ch
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

前往频道在 Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

显示更多
2 929
订阅者
+224 小时
+3727 天
+36730 天
帖子存档
የ117ኛ ክፍለ ጦር ቃኝ አና መሀንዲስ እና ሚሊሻው ፋኖን ተቀላቅለዋል። ========================== .......ነሐሴ 07/2018 ዓ.ም 1.ጌታቸው ባይሌ...ሚሊሻ ከግንደወይን 2.ይር
+4
የ117ኛ ክፍለ ጦር ቃኝ አና መሀንዲስ እና ሚሊሻው ፋኖን ተቀላቅለዋል። ========================== .......ነሐሴ 07/2018 ዓ.ም 1.ጌታቸው ባይሌ...ሚሊሻ ከግንደወይን 2.ይርጋ እማኘው..ከ‎117ኛ ክ/ጦር ቃኝ እና መሀንዲስ 201ኛ ኮር 54ኛ እና 74ኛ ክ/ጦርን ተቀላቅለዋል። በከፍተኛ ሁኔታ ያለ አንድ ጥይት ጩኸት በየቀኑ ስቦ ማስከዳት ስራው ተጠናክሮ ቀጥሏል። የአፋብን ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህ/ግንኙነት ‎

የአምባገነኑና ዘረኛው ስርዓት ሠራዊት ያለውጊያ መበተኑን ቀጥሎበታል! ነሃሴ 07/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ያለ ምንም ጦርነትና መስዋዕትነት የአገዛዙን ጦር በመረጃና ደሕንነት እዲፈርስ ማድረጉ ታወቀ። የአማራን ሕዝብ ከዘር መጥፋት ለመታደግ ዋስ ይሆነው ዘንድ ድርጅት መስርቶ በአራቱም አቅጣጫ እየተዋደቀ የሚገኘው "የአፋብን" ሠራዊት የጠላትን ኃይልን በመቀበል ወደ ፋኖ እዲቀላቀሉ እያደረገ ይገኛል። በዚሕም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝን በጥቂት ቀናቶች በርካታ የስርዓቱ ጠባቂ ኃይሎች ከድተው እዲቀላቀሉ ለማድረግ ተችሏል። 1.ሀብታሙ ብርሀኑ--የሻለቃ መሪ አጃቢ 2.በለጠ አዳነ--ዶሽቃ ተኳሽ ➠2 ጥርጥር ክላሽ ➠230 ተተኳሽ ➠2ቦንብ ➠ 2 ትጥቅ 👉 ከ112ኛ አየር ወለድ ክ/ር --ወደ አፄ ምኒልክ ክ/ር 3.ም/፲ አለቃ ስመኝ ሙላቱ--መሰናክል አስወጋጅ 4.ም/፲ አለቃ ኤሊያስ ዳምጤ-- '' '' '' '' ➠2 ጥቁር ክላሽ ➠2 የደረት ትጥቅ ➠2ቦንብ ➠180 ተተኳሽ 👉 ከ605ኛ ኮር ኮማዶ ክ/ር--ወደ ራስ አበበ አረጋይ ክ/ር 5.ክንዱ ቸሩ ስናይፐር ተኳሽ 6.ይሳቅ ፈቃዱ ዶሽቃ ተኳሽ ➠3F1 ቦንብ ➠1 ሳንጃ(ጩቤ) 👉 ከ101ኛ አየር ወለድ ክ/ር 5ኛ ሻለቃ-ወደ አፄ ዳዊት ክ/ር 7.መሠረታዊ ወ/ር ኤልያስ ፀጋዬ(RSF) 8." " " ጊዜው የማታ(RSF) ➠2 ጥርጥር ክላሽ ➠ 4ቦንብ ➠2ትጥቅ ➠440 ተተኳሽ 👉 ከ112ኛ አየር ወለድ ክ/ር--ወደ ንጉሥ ሣህለ ሥላሴ ክ/ር 9. ሁለት(2) ለደሕንነታቸው ስማቸው ያልተጠቀሱ ➠2ክላሽ ➠2ትጥቅ ➠3 ቦንብ ➠175 ተተኳሽ 👉 ከ111ኛ ኮማዶ ክ/ር--ወደ ሀ/ማርያም ማሞ ክ/ር ✔ በጠቅላላ፦ 10 =የሠራዊት አባል 8=ትጥቅ 14=ቦንብ 1025= ተተኳሽ 8= ክላሽኮቭ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አምደ ጽዮን ኮር ገቢ ማድረግ መቻሉን የኮሩ ሚዳያና ኮሙኒኬሽን አስታውቋል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ነሐሴ 06 ቀን 2018 ዓ.ም ከአፋብን አባት አርበኞች ምክር ቤት የተሰጠ ወቅታዊ  መግለጫ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የሚያደርገው የህልውና ተጋድሎ የአገዛዙን ሰራዊት አከርካሪ በመስበር ላይ ይገኛል። ይህ ትግል ዛሬ የደረሰበት ደረጃ ይደርስ ዘንድ በእሳት የታጠሩ መሰናክሎችን በማለፍ መስዋዕትነት እየከፈሉ ፋኖነትን  ያቆዩ አርበኞች በታሪክ ፊት ልዩ ክብር ይገባቸዋል። ይህንን የተገነዘበው ድርጅታችን አፋብን የአባት አርበኞች ምክር ቤትን አቋቁሞ አርበኞች የትግሉ አካል የምንሆንበትን አደረጃጀት በመፍጠሩም የሚያስመሰግነው ተግባር ነው። የአፋብን አባት አርበኞች ምክር ቤት አባላት ወቅታዊ የሀገራችንን  ሁለንተናዊና ነባራዊ ሁኔታ በመገንዘብ በተለይም የአማራ ህዝብ ላይ  እየደረሰ ያለውን መጠነ ሰፊ ስርዓታዊ ጭቆና፣ የህልውና አደጋና የዘር ማጥፋት ወንጀል በመገንዘብ ህዝብን ከእልቂት ለመታደግ ሲባል ይህንን ወገናዊ  ጥሪ የያዘ መግለጫ አውጥተናል። በመሆኑም ይህ ጥሪ የሚመለከታችሁ መላው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት፤ የአማራ ክልል አድማ ብተና፣ ፖሊስ እና ሚሊሻ አባላት በሙሉ ከዚህ በታች በተዘረዘሩት መሠረት ጥሪ ተግባራዊ ስለሚደረግ ጥሪውን ተቀብላችሁ አገራዊ እና ሰብአዊ ግዴታችሁን እንድትወጡ የአፋብን አባት አርበኞች ምክር ቤት ያሳስባል። 1ኛ. ማንኛውም የመከላከያ ሰራዊት አመራርና አባል በሙሉ፡ ይህ ስርዓት የሃገርን ዳር ድንበር ዘብ እንዲሆን የተቋቋመን የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ለራሱ የስልጣን ማራዘሚያ አድርጎ በገዛ ህዝቡ ላይ በማስተኮስና ነጻነት ፈላጊ ህዝብ በሰራዊቱ ላይ መልሶ እንዲተኩስ በማድረግ አመታትን ያስቆጠረ ጉዳይ ሆኗል፡፡ የተከበርከው የሃገር መከላከያ ሰራዊት በየቀኑ እየተኮስክበትና እየገደልከው ያለው ህዝብ የራስህ ህዝብ ነው፡፡ ባልና ልጆቻቸው ተሰውተውባቸው የሚያለቅሱ እናቶች፣ ሴቶችና ህጻናት ሃገርህ ኢትዮጵያ እንድትጠብቃቸው አደራ የወጣህባቸው መሆናቸውን ፈፅሞ መዘንጋት የለብህም፡፡ በመሆኑም ይህን የአፋብን አባት አርበኞች ምክር ቤት የምህረት ጥሪን በመቀበል ከስነ ስርዓት አልባው የብልፅግና ስርአት ከነመሳሪያችሁና ሙሉ ትጥቃችሁ በመውጣት የአፋብን ሠራዊትን እንድትቀላቀሉ ስንል የአፋብን አባት አርበኞች ምክር ቤት ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡ 2ኛ. ማንኛውም የልዩ ሀይል: የአድማብተና: የፖሊስና የሚሊሻ አመራርና አባላት በሙሉ፡ ለማያዛልቅ ደሞዝ ፣ ቤት መስሪያ ቦታ እና ርካሽ ጥቅማጥቅም ብላችሁ በአማራ ህዝብ እየደረሰ ያለውን ግፍና መከራ ችላ በማለት አሁንም ድረስ ህዝብን እንደ ይሁዳ በሰላሳ ዲናር መሸጡ የይሁዳን እጣፋንታ ከማድረግ ባለፈ ዘላቂ ምቾትን አያስገኛችሁም፡፡ በመጨረሻም ጨፍጫፊው ስርዓት ይፈርሳል፣ አለቆቻችሁ በዘረፋ ባከማቹት ገንዘብ ራሳችውን ያሸሻሉ፣ እናንተና ቤተሰቦቻችሁ ግን ከማህበረሰቡ ትቀራላችሁ፡፡ ይህን ጉዳይ ግንዛቤ በማስገባት መሳሪያና ሙሉ ትጥቃችሁን በመያዝ አፋብንን እንድትቀላቀሉ የአፋብን አባት አርበኞ ምክር ቤት ጥሪ እናቀርባለን፡፡ 3ኛ. ማንኛውም የአማራ ክልል የብልፅግና ስርዓት አመራር ፣ ካድሬና ካቢኔ አባላት በሙሉ፡ የዚህን ደም አፋሳሽ ስርዓት ተልዕኮን ተቀብላችሁ በተለያዬ መልኩ በመፈጸምና በማስፈፀም በአማራና በመላ የሀገሪቱ ህዝብ ላይ እየደረሰ ባለው የዘር ማጥፋት ወንጀል ላይ ያላችሁን ሚና ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በማቆም ለአማራ ብሎም ለአሁኗና ለወደፊቷ ኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ሰላም ማምጣት አማራዊ; አገራዊ እና ሰብአዊ ግዴታችሁ በመሆኑ አፋብንን በመቀላቀል የበኩላችሁን እንድትወጡ ስንል የአፋብን አባት አርበኞች ምክር ቤት ጥሪ እናቀርባለን::                   ድል ለፋኖ !!!                 ድል ለአማራ!!!               ድል ለኢትዮጵያ!!! 1 ኛ ኮማንደር አረጋ አለባቸው ጎንደር ............ 2 ኛሻለቃ አብነው ታደሰ ቤተአማራ ወሎ 3 ኛ አሺኔ ዘመዱ ሸወ/ጠቅላይ ግዛት 4 ኛቢያዝን በዜ ጎጃም 5 ኛአርበኛ እሸቴ በዬ ጎንደር 6 ኛ አረበኛ ሠፈር መለስ ሰሜን ጎንደር 7 ኛ ሻምበል ገብሩ ልይህ ሰሜን ጎንደር 8ኛ አርበኛ ደስታው ደመላሽ ደቡብ ጎንደር 9ኛ ሻምበል መሠረት አለሙ ሰሜን ጎንደር

ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ ​ቀን፦ ነሐሴ 06 ቀን 2018 ዓ.ም ​በንጹሐን ወጣቶች ላይ የሚፈጸመውን የግፍ ግድያ፣ ወታደራዊ የግዳጅ አፈሳ እና የአዲስ አበባን የፖለቲካ ሴራ አስመልክቶ ከአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የተሰጠ መግለጫ ​የአማራ ህዝብ የተደቀነበትን የህልውና አደጋ ለመመከት እና ተፈጥሮአዊ ወይም ሰብአዊ መብቱን ለማስከበር የሚያደርገው ፍትሃዊ ትግል በከፍተኛ ህዝባዊ ደጋፊነት ወደፊት እየገሰገሰ ይገኛል። ነገር ግን የስርዓቱ አስፈጻሚዎች ትግሉን ማቆም ሲሳናቸው በንጹሐን ወላጆች እና ወጣቶች ላይ የሚያደርሱትን የግፍ እርምጃ እና የሽብር ተግባር አጠናክረው ቀጥለውበታል። ​በመሆኑም አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ወቅታዊ እና አስቸኳይ የፖለቲካ እና ወታደራዊ ሁኔታዎችን አስመልክቶ የሚከተለውን የአቋም መግለጫ አውጥቷል፦ ​1. በንጹሐን ወጣቶች ላይ በአገዛዙ ብልፅግና የተፈጸመውን አሰቃቂ የእብሪት ግድያ ( መረሸንን) በተመለከተ:- በቀን 04/12/2018 ዓ.ም በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ከተሳፈሩበት የሕዝብ ማጓጓዣ መኪና ላይ “ፋኖ ናችሁ” በሚል መላ ምት እና ውንጀላ ተገደው እንዲወርዱ ከተደረጉ በኋላ በማንነታቸው ብቻ በአሰቃቂ ሁኔታ የተረሸኑትን የሶስት ንጹሐን አማራ ወጣቶች ግድያ እዛችን በጽኑ ያወግዛል። 1ኛ. ​ወጣት ተመስገን ጌታቸው 2ኛ. ​ወጣት ይታገሱ አሰግደው 3ኛ. ​ወጣት ግዛው ግርማ ​ፋኖነት የአማራ ህዝብ የታሪካዊ እሴቱ፣ የጀግንነቱ እና የህልውናው መገለጫ እንጂ ንጹሐን ዜጎችን ያለ ህግ አሰራር የሚያስገድል "ወንጀል" ወይም ኮድ አይደለም። በህዝብ ማጓጓዣ ላይ የሚጓዙ ንጹሐን ዜጎችን በማንነታቸው ብቻ ተለይቶ መረሸን የስርዓቱን አረመኔነት እና የሞራል ውድቀት ወይም መፍረስን የሚያሳይ ግልጽ የጦር ወንጀል ነው። ​2. የግዳጅ ወታደራዊ አፈሳ እና የከተሞች ወታደራዊ ከበባን አስመልክቶ :- ​በአሁኑ ወቅት በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ሁሉም ከተሞች ማለትም በአዲስ አበባ፣ በናዝሬት ፣ በደብረዘይት ፣ ደብረብርሃንን ጨምሮ በሁሉም አውራጃዎች ስር ባሉ ወረዳዎች ይህ አረመኔ ስርዓት ሰፊ ወታደራዊ የግዳጅ አፈሳ ጀምሯል። ወጣቶችን ከመንገድ፣ ከስራ ቦታ እና ከሙያ መስካቸው እያፈሰ የአማራን ህዝብ እየጨፈጨፈ ያለ ፀረ -ህዝብ እና ፀረ- አንድነት የሆነው አገዛዝ በግዳጅ ከተሸናፊነት ለማያድነው ጉዞ ወጣቶችን ወደ ጦርነት ማግዳ በመክተት ላይ ይገኛል። ​ይህ ህገ-ወጥ አፈሳ የስርዓቱን ውድቀት የሚያፋጥን እንጂ ህዝባዊ ትግሉን የሚያስቆም አይደለም። በመሆኑም በነዚህ ከተሞች የምትገኙ የአማራ ወጣቶች ለገዢው ቡድን የመሳሪያ ማኖሪያ ከመሆን ይልቅ፣ የህዝባችሁን ህልውና ለማስከበር በግንባር ቀደምትነት እየታገለ የሚገኘውን አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝን እንድትቀላቀሉ ጥሪ እናስተላልፋለን። ​3. የአዲስ አበባ ህልውና እና የፖለቲካ ደባ :- ​የአማራን ህዝብ "ወደ ዋና ከተማህ አዲስ አበባ አትገባም" ሲል የቆየው የገዢው ቡድን ፖለቲካዊ መዋቅር፣ ዛሬም በአዲስ ማጭበርበሪያ የከተማዋን ነዋሪዎች እና ተወላጆች ከመንግስታዊ እና ኢኮኖሚያዊ መዋቅር በማግለል ላይ ይገኛል። ​ከተማዋን ሙሉ በሙሉ ለመዋጥ እና የስነ-ሕዝብ (demographic) ስብጥርን ለመቀየር የሚደረገው የተቀናጀ ሴራ፣ መብታቸውን የሚጠይቁና የሚሟገቱ ሰዎችን በማሰር፣ በማሳደድ እና በማስፈራራት አደገኛ ደባውን እያከናወነ ይገኛል። ይህ የሀገርን ጥቅም ለመሸጥ እና ለመቀራመት የሚደረግ እቅድ የመላው ኢትዮጵያውያን ስጋት ነው። ​4. አጽንኦት የሚሰጠው የትግል አቅጣጫና ጥሪ • ​ለአማራ ወጣቶች፦ የግፍ ሰለባ ከመሆን እና በግዳጅ አፈሳ ወደማታምኑበት እቅድ ከመነዳት ይልቅ ህልውናችሁን እና የህዝባችሁን ክብር ለማስከበር የፋኖን ትግል ተቀላቀሉ። • ​ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች እና መላው ኢትዮጵያውያን፦ በከተማችሁ እና በሀገራችሁ ላይ እየተፈጸመ ያለውን ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖ በጋራ እንድትታገሉ፣ የፋኖን ህዝባዊ የህልውና ትግል በገንዘብ፣ በሀሳብ እና በፅናት እንድትደግፉ ጥሪያችንን እናቀርባለን። • ​ለስርዓቱ የፀጥታ መዋቅር/የደህንነት አባላት፦ ህዝብን ጨፍጫፊ እና ሀገር አፍራሽ ለሆነው አገዛዝ መሳሪያ ከመሆን ተቆጥባችሁ ወደ ህዝባችሁ ጎን እንድትቆሙ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ እንሰጣለን። ''ክብር ለትግሉ ሰማዕታት'' ​ ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ነሐሴ 06 ቀን 2018 ዓ.ም

#ሰበርዜና:- "የአገዛዙ ሰራዊት እየፈረሰ ፋኖን መቀላቀሉን ቀጥሎበታል":-ፋኖ ላቃቸው በላይ (ድል አብሳሪው!!) ዛሬ በቀን 06/12/2018ዓም የብረሀኑ ጅላ ሰራዊት "እየፈረሰ የአፋብን/ጎጃም/ጠቅላይ/ግዛት/ቴዎድሮስ /ዕዝ/206ኛ/ኮር/የ14ክ/ጦር በረኸኛው ጅበላሙተራ ሻለቃን እየተቀላቀለነው":: 1ኛ:አስር አለቃ እሸቴ መርሻ ከ6ኛ ዕዝ ከ10ኛ /ክ/ጦር ከ5ኛ ሬጅመት ከሻበል አንድ የጋታመሪ የነበረው ከጎዛምን ወረዳ ከቸርተከል ታዳጊ ከተማ በመክዳት አንድ ዶጅ ክላሺ ከእነ ሙሉ ትጥቁ በመያዝ የበረኸኛው ጅበላ ሙተራ ሻለቃን ተቀላቀለ:: 2ኛ:ወታደር ሀብታሙ ጊዜ የአገዛዙ የፓራ ኩማዶ አባል የነበረው ከጎዘምን ወረዳ ከቸርተከል ታዳጊ ከተማ ከጥምር ጦሩ አንድ ኤስኪየስ መሳሪያ በመያዝ የበረኸኛው ጅበላ ሙተራ ሻለቃን ተቀላቀለ:: 3ኛ:ወታደር ነብዩ ስታየሁ የአገዛዙ የፓራ ኩማዶ አባል ከደብረኤልያስ ከመሸገው ጥምር ጦር አንድ ዶጅ ሰደፍ ክላሺ ከእነ ሙሉ ትጥቁ በመያዝ የበረኸኛው ጅበላሙተራ ሻለቃን ተቀላቀለ:: 4ኛ:ወታደር ጌታቸው ገደፈው የአገዛዙ የመከላከያሰራዊት6ዕዝ/ የ10ኛ/ክ/ጦር የሻለቃ ፐርሶኔል የነበረው ከጎዛም ወረዳ ቸርተከል ታዳጊ ከተማ አንድ ጥቁር ክላሺ ከእነሙሉ ትጥቅ በመያዝ ከሳምት በፊት የበረኸኛው ጅበላ ሙተራ ሻለቃን ተቀላቅሏል:: 5ኛ:ወታደር አበባው ዳኘ ከ6ኛ ዕዝ ከ10ኛክ/ጦር ከ5ኛ ሬጅመንት ምክትል ጋታመሪ የነበረው ከሳምት በፊት ከጎዛምን ወረዳ ከቸርተከል ታዳጊ ከተማ በመክዳት አንድ ጥቁር ክላሺ ከእነ ሙሉ ትጥቁ በመያዝ ወደ በረኸኛው ጅበላ ሙተራ ሻለቃ ተቀላቅሏል:: 👉ኑ ?በሰላም ለመጣ በራችን ክፍት ነው:-🤝🤝 👉በክፉ ለመጣብንን ክንዳችን የእሳት ነበልባል ነው!!💪💪 -አዲስ ትውልድ! -አዲስ አስተሳስብ!! -አዲስተስፋ!!! የአፋብን/ጎጃም/ጠቅላይ/ግዛት/ቴዎድሮስ/ዕዝ/206ኛ/ኮር/የ14ኛ/ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

Alert አሁን በዚህ ሰአት  ቦንብ ጣይ ድሮኖች  ከዚህ ከባህር ዳር እየተነሱ ነው ወደየት እንደሆነ አልታወቀም። በሁሉም ቀጠና ያላችሁ ጥንቃቄ አድርጉ

በደቡብ ወሎ ዞን ደላንታ ወረዳ የባጃጅ ማህበራት ጋር ዉይይት ተደረገ !! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ከአዉደ ዉጊያ ጎን ለጎን ህዝባዊ ዉይይቶችን እያደረገ ሲሆን በዚህም በዛሬዉ ዕለት ማለትም ነሀሴ 5/2018 ዓ.ም ከደላንታ ወረዳ ወገልጤና ከተማ ከሚገኙ የባጃጅ ማህበራት ጋር የምኒልክ ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ዉይይት ተደርጓል። በዚህ ዉይይት ላይ" አሁናዊ የአማራ ፋኖ ትግል ምን ይመስላል "በሚል እና በሌሎች አጃንዳወች ዉይይት የተደረገ ሲሆን ማህበሩም ለተሰጣቸዉ ግልፅ ማብራሪያ አመስግነዉ "ይህን የአማራ ህዝብ የህልዉና ትግል በማንኛዉም መንገድ ለመደገፍ ዝግጁነታቸዉን ገልፀዋል። በዚህም የምኒልክ ዕዝ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አርበኛ አለምነዉ መብራቱ፣የምኒልክ ዕዝ የፋይናስ ኃላፊ አርበኛ ንጉስ አዳነ፣ የምኒልክ ዕዝ ህዝብ አስተዳደር መምሪያ አርበኛ አበበ ቀዮ፣ የምኒልክ ዕዝ ሐብት አፈላላጊ አርበኛ ምኒልክ ፋንታሁን እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ተካሂዷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!! ነሀሴ :- 06/ 2018 ዓ/ም

ነሐሴ 6/2018 ዓ.ም አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት ​በላይ ዕዝ 202ኛ ኮር በጌምድር ክፍለ ጦር አይሸሽም ብርጌድ በጠላት ኃይል ላይ የተጠና የደፈጣ ጥቃት ፈጸመ ! ​አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሥር የሚገኘው የ202ኛ ኮር በጌምድር ክፍለ ጦር አይሸሽም ዮሐንስ ብርጌድ በዛሬው ዕለት ነሐሴ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው የተቀናጀ የደፈጣ እና ድንገተኛ የማጥቃት እርምጃ በጠላት ኃይል ላይ ከፍተኛ ሰብአዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ አድርሷል። ​የጠላት ኃይል መነሻውን ላይ አርማጭሆ ወረዳ ቆላ ሮቢት ከተማ በማድረግ ሌሊቱን ሙሉ ወደ ጋና ዮሐንስ ቀበሌ ሲጓዝ አድሮ ትንኮሳ ለማድረግ ቢሞክርም ቀድሞ መረጃው የነበራቸው የብርጌዷ ቃኝ ሻለቃ ከፍተኛ ምት እንዲያፍበት አድርገዋል ። ​በዚህ ቅንጅታዊ ወታደራዊ እርምጃ በጠላት በኩል የደረሰ ሰባዊና ቁሳዊ ኪሳራ ፦ ➛31 የአድማ ብተና እና የሚሊሻ አባላት ሙትና ቁስለኛ፤ ➛5 ክላሽ ኮቭ እና 2 የቃታ መሳርያ ከነ ተተኳሹ ፤ ➛5 የጠላት ስልክ እና የወገብ ትጥቆች ተማርከዋል ሲል መረጃውን ያደረሰን የኮሩ የህዝብ ግንኙነት ነው። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ​አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ከሃዲ ኑሮው የአሳማ፤ ሞቱ የውሻ ነው! መቶ አለቃ ዳኜ ደነቀው የተባለ ግለሰብ አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 109ኛ ኮር ከ77ኛ ክፍለ ጦር ቢተው አለነ ሻለቃ በመክዳት አንድ ክላሽና ብሬን በመያዝ ማንኩሳ
+1
ከሃዲ ኑሮው የአሳማ፤ ሞቱ የውሻ ነው! መቶ አለቃ ዳኜ ደነቀው የተባለ ግለሰብ አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 109ኛ ኮር ከ77ኛ ክፍለ ጦር ቢተው አለነ ሻለቃ በመክዳት አንድ ክላሽና ብሬን በመያዝ ማንኩሳ ከተማ ለሰፈረው አምባገነን ብል(ፅ)ግና ስርዓት እጅ የሰጠው ባንዳ በሰርጎገብ ቆንጆዎች ዛሬ ተሸኝቷል። አፋብን|ቴዎድሮስ ዕዝ ነሐሴ 6/2018 ዓ/ም

ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር በመገጭ ግድብ ዙሪያ በሰፈረው የጠላት ኃይል ላይ ጥቃት ፈጸመ! ​አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ፣ ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር አካል የሆነው ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር፤ በስሩ ከሚገኙ አሃዶች ማለትም ከአፄ ፋሲለደስ፣ ከጎንደር፣ ከቃኘው እና ከቴዎድሮስ ብርጌዶች በተወጣጡ አመራሮችና አባላት አስተባባሪነት ነሐሴ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ሰዓት ጀምሮ በመገጭ ግድብ ዙሪያ በሰፈረው የብልፅግና ሠራዊት ላይ የተቀናጀ ጥቃት ሰንዝሯል። ​በክፍለ ጦሩ አመራሮችና አባላት ቅንጅት በተመራው በዚህ አውደ-ውጊያ የጠላት ኃይል በከፍተኛ ድንጋጤና ውጥረት ውስጥ በመግባት ከአዘዞ ካምፕ በ ዙ-23 የታገዘ ተጨማሪ እግረኛ ሠራዊት በማስጠጋት እራሱን ለመከላከል ሲጥር ያመሸ ሲሆን፣ በዚህም ምክንያት በጎንደር እና በጠዳ ከተሞች ከፍተኛ ወታደራዊ ውጥረት ሰፍኖ አድሯል። ​በዚህ አውደ-ውጊያ 5 ሲደመሰሱ፣ ከ10 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ቀላልና ከባድ ጉዳት አስተናግደዋል ሲል መረጃውን ያደረሰን የክፍለ ጦሩ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ነው። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ​አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

የመሀመድ ተሰማ ጦር በኢቲዮ-ቴሌኮም የህዝብ መገልገያ ታወር ላይ ያደረሰው ጥፋት!! ========================= ......ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም ሞጣ በሁለት እጁ እነሴ ወረዳ አስቴሪዮ በምትባል ታዳጊ ከተማ ላይ ከሐምሌ 26_ነሐሴ 02/2018 ዓ.ም መሽጎ የቆየው የህዝብ መገልገያ ተቋማትን ካምፕ እና ምሽግ በማድረግ አስቴሪዮ ከተማ ላይ የሚገኘውን የኢትዮ-ቴሌኮም ታወር ካምፕ በማድረግ ለ1ሳምንት መሽጎ በመቆየት ህዝቡ የስልክ አገልግሎት እንዲቋረጥ የሶላር ሲስተም ባትሪወችን እና ፓኔሎችን ሙሉ የኤሌክትሪክ መስመሩን በመቆራረጥ እና ቦክሶችን በመሰባበር ጉዳት ያደረሰ ሲሆን በከተማው ውስጥ የሚገኙ በርካታ የንፁሀን መኖሪያ ቤቶችን ሱቆቹን እና ሆቴሎችን በመዝረፍ ነሐሴ 3 የዘረፋቸውን እቃ በተሽከርካሪ ጭኖ ወጥቷል። የ54ኛ ክ/ጦር የሁለት እጅ እነሴ ወረዳ ጊዜያዊ መንግስት እና የፀጥታ ዘርፍ ተጠሪወች የኢትዮ -ቴሌኮም ባለሙያወችን በማስመጣት ጥገና ተደርጎለት አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ ሁለተኛ ቀን የወሰድ በባለሙያወች የመጠገን ስራ እየተሰራ ይገኛል። ለሀገር ሰላም እና ደህንነት ነው የወጣው የሚለው የአብይ ዙፋን አስጠባቂ በተግባር ሲገለጥ ይኸው ነው.. የኢቲዮ-ቴሌኮም ባለሙያወች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ላደረጋቹህት ረብርብ በ201ኛ ኮር ስም ምስጋናየን አቀርባለሁ። የአፋብን ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት