Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union
前往频道在 Telegram
This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.
显示更多4 481
订阅者
-124 小时
+147 天
+3130 天
帖子存档
+5
"ለእኔም ለቤተሰቦቼም ዱዓ አድርጉ!" - ከመልዕክቶች አንዱ ነው:: በዚህ በተከበረው ወር ውስጥ ያለውን ኸይር ነገር ሁሉ ይወፍቃቸው:: በአሁኑ ዙር ከጂማ: ወራቤ: ሐዋሳ: AASTU እና አርሲ ተሳትፈዋል:: እንደ አጠቃላይ:-
♧ ከAAU ••• 1200 🎉 🎉 🎉
♧ ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ••• 1100
♧ ከAASTU ••• 450
♧ ሐዋሳ ••• 300
♧ አርሲ ••• 200
♧ ወራቤ ••• 50
ላይ ተቀምጠው 4130 ብር ለወሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መስጂድ ደርሰናል:: ለሰጡት ሁሉ አላህ ይስጥልን:: ከእህት ወንድሞቻቸው ጎን ቆመዋልና አላህ ለሐጃዎቻቸው ሁሉ ይቁምላቸው:: ዱንያ አኼራቸውን አሳምሮ ጀነት በጀነት ያድርግ:: አሚንንን!!!
ቀጣይ ማን ይሆን?
ከየት ይሆን?
ለወሎ ዩኒቨርሲቲ ጤና ካምፓስ ጀመዓ መስጂድ ማለት ነው!!
+4
ተጀምሯል ••• አጅሮች እጥፍ ድርብ በሚሆኑበት የረመዷን ወር ለወሎ ዩኒቨርሲቲ ጤና ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች መስጂድ ማጠናቀቂያ ርብርብ ተጀምሯል ! ! !
♧ ከAAU ••• 1200 🎉 🎉 🎉
♧ ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ••• 600
♧ ከAASTU ••• 250
ሌሎችም ከ30 ብር ጀምሮ የሰጡ ልበቀናዎች አሉ:: አላህ ለሁላቸውም ኸይር ጀዛን ይክፈል:: ከረመዳን በረካ ይግጠማቸው:: ሲሳያቸውን ያስፋ: ጤናቸውን ይሙላ: ኢማናቸውን ያጠንክር: ዱንያ አኼራቸውን ያሳምር:: የእስልምና እህት ወንድማማችነት እንዲህ ነው:: ከሰሜን ያለው ሲጣራ በደቡብ: በምስራቅ: በምዕራብ ያለውም አቤት ብሎ ይመጣል::
አላህ ያበርታን!
ቀጣይስ ማን ይሆን? ከየትስ ይሆን? መሪነቱስ ለማን ይሆን? በኸይር ስራ እንሽቀዳደም !!!
ማሰባሰቢያ አካውንት:- 1000699582976 (Bilal Ethiopian Higher Education Muslim Students Union) --- ያስገባችሁበትን screenshot @eheimsubot ላኩልን::
አላህ ለመልካም ለውጥ ሰበብ ያድርገን!
https://t.me/EHEMSU
Barattoota Muslimaa Kaampaasii Ogeessa Fayyaa Olaanaa Yunivarsiitii Wolloo Masjiida Jumu’aa isaanii ijaaruuf deeggarsa keenya barbaadu! ! !
Masjiidichi tattaaffii barattootaatiin ijaaramaa jira; amma sadarkaa amma irra gaheera. Haa ta’u malee, hanga ammaatti mana fincaanii isaa hin xumuramne, koorniisiin isaa hin hojjetamne, akkasumas hojii giriifii fi lissinii barbaachisu hin raawwatamne. Kanaafis barattoonni rakkoo keessa akka jiran nutti ibsaniiru. Dandeettii mataa isaanii qofaan xumuruun waan hin danda’amneef, dhaabbilee barnoota olaanaa Itoophiyaa keessatti argamnu barattoonni Muslimaa akka isaan gargaaru nu gaafatan.
Kanaafuu akkuma barame wal gargaaruun, rakkoo obboloota keenyaa haa salphifnu. Dandeettii qabnuun wal tumsinee hanqina masjiidootaa naannoo yunivarsiitiiwwanii jiru furuuf haa hojjenne. Barataan masjiida dhabuun miidhaa guddaa yoo ta’u, argachuun isaa immoo faayidaa guddaa qaba. Eeyyama Rabbiitiin mana Rabbii ijaaruun mana Aakhiraa keenya haa ijaarru.
Bismillaah haa jennu!
Eessaa ta’a?
Eenyu ta’a?
Masjiida barattootaatiif!!!
Lakkoofsa herregaa walitti qabinsaa:
1000699582976
(Bilal Ethiopian Higher Education Muslim Students Union)
Maallaqa galchitan screenshot isaa gara @MOHAMMADAMMINM nuuf ergaa.
Rabbiin jijjiirama gaariif sababaa nu haa godhu!
+1
የወሎ ዩኒቨርሲቲ ልዕለ ሕክምና ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ መስጂድ ድጋፋችንን ይሻል ! ! !
መስጂዱ በተማሪዎች ጥረት እየተገነባ አሁን ካለበት ደረጃ የደረሰ ቢሆንም አሁንም ድረስ ሽንት ቤቱ ያላለቀ: ኮርኒሱ ያልተሰራለት እንዲሁም የሚያስፈልገው ግርፍ እና ልስን ያልተካሄደለት ነው:: ለዚህም ከ400 ሺህ ብር በላይ እንደሚያስፈልጋቸው ባለሙያ አሳውቋቸዋል:: በዚህም ተማሪዎቹ ችግር ውስጥ እንዳሉ ገልፀውልናል:: ይህንንም በራሳቸው አቅም ማሟላት ስላልቻሉ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የምንገኝ ሙስሊም ተማሪዎች እንድናግዛቸው ጠይቀውናል::
ስለሆነም እንደተለመደው አንድኛችን ለሌላኛችን በመቆም የወንድሞቻችንን ችግር እናቅልል:: በተቻለን አቅም ተረባርበን በዩኒቨርሲቲዎች ዙሪያ ያለውን የመስጂዶች እጥረት ለመቅረፍ እንታትር:: ተማሪ መስጂድን ማጣቱ ትልቅ ጉዳት ሲሆን ማግኘቱ ደግሞ ብዙ ነገሩ ነው:: በአላህ ፈቃድ የአላህን ቤት በመገንባት የአኼራ ቤታችንን እናንፅ::
ቢስሚላህ እንበል!
ከየት ይሆን?
ማን ይሆን?
ለተማሪዎች መስጂድ !!!
ማሰባሰቢያ አካውንት:- 1000699582976 (Bilal Ethiopian Higher Education Muslim Students Union) --- ያስገባችሁበትን screenshot @MOHAMMADAMMINM ላኩልን::
አላህ ለመልካም ለውጥ ሰበብ ያድርገን!
ይህ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው:: በቻናሉ ከዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጋር ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮች እና የህብረቱ የዕለት ተዕለት ክዋኔዎች ይቀርባሉ::
በአላህ ፍቃድ እና እርዳታ ከዚያም ከሙስሊም ተማሪዎች ጋር በሚኖር መናበብና መተጋገዝ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያሉ ሙስሊም ተማሪዎች መብታቸው ተከብሮ ይማሩ ዘንድ እንተጋለን::
መረጃዎች ለሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ይደርሱ ዘንድ ቻናሉን ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ::
@EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU
@EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU
@EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU
+5
ላኩላቸው ... ያዩት ዘንድ
አሳዯቸው ... ይረዱ ዘንድ
ከታች ጀምሮ እስከ ላይ ድረስ ሙስሊም ተማሪዎችን ሴኩላሪዝምን ከማጣመም ጀምሮ ሌሎች ምክንያቶችን በመደርደር ሶላት እና ኒቃባቸውን ሲላቸው በመመሪያ ሲላቸው በተግባር ለመከልከል ለሚሞክሩ አካላት ላኩላቸው:: የመንግስት ተቋማት ሁሉ ቁንጮ በሆኑው ቤተ- መንግስት የተካሄደውን ነገር አሳዯቸው:: በምስሉ ላይ የሚታየው ትላንት እና ዛሬ የሆነ ሲሆን ኒቃቢስት እህቶቻችን ከጠቅላይ ሚኒስቴሩ ጋር በነፃነት ሲያፈጥሩ: በጀመዓ ሲሰግዱ የሚያሳይ ነው::
ቤተ- መንግስቱ እንዲህ ሆኖ ሳለ እነርሱ ምን ካልሆን ብለው ነው ተማሪዎችን የሚያንገላቱት? የእነርሱ ሴኩላሪዝም ከቤተ- መንግስቱ ይለያል? ወይንስ ከላይ ያለን አሰራር እና ሂደት አይከተሉም? ያም ሆነ ይህ ግን ተፈጥሯዊ መብታችን እንደሆነ ከዚህ በላይ አፅኚ የለም:: ያዩት ዘንድ ለሌሎች አጋሩት:: ክፍተት ካለም መጠየቃችሁን ቀጥሉ::
+2
ተምሳሌትነት!
ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ጀመዓዎች !!
ምስል 1:- በቅርቡ የተቋቋመው በጅማ ዩኒቨርሲቲ አጋሮ ካምፓስ በቅርቡ የተቋቋመው ጀመዓ መስጂድ ነው:: ፀሐይ ብርድ እና ነፋስ የሚያስገባ: ምንጣፍ የሌለው መስጂድ ነው::
ምስል 2:- በጅማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት አስተባባሪነት የሁሉም ካምፓስ ጀመዓዎች ንቅናቄ ፈጥረው ከ100 ሺህ ብር በላይ በማውጣት ለመስጂድ የተሻለ ግድግዳ እና ምንጣፍ ከሰሩ ቡሃላ ነው::
ማሻ አላህ!😍! ተማሪዎችን ለኸይር ስራ አስተባብሮ ውጤት የሚያመጣ ስራ የሚሰራ ጀመዓ ሲኖር እንዲህ ነው:: አላህ ከዚህም ከተሻለ ስኬት ያድርሳቸው:: ለሁላችንም ተምሳሌት የሚሆን ተግባር ነው::
ስለ ጁምዓ የትምህርት ክ/ጊዜ ልንማር የሚገባው:-
በጁምዓ ሶላት ሰዓት ማለትም ከ5:30 - 7:30 የመውጫ ፈተና ሊሰጥ መታሰቡን ተከትሎ ሕብረታችን ለትምህርት ሚኒስቴር በፃፈው አንድ ደብዳቤ መሠረት ሊስተካከል ችሏል:: ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎችም በጁምዓ ሶላት ምክንያት የትምህርት ክ/ጊዜው እንደተሸጋሸገ እና ከ5:30 - 7:30 እንደማይሰጥ በይፋ አሳውቀዋል:: ከዚህ የምንረዳው በጁምዓ ሰዓት ትምህርት መስጠት ከሕግ አንፃር ክልክል እንደሆነ ነው:: ሆኖም ግን ትምህርት ሚኒስቴር ሕጉን ጥሶ የፈተና ፕሮግራም እንዳወጣው ሁሉ ከመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ጀምሮ እስከ ዩኒቨርሲቲዎች ድረስ ከ5:30 - 7:30 ትምህርት / ፈተና የሚሰጡ አሉ::
ከሰሞኑ ክስተት ትምህርት ወስደን በቃ ልንላቸው ይገባል:: ስለ መብታችን በአግባቡ ስንጠይቅ ምላሽ እንደምናገኝ ተረድተናልና በየቦታው ልንጠይቅ ይገባል:: በጁምዓ ቀን ከ5:30 - 7:30 ባለው ሰዓት ውስጥ ምንም አይነት ትምህርት ሊሰጥ አይገባም:: ይህንን በጀመዓዎቻችሁ በኩል ሕግ እና ስርዓቱን ተከትላችሁ በመጠየቅ ይስተካከል ዘንድ ስሩ:: እኛም እንደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ከሐሳብ ጀምሮ ማገዝ በሚጠበቅብን ሁሉ በማገዝ ዝግጁ መሆናችንን እንድታውቁ እንፈልጋለን::
የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄዎች የዚህ ትውልድ ሀላፊነቶች ናቸው ! ! !
Sagantaan Qormaataa Ba'umsaa guyyaa jumu'aa sa'aa salaataa irratti kennamuuf ture Haqame.
Guraandhala 19 / 2018 A.L.I
Bakka buutoonni Gamtaa Barattootaa Dhaabbilee olaanoo Itiyoophiyaa Qaamaan Gara qaama Dhimmi ilaallatuu Deemuun Akka Mirkaneeffatanitti Guyyaa Boruu Sa'atii 5:00 - 7:30 Qormaanni Kennamuuf ture Haqamee jira.
Kun akka milkaa'uuf Rabbii keenya nu gargaare galateeffachaa Barattoota Mirga isaaniif falmachuuf tokkummaan Dhabbataniif akkasumas jama'aalee gamtoomaan dhimma kana irratti hojjataniif kabaja keenya ibsuu barbaadna. Dogogorroonni Akkasii akka hin Uumamneef Ministeerri Barnootaaa itti fufiinsaan akka hojjettu yaadachiisuu barbaadna.
Gamtaa Barattootaa Dhaabbilee olaanoo Itiyoophiyaa.
https://t.me/EHEMSU
በጁምዓ ሶላት ምክንያት የተሻሻለው የመውጫ ፈተና ፕሮግራም ! ! !
+1
የተሻሻለውን የመውጫ ፈተና ፕሮግራም መቱ ዩኒቨርሲቲ ይፋ አድርጓል:: "በጁምዓ ሶላት ምክንያት ...!" - ከሚል ማያያዣ ጋር ከ5:00 - 7:30 ሊሰጥ የነበረው ፈተና መሰረዙን ግልፅ አድርጓል::
ከመጠየቅ መልስ ይመጣል
ከመታገል መብት ይገኛል ! ! !
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ተወካዮች ከትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ደኤታ ጽ/ቤት በአካል ሄደው እንዳረጋገጡት በነገው እለት ከ5:00 - 7:30 ሊሰጥ የነበረው የመውጫ ፈተና ፕሮግራም እንደተሰረዘ ማረጋገጥ ችሏል::
ይህ እንዲሳካ ለፈቀደው አላህ ምስጋና ይገባ:: ለመብታቸው በሕብረት ለቆሙት ሙስሊም ተማሪዎች እና የዩኒቨርሲቲ ጀመዓዎች አክብሮታችንን እንገልፃለን:: መሠል ስህተቶች በድጋሚ እንዳይፈጠሩ የትምህርት ሚኒስቴር በዘላቂነት ይሰራም ዘንድ ለማሳሰብ እንወዳለን::
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት!!!
https://t.me/EHEMSU
ተፅዕኗችን ጀምሯል
የመቱ ሪጅስትራር ሀላፊ ከጁምዓ ጋር ተያይዞ ለተነሳው ቅሬታ ከበላይ አካላት ጋር ተነጋግሮ መፍትሔ እንደሚያበጅ ገልፇል::
ከመጠየቅ መልስ ይገኛል
ከመታገል መብት ይከበራል ! ! !
+3
ቲክቫህ ሀላፊነቱን በመወጣት ድምፃችንን አሰምቷል ... አሁንም ቢሆን ትምህርት ሚኒስቴር በጁምዓ ሰዓት ያወጣውን የመውጫ ፈተና ፕሮግራም ከማስተካከል ባሻገር ችግሩን እየፈጠሩ ያሉ አካላትን ተጠያቂ እንዲያደርግ እንጠይቃለን ! ! !
የወለጋ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ በጁምዓ ሰዓት የወጣው የመውጫ ፈተና ፕሮግራም እንዲሻሻል እና መሠል ጥፋቶችን የሚፈፅሙ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ ለዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፅ/ቤት ባስገባው ደብዳቤ ጠይቋል!
+1
ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጀምሮ ላሉ የሚዲያ ተቋማት ላኩላቸው:: በየአመቱ ለሚፈጠረው ችግር ምክንያቱ ምን እንደሆነ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ጠይቀው በይፋ እንዲነግሩን እንፈልጋለን:: የቲክቫህ የመልዕክት መቀበያ @tikvahethiopiaDM ነው:: በሌሎቹም ቀጥሉ!!
ለምታውቁት ሁሉ አሰራጩ
ድምፃችን ከፍ ብሎ ይሰማ
ስለ መብቶቻችን ያለንን ቁርጠኝነት ይወቁ
ይህ ትውልድ ዝም ብሎ የሚያልፈው የመብ ጥሰት እንደሌለም ይገንዘቡ ! ! !
https://t.me/EHEMSU
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተናን (Exit Exam) በመጪው አርብ በጁምዓ ሰዓት ማለትም ከ5:00-7:30 ለመስጠት ያወጣውን ፕሮግራም እንዲቀይር ጠየቀ!
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የካቲት 18 / 2018 ዓ.ል
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ህብረቱ ለትምህርት ሚኒስቴር ባስገባው ደብዳቤ ጁምዓ የሙስሊሞች ሳምንታዊ በዓል መሆኑንና ከ5:30-7:30 በሀገር ደረጃ የመንግስት መስሪያ ቤቶች እረፍት መሆናቸውን ጠቅሶ በዚህ ሰዓት የፈተና ፕሮግራም ማውጣት የሙስሊም ተማሪዎችን እሴቶችን እና መብቶችን መጋፋት እንደሆነ ገልፇል:: መሠል ጥፋቶች መደጋገማቸው ሙስሊሙን ተማሪ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚያራርቁ በመሆናቸውም ተመሳሳይ ችግሮች በዘላቂነት እንዳይፈጠሩ መስመር እንዲደረገም ጠይቋል:: ይኼው ችግር በባለፈው አመት ተስተካክሎ ዳግም ዘንድሮም መፈጠሩ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ቸልተኝነት እንደሚያሳይ በመግለፅም ይህ እንዲፈጠር ምክንያት የሚሆኑ አካላት ይጠየቁ ዘንድም ጠይቋል::
@MohammadamminKassaw
ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ እስከ ዛሬ ባለው ለስሁር ምግብ የማይዘጋጅ ቢሆንም በተማሪዎች ጥያቄ መሠረት ከትላንት ጀምሮ እንደተስተካከለላቸው የዩኒቨርሲቲው ጀመዓ አሳውቋል::
ማሻ አላህ ! ! !
https://t.me/EHEMSU
