ch
Feedback
ኢት-መጽሐፍት | ETHIO-BOOKS

ኢት-መጽሐፍት | ETHIO-BOOKS

前往频道在 Telegram

👉 "የምታነበው መጽሐፍ ለአንተ የሚያስብልህ ሳይሆን አንተ እንድታስብ የሚያደርግ ነው።" ሃርፐር ሊ Fiction (ልቦለድ), History (ታሪክ), Politics (ፖለቲካ), Psychology (ስነልቦና), Biography (ግለ-ታሪክ), Self-help(ራስ አገዝ),& Philosophy(ፍልስፍና) የሀገር ውስጥ & የውጪ ሀገር መጽሐፎችን ያገኛሉ!አስተያየትዎን እዚህ @Desutech_bot ያድርሱን

显示更多
1 989
订阅者
-324 小时
-67
-5630
帖子存档
“ህይወት ለማንም ነፃ ትምህርት አትሰጥም፤ 'ህይወት አስተማረኝ' ስትል ዋጋ እንደከፈልክ እርግጠኛ ሁን!።” Nagib mahfouz 👉 @et_books1 👉 @et_books1

#ተስፋ የምታደርገው ነገር ካለ ተጨፍልቀህም ትድናለህ አላለኝም መሰላችሁ! በአንድ ወቅት አባቴ "በእምነት ደካማ ጎንህን ለሚስጥረኛ ጓደኛ እንኳን እንዳትናገር" አለኝ። ለምን? አልኩት፤"ምክንያቱም ሰዎች ደካማ ጎንህን ካወቁ በኃላ መጀመሪያ የሚያደርጉት አንተን መጣል መጀመር ነው"አለኝ። "ታዲያ ከጣሉክ በኃላ እንዳትነሳ የሚያደርጉ መርዝ መርዝ የሆኑ ቃላቶችን ይረጩብሀል። አትችልም፣አታሸንፍም፣ተስፋ ቁረጥ እያሉ ምራቃችሁን እየተፉብህ ሞትህን እንድትመኝና ራስህን እንድታጠፋ ይገፋፉሀል" አለኝ ላላፉት 4 አመታትም በዚህ ከባድ ስቃይ ውስጥ እንዳሳለፈ ነገረኝ፤እኔም በጣም ተገረምኩ።ግን እንዴት ቻልከው አልኩት፤በምድር ላይ ተስፋ የምታደርገው ነገር ካለ ከገባህበት ሰቀቀን እንደምንም ብለህ ትወጣለህ።የሚገርምህ የእኔዋ ተስፋ እናትህ ወጓ ነበረች፤ከሷ ጋር የመኖር ፍላጎቴ እስከ ጥግ ድረስ በልቤ ውስጥ አየሉ ስለነበር በተጎዳሁና በተሰበርኩ ጊዜ እኔና እሷ ያሳለፍናቸውን ጥዑም ትዝታ እያስታወስኩ ስቃዬን እረሳለው አለኝ፤"ስለዚህ በየትኛውም ነገር ብንጎዳ ተስፋ የምናደርገው ነገር ካለ የመኖር ተስፋችን ዕድል አለው እያልከኝ ነው" አልኩት።"አዎ እንደዛ እያልኩህ ነው፤ነገር ግን የአንተን ችሎታና ተሰጥኦ ደስትቢን ውስጥ ለመጣል የሚሞክሩ፤መኖርህን እንድትጠራጠር የሚያደርጉና ተስፋህን ከአንተ ለመውሰድ ቀን ከሌት የሚጥሩ ሰዎች ባጋጠሙክ ጊዜ ምንም ሳትል ዝም ብለህ ከቀቀጠልክ ነውአለና ፀጉሬን አሻሽቶኝ እየተሯሯጠ ወጣ። 👉 @et_books1 👉 @et_books1

ያንድ ምሽት ሀሳብ (በእውቀቱ ስዩም) ልማድ ሆኖበት፥ ሌቱ ቢገፋ ምን ሊጠቅመኝ፥ ነው የማንቀላፋ ህልም ሸክም ነው፥ ፈቺው ከጠፋ፤ ሳይጎድለኝ ለዛ ሳያንሰኝ ውበት የቀን ጨረቃ፥ ላይንሽ ሆኘበት፥ ቀልብን የማይስብ፥ የሳር ቀለበት መወደዴ ብላሽ ምኞቴ ዘበት፤ የአሻንጉሊት ላም፥ ጡት እንደማለብ የፈረስ ሀውልት፥ እንደመጋለብ ሲሳይሽ ፈልቆ፥ ጣት አያርስም የትም ብትኖሪ፥ የትም አልደርስም፥ የሚፈሰውን አልፎ ገደቤን -እንባየን ልሼ ደረቴን ሰብሮ ፥ የሸሸ ልቤን ቦታው መልሼ በፍቅር ፈንታ ፥እረፍት ሸመትሁኝ ቁርጤን አወቅሁኝ ፤ ለካ ሰው ቢማር፥ ከሊቅ፥ ከመጻፍ፥ ከኑሮ ከእድሜ ቁርጥን ማወቅ ነው የእውቀት ፍጻሜ;: 👉 @et_books1 👉 @et_books1

📚ርዕስ:- ነቃዮድ 77 📝ደራሲ:- ቴዎድሮስ መዝገቡ 📜ዘውግ:- ልብ ወለድ 📅ዓ.ም:- 20** 📖የገፅ ብዛት:- ከ1 - 57 👉 @et_books1 👉 @et_books1

ሰላም ጤና፡ ስለ ራስ ጎበና፣ ጸሐፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ እና አጽመ ጊዮርጊስ ገብረ መሲህ ጋሽ ባይሩ የጻፉትን Three Portraits ታውቁታላችሁ? ቆንጆ ሥራ ነው ! 👉 @et_books1 👉 @et_books1

📚The World is Flat ✍Thomas L Friedman 👉 @et_books1 👉 @et_books1

+1
✅ርዕስ:- ዛምራ ✅ደራሲ:- ይስማዕከ ወርቁ ✅ይዘት:-  ልቦለድ ✅የገፅ ብዛት:- 234 📆ዓ. ም:- 2013 ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ 👉 @et_books1 👉 @et_books1

📚ርዕስ:- ግዮናዊነት 📝ድርሰት:- ምስጋናው አንዱዓለም 📜ይዘት:- . 📆የመጀመሪያ ዕትም:-... 2010 📖የገፅ ብዛት:- 413 👉 @et_books1 👉 @et_books1

📚ርዕስ:- ጂንየስ መሆን እንዴት ይቻላል- 📝ደራሲ:- 📅ዓ ም:- 2010 📖የገፅ ብዛት:-200 #Join & share ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ 👉 @et_books1 👉 @et_books1

📍ያልነቀልከው ነገር መባዛቱ አይቀርም ✨ብዙዎች የተሳሳቱትን ስህተት እንዳትሳሳት ይህችን ምክር ጣል ላድርግልህ፡፡ በሕይወትህ አንድ ችግር አይተህ በቸልተኝነት “በራሱ ጊዜ ይሄዳል” ብለህ ከመተው ተ
📍ያልነቀልከው ነገር መባዛቱ አይቀርም ✨ብዙዎች የተሳሳቱትን ስህተት እንዳትሳሳት ይህችን ምክር ጣል ላድርግልህ፡፡ በሕይወትህ አንድ ችግር አይተህ በቸልተኝነት “በራሱ ጊዜ ይሄዳል” ብለህ ከመተው ተጠበቅ፡፡ ማንኛውም ችግር ዝም ካልከው በራሱ ጊዜ ይሄዳል የሚል አመለካከት ያላቸው ሰዎች ችግሩ ገዝፎና በዝቶ ከአቅም በላይ ሲሆን ነው የሚባንኑት፡፡ ✨እስቲ አቤትህ ብቅ ጥልቅ ሲሉ ያየሃቸውን ተባዮች ዝም በላቸው፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ተባዝተው ካልወረስንህ ይሉሃል፡፡ የተቀረውንም በሕይወትህ አላስፈላጊ የሆኑ ሁኔታዎችንም በዚህ መልኩ ማየት መጀመር አለብህ፡፡ ✨እውነታው፡- ያላከምከው ቁስል በቶሎ አይድንም . . . ያልነቀልከው አረም በራሱ አይሄድም . . . መስመሩን ያላበጀህለት ሰው በላይህ ላይ መረማመዱ አይቀርም . . . ያልቀጣኸው ልጅ መሞላቀቁና መበላሸቱ አይቀርም . . . እምቢ በማለት ያላባረርከው ሃሳብ ወደተግባርና ወደልማድ መለወጡ አይቀርም፡፡ ✨ዛሬ ምን ምን እንዳከናወንክ የማሰብህን ያህል ከዚያው ጋር ሊያሳስብህ የሚገባው ነገር አለ፡፡ ዝም ብለህ እንደፈለገ እንዲሆን ስለተውከው ጉዳይም ጭምር ልታስብና የእርማት እርምጃን ልትወስድ ይገባሃል፡፡ አለዚያ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ ነገ ችግሩን መጋፈጥህ አይቀርም፡፡ ለዚያውም ገዝፎና አይሎ!                        ✍  ዶ/ር እዮብ ማሞ 👉 @et_books1 👉 @et_books1

+1
ተርጓሚ: ኤፍሬም እንዳለ የሲድኒ ሺልደን ልብ አንጠልጣዩና በህክምና ወንጀል ዙሪያ የሚያጠነጥነው "Nothing Lasts Forever" የአማርኛ ትርጉም 👉 @et_books1 👉 @et_books1

🇺🇸 በ1845 በታላቋ ብሪታንያ አንድ ብዙዎችን ያስገረመ ሕግ ወጥቶ ነበር ህጉ ራሱን ለማጥፋት የሞከረ ሰው በስቅላት ይቀጣል። 👉 @et_books1 👉 @et_books1
🇺🇸 በ1845 በታላቋ ብሪታንያ አንድ ብዙዎችን ያስገረመ ሕግ ወጥቶ ነበር ህጉ ራሱን ለማጥፋት የሞከረ ሰው በስቅላት ይቀጣል። 👉 @et_books1 👉 @et_books1

✍ሰመመን ደራሲ ሲሳይ ንጉሱ የዩንቨርስቲ ተማሪዎች ሊያነቡት የሚገባ መፅሀፍ ነው ። ደራሲው የዩንቨርስቲን ላይፍ ቁልጭ አድርጎ ያሳየናል ። 👉 @et_books1 👉 @et_books1

+1
📕ርዕስ:- 25 የስኬት ቁልፎች 📝ደራሲ:-እዮብ ማሞ 📅ዓ.ም:-... 📖የገፅ ብዛት:- 1 - 77 👉 @et_books1 👉 @et_books1

Motherfucker ብዙውን ግዜ ፊልሞችና ሙዚቃዎች ላይ እንሰማዋለን። ይህ የጥቁር አሜሪካውያን ባህል ነው። ቃሉ የሚሰማው በጥቁሮች አንደበት በተለይ በሂፕሆፕ ሙዚቃ ውስጥ ነው። ለመሆኑ ቃሉ ከየት መጣ? በባርነት ዘመን፣ በ18ተኛው ክፍለዘመን አሜሪካውያን ሰፋፊ የጥጥ እርሻ ያለማሉ። እርሻዎቹ ሙሉ ለሙሉ የሚለሙት በጥቁር ባሪያዎች ጉልበት ነው። እርሻዎቹ በጣም ሰፋፊ በመሆናቸው፣ ብዙ የባሪያ ኃይል ፍላጎት ነበር። አዳዲስ ባሪያዎች የሚመለመሉበት ሁለት መንገድ ነበር። አንደኛው በቀጥታ ከውቅያኖሱ አፍሪካ ሄዶ ባሪያዎችን መጥለፍ ሲሆን፣ ሁለተኛው እዚያው አሜሪካ ያሉ ባሮች ሲዋለዱ፣ እነዚህ ምንም የማያውቁ ህጻናት ወደ ባርነት ህይወት መክተት ነው። አስቡት! ባርነትን ለልጅህ ስታወርስ። ግፉ በዚህ አይበቃም። የባሪያ አሳዳሪዎች የባሪያዎቻቸው ቁጥር እንዲጨምር ወንድ ባሮች ከገዛ እናቶቻቸው ጋር ግብረ ስጋ ግንኙነት እንዲፈጽሙና እንዲያስረግዟቸው ያስገድዱ ነበር። motherfucker የሚለው ቃል የመጣው ከዚያ ነው። ከባርነት ታሪክ በጣም አስቀያሚው ክፍል ይሄ ነው። ባሮች ቀን ሙሉ የማያቋርጥ ስራ እንዲሰሩ ይገደዳሉ፤ ላብና ደም ያፈሳሉ። እንደ አህያ ይሰራሉ፤ እንደ አህያ ይገረፋሉ። ነገር ግን ከዚህ ሁሉ የባሰው ከገዛ እናታቸው ጋር እንዲተኙ ሲገደዱ ነው። ፈረሶች ለዘር ሲባል ከገዛ እናታቸው ጋር ይዳቀላሉ። ለባሪያ አሳዳሪዎች ባሮች ከፈረስ የማይለዩ ተራ እንስሳት ነበሩ። አንዲት ባሪያ ሴት ከብዙ ወንዶች ጋር እንድትተኛ ትገደዳለች። ስታረግዝ አባቱ ማን እንደሆነ እንኳን እሷ ፈጣሪ አያውቀውም። ባሪያ አሳዳሪዎችም አንዲት ሴት ባሪያን የሚመለከቱት እንደ ሰው ሳይሆን፣ ብዙ ጩጬ ባሪያዎችን እንደምትፈለፍል ኢንኩቤተር ነው። ነጮች ባሮችን nigger, negro ወዘተ እያሉ በጣም offensive እና ክብረ-ነክ ቃል ይጠቀማሉ። ነገር ግን እንደ motherfucker ቀፋፊ የለም። አንድ ሁለት ነገሮች ከባርነት ጋር በተያያዘ፦ አይታችኋል አሜሪካን፣ እስር ቤት ውስጥ እስረኞች የሚለብሱት ዩኒፎርም ብዙውን ግዜ ቀለሙ ቢጫ፣ ወይም ብርቱካናማ ነው። አጥጋቢ ምክንያት አለው። እስረኞች ለማምለጥ ቢሞክሩ፣ ጠባቂዎቻቸው በቀላሉ ማስተዋል ይችላሉ። በባሮችም ግዜ ያው ነበር። ባሪያዎች በሰፊው እርሻ ውስጥ ተሰማርተው ሲለፉ እየዋሉ፣ በመሀል ለማምለጥ ቢሞክሩ፣ ነጭ ጠባቂዎቻቸው ከሩቁ ተመልክተው እንዲተኩሱባቸውና ከማምለጥ እንዲከለክሏቸው ያስችላል። ሌላው ታሪክ ደግሞ ከስም ጋር የተያያዘ ነው። ከላይ እንደተገለጸው በባርነት የተወለዱ ልጆች አባታቸው አይታወቅም። ነጭ የባሪያ አሳዳሪዎችም ገና ለሚወለዱ ህጻናት ነጭ የባእድ ስም ይሰጧቸዋል። አንዱም ምክንያቱ፣ ስም ከማንነት መገለጫዎች አንዱ በመሆኑ ይህንን ስሜት ለማጥፋት ነው። የባርነት ታሪክ ካበቃ በኋላ ብዙ ጥቁሮች ስማቸውን እየለወጡ በX ተክተውታል። ለምሳሌ Malcolm X የመጀመሪያ ስሙ ማልኮም ሊትል ነበር። X የሚያሳየው ያልታወቀውን አፍሪካዊ ማንነት ነው። 👉 @et_books1 👉 @et_books1

+1
📚ርዕስ:-የቀይ ኮከብ ጥሩ 📝ደራሲ:-በዓሉ ግርማ 📜ዘውግ:- ልብ ወልዳዊ ታሪክ ነክ 📅ዓ.ም:- 1973 ክፍል:- ሁለት 2 📖የገፅ ብዛት:- 264 👉 @et_books1 👉 @et_books1

ርዕስ፡ ጨዋታ (ጦቢያ በየሩሳሌም) ደራሲ፡ ተስፋ ስንታየሁ ዘውግ፡ አጫጭር ልቦለድ ዓ.ም፡ 1989 የገፅ ብዛት፡ 446 SHARE and JOIN🙏 👉 @et_books1 👉 @et_books1

📔 ከዕለታት ግማሽ ቀን ✍ደራሲ፡- አሌክስ አብርሀም መሉ መፅሐፉን እነሆ 👉 @et_books1 👉 @et_books1

የባከነሌሊት! #/በበዕውቀቱ ስዩም/ ወይ ሮንድ አላደርኩ ወይ ኮኮብ አልቆጠርኩ ወይ ደልቶኝ አልጨፈርሁ ወይ ውስኪ አልተዳፈርሁ የባለጌ ወንበር:ኮርቻ አልተሳፈርሁ ወይ ሰአታት ቁሜ ቤተክስያን ስሜ ሰይጣን አላሳፈርሁ። ሌቦች ደብድበውት አንዱን ምስኪን ላሥር ባምቢስ ድልድዩ ሥር ቆስሎ የወደቀ ገላው በላዩ ላይ :እንደጨርቅ ያለቀ ፊቱ ተሸፍኖ :በደምናአቧራ “ በኡራኤል ርዱኝ”ብሎየሚጣራ ምስኪን አባወራ ብብት ሥር ገብቼ አፋፍሼ አንስቼ ተሸክሜ አድኜ ስፈልግ አምቡላንስ :ሲሻኝ ዶክተር ሁኜ ወይ ምግባር አልሠራሁ ወይ ጀብድ አልፍፀምኩኝ :ወይፅድቅ አላፈራሁ። አንድ በትረ-ሙሴ ሁለት ስስ አሎሎ ከጭኔ መሀከል ሲያመሽ ተንጠልጥሎ ሲባክን ዝምብሎ ”እሸኝ የኔ ጀግና እንደ ሰነፍቆሎ” የምትልመለሎ ልቤንሳትሰውረው አልጋየንሳትሰብረው። ወግቢጤ ሞንጭሬ:ፌስቡክላይ ሳለጥፍ ”እናትዋን ጨረቃ”የሚል ግጥም ሳልጥፍ። አንዲት ሴት-አዳሪ:ቺቺንያ ምንገድ ላይ እድሉዋ ሰባራ:ሰውነቱዋ አማላይ ካፍያውና እንባዋ:ተጋግዞ ሚያረጥባት ደምበኛ ስትጠበቅ:ደመኛ ጥሎባት አምስት ደፋሪዎች:ከበውሲያዋክቧት ሲገፉሲስቧት ”እረ በናታችሁ በወላድ ማህፀን እህትየላችሁም? ”ብላ ስትማፀን ልመናዋ ስቦኝ እንዳበጀ በለው :በደሏ አንገብግቦኝ ከሁዋላ ደርሼ ነበልባልለብሼ:ነበልባልጎርሼ እንደ ብሩስሊ :እንዳየሩ ጋኔን እግሬን ወንጨፍ ወንጨፍ ወዝወዝወዝወዝ ጎኔን በማረግ ቃኝቼ ከሁዋላ ነው ሲሉኝ ከፊት ተገኝቼ ካምስቱ መከከል አራቱን ነጥየ ከቻልኩ በካራቲካልቻልኩ በሳቅጥየ። ድል ሳላስ መዘግብ ውጥረት ሳለረግብ ወይ ታሪክ ሳልሰራ-ወይታሪክ ሳልዘግብ ያለ ምንም ጣጣ: ያለ ምንም ፀጋ አለሰበብ መሽቶ አለሰበብ ነጋ SHARE and JOIN🙏 👉 @et_books1 👉 @et_books1