ch
Feedback
Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

前往频道在 Telegram

This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.

显示更多
4 481
订阅者
-124 小时
+147 天
+3130 天
帖子存档
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በኢትዮጵያ ፕሬስ ኤጀንሲ በመገኘት ድምፃቸውን አሰሙ ! ! ! ------------------------------------------- መጋቢት 25 / 2018 ዓ.
+3
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በኢትዮጵያ ፕሬስ ኤጀንሲ በመገኘት ድምፃቸውን አሰሙ ! ! ! ------------------------------------------- መጋቢት 25 / 2018 ዓ.ል ------------------------------------------- ሀገር ብዝሐ ሀይማኖት ባሏቸው ዜጎች የምትሰራ፣ የምታድግ እና የምትለማ የጋራ ቤት ሲሆን የዜጎች ነፃነት፣ እኩልነት እና ፍትሕ የቤቱ ምሰሶ እና ማገር ናቸው። ነፃነት ሲገፈፍ አቤት በማለት፤ ፍትሕ ሲጣስ ድምፅ በመሆን ለጋራ ሀገር ማደግ አስተዋፅዖ ማድረግ ከምንም እና ከማንም በላይ በሀገር ሀብት የተገነቡ ተቋማት እና የዜጎች ላብ ደመወዛቸው የሆኑ መሪዎች ሀላፊነት ነው። ይህ ሆኖ ሲታይ የሁላችን የሆነችዋ ኢትዮጵያ ተስፋ ይለመልማል። "ኒቃብ የለበሰች ሴት አትማርም!" - የሚልን መመሪያ አውጥቶ በቅኔ መልክ ሙስሊም ተማሪን ላስተምር አልችልም የሚልን መልዕክት በማስተላለፍ በጋራ ሀገር በጋራ ሀብት የተገነባን የጋራ ተቋም ስም እና ግብር እያበላሹ ያሉ አመራሮችን በመቃወም ሰብዓዊ መብታቸውን ለማስከበር ንቅናቄ የጀመሩት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሴቶች ቅፍለት ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ከትሞ ነበር። እዚያም እየደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት በመናገር ተቋሙ የደረሰውን በደል በማጋለጥ ሀገራዊ ሀላፊነቱን ይወጣ ዘንድ ጠይቀዋል። ንቅናቄያችን ፍትሕ እስኪሰፍን ይቀጥላል። እንቅስቃሴያችን ሰብዓዊ መብታችንን የሚጥሰው መመሪያ እስኪሻሻል ይቀጥላል። ፍትሕ ቀባሪዎቿን ትቀብራለች። ጥያቄ አለን __ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! @aaumsu

"ምንም በማናውቀው አስከሰሳችሁን። ሴኩሪቲዎች መጥተው አነጋግረውናል። ሲጀመር የእኛ ስራ ይሄ አይደለም። መብታችሁ ከተጣሰ ሌላ ቦታ ሂዱ።" - በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሰብዓዊ መብት ማዕከል የአዲስ
+3
"ምንም በማናውቀው አስከሰሳችሁን። ሴኩሪቲዎች መጥተው አነጋግረውናል። ሲጀመር የእኛ ስራ ይሄ አይደለም። መብታችሁ ከተጣሰ ሌላ ቦታ ሂዱ።" - በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሰብዓዊ መብት ማዕከል   የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ሴቶች በአደባባይ በለቀቀው ወረቀት ስለ ሰብዓዊ መብት እንደሚቆም ካስታወቀው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሰብዓዊ መብት ማዕከል በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት አቤት ለማለት ከሁለት ቀን በፊት ሄደው ነበር። በወቅቱ የነበሩት የማዕከሉ ሀላፊዎች ሙስሊም ተማሪዎች ላይ የደረሰው የሰብዓዊ መብት ጥሰት አግባብነት እንደሌለው በመግለፅ ይስተካከል ዘንድ እንደሚሰሩ በመግለፅ ከሁለት ቀን ቡሃላ ከጧቱ 4:00 ሰዓት ላይ እንደሚጡ እና ከበላይ ሀላፊዎች ጋር እንደሚገናኙ ገልፀውም ነበር። ሆኖም ይህ በሆነበት ሰዓት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጥበቃ ሀላፊዎች ከቦታው በመምጣት የተማሪዎችን ID ከመቀማት ጀምሮ እስከ 9:00 ሰዓት የደረሰ ማዋከብ ፈፅመውባቸው ነበር። ሙስሊም ተማሪዎቹ ቀጠሮውን በማክበር በሰዓቱ የደወሉ እና ሊገኙ የሄዱ ቢሆንም የማዕከሉ ተወካይ "ምንም በማናውቀው አስከሰሳችሁን። ሴኩሪቲዎች መጥተው አነጋግረውናል። ሲጀመር የእኛ ስራ ይሄ አይደለም። መብታችሁ ከተጣሰ ሌላ ቦታ ሂዱ።" በማለት መልስ ሰጥተዋል። ይህ አግባብነት የሌለው አካሄድ ነው። ስለ ሰብዓዊ መብት የተቋቋመን አካል ተማሪዎችን አወያያችሁ ብሎ መወንጀል፤ ለሰብዓዊ መብት የተቋቋመም ማዕከል ተወነጀልኩ ብሎ ከፍትሕ ማፈግፈግ የተቋማቶቻችንን የቁልቁለት ጉዞ የሚያፋጥን ነውና ሁሉም ተስተካክሎ ወደ መስመር ይገባ ዘንድ ጥሪያችን ነው። ጥያቄ አለን __ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! @aaumsu

"የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች መገፋት እና ተግዳሮቶች!" - የጉዳያችን ፖድካስት የመጀመሪያ ርዕስ ሆኗል። ጥሪውን በዘመቻ ላቀረባችሁ ተማሪዎቻችን፤ ጥሪውንም ለሰማው የጉዳያችን ፖድ
"የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች መገፋት እና ተግዳሮቶች!" - የጉዳያችን ፖድካስት የመጀመሪያ ርዕስ ሆኗል። ጥሪውን በዘመቻ ላቀረባችሁ ተማሪዎቻችን፤ ጥሪውንም ለሰማው የጉዳያችን ፖድካስት አዘጋጅ ወንድም ዲኑ ዓሊ ምስጋናችን የላቀ ነው። ሀላፊነቱ የሁሉም ቢሆንም ግብር ከፍለን በራሳችን ሀብት የተቋቋመው ዩኒቨርሲቲያችን ገፊ ሆኖ በቀረበበት፤ አንዳንድ የሀገራችን ሚዲያዎች እና አካላት ፈጣን መልስ ለመስጠት ባልተነሱበት መልስ የሰጠውን ወንድም አመስጋኝ ነን። ጉዳያችን በመጀመሪያው ፕሮግራም " ስለእህቶቻችን መብት፤ የአለባበስ ነፃነት እና እየደረሰባቸው ያለው ጫና በጥልቀት ይዳሰስበታል። ድምፅ ለሌላቸው ድምፅ የምንሆንበት ልዩ ቆይታ ይኖረናል።" - ብሎናል። ወደ ተግባር! እያንዳንዷ እንቅስቃሴ ለሚመጣው ለውጥ አስተዋፅዖው የጎላ ነውና ትኩረት እንስጥ!! ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን!! @aaumsu

ቀላል ቻሌንጅ ለመብት ጥያቄያችን ወንድም ዲኑ ዓሊ ጉዳያችን የሚል ፖድካስት ሊጀምር የመጀመሪያው እንግዳ በድምፅ እንዲመረጥ አቅርቧል። ሕብረታችንም ስለመብት ጥያቄያችን ለሚዲያ ለማድረስ እንቅስቃሴ ላ
ቀላል ቻሌንጅ ለመብት ጥያቄያችን ወንድም ዲኑ ዓሊ ጉዳያችን የሚል ፖድካስት ሊጀምር የመጀመሪያው እንግዳ በድምፅ እንዲመረጥ አቅርቧል። ሕብረታችንም ስለመብት ጥያቄያችን ለሚዲያ ለማድረስ እንቅስቃሴ ላይ ያለበት ሰዓት ነውና አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት በማለት የሚዲያ ዘመቻ ላይ ላለው ጀመዓችን የሚዲያ እድል እናመቻች። ሊንኩ https://www.facebook.com/100063706240231/posts/1589231966543663/?app=fbl ነው። ይህ ለቢላል እና ሱመያ ልጆች ትንሹ ቻሌንጅ ነው። እውን እናድርገው። የጻፋችሁትን አስተያየት ስክሪንሾት (Screenshot) በማንሳት በቦታችን @Niqab_issueBot በኩል ላኩልን። ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን!! @aaumsu

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆኑ ዘንድ በARTs TV ቅሬታ አቀረቡ ! ! ! ---------------------------
+2
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆኑ ዘንድ በARTs TV ቅሬታ አቀረቡ ! ! ! ------------------------------------------- መጋቢት 24 / 2018 ዓ.ል ------------------------------------------- ከሚዲያ የመጀመሪያ ደረጃ ተግባራት መካከል በደልን ማጋለጥ፤ ለፍትሕ መትጋት እና ማህበረሰብን በእኩልነት ማገልገል ይጠቀሳሉ። የሀገር ብሌን የሆኑ የልሕቀት ማዕከላት ከፍትሕ እና ነፃነት ይልቅ በደልን እና ጭቆናን መታዎቂያ አድርገው የሀገርን ስም ሲያጠፉ ቀድሞ በመሠለፍ ስለሀገር ስም እና የነገ እድል ድምፅ መሆን ከሚዲያዎች ሀላፊነት ነው። በዚህም ምክንያት ስለ ፍትሕ ጉዞውን የጀመረው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች ቅፍለት ከARTs ቲቪ ከትመው ውለዋል። እየደረሰባቸው ስላለው በደል ጩኸው፤ ስለ ነፃነታቸው ጠይቀው፤ ስለ ፍትሕ ሁሉም ዘብ ይሆን ዘንድ አስገንዝበው ተመልሰዋል። ቁጭ ብለው ያወጡትን ጨቋኝ መመሪያ ቆመን ልንታገል ግድ ሆኗልና እየተንቀሳቀስን ነው። ስለ ሀገራችን ልጆች መብት ሳያስቡ 12 አመት የለፉበትን ትምህርት ለማምከን በመመሪያ ስም ሴራ ይዘው መጥተዋልና እርሱን ማምከን ግዴታችን ሆኗል። ነፃነት በነፃ አይገኝም የተባለው ለዚህ ነው። መብትም በትግል እንጂ ተለምኖ አይወሰድም። ጥያቄ አለን ! መልስም እንፈልጋለን ! ! ! @aaumsu

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በአባይ ቲቪ በመገኘት በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆኗቸው ዘንድ አቤቱታ አቀረቡ ! ! ! -------------------
+2
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በአባይ ቲቪ በመገኘት በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆኗቸው ዘንድ አቤቱታ አቀረቡ ! ! ! ------------------------------------------- መጋቢት 24 / 2018 ዓ.ል ------------------------------------------- አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እያደረሰ ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለሕዝብ የተቋቋሙ ሚዲያዎች እንዲያጋልጡ እና ስለ ፍትሕ ዘብ እንዲቆሙ በዩኒቨርስቲው ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ዘመቻ መጀመሩ ይታወቃል። በዛሬው እለትም ተማሪዎቹ በARTs ቲቪ ዋና ፅ/ቤት በመገኘት ሚዲያዎው ድምፅ በመሆን ተቋማዊ ሀላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ አልፎ እንደ አፍሪካ ተምሳሌት ተደርጎ የሚወሰድ የልሕቀት ማዕከል ነውና አመራሮቹ ሕግን ጥሰት ባወጡት መመሪያ መካከል ስሙ ሊጠፋ አይገባም። ስለሆነም ፍትሕ ሰፍኖ ተማሪዎች መብታቸው ተጠብቆ እስኪማሩ ድረስ በሁሉም ቦታ በሁሉም መንገድ ጥያቄያችን ይቀጥላል። መጅሊስ፣ ሰላም ሚኒስቴር፣ የሴቶች እና ሕፃናት ጉዳዮች ሚኒስቴር፣ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን፣ ሚዲያዎች እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰዎች እንደአጠቃላይ አጀንዳውን አጀንዳቸው አድርገው ለሚመጣው ፍትሐዊ ለውጥ አስተዋፅዖ ያደርጉ ዘንድ ጥሪያችን ነው። @aaumsu

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆናቸው ዘንድ ለአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ቅሬታ አቀረቡ ! ! ! --------------
+3
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆናቸው ዘንድ ለአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ቅሬታ አቀረቡ ! ! ! ------------------------------------------- መጋቢት 23 / 2018 ዓ.ል ------------------------------------------- በዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ፕሬዚዳንትነት የሚመራው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ል አዲስ መመሪያ አውጥቶ የተማሪዎችን ሰብዓዊ መብት እየጣሰ እንደሆነ ይታወቃል። ይህንንም ተከትሎ ከተማሪዎች ከፍተኛ ቅሬታ እና አቤቱታ ቢቀርብም ዩኒቨርስቲው ለውይይት በሩን ዘግቶ መመሪያውን ሳያሻሽል በደሉን በመቀጠል ላይ ነው። የተማሪዎችን ድምፅ በማስተጋባት ድምፅ ይሆን ዘንድ ለአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ በማህበራዊ ሚዲያ ቻሌንጅ ቢነገራቸውም ምላሽ አለመስጠታቸውን ተከትሎ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በዛሬው እለት ከዋና ጽ/ቤታቸው በመገኘት ድምፅ ይሆኗቸው ዘንድ ጠይቀዋል። ጨቋኙ መመሪያ ተሻሽሎ ፍትሕ እስኪሰፍን ድረስ ጥያቄያችን ይቀጥላል። ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን!! @aaumsu

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በነጃሺ ቲቪ ዋና ጽ/ቤት በመገኘት በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆኗቸው ዘንድ አቤቱታ አቀረቡ ! ----------
+1
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በነጃሺ ቲቪ ዋና ጽ/ቤት በመገኘት በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆኗቸው ዘንድ አቤቱታ አቀረቡ ! ------------------------------------------- መጋቢት 23 / 2018 ዓ.ል ------------------------------------------- ብልፅግና ፓርቲ በአራዳ ክ/ከተማ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እጩ አድርጎ ያቀረባቸው ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ከሆኑ ቡሃላ የተማሪዎችን ሰብዓዊ መብት የሚጥስ መመሪያ አውጥተው መጠነሰፊ የመብት ጥሰት እየተፈፀመ መሆኑ የሚታወቅ ነው። ይህንንም ተከትሎ ሙስሊም ተማሪዎች ያሉ ቅሬታዎችን በማቅረብ በውይይት ይፈታ ዘንድ አቤቱታ ያቀረቡ ቢሆንም የእርሳቸው አመራር የውይይት በሮችን በመዝጋት የተማሪዎችን ድምፅ ችላ ብለዋል። ሙስሊም ሴት ተማሪዎችም በዛሬው እለት ከነጃሺ ቲቪ ዋና ፅ/ቤት በመገኘት እየደረሰ ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ማብራሪያ በመስጠት ድምፅ በመሆኑ ከፍትሕ ጎን ይቆሙ ዘንድ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። የሚፈፀሙት በደሎች ቆመው ፍትሕ እስኪሰፍን ድረስ ድምፃችንን ማሰማታችንን የምንቀጥል ይሆናል። ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን!! @aaumsu

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብቶች ማዕከል በመገኘት እየደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት አቤቱታ ያቀረቡ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በዩኒቨርስቲው የፀጥታ አካላት መዋከብ ደረሰባቸው ! ! ! ---
+1
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብቶች ማዕከል በመገኘት እየደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት አቤቱታ ያቀረቡ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በዩኒቨርስቲው የፀጥታ አካላት መዋከብ ደረሰባቸው ! ! ! ------------------------------------------- መጋቢት 22 / 2018 ዓ.ል ------------------------------------------- የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በዛሬው እለት ከ5:00 ጀምሮ FBE ካምፓስ በሚገኘው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብቶች ማዕከል (AAU Center for Human Rights) በመገኘት በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስለሚገኘው የሰብዓዊ መብት ጥሰት የገለፁ ሲሆን ማዕከሉ በሕግ አግባብ ዩኒቨርስቲውን ተጠያቂ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። ሆኖም ግን ይህ ሆኖ ሊጠናቀቅ ባለበት ሰዓት የዩኒቨርስቲው የጥበቃ ሀላፊዎች እና አካላት ተማሪዎቹ ማዕከሉን መጠየቃቸው ስህተት መሆኑን በመግለፅ በተማሪዎቹ ላይ ማዋከብን ፈፅመዋል። የአንዲት ተማሪንም የመታዎቂያ ካርድ የነጠቁ ሲሆን የሌሎቹንም ፎቶ በማንሳት ሄደዋል። እስከ አሁኑ ሰዓት ድረስም ልጆቹን ወደ ፀጥታ ቢሮ በመጥራት በማናገር ላይ ይገኛሉ። ስለ ሰብዓዊ መብቱ በሰላማዊ መንገድ ሊጠይቅ የተሰባሰበ ተማሪ ላይ አግባብነት የሌላቸው ማዋከቦችን መፈፀም ትክክል እንዳልሆነ እናምናለን። ሙስሊም ተማሪዎች እየጠየቁ ያየው ጥያቄ ግልፅ እና ግልፅ ነው። የሰብዓዊ መብታችንን የሚጥሰው ኢሕገ- መንግስታዊ መመሪያ ይሻር ጥያቄያችን ነው። ከዚህ ውጪ ያለግብር ስም እየሰጡ ተማሪን በማንላታት የሚቀር ጥያቄ እና የሚዳፈን ጥያቄ የለም። የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ሁሉ ትኩረት በመስጠት ችግሩን ይፈቱ ዘንድ ጥሪያችን ነው። @aaumsu

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች በትላንትናው እለት ለEBC ካስገቡት ደብዳቤ፦ ፨ ዩኒቨርሲቲው በ2017 ዓ.ል አዲስ መመሪያ ማውጣቱን ተከትሎ ከፍተኛ የሆነ ስቃይ እና እንግልት እየደረሰብን
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች በትላንትናው እለት ለEBC ካስገቡት ደብዳቤ፦ ፨ ዩኒቨርሲቲው በ2017 ዓ.ል አዲስ መመሪያ ማውጣቱን ተከትሎ ከፍተኛ የሆነ ስቃይ እና እንግልት እየደረሰብን ነው። ፨ መመሪያው በአንቀፅ 6.6 ሒጃብን (ኒቃብ) በመከልከል እንዲሁም በአንቀፅ 11.1 የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ልብስ የሆነውን ነጠላ ከአላስፈላጊ ልብስ በመጥቀስ ግልፅ የሆነ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈፅሟል። ፨ በሁሉም ኢትዮጵያውያን ርብርብ ግማሽ ክ/ዘመንን በስኬት የተሻገረው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጥያቄያችንን በመቀበል ድምፃችንን አሰምቶ ለፍትሕ ያለውን ውግንና በተግባር ያሳይ። ፦ በአላህ ፈቃድ ድምፃችንን በሰላማዊ መንገድ በሁሉም ለሁሉም እናሰማለን። አለምአቀፍ ሚዲያዎችን ጨምሮ በማህበራዊ ሚዲያ ጠይቀን ምላሽ ያልሰጡንን ሁሉ በቢሯቸው ተገኝተን ከፍትሕ ጎን ይቆሙ ዘንድ እንወተውታለን። ፍትሕ ቀባሪዎቿን ትቀብራለች! ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን!! @aaumsu

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በዩኒቨርሲቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆኗቸው ዘንድ በEBC እና ፋና ዋና ፅ/ቤት በመገኘት አቤቱታ አቀረቡ ! ! ! --------
+4
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በዩኒቨርሲቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆኗቸው ዘንድ በEBC እና ፋና ዋና ፅ/ቤት በመገኘት አቤቱታ አቀረቡ ! ! ! -------------------------------------------- መጋቢት 22 / 2018 ዓ.ል -------------------------------------------- ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ከሆኑ ቡሃላ የሙስሊም ተማሪዎችን ሒጃብ (ኒቃብ) የመልበስ ሰብዓዊ መብት የሚከለክል ኢ- ሕገመንግስታዊ መመሪያ ወጥቶ ተማሪዎች ለመጠነ ሰፊ እንግልት መዳረጋቸው የሚታወቅ ነው። ይህንንም ተከትሎ ላለፉት 18 ወራት ዘርፈ ብዙ እንቅስቃሴዎች የተደረገ ሲሆን ባለፉት ሳምንታት ውስጥ በማህበራዊ ሚዲያ በተደረገ ዘመቻ የሁሉም ኢትዮጵያዊ የጋራ ሐብት የሆኑት እነ EBC: FANA እና ሌሎች ሚዲያዎች የተማሪውን ድምፅ እንዲያስተጋቡ፤ ዩኒቨርሲቲውን እና አመራሩንም ተጠያቂ እንዲያደርጉ ሲጠየቅ ነበር። ሆኖም ምላሽ ባለመገኘቱ በዛሬው እለት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በሚዲያዎቹ ጽ/ቤት በመገኘት ሚዲያዎቹ ሚዛናዊ እና ፍትሐዊ ዜናዎችን በመስራት እና ዘገባዎችን በማውጣት በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት ድምፅ ሆነው ሀላፊነታቸውን ይወጡ ዘንድ ጠይቀዋል። በአላህ ፈቃድ መሠል እንቅስቃሴዎች በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው ግፍ እስኪቆም ድረስ የሚቀጥል ይሆናል። በቀጣይ የሚኖሩ እንቅስቃሴዎችን እና ውጤቶችንም የምናሳውቃችሁ ይሆናል። ጥያቄ አለን: ዛሬም ነገም! ጥያቄ አለን: ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!! ጥያቄ አለን: ቢሮ ውስጥም በአደባባይም! @aaumsu

አላሁ አክበርርር! 8850 ብርርር !!! ለወሎ ዩኒቨርሲቲ ጤና ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች መስጂድ ማስጨረሻ። በጠቅላላው 24ሺ ብር ላይ ደረስን ማለት ነው። ለሰጡት አላህ ይስጥልን። የረመዷንን ትሩፋት
+1
አላሁ አክበርርር! 8850 ብርርር !!! ለወሎ ዩኒቨርሲቲ ጤና ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች መስጂድ ማስጨረሻ። በጠቅላላው 24ሺ ብር ላይ ደረስን ማለት ነው። ለሰጡት አላህ ይስጥልን። የረመዷንን ትሩፋት ይግጠማቸው። ለይለተልቀድርን ከተወፈቁት ያድርጋቸው። ዱንያ አኼራቸውን የስኬት ያድርግ።

ዒዱኩም ሙባረክ!!! ነገ ሐሙስን ፁመን ጁምዓ ኢድን እንደምንውል ተገልፆል። እንኳን አደረሰን!!!
ዒዱኩም ሙባረክ!!! ነገ ሐሙስን ፁመን ጁምዓ ኢድን እንደምንውል ተገልፆል። እንኳን አደረሰን!!!

አላሁ አክበር! የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ ለወሎ ዩኒቨርሲቲ ጤና ካምፓስ መስጂድ ማስጨረሻ 5000 ብር አበርክተዋል። በመልዕክታቸውም "ምንም እንኳ እኛም የመስጂድ ግንባታ ላይ ብንሆን
+1
አላሁ አክበር! የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ ለወሎ ዩኒቨርሲቲ ጤና ካምፓስ መስጂድ ማስጨረሻ 5000 ብር አበርክተዋል። በመልዕክታቸውም "ምንም እንኳ እኛም የመስጂድ ግንባታ ላይ ብንሆንም ከወንድሞቻችን ጎን መሆናችንን ለማሳየት የምንችለውን አድርገናል።" በማለት አስተላልፈዋል። አላህ ሁልጊዜ ከጎናቸው ይሁን። ዱንያ አኼራቸውን የደስታ እና የስኬት ያድርግ። የእነርሱንም መስጂድ በቶሎ ተጠናቆ የምናይ ያድርገን። ኢስላማዊ ወንድማማችነት ሲገለፅ እንዲህ ነው። ሁላችንም በቻልነው እንረባረበ። በተለይ ደግሞ ዛሬ; 27ኛው ሌሊት ነውና።

መልዕክት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት27ኛው ሌሊት ገብቷል! ሌሊቱ ለይለተልቀድር ከሌሎቹ በተለየ የሚከጀልበት ነው። በያላችሁበት ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ዱዓ አድርጉ። በእነርሱ ላይ የወጣው ጨቋኝ መመሪያ ተሻሽሎ መብታቸውን የሚያከብር፥ ለመብታቸው ከለላ የሚሆን መመሪያ እንዲወጣ ዱዓ አድርጉ። ይህ መልዕክት ለሁሉም የዩኒቨርሲቲ ጀመዓዎች ነው፤ ይህ መልዕክት ለሁሉም የመስጂድ ኢማሞች ነው። ወንድም እህቶቻችሁን በቁኑት ውስጥ አስቧቸው። መልዕክቱን ላልሰማ አሰሙ። በአላህ ፈቃድ ፍትሕ ይመጣል። በአላህ ፈቃድ የአላህ ነስር ቅርብ ነው። ©aaumsu https://t.me/EHEMSU

ሰምተናል ... ታዘናልም ! ! ! "ጨቋኝ በጭቆናው ላይ ሳይደክም: ታጋይ በትግሉ ላይ መድከሙ ነውር ነው::" - ሁዳ ከላይ ያለውን ምስል እስቶሪ ላይ እና ፕሮፋይል በማድረግ መብታቸው ደጋግሞ እየተ
ሰምተናል ... ታዘናልም ! ! ! "ጨቋኝ በጭቆናው ላይ ሳይደክም: ታጋይ በትግሉ ላይ መድከሙ ነውር ነው::" - ሁዳ ከላይ ያለውን ምስል እስቶሪ ላይ እና ፕሮፋይል በማድረግ መብታቸው ደጋግሞ እየተጣሰ ላሉት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ድምፅ እንሁን:: ጨቋኙ መመሪያ ተስተካክሎ ኒቃቢስቶች ሳይሳቀቁ በነፃነት እስኪማሩ ድረስ ድምፃችንን በማሰማት አለን እንበል::

አላህ የጀነት ቤታቸውን በፊርደውሰል አዕላ ይገንባ ... የዱንያ ሲሳይን አስፍቶ እና አሟልቶ ይወፍቃቸው ... ለወንድም እህቶቻቸው ሐጃ አለሁ ብለዋልና ለሐጃዎቻቸው ሁሉ አለሁ ይበላቸው:: ለወሎ ዩኒ
+4
አላህ የጀነት ቤታቸውን በፊርደውሰል አዕላ ይገንባ ... የዱንያ ሲሳይን አስፍቶ እና አሟልቶ ይወፍቃቸው ... ለወንድም እህቶቻቸው ሐጃ አለሁ ብለዋልና ለሐጃዎቻቸው ሁሉ አለሁ ይበላቸው:: ለወሎ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች መስጂድ ግንባታ ማስጨረሻ ከወራቤ: ጂማ: ሐረማያ እና AASTU አለሁ እያሉ ነው:: በአጠቃላይ 6320 ላይ ደርሰናል:: ይህ የደረሰው ከ10 ብር ጀምሮ በለገሱ ልበቀናዎች ርብርብ ነው:: ሆኖም ካቀድነውና ከሚያስፈልገው አንፃር ገና እየጀመርን ነው:: እንረባረብ ... ካለን ላይ በመስጠት እንረባረብ ... ሌሎች ይሰጡ ዘንድ በመጠቆም እንረባረብ ... የወንድም እህቶቻችንን መስጂድ በመገንባት ማሰባሰቢያ አካውንት:- 1000699582976 (Bilal Ethiopian Higher Education Muslim Students Union) --- ያስገባችሁበትን screenshot @eheimsubot ላኩልን:: አላህ ለመልካም ለውጥ ሰበብ ያድርገን! https://t.me/EHEMSU

ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው እለት የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጅቷል:: በፕሮግራሙ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች የተገኙ ሲሆን ከተማሪዎቹ ጋር ተቀራርበው ጥሩ ጊዜ አሳልፈዋል:: :- ሀላፊነትን ያለአግባብ በ
+4
ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው እለት የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጅቷል:: በፕሮግራሙ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች የተገኙ ሲሆን ከተማሪዎቹ ጋር ተቀራርበው ጥሩ ጊዜ አሳልፈዋል:: :- ሀላፊነትን ያለአግባብ በመጠቀም የሙስሊም ተማሪዎችን መብት ለመጣስ እና እውቅናን ለመንፈግ የሚሞክሩ የዩኒቨርሲተ አመራሮች ባሉበት ሀገር ተማሪን ከአመራሩ የሚያቀራርቡ ሰናይ ተግባራትን የሚፈፅሙ የዩኒቨርሲቲ አመራሮች ምስጋናም እውቅናም ይገባቸዋል:: የሌላ ዩኒቨርሲቲ አመራሮችም ጥሩ ተምሳሌትነትን ከእነዚህ ግቢዎች ወስደው ለተማሪውም ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብም የሚበጀውን ነገር ቢያደርጉ ጥሩ ነው::

ከሰመራ ዩኒቨርሲቲ ቢማሩ ! ከላይ የሚታየው በዛሬው እለት የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ያዘጋጀው የኢፍጣር ፕሮግራም ነው:: የግቢው አመራሮች ከተማሪዎች ጋር ተቀራርበውና በአንድ ሆነው በጀመዓ ሲሰግዱ ብሎም አ
+5
ከሰመራ ዩኒቨርሲቲ ቢማሩ ! ከላይ የሚታየው በዛሬው እለት የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ያዘጋጀው የኢፍጣር ፕሮግራም ነው:: የግቢው አመራሮች ከተማሪዎች ጋር ተቀራርበውና በአንድ ሆነው በጀመዓ ሲሰግዱ ብሎም አብረው ሲያፈጥሩ ነበር:: መሠል ተግባራት የዩኒቨርሲቲው አመራሮች እና ተማሪዎች መካከል አዎንታዊ መስተጋብር እንዲኖር እንደሚያግዝም ዩኒቨርሲቲው በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ ገልፇል:: ማሻ አላህ! ለሁሉም ግቢ ተምሳሌት ሊሆን የሚችል ሰናይ ተግባር ነው !!!

ወንድም ኻሊድ ኺያር ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ያስተላለፈው መልዕክት:- "አብሽሩ ጠንክሩ ጀግኑ አይደለም ወሎን  የኢትዮጵያን ዩኒቨርሲቲ በመስጂድ እና በአዛን በጠንካራ ጀመዓ ግንባታ ከከፍታው ማማ እናደርሳታለን
''መን ጀድ-ደ ወጀደ ''-----''መን ሰበተ ነበተ ''
አብሽሩ ቀዳዳዎቻችን በጋራ ስንካፈላቸው እንቀርፋቸዋለን !🍃" ሐቅ ነው:: እንዲህ ለኸይር ስራ የሚጠራሩ ወንድም እህቶች እስካሉ ድረስ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ: ከሰሜን እስከ ደቡብም ተቋማቶቻችንን መስራት እንችላለን:: በሉ እንበርታ ለአሁን ፕሮጀክታችን የወሎ ዩኒቨርሲቲ ጤና ካምፓስ መስጂድ ነው ማሰባሰቢያ አካውንት:- 1000699582976 (Bilal Ethiopian Higher Education Muslim Students Union) --- ያስገባችሁበትን screenshot @eheimsubot ላኩልን:: አላህ ለመልካም ለውጥ ሰበብ ያድርገን! https://t.me/EHEMSU