራቸው የሀገሪቱን ወሰን በማስፋትና ሕዝቦችን በማስተሳሰር ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል። ​የእቴጌ ጣይቱ የዲፕሎማሲ እውቀትና ሀገር ገንቢነት ​እቴጌ ጣይቱ ብጡል በሀገር ፍቅር፣ በጽናትና በረቀቀ የዲፕሎማሲ እውቀታቸው የሚታወቁ ታላቅ ሴት ነበሩ። • ~የዲፕሎማሲና የፖለቲካ ብልህነት፦ የውጭ ኃይሎችን ተንኮል ቀድመው በመረዳት፣ በተለይም በውጫሌ ውል አንቀጽ 17 ላይ የተሸረበውን ተንኮል በማጋለጥና "እኔ ሴት ነኝ፤ ጦርነት አልወድም፤ ነገር ግን ይህንን ውል ከመቀበል ይልቅ ጦርነትን እመርጣለሁ" በማለት የሀገርንሉዓላዊነት አስከብረዋል። ~የሀገርና የመዲና ግንባታ፦ የዛሬዋ ዋና ከተማችን አዲስ አበባ እድትቆረቆርና እንድታድግ ዋና አሳቢና መሐንዲስ ነበሩ። ~ጽናትና ቁርጠኝነት፦ በአደዋ ዘመቻ ወቅት በጦር ሜዳው ግንባር ድረስ በመገኘት፣ ምግብና የሕክምና እርዳታ በማስተባበር እንዲሁም ወታደሩን በማበራታት አርአያነት ያለው አመራር አሳይተዋል። ​ዛሬ የልደት ቀናቸውን ስናስብ ያለፈውን ታሪክ ለማድነቅ ብቻ ሳይሆን፣ ለዛሬዋ ኢትዮጵያ የሚሆን ትምህርት ለመውሰድ ነው። ~ዲፕሎማሲና ሉዓላዊነት፦ የእቴጌ ጣይቱ የፅናትና የረቀቀ ዲፕሎማሲ ትምህርት ዛሬም ሀገራችን በዓለም አቀፍ መድረክ መብቷን እንድታስከብር መንገድ ያሳያል። ~አንድነትና ዘመናዊነት፦ የአፄ ምኒልክ አርቆ አስተዋይነትና ለዘመናዊነት የነበራቸው ፍላጎት፣ ዛሬ ለምናደርገው የሀገር ግንባታና የቴክኖሎጂ ዕድገት ትልቅ ማነቃቂያ ነው። ​እነዚህን ሁለት ታላላቅ የሀገር ባለውለታዎች ስናስብ፣ የተዉልንን የነጻነት፣ የዲፕሎማሲ ብልህነትና የሀገር ፍቅር መሠረት በማድረግ ለተሻለች ሀገር ለማፅናት መሥራት ሊሆን ይገባል።

ሰበር ዜና 1ኛ ምኒልክ ዕዝ አሃድ የሆኑት 12ኛ ኮር ፣ ልዩ ዘመቻ እና የ16ኛ ኮር በጋራ ባካሄዱት የተቀናጀ ኦፕሬሽን ታላቅ ድል ተጎናፀፉ! ​በሰሜን ወሎ ዞን አውተገኝ፣ እዜትበር፣ ወልድያ፣ መርጦ፣ ሲሪንቃ እና ጋሸና አቅጣጫዎች መነሻቸውን አድርገው ተንቀሳቅሰው የነበሩ የአገዛዙ የ16ኛ እና 31ኛ ክፍለ ጦር ኃይሎች ላይ የተቀናጀ እርምጃ ተወስዶባቸዋል ። ​የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) 1ኛ ምኒልክ ዕዝ ልዩ ዘመቻ፣ የ16ኛ ኮር፣ 12ኛ ኮር በጋራ በወሰዱት የተቀናጀ ዉጊያ ጠላት ያቀደውን ዓላማ ሳያሳካ ከፍተኛ የስነ-ልቦና ስብራት እና የሰው ኃይል ጉዳት አስተናግዶ ተመልሷል። ​ በተረፌ፣ ኩረታ፣ ጠጠር መልቀሚያ፣ ድልበት ሚካኤል፣ ላም ድንጋይ እና ኩቤ ተራራ በተባሉ አካባቢዎች ለሁለት ቀናት የዘለቀ እልህ አስጨራሽ ውጊያ ተካሂዷል። የአገዛዙ ሰራዊት ያለ የሌለ አቅሙን ቢጠቀምም፣በምኒልክ ዕዝ ፋኖ አባላት የበላይነት በተጠናቀቀው በዚህ ውጊያ በርካታ ሙትና ቁስለኛ ተሸክሞ ሽንፈትን ተከናንቦ ወደ መጣበት ፈርጥጧል። በፋኖወች ክንድ ክፉኛ የተደቆሰዉ የአገዛዙ መከላከያ ህዝቡን "ለፋኖ መረጃ ትሰጣላችሁ" በሚል ምክንያት በመደብደብ እና በማስፈራራት እያፈሰ ወደ ጦር ግንባር እንደወሰዳቸው ከውስጥ የተገኙ መረጃዎች አመልክተዋል። ​መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ወሎ ቤተአማራ 1ኛ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ነሃሴ 12/2018 ዓ.ም

ከአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሴቶች ጉዳይ መምሪያ የተላለፈ ወቅታዊ ጥሪ።      ነሃሴ 12/2018 ዓ.ም የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሴት አርበኞቻችን ላሳዩት ተጋድሎ እውቅና የሚሰጥ እና የአማራ ህዝብ እያደረገ ባለው ቅዱስ ትግል የሴት አርበኞች ተሳትፎ በፖለቲካዊ ትጥቅ ትግሉ ያላቸውን ሚና እንዲያጠናክሩ የሚያበረታታ ከሴቶች ጉዳይ መምሪያ የቀረበ ወቅታዊ ጥሪ ነው። የከበረ ሰላምታችን ​ይድረስ ለዘመናችን የእቴጌ ጣይቱ የመንፈስ ልጆች፣ለቁርጠኛዋ ሴት የነፃነት አርበኛ የሸዋረገድ ገድሌ የቃል ኪዳን አደራ ጀግኖቻችን። እንደሚታወቀውና የታሪክ ድርሳናት እንደሚነግሩን አለም ስለ ፆታዊ እኩልነት በሚያወራበት ዘመን የኛ የሴት አርበኞች ሀገርን በመሪነት ደረጃ ይመሩ እንደነበረ አውቀን የእነሱን አርአያነት መከተልና ለአማራ ህዝብ ሰላም ፣ፍትህና እኩልነት (ህልውና) መረጋገጥ ሲባል በርካታ የሴት ገድሎችን እየፈፀሙ በደማቸው ወርቃማ አሻራቸውን እያሳረፉ በመሆኑ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሴቶች ጉዳይ መምሪያ ታላቅ ክብርና ምስጋና በማቅረብ እንደሚከተለው መልዕክቱን ያስተላልፋል። ​ክቡራት እህቶቻችን እና እናቶቻችን! ​ታሪክ እንደሚመሰክረው የአማራ ሴት አርበኞች የጥንካሬ፣ የጥበብ እና የጀግንነት ተምሳሌቶች ናቸው። በጦር ሜዳ ካሳዩት ሀገርን በማፅናት፣ ቤተሰብን በማክበርና በማስከበር እና ባህልን ጠብቆ በማቆየት ረገድ የተጫወቱት ሚና የሀገራችን የጀርባ አጥንት ሆነው ቆይቷል። ውድ የሴት አርበኞቻችን! ዛሬ ላይ ሆነን ወደ ኋላ ስንመለከት እንደ እነ እቴጌ ጣይቱ ብጡል፣  አርበኛ ሸዋረገድ ገድሌ፣  አርበኛ ተናኘወርቅ ኃ/ስላሴ፣  አርበኛ አየለች እሸቴ እና አርበኛ እቴጌ መነን አስፋው ያሉ ሴት እናት አርበኞች የከፈሉት መስዋዕትነት የእኛ ኩራትና የመንፈስ ጥንካሬ ምንጭ እንድሁም አሁን ላለንበት ህልውናን ለማቆዬት በሚደረገው ትግል የ50% ድርሻ የኛ የሴቶችም መሆን እንዳለበት የሚያሳይ መሆኑን ነው። አገዛዙ በአማራ ህዝብ ላይ ከሚያደርሰው መጠነ ሰፊ ጭፍጨፋ ባለፈ በሴቶች ላይ የሚያደርሰው ደፈራ እና ግድያ የከፋ መሆኑ ፀሀይ የሞቀው ሀገር ያወቀው የአደባባይ ምስጥር መሆኑ እየታወቀ እኛ ሴቶች ይህን ማንነትን፣ታሪክ ባህልን፣እውቀትን እንድሁም ጤናን ጭምር የሚያጠፋ የብልፅግና አገዛዝ በጦር ሜዳው አውድማ ተሰልፈን ልንታገለው ይገባል፣በፅናት እየታገልነውም እንገኛለን። በትግል ሜዳው ያላችሁ የኔ ዘመን ጀግኖች እየሰራችሁት ያላችሁት ታሪክ ለዛሬ ኩራታችሁ ለነገ ታሪካችሁ ነውና በርቱ ፤ጠላታችን የወደቀና የደቀቀ ነው እናሸንፋለን። ለምታደርጉት ዘርፈ ብዙ ተጋድሎ በሰፊው የአማራ ህዝብ እና በመላው የሴት አርበኞቻችን ስም ላመሰግናችሁ እወዳለሁ ሁልጊዜም በአካልም በመንፈስም ከጎናችሁ ነኝ ። ውድ አርበኞቻችን! ​እኛ ሴቶች! በማይበገር ማንነት፣ በፈተናዎች ውስጥ ተስፋ አለመቁረጥና ለፍትህ መቆም የሴት አርበኞች መለያ ባህሪ በማድረግ መታመንን በማሳዬት አርበኝነትን ወደ ላቀ ደረጃ እናሸጋግራለን። ዛሬም እንደ ትላንቱ አማራን ከዘር መጥፋት መታደግና ፣ታሪክና ባህል ከውድመት እና ሀገራችን ኢትዮጵያ ከመበተን የእኛን ብርታት ትሻለች። አሁናዊው "ትግል" የአማራን ህልውና የማስከበር እንደ ህዝብ ከመጥፋት በህይዎት ለመኖር ሲባል በጀግናው የአማራ ፋኖ ፊትአውራሪነት እንደ ህዝብ የምናደርገው ህዝባዊ ትግል ነው። በመሆኑም እያንዳንዳችሁ ሴቶች በዚህ የአማራ ብሔርተኝነት ትግል፤ በፖለቲካዊ ትጥቅ ትግል ውስጥ ግንባር ቀደም ተሰላፊ ትሆኑ ዘንድ የሚከተለውን ጥሪያችንን እናቀርባለን። ➛እናቶች እና እህቶች ራስን በማብቃት እና ወሳኝ አካል በመሆን ለገዳይሽና ለሚደፍርሽ አገዛዝ ብልፅግና ያደረ ፍቅረኛን፣ ወንድምን ፣ባልን(የትዳር አጋርን)፣ልጅን ከድርጊቱ እንዲቆጠብ በማድረግ ትግሉን ከቤት በመጀመር የዕይታ አድማሳችሁን በማስፋት ትግሉን ተቀላቀሉ። ➛በትግል ሜዳውም በአመራርነት በመሳተፍ በውሳኔ ሰጪነት ቦታዎች ላይ በመገኘት ሴቶች የምንችል መሆናችንን ለማሳዬት በተመደብንበት ኃላፊነት ሁሉ በብቃት እንወጣ። ➛እህትማማችነትን እና ከወንድሞች ጋር ወንድማዊ ትስስርን በማጠናከር፡ አንዷ/ዱን፣ ሌላዋን /ውን በማንሳት የጋራ ጥንካሬን መገንባት ላይ እንስራ። ​"አንዲት ሴት ስትበረታ ቤተሰብ ይበረታል፣ ቤተሰብ ሲበረታ ደግሞ አማራ ያሸንፋል፣ አማራ ሲያሸንፍ ሀገር ትጸናለች።" ውድ አርበኞቻችን! ​እኛ የጥንት አርበኞች ልጆች፣ የዛሬ የአማራ ህዝብ አደራ ያለብን የቁርጥ ቀን ጀግኖች በመሆናችን ታሪክ የጣለብንን አደራ በተሰጠን መክሊት በብቃት እንድንወጣ። በሀገር ውስጥ ከሀገር ውጭም ያላችሁ ውድ የአማራ ህዝብ በሙሉ የትግሉ አካል በመሆን ብዙዎች የወደቁለትን ፅኑ ዓላማ በጋራ ከዳር እናደርስ ዘንድ የከበረ ጥሪዬን እያቀረብኩ በመራሩ የትግል ጉዞ በማለፍ ለተቀደሰው ትግላችን በፅናት እንድንቆም በድጋሚ የጓዳዊ እና የእህትነት መልዕክቴን በመምሪያው ስም አስተላልፋለሁ።     ክብርለትግሉ ሰማዕታት!    ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!          ​ከከበረ ሰላምታ ጋር   አርበኛ ቀኝአዝማች ትንቢት ኃ/ማሪያም ከአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሴቶች ጉዳይ መምሪያ      ነሃሴ 12/2018 ዓ.ም