ch
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

前往频道在 Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

显示更多
2 940
订阅者
-1524 小时
+287 天
+37030 天
帖子存档
ፋኖ እና የአባት አርበኞች በባሶና ወረና ወረዳ የአገዛዙ ጥምር ጦር ላይ አስደናቂ ርምጃ ወሰዱ ​ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ​በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ኮር የነጎድጓድ ክፍለ ጦር ስር የሚንቀሳቀሱት የፋኖ ሰራዊት እና የአባት አርበኞች በትናንትናው ዕለት (ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም) በደብረብርሃን ዙሪያ በሚገኘው ባሶና ወረና ወረዳ ልዩ ስሙ "ጨርቆስ" በተባለ ቦታ ላይ በተደረገ ውጊያ በብልፅግና ጥምር ጦር ላይ ድል መቀናጀታቸውን የግንባር መረጃዎች አስታወቁ። ​ከመንዲዳ እና ከአንጨቆረር ከተሞች በሶስት አቅጣጫዎች የተንቀሳቀሰው የአገዛዙ ሰራዊት፣ የክ/ጦሩ ቃኝወችን እና የአካባቢውን የአባት አርበኞች ከበባ ውስጥ ለማስገባት ሙከራ ያደረገ ቢሆንም፤ያሰበው ሳይሳካለት ቀርቶ እራሱ ከበባ ውስጥ ገብቶ ከሌሊቱ 10:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 06:30 ሰዓት ድረስ በቆየው ከባድ ውጊያ፣ የአገዛዙ ሰራዊት ተገቢ ምት አስተናግዷል። በዚህም ▸ከ10 በላይ የአገዛዙ ሰራዊት አባላት መሞታቸው፣ ▸ከ17 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ከባድ ቁስለኛ መሆናቸው ታውቋል። ▸በተጨማሪም በርካታ ተተኳሽ መሳሪያዎች፣ የብሬን ሸንሸል፣ ወታደራዊ የደንብ ልብሶች እና ሬሽኑ በፋኖ እና በአባት አርበኞች እጅ ገብቷል። ​​የነጎድጓድ ክፍለ ጦር ሪፖርተር ክፍል እንደገለጸው፣ የአገዛዙ ሰራዊት ሽንፈት ከገጠመው በኋላ በጨርቆስ ቀበሌ የሚገኘውን ቤተክርስቲያን ለማቃጠል ሙከራ አድርጓል። ይህንን ድርጊት የተቃወሙና " በልመና የተከላከሉ" የሃይማኖት አባቶች ላይ ድብደባና ዘረፋ የተፈጸመባቸው ሲሆን፣ 4 ንጹሃን ዜጎችም መረሸናቸው ታውቋል። ​ድርጊቱን ተከትሎ የአካባቢው ነዋሪዎች ከፍተኛ ቁጣን የገለጹ ሲሆን፣ ከዚህ በኋላ ራሳቸውን ለመከላከል ትግሉን ወደ "ህዝባዊነት" እንደሚቀይሩት ገልፀዋል ። ምንጭ-የአፄ ዘረያዕቆብ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል ክብር ለትግሉ ሰማዕታት ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

የብልፅግና ሰራዊት አባላት ሦስት ጥቁር ክላሽ በመያዝ  303ኛ አሳምነዉ ኮርን  ተቀላቅለዋል!! መነሻቸውን ከቡግና ወረዳ አይና ከተማ ያደረጉ  ሦስት መሠረታዊ የጁላ ሰራዊት አባላት አገዛዙን በመቃወም ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ/ም የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር 19ኛ (ተፈራ ማሞ) ክፍለ ጦርን ተቀላቅለዋል። የተቀላቀሉ አባላትም:- 1.  መሰረታዊ ወታደር ናቃቸው አብራራው 2.  መሰረታዊ ወታደር አለበል አባቸው 3.  መሰረታዊ ወታደር ተመስገን አበራ የተባሉት ከ204 ኮር 38 ክፍለ ጦር 5ኛ ሻለቃ 3ኛ ሻምበል 3ኛ መቶ የመጡ ሲሆን:-    👉 ሦስት ጥቁር ክላሽ    👉 ስድስት የክላሽ ካዝና    👉 542 የክላሽ ተተኳሽ    👉 ሦስት የወገብ ትጥቅ    👉 ስድስት የእጅ ቦምብና ሌሎች ወታደራዊ ቁሳቁሶችን በመያዝ ተቀላቅለዋል። አባላቱ አያይዘውም ፋኖዎቹ ያደረጉላቸውን አቀባበል አመስግነው በመከላከያ ተቋም ዘረኝነትና ባለጊዜነት መኖሩን አሳውቀው አማራ ክልል ሳንገባ ወደ ቀይ ባህር ወደብ ለማስመለስ እንደምንላክና ለእናት ሐገር ግዳጅ እንድንዘጋጅ ተነግሮን ነበር ሲሉ ቃላቸውን ሰጥተዋል። ኦሮምያ ክልል እያለን ብሬንና ስናይፐር ተኳሽ የነበርነው አብዛሃኛው አማራ የነበርን ቢሆንም ከሦስት ወር በፊት አማራ ክልል ስንገባ እኛ አማራዎችና የሌሎች ብሔር ተወላጆች የቡድን መሳሪያዎችን እንዳንይዝ ተከለከልን። አሁንም ከ30 በላይ የአማራ ተወላጆች የመከላከያ ሰራዊት አባላት ገና በጥርጣሬ ይሔዳሉ ተብለው የታሰሩ ሲሆን እናንተም ትሔዳላችሁ ተብለን ታስረንና ተጠይቀን ነበር። እኛም የአሁኑ የመከላከያ ተቋም ለሐገር ሉዓላዊነትና ዳር ደንበር መከበር፣ እንደ ሐገር መታፈር እንዲሁም ትክክለኛ ትግል እንዳልሆነና የፋኖ ትግል ብሶት የወለደው ትክክለኛ፣ ሃቀኛና የህልውና ትግል መሆኑን ተረድተን በትክክል አማራው ሲታረድና ሲገደል ስላየን ተገቢ ትግል ነው በሚል ወደ ፋኖ መንደር ተቀላቅለናል ብለዋል ሲል የ303ኛ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን  መምሪያ!!      ሰኔ:-14/ 2018 ዓ/ም

የድል_ዜና፦ 102ኛ ኮር ኮሶበር_በጀግኖች_እጅ_ገባች ༻༺༻༺༻༺༻༺ ሰኔ 14/2018 ዓ.ም በዐፋብን ምዕራብ ዐማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 102ኛ ኮር በ33ኛ ክፍለ-ጦር የተደረገው የተጠና እና ፈጣን
የድል_ዜና፦ 102ኛ ኮር ኮሶበር_በጀግኖች_እጅ_ገባች ༻༺༻༺༻༺༻༺ ሰኔ 14/2018 ዓ.ም በዐፋብን ምዕራብ ዐማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 102ኛ ኮር በ33ኛ ክፍለ-ጦር የተደረገው የተጠና እና ፈጣን የማጥቃት ኦፕሬሽን በድል ተጠናቋል። በቋሪት ወረዳ ብር አዳማ ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው ኮሶበር አካባቢ በተካሄደው እርምጃ፣ የጠላት ኃይል ላይ ከባድ ጉዳት በማድረስ ኮሶበርን መቆጣጠር ተችሏል። የ33ኛ ክፍለ-ጦር 4ኛ ሻለቃ በአጭር ጊዜ በፈጸመችው የማጥቃት እርምጃ፣ የጠላት አመራርና አባላት ላይ ከባድ ኪሳራ መድረሱ ተገልጿል። ከድሉ ገጸ-በረከቶች መካከል በብልጽግና 302ኛ ኮር 76ኛ ክፍለ ጦር 5ኛ ሬጅመንት የ2ኛ ሻምበል አዛዥ ሻለቃ "አበራደሸ ዲቃቃ" እና ቁጥራቸው ያልታወቀ አባላት ይህችን ዓለም ሲሰናበቱ፤ በካምፕ የነበረ ሙሉ ሬሽን 12 ወታደራዊ ሻንጣዎች፣ አንድ ጥቁር ክላሽንኮቭ ከሙሉ ጥይቱ ጋር፣ አንድ ባለ85 ጉድጓድ የብሬን ሸልሸል ከነጥይቱ፣ ፍራሽ እና ሌሎች ወታደራዊ ቁሳቁሶች በምርኮ መያዛቸው ተነግሯል። በነጎድጓዱ ሻለቃ ገበያው ሽመላሽ መሪነት የተካሄደው ኦፕሬሽን በተሳካ ሁኔታ ተጠናቆ፣ ኮሶበር ከጠላት ተጽዕኖ ነጻ መውጣቷ ተገልጿል። ▶ ድል ለሕዝብ ነው! ▶ የጀግኖች መስዋዕትነት የነጻነት መሠረት ነው!

ሰበር ሰበር!!! የድል ዜና ዘመቻ አርበኛ ፈንታሁን ገበየሁ በመደምሰስ፣ በመማረክ እና ባንዳን በመቅጣት በስኬት ቀጥሏል። ሁለተኛ ቀኑን ያስቆጠረው ማለትም ትናንት ሰኔ 13/2018 የጀመረው ልክ እንደ አፄ ቴዎድሮስ ከጠላት ጋር ሲፋለም ውሎ ሰኔ 10/2018 ተተኳሹን ሲጨርስ በራሱ ሽጉጥ መስዋትነትን የከፈለው ታላቁ አርበኛ ፈንታሁን ገበየሁ የከፈለውን ታላቅ ተጋድሎ ምክንያት በማድረግ ጀግና ቢሞት ጀግና ይወለዳል ይሉሻል እንዲህ ነው። በመተማ ወረዳ ዳስጉንዶ እና አካባቢው ላይ የሰፈረውን የአማራ ደም መጣጭ የአገዛዙ ጥምር አራጅ ቡድን በአይበገሬዎቹ አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ (፪ኛ) ኮር ካራማራ ክ/ር በአርበኛ አጠቃ ሞገስ የተመራው ነበልባሉ የበረሀው ነብሮች ጠላትን በመደምሰስ፣ በመማረክ ቀጠናውን እያፀዱ ታላቅ ድል በማስመዝገብ ታሪክ እየሰሩ ይገኛሉ። አሁንም የአገዛዙ ጭራቅ ስብስብ መውጫ መግቢያ አጥቶ ጠራሞት ላይ ይገኛል ሲል የክ/ሩ የህ/ግ አርበኛ ቴዎድሮስ ግዛው መረጃውን አድርሶናል። በትናንትና እና በዛሬው እለት የተገኘ ድል: -የተደመሰሰ= ከ60 በላይ የአርበኛ ደጀኔ መንግስቱ ገዳይ እና አሁን የፀረሽምቅ መሪ የሆኑት ሁለቱ ትልልቅ ባንዳዎች እባቡ አላየ እና ይርታው አደራጃው ተደምስሰዋል። - ከ25 በላይ እጅ የሰጠ - 90 የነፍስ ወከፍ ክላሽ ፣ 2 ኢንፎርቲና 5 ብሬን ተማርኳል፣ ከ 15,000 በላይ ተተኳሽ እና መሰል ቁሳቁሶች ገቢ ሆነዋል አንድ ጀግና ሲሰዋ እሽ ጀግና ይወለዳል!!! በጀግናው አርበኛ ስም የጀመረው ዘመቻ አሁንም እንደቀጠለ ይገኛል። ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!! አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ (፪ኛ) ኮ/ር የህ/ግ    ሰኔ 14/2018

ፋኖ እና የአባት አርበኞች በባሶና ወረና ወረዳ የአገዛዙ ጥምር ጦር ላይ አስደናቂ ርምጃ ወሰዱ ​ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ​በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ኮር የነጎድጓድ ክፍለ ጦር ስር የሚንቀሳቀሱት የፋኖ ሰራዊት እና የአባት አርበኞች በትናንትናው ዕለት (ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም) በደብረብርሃን ዙሪያ በሚገኘው ባሶና ወረና ወረዳ ልዩ ስሙ "ጨርቆስ" በተባለ ቦታ ላይ በተደረገ ውጊያ በብልፅግና ጥምር ጦር ላይ ድል መቀናጀታቸውን የግንባር መረጃዎች አስታወቁ። ​ከመንዲዳ እና ከአንጨቆረር ከተሞች በሶስት አቅጣጫዎች የተንቀሳቀሰው የአገዛዙ ሰራዊት፣ የክ/ጦሩ ቃኝወችን እና የአካባቢውን የአባት አርበኞች ከበባ ውስጥ ለማስገባት ሙከራ ያደረገ ቢሆንም፤ያሰበው ሳይሳካለት ቀርቶ እራሱ ከበባ ውስጥ ገብቶ ከሌሊቱ 10:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 06:30 ሰዓት ድረስ በቆየው ከባድ ውጊያ፣ የአገዛዙ ሰራዊት ተገቢ ምት አስተናግዷል። በዚህም ▸ከ10 በላይ የአገዛዙ ሰራዊት አባላት መሞታቸው፣ ▸ከ17 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ከባድ ቁስለኛ መሆናቸው ታውቋል። ▸በተጨማሪም በርካታ ተተኳሽ መሳሪያዎች፣ የብሬን ሸንሸል፣ ወታደራዊ የደንብ ልብሶች እና ሬሽኑ በፋኖ እና በአባት አርበኞች እጅ ገብቷል። ​​የነጎድጓድ ክፍለ ጦር ሪፖርተር ክፍል እንደገለጸው፣ የአገዛዙ ሰራዊት ሽንፈት ከገጠመው በኋላ በጨርቆስ ቀበሌ የሚገኘውን ቤተክርስቲያን ለማቃጠል ሙከራ አድርጓል። ይህንን ድርጊት የተቃወሙና " በልመና የተከላከሉ" የሃይማኖት አባቶች ላይ ድብደባና ዘረፋ የተፈጸመባቸው ሲሆን፣ 4 ንጹሃን ዜጎችም መረሸናቸው ታውቋል። ​ድርጊቱን ተከትሎ የአካባቢው ነዋሪዎች ከፍተኛ ቁጣን የገለጹ ሲሆን፣ ከዚህ በኋላ ራሳቸውን ለመከላከል ትግሉን ወደ "ህዝባዊነት" እንደሚቀይሩት ገልፀዋል ። ምንጭ-የአፄ ዘረያዕቆብ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል ክብር ለትግሉ ሰማዕታት ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

ፋኖ እና የአባት አርበኞች በባሶና ወረና ወረዳ የአገዛዙ ጥምር ጦር ላይ አስደናቂ ርምጃ ወሰዱ ​ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ​በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ኮር የነጎድጓድ ክፍለ ጦር ስር የሚንቀሳቀሱት የፋኖ ሰራዊት እና የአባት አርበኞች በትናንትናው ዕለት (ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም) በደብረብርሃን ዙሪያ በሚገኘው ባሶና ወረና ወረዳ ልዩ ስሙ "ጨርቆስ" በተባለ ቦታ ላይ በተደረገ ውጊያ በብልፅግና ጥምር ጦር ላይ ድል መቀናጀታቸውን የግንባር መረጃዎች አስታወቁ። ​ከመንዲዳ እና ከአንጨቆረር ከተሞች በሶስት አቅጣጫዎች የተንቀሳቀሰው የአገዛዙ ሰራዊት፣ የክ/ጦሩ ቃኝወችን እና የአካባቢውን የአባት አርበኞች ከበባ ውስጥ ለማስገባት ሙከራ ያደረገ ቢሆንም፤ያሰበው ሳይሳካለት ቀርቶ እራሱ ከበባ ውስጥ ገብቶ ከሌሊቱ 10:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 06:30 ሰዓት ድረስ በቆየው ከባድ ውጊያ፣ የአገዛዙ ሰራዊት ተገቢ ምት አስተናግዷል። በዚህም ▸ከ10 በላይ የአገዛዙ ሰራዊት አባላት መሞታቸው፣ ▸ከ17 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ከባድ ቁስለኛ መሆናቸው ታውቋል። ▸በተጨማሪም በርካታ ተተኳሽ መሳሪያዎች፣ የብሬን ሸንሸል፣ ወታደራዊ የደንብ ልብሶች እና ሬሽኑ በፋኖ እና በአባት አርበኞች እጅ ገብቷል። ​​የነጎድጓድ ክፍለ ጦር ሪፖርተር ክፍል እንደገለጸው፣ የአገዛዙ ሰራዊት ሽንፈት ከገጠመው በኋላ በጨርቆስ ቀበሌ የሚገኘውን ቤተክርስቲያን ለማቃጠል ሙከራ አድርጓል። ይህንን ድርጊት የተቃወሙና " በልመና የተከላከሉ" የሃይማኖት አባቶች ላይ ድብደባና ዘረፋ የተፈጸመባቸው ሲሆን፣ 4 ንጹሃን ዜጎችም መረሸናቸው ታውቋል። ​ድርጊቱን ተከትሎ የአካባቢው ነዋሪዎች ከፍተኛ ቁጣን የገለጹ ሲሆን፣ ከዚህ በኋላ ራሳቸውን ለመከላከል ትግሉን ወደ "ህዝባዊነት" እንደሚቀይሩት ገልፀዋል ። ምንጭ-የአፄ ዘረያዕቆብ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል ክብር ለትግሉ ሰማዕታት ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

ወለጋ ቢዛሞ ቀጠና አይሻ ሰይድ ዕዝ ትናንት በምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ ሓሮ አከባቢ ባደረገው ተጋድሎ ከማረካቸው ምርኮኛ የአገዛዙ ወታደሮች መካከል በጥቂቱ። *** ፀረ አማራውና ሃገር አፍራሹ የብፅግና አገዛዝ በጦር ጀት፣ በሰው አልባ አውሮፕላን፣ በመድፍ፣ በአየር መቃዎሚያና በሌሎች ከባባድ መሣሪያዎች ሽፋን ሰጭነት፡ ከማዕከላዊ ዕዝ ሠራዊት በተጨማሪ የኦሮሚያ ክልል ልዩ ኃይልንና የገዳ ልዩ ኮማንዶን በሚኒሻና አድማ ብተና መንገድ መሪነት አሰልፎ ከትናንት ሰኔ 13/2018 ዓ/ም ጀምሮ በሆሮጉድሩ ወለጋ እና በምስራቅ ወለጋ ዞኖች ላይ ንፁኋንን ኢላማ ያደረገ ጥቃት መክፈቱን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል። እራስን ከእልቂት የመታደግ ተፈጥሯዊ መብቱን ተጠቅሞ የተደራጀውና ብሶት የወለደው ጀግናው የአይሻ ሰይድ ዕዝ ሠራዊት ብርቱ የሆነ የፀረ ማጥቃት እርምጃ በመውሰድ የሕዝቡን ሕልውና ለማረጋገጥ የሚያደርገውን ተጋድሎ አጠናክሮ ቀጥሏል።

አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ሚኒሊክ ዕዝ 106ኛ ኮር 31ኛ ሰንጥቅ ክፍለጦር በዳውንት ወረዳ የአገዛዙን ሰራዊት ዶግ አመድ ሲደረግ ፤የፋኖን ከባድ በትር መቋቋም የተሳነው ሰራዊት በአብሪ ጥ ተራራዎችን እና የአርሶአደር የግጦሽ መሬቶችን ሲያቃጥል ውሏል!! ሰኔ 14/2018 ዓ/ም በዳውንት ወረዳው  09 ቀበሌ ሰንተል በተባለ ቦታ ላይ በተደረገ አውደ ውጊያ በርካታ የጥላት ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ ተደርገዋል። አገር ሰላም ብሎ በሰልፍ ሲግተለተል በነበረ የአገዛዙ ሰራዊት ላይ የ31ኛ ሰንጥቅ ክፍለጦር አካል የሆነችው ሻለቃ አንድ በፈፀመችው መብረቃዊ ጥቃት እጅጉን የተጎዳው የጥላት ሰራዊት አህያውን ፈርቶ ዳውላውን ይሉ ዘንድ የግሃ ማርያም ጥቁር አምባ ተራራን በሞርተርና ድሽቃ ሲደበድብ የዋለ ሲሆን፤አማራን መቃብሩን ቆፍረንም ቢሆን አፅሙን  እናቃጥለዋለን እንዳሉት በአብሪ ተተኳሽ ተራራውን በመደብደብ ሙሉ ለሙሉ አካባቢውን በእሳት አቃጥለውታል። በዳውንት ወረዳ አመራሮች አጋርና ተባባሪነት በአብሪ ጥይት ሲደበደብ የዋለው ተራራና ደን ይህ ዜና አየር ላይ እስከዋለበት ሰዓት የቃጠሎ አድማሱን አስፍቶ በተራራውና በደኑ ያሉ እንስሶችም ጭምር በነድዱ እየተቃጠሉ ይገኛሉ። በወረዳው ሎሌዎች የተሰነዘረው የኦህዴድ ጡንቻ  አማራዊ ጥላቻውን እንስሳት፣እፅዋት፣ምድርና ሳር ቅጠል ሳይል የጥፋት እኩይ ተግባሩን እየፈፀመ ይገኛል። መዳረሻውን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 106ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሰኔ 14/2018 ዓ/ም

ሰበር- በወለጋ ቢዛሞ ንፁኋንን ለመጨፍጨፍ በታንክ ሽፋን ታግዞ ሲንቀሳቀስ በነበረ የጠላት ኃይል ላይ በተፈፀመ የሽምቅ ጥቃት በርካታ ወታደሮች ተደመሰሱ። በወለጋ ቢዛሞ ከሆሮጉድሩ ወለጋ ቱሉጋና ከተማ ወደ ምስራቅ ወለጋ ሓሮ አከባቢ በሚገኙ ንፁኋኖች ላይ ጥቃት ለመፈፀም በእንቅስቃሴ ላይ በነበረ የጠላት ብልፅግና መከላከያ ሠራዊት ላይ የአይሻ ሰይድ ዕዝ አርበኞች በወሰዱት የቆረጣ-ሽምቅ እርምጃ የጠላትን አከርካሪ ሰብረው አንፀባራቂ ድል ተቀዳጅተዋል። በአይሻ ሰይድ ዕዝ የአንገር ጉትን ክፍለጦር አርበኞች ዛሬ ሰኔ 13/2018 ዓ/ም አመሻሹን በሁለት ኦራል ተጭኖ በታንክ ሽፋን በመታገዝ ሲንቀሳቀስ የነበረ የጠላት ኃይልን እንዳይሸሽና እንዳያመልጥ በመቁረጥና፡ ዙሪያ ገባውን በመቆለፍ ከነተሽከርካሪው ዳሽቆ እንዲቀር ማድረግ ችለዋል። በላያቸው ላይ የሚያንዣብበውን የጠላት የጦር ጀትንና ድሮንን እንዲሁም የታንክና የመድፍ መርመስመስን ከመጤፍ ያልቆጠሩት በአይሻ ሰይድ ዕዝ የአንገር ጉትን ክፍለጦር ጀግኖች፡ ሁለት ተሽከርካሪ ሙሉ የጠላት ኃይልን ቆርጠው ከመምታት ባለፈ፡ ተርፎ ሲሸሽ ከነበረው የጠላት ኃይል ጋር እጅ በእጅ የሳንጃውግ ጨበጣ ውጊያ ጭምር በመግጠም አኩሪ ገድል ፈፅመዋል። የጠላት ጦር ከወደ ቱሉጋና ከተማ እንዲሁም ከወደ ኡኬና አንገር ጉትን ተጨማሪ ባንቀሳቀሰው በአየር መቃዎሚያና በመድፍ ሽፋን የታገዘ ኃይል ሙትና ቁስለኛውን ጭኖ፡ የወደመውን ተሽከርካሪ በክሬን አስነስቶ ወደ ኋላ ለማፈግፈግ ተገዷል። ግፍ የወለደን፡ ግፈኞችን የምንቀጣ የአይሻ ሰይድ ወንድሞች ነን! በአፋብን ወለጋ (ቢዛሞ) አንሻ ሰይድ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ፋኖ ዳዊት አማረ!

ሰበር የድል ዜና! ​የአማራ ሕዝብን የሕልውና ፅናት እና የፍትሕ የበላይነት ዳግም ያረጋገጠው፣ በወታደራዊ ስትራቴጂ ረገድ የሚሊታሪ ሚዛኑን ሙሉ በሙሉ የቀየረ አንጸባራቂ ድል በወለጋ ምድር ተመዝግቧል። የአፋብን -ወለጋ (ቢዛሞ) ቀጠና አንሻ ሰይድ ዕዝ — ይበልጣል መኮነን አዲስ ዓለም ክፍለ ጦር ፣ ልዩ ቦታው ሾሆሮ መድኃኔዓለም ላይ በወሰደው የተቀናጀና መብረቃዊ የማጥቃት እርምጃ፣ የገዥውን ወራሪ ኃይል አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ታሪካዊ ድል ተቀዳጅቷል። ​ የፋኖን ውጊያ መቋቋም ያቃተውና የሞራል ስብራት የገጠመው የገዥው ሥርዓት ኃይል፣ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶችና የጦርነት ሕጎችን በደፈጠጠ መልኩ፣ ሰሞኑን በሰላማዊው ማኅበረሰብ ላይ ከባድ መሣሪያዎችን — ሞርተር፣ ዙ-23፣ ከባድ መድፍ፣ የጦር ጄቶችን እና የሰው አልባ ድሮኖችን (Drones) — በመጠቀም ንጹኃንን ሲጨፈጭፍ፣ የሕዝብ ሀብትና ንብረትን ሲዘርፍና ሲያወድም ሰንብቷል። ​ ለጥፋትና ለወረራ የተሰማራው ጠላት በኪረሙ ወረዳ ልዩ ቦታው ሾሆሮ መድኃኔዓለም ውስጥ ማዕከላዊ እዝ ህዳሴ ኮር 69ኛ ክፍለ ጦር 3ኛ እና 5ኛ ሬጅመንቶች በጥምረት ታይቶ የማይታወቅ ሽንፈት አስተናግደዋል። ​የውጊያው ውሎና የጠላት ሰብአዊ ኪሳራ ​ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 11:00 ሰዓት ድረስ ለ9 ተከታታይ ሰዓታት በተደረገውና የወለጋን ምድር በጀግንነት ታሪክ ባደመቀው ከባድ ውጊያ፦ ​3ኛው ሬጅመንት፦ በዕዛችን ኃይሎች ፍጹም የበላይነት ሙሉ በሙሉ ተደምስሶ ከውጊያ ውጪ ሆኗል። ​5ኛው ሬጅመንት፦ ሙሉ በሙሉ የመከላከል አቅሙን በማጣቱ፣ የቆሰሉና የተረፉት አባላቱ ትጥቃቸውን እየጣሉ በየጢሻው ወድቀዋል። የክፍለ ጦሩ የልዩ ግዳጅ አባላት የፈረጠጠውን ኃይል እግር በእግር በመከታተል የመልቀምና የመማረክ ሥራውን በላቀ ስኬት አጠናቀዋል። ​ቀኑን ሙሉ በተካሄደው ታሪካዊ ውጊያ በጠላት ኃይል ላይ የደረሰው አጠቃላይ ሰብአዊ ኪሳራ እንደሚከተለው ነው፦ ​የተደመሰሰ (የተገደለ) የጠላት ኃይል፦ 306 ​በምርኮ የተያዘ የሰው ኃይል፦ ​6 ከፍተኛ የጦር መስመራዊ መኮንኖች ​43 የእግረኛ ሰራዊት አባላት ​(የምርኮኞች ሁኔታ፦ ሁሉም ምርኮኞች በጄኔቫ ኮንቬንሽን እና በዓለም አቀፍ የጦር ምርኮኞች ሕግ መሠረት ሙሉ ሰብአዊ አያያዝ እየተደረገላቸው ይገኛል። ​የተማረኩ የጦር መሣሪያዎችና ተተኳሾች ​ይህ ታሪካዊ ድል የወራሪውን ኃይል ወታደራዊ የጀርባ አጥንት የሰበረ ሲሆን፣ የደረሰው የቁሳቁስ ምርኮ ስብስብ፦ ​1  ድሽቃ ​4 የብሬን መሣሪያዎች ​2 ስናይፐሮች ​120 የክላሽንኮቭ ጠመንጃዎች ​1,000 የድሽቃ ተተኳሽ ፍሬዎች ​3,000 የብሬን ተተኳሽ ፍሬዎች ​15000 የክላሽ ጥይቶችና ወታደራዊ ትጥቆች ተማርከዋል። ​የገዥው ሥርዓት የደረሰበትን ታሪካዊ ውድቀት ለመሸሸግ እና በአካባቢው የሚፈጽመውን የሰብአዊ መብት ጥሰት ከዓለም ዓይን ለመደበቅ የኢንተርኔትእና የስልክ መስመሮች ዘግቶ ይገኛል። ይሁን እንጂ የፍትሕ ድምፅ ሊታፈን አይችልም። ይህንን ታላቅ ድል እና የወራሪውን ኃይል ውድቀት የሚያሳዩ የፎቶና የቪዲዮ ዲጂታል ማስረጃዎች በቅርብ ቀናት ውስጥ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ፣ ለሰብአዊ መብት ተሟጋቾችና ለሚዲያ አካላት ይፋ ይደረጋሉ። ​"ይህ የነፃነት፣ የፍትሕ እና የሕዝባችንን ሰብአዊ መብት የማስከበር የተቀደሰ ተጋድሎ ነው። መዳረሻው ሙሉ ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ እስከ ፍጻሜው በጽናት ይቀጥላል!" ​ድል ለጭቆና ቀንበር ለማይበረከከው ሕዝባችን! ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ቢዛሞ/ወለጋ ኢትዮጵያ

የአድማ ብተና እና የሚሊሻ ሀይሎች ፋኖን ተቀላቀሉ የብልፅግና ካምፕ እየፈራረሰ ነው ========================= ሰኔ 13/2018 ዓ.ም ከአገዛዙ ጋር ወግነው የነበሩ የታጠቁ ሀይሎች አድ
+4
የአድማ ብተና እና የሚሊሻ ሀይሎች ፋኖን ተቀላቀሉ የብልፅግና ካምፕ እየፈራረሰ ነው ========================= ሰኔ 13/2018 ዓ.ም ከአገዛዙ ጋር ወግነው የነበሩ የታጠቁ ሀይሎች አድማ ብተና እና ሚሊሻ ከመርጦ ለማሪያም እና ከደብረወርቅ ከተማ በመውጣት 201ኛ ኮር 74ኛ ክፍለ ጦርን ተቀላቅለዋል። 1.የሸዋስ ታድሎ...... ኮሪያ 2.አየነው መንግስት.....ኮሪያ 3.ምኒችል ገደፋው.....ሰሜን ክላሽ 4.ደጓለ አይተነው......ቁም ክላሽ በመያዝ 74ኛ ክ/ጦርን የተቀላቀሉ ሲሆን በክፍለ ጦር አመራሮችም ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። አሁንም ጊዜው አልረፈደም ወደ ትክክለኛ ማንነታቹህ ተመለሱ የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

አይበገሬው 64ኛ ክፍለ ጦር የ3 ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማውን በ3 ቀናት ስብሰባ አጠናቆ ወደ ሥራ ገባ ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር አይበገሬው 64ኛ ክፍለ ጦር የ3 ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማውን በስኬት አጠናቋል። ክፍለ ጦሩ ላለፉት ሦስት ቀናት ባካሄደው በዚህ መድረክ የወቅቱን የትግል ሁኔታ በጥልቀት የዳሰሰ ሲሆን፣ አደረጃጀቱን ይበልጥ በማጠናከር ወደ ቀድሞ ቁመናው የመመለስ ሰፊ ሥራዎችን አከናውኗል። ከግምገማ መድረኩ የተገኙ ዋና ዋና ነጥቦች እንደሚከተለው ቀርበዋል፦ 64ኛ ክፍለ ጦር በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ ውስጥ የሚገኝ አንጋፋ ክፍለ ጦር መሆኑን የጠቀሱት አመራሮቹ፤ ክፍለ ጦሩን ለማፍረስ ከውስጥና ከውጭ ያሉ ጠላቶች በማኅበራዊ ሚዲያ የሐሰት ስም የማጥፋት ዘመቻ በተደጋጋሚ ቢከፍቱም፣ በትግሉ ውስጥ ሰርገው የገቡ ስውር እጆችን ቆርጦ በመጣል የክፍለ ጦሩን አንድነት ማስጠበቅ ተችሏል። ክፍለ ጦሩ በቀጠናው ብቁ የሆኑ ልዩ ኮማንዶዎችንና የሰለጠነ የሰው ኃይል በማፍራት ረገድ ከፍተኛ ስኬት አስመዝግቧል። በተጨማሪም ጠላት ከታጠቃቸው በላይ በርካታ የነፍስ ወከፍና የቡድን መሣሪያዎችን በመታጠቅ ድርጅቱን፣ መሪዎቹንና ሕዝቡን በንቃት እየጠበቀ እንደሚገኝ ተገልጿል። የጀግኖች መስዋዕትነት ያለበትን የትጥቅ ትግል ወደኋላ ለመጎተትና የግል ጥቅማቸውን ለማካበት በትግሉ ውስጥ ሰርገው ለመግባት የሞከሩ አካላት ያቀረቡት አጀንዳ ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዳይሆን ተደርጓል። ክፍለ ጦሩ ባለፉት 3 ወራት ባከናወናቸው ወታደራዊና አስተዳደራዊ ተግባራት፣ በጊዚያዊ መንግሥት ከወረዳ እስከ ቀበሌ ባሉ መዋቅሮች አሠራር እንዲሁም በክፍለ ጦሩ ሥር ባሉ ሻለቃዎች ግንኙበትግል ሪያ የነበሩ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመገምገም ለቀጣይ ክፍተቶችን ለመሙላት የሚያስችል አቅጣጫ አስቀምጧል። አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክፍለ ጦር ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ

የፋኖን ምት መቋቋም ያቃተው የብልፅግና ሰራዊት ንፁሃን አማራዎችን መረሸኑን ኃብትና ንብረታቸውን መዝረፉንና ማውደሙን አጠናክሮ ቀጥሎበታል! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር በሚንቀሳቀስባቸው አካባቢዎች የፋኖዎችን አለመኖር ተከትሎ በአርበኞቹ ብርቱ ክንድ ሲቀጠቀጥ የሰነበተው የአገዛዙ ሰራዊት በተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር በንፁሐን የማህበረሰብ ክፍሎች ላይ የበቀል በትሩን እያሳረፈ ይገኛል። ላስታ ወረዳ 04 ሳርዝና ቀበሌ በመግባት የብድር ብር አውጥተው የሚነግዱ ነጋዴዎችን ሐብትና ንብረት ዘርፎ ወደ ላሊበላ ከተማ በሦስት መኪናዎች ጭኖ በመውሰድ የፋኖን ሎጅስቲክ ጭነን አመጣን እያሉ ለላሊበላ ከተማ ህዝብ የሐሰት ፕሮፓጋንዳውን ሲነዛ ውሎ አድሯል። ሳርዝና ቀበሌ ላይ የነጋዴ አድሴ ወዳጁንና የነጋዴ ደርብ ሲሳይ የተባሉ ግለሰቦችን ንብረት ማለትም:-     ፨ የነጋዴ አድሴ ወዳጁን:-    👉 ለንግድ የመጣ 120 ኩንታል ማሽላ    👉 30 ኩንታል ጤፍ    👉 20 ኩንታል ሽምብራ    👉 15 ኩንታል ባቄላ ለትርፍ የተገዛ    👉 28 ኩንታል ስንዴ    👉 37 ጀሪካን ናፍታ ለወፍጮ የተገዛ    👉 ለክረምት የተዘጋጀ ስድስት ኪሎ አብሽ፣        አንድ ባልዲ ሽሮ፣ 10 ሊትር ባልዲ በርበሬ፣        አንድ በርሜል ዱቄት እና ሙሉ የቤት እቃ     ፨ የነጋዴ ደርብ ሲሳይን:-    👉 ሁለት ሴንጀር ባለ ዲናሞ የልብስ ስፌት          ማሽን (2×60,000 =120,000 ብር)    👉 25,000 ብር የተገዛ የወንድ ጣቃ ልብስ    👉 15,000 ብር የተገዛ የሴት ጣቃ ልብስ የሚላስ የሚቀመስ ሳያስቀር አፋፍሶ ወስዶባቸዋል። በዚህም ያልበቃው ምስለኔ የብልፅግና ጋሻ ላስታ ወረዳ 02 ብልባላ ገጠሩ ቀበሌ አርጨቆ ተክለሐይማኖት ደብር ጣይዱባ ከሚባል ቦታ በመግባት የአንድ ቤተሰብ አባላት በመደብደብና ከቤታቸው እንዲወጡ በማድረግ የበሰለ እህልውኃቸውን እንደ ግሪሳ ካወደሙ በኋላ እህል ሽጠው ማዳበሪያ ለመግዛት ያስቀመጡትን 25 ሽህ ብር እንዲሁም ገዳማይት ደብር የአንድን ግለሰብ 5 ሽህ በመዝረፍና የ10፣ የ12 እና የ15 ዓመት የአንድ ቤተሰብ ህፃናትን እየደበደቡ ወደ ብልባላ ከተማ ወስዶ በማሰር የጭካኔ ጥጉን አሳይቷል። በተጨማሪም ሰሞነኛውን የፋኖን ምት መቋቋምና ማስተባበል ያቃተው የብርሐኑ ጁላ ሰራዊት የአማራ ንፁሃን ላይ የፍርሃት በትሩን ያሳረፈ ሲሆን ቡግና ወረዳ 012 ቆብ ቀበሌ አጠልዝባ ስላሴ ወይዘሮ ደመቅ አዱኛው በላይ ባለትዳርና የሁለት ልጆች እናት፣ አቅላ ሚካኤል ወይዘሮ ሰውነት ማሞ ባለትዳርና የአራት ልጆች እናት፣ 011 ብርኳኳ ቀበሌ ባውዛን የተባለ ቦታ እንስሳት ሲጠብቁ የነበሩ ሁለት ህፃናት በተተኮሰባቸውና በተወረወረባቸው የድሽቃ ጥይትና የሞርታር ቅንቡላ አንድያ ህይወታቸውን ተነጥቀዋል። በተያያዘ መረጃ ቡግና ወረዳ አቅላ ሚካኤል ላይ በተተኮሰ አብሪ የድሽቃ ጥይት የአቶ ገላው ሙጨ ቤት ሲቃጠል ቤቱ ከነሙሉ ንብረቱ እንዲሁም በቤቱ ዙሪያ የነበሩ 25 ቀፎ ንብ አብሮ መውደሙና በተኩስ መሃል ማህበረሰቡ የእሳት ቃጠሎውን ማዳን እንዳልቻለና አገዛዝ መሩ ማህበረሰባዊ በቀል እንደቀጠለ ነው ሲሉ አንዳንድ የህብረተሰብ ክፍሎች ሃሳባቸውን አጋርተዋል ሲል የ303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! አፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ ዕዝ  ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!!          ሰኔ:- 13/ 2018 ዓ/ም

የኦርዲናንስ ሃላፊው የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ ቴዎድሮስ ዕዝን ተቀላቀለ። ሰኔ : 13/2018 ዓ.ም ከአዲስ ቅዳም ከተማ መሽጎ የሚገኘው የብል(ፅ)ግና ወንበር አስጠባቂ ስብስብ በወረዳው ውስጥ በን
+2
የኦርዲናንስ ሃላፊው የአማራ ፋኖ ብሄራዊ  ንቅናቄ ቴዎድሮስ  ዕዝን ተቀላቀለ።    ሰኔ : 13/2018 ዓ.ም ከአዲስ ቅዳም ከተማ መሽጎ የሚገኘው የብል(ፅ)ግና ወንበር አስጠባቂ ስብስብ በወረዳው ውስጥ በንፁሃን ላይ  እያደረሰ ያለውን ግፍ እና በደል የተመለከተው የስርዓቱ የሻለቃ #ኦርዲናንስ #ኢ/ር ጌትነት አስራት  የተባለ የአድማ ብተና አመራር ከአዲስ ቅዳም ከተማ በተለምዶ አባ አይናለም ተብሎ ከሚጠራው የጠላት #ካምፕ በመነሳት ዋርድያው ላይ እርምጃ በመውሰድ፤ ➥ #4 ክላሽ እንኮቭ ➥# 570 የክላሽ ተተኳሽ ➥#2 ቦንብ ➥#1 የወገብ ጥጥቅ በመያዝ  አፋብን  ቴዎድሮስ  ዕዝ 105ኛ ኮር 44ኛ ክ/ጦር የጀግና አቀባበል አድርጎለታል። ፋኖ ይችላል። አዲስ ትውልድ አዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ፤

📌 ደቡብ ጎንደር እስቴ ወረዳ እና ስማዳ ወረዳ አረመኔው ስርዓት ንፁሃንን በግፍ መግደሉን እና ከፍተኛ ቁሳዊ ጉዳቶችን አደረሰ። ===================== ሰኔ 13/2018ዓ/ም አፋብን ሰሜን አማራ በላይ ዕዝ ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ፩ ኮር ጉና ክፍለ ጦር በሚንቀሳቀስባቸው ቀጠናዎች የአብይ አህመድ የብልፅግና ኦህዳድ መራሹ ስራዓት  ፀረ-አማራ ህዝብ ላይ ጦርነት በማወጅ የዘር ፍጅት እየፈፀመ ዛሬ አባብሶ ቀጥሎበታል። ይህ የተኩላ ቡድን በመንትዮች በጦር ሜዳ አናብስቶች እስቴ ዴንሳ ብርጌድ እና ሃገረ ቢዘን ብርጌድ በተደጋጋሜ  በደረሰበት ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ሽንፈትና ውረደት በንፁሃን ማህበረሰብ ላይ  ሒሳቡን እያወራረደ ይገኛል። አገዛዙ በየ ቀጠናው የተለያዩ ጉዳቶችን  እያደረሰ የተጓዘ ቢሆንም  በተለይ ፀዶየ ከተማ ፣በቆማ ፋሲለደስ፣  ከተማ ውስጥ እና በሌሎች አካባቢዎች በህዝቡ ላይ ህይወትን መቅጠፍ፣  ሰብአዊ ጥሰትእና ኢኮኖሚያዊ ጉዳቶች አባብሶ የቀጠለ ሲሆን በዋናነት የሚከተሉትን ያካተተ ነው፦ 🔹ፀዶየ ከተማ  አንድ ወጣት የባጃጅ ሹፊር በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደለ፤ ➥ ቆማ ፋሲለደስ ከተማ አንድ አርሶ አደር መልካም ባንቴ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደለ፤ ➥ ቆማ ፋሲለደስ ከተማ አንድ የግል ክሊኒክ መድሃኒት ቤት ሙሉ በሙሉ ተቃጥሏል፤ ➥ ቆማ ፋሲለደስ ከተማ የግለሰቦች አራት በዝቦልድ አልጋዎች እና በረካታ አልባሳት ተቃጥለዋል፤ ➥  እስቴ ወረዳ ደንባ ቀበሌ አንድ ሞተር ሳይልተ ቃጥሏል፤ ➥ ገበሬዎች የአፈር ማዳበሪያ  ተደፍቷል፤ ➥ አስቴ ወረዳ ደንባ ቀበሌ አንድት ሴት አዳሪ 40 ሊትር አርቄ በጉልበት የተደበደበች በነፃ ታጣቂ ሃይሉ የተጣባት፤ ➥ ደንባ ቀበሌ የግለሰቦችን ናፍጣና ቤንዚል ተዘርፋል፤ ➥ በረካታ ወጣቶች እና አዛውንቶች በምክሬ ከተማ፣ በፀዶየ ከተማ፣ በገና መምቻ፣ በሸንበቆችና ሌሎች ቦታዎች ላይ አካላዊ ጉዳት እና ለእስር ተዳርገዋል። የጥፋት ሃይሉ እጁ በደም የጨቀየው የአብይ የግል ታጣቂ ሃይል ከመካነ-ኢየሱስ እሰከ ቆማ ከተማ ድርስ በህዝብ ላይ የሰብአዊና የኢኮኖሚያዊ ውድመት በከፍተኛ ሁኔታ ጉዳት አድርሷል፤ እያደረሰም ይገኛል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ሜ/ ጀኔራል ውባንተ አባተ፩ኛ ኮር ጉና ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ