ኢት-መጽሐፍት | ETHIO-BOOKS
前往频道在 Telegram
👉 "የምታነበው መጽሐፍ ለአንተ የሚያስብልህ ሳይሆን አንተ እንድታስብ የሚያደርግ ነው።" ሃርፐር ሊ Fiction (ልቦለድ), History (ታሪክ), Politics (ፖለቲካ), Psychology (ስነልቦና), Biography (ግለ-ታሪክ), Self-help(ራስ አገዝ),& Philosophy(ፍልስፍና) የሀገር ውስጥ & የውጪ ሀገር መጽሐፎችን ያገኛሉ!አስተያየትዎን እዚህ @Desutech_bot ያድርሱን
显示更多1 990
订阅者
-124 小时
-47 天
-5230 天
帖子存档
📖የኛ ሰው ገመና
➡️በልቅ ወሲብ መዘመን
➡️የሀዋሳ እብደቶች
➡️የድንግልና ንግድ
➡️የኢትዮጵያዊያን ገመና በደቡብ አፍሪካ
ከ18 አመት #በታች #የተከለከለ
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
የቱ ነው ሰው ማለት
በውስጡ እያደባ በአፉ የሚጫወት
እኔን ግራ ገባኝ የቱ ነው ሰው ማለት?
ወይስ እያበላህ ዞር ብሉ የሚያማህ
ዛሬ የኔ ነው ስትል ነገ የሚከዳህ
ጓደኛ ስትለው የሚሆንህ ጠላት
እስቲ እንነጋገር የቱ ነው ሰው ማለት?
እኔ አንዳንድ ጊዜ ጓደኛዬ እልና
የሆዴን በሙሉ ዘክዝኬ እነግርና
መፍትሔ ስጠብቅ ለነገርኩት ሚስጥር
ሲወራ እሰማለሁ ጉዳዬ ከመንደር።
እኔም ጓደኛዬን ምነው እባክህ ብለው
ችግሬን አዳምጠህ መፍትሔ ሳትሰጠው
ምን በደልኩህና ለአገር ነዛኽው?
ብዬ ብጠይቀው ብሎ መለሰልኝ ለአንድ ሰው ብቻ ነው።
ሚስጥር ከሁለት ሰው ካለፈ ጨዋታው
ነገር መባከኑን እንደምን አጣኽው?
መፍትሔ ሳይሰጥህሚስጥር የሚያወጣው
የጓደኝነት እምነት መለኪያ ምንድነው?
ለጥያቄዬ መልስ ሃሣብ እፈልጋለሁ።
እናንተም ንገሩኝ ሰው ማለት የቱነው ሰው ያለሰው መኖር እንደማይችል አውቀህ ሰው ሆይ ለጓደኛህ ታማኝ ሁን እባክህ።
#ህልምና ስኬት ላይ የተወሰደ
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
📚ርዕስ :-ገመና
📝ደራሲ :- ሰለሞን ሹምዬ
💠ዘውግ :- ልብ ወለድ
#18+ Only
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
አንጋረ ፈላስፋ. (የፈላስፎች አነጋገር) ከሊቀ መዘምራን ሞገስ ዕቁበ ጊዮርጊስ (ከግዕዝ ወደ አማርኛ ተተረጎመ) ጥቅምት 23 1953 ዓም
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
ዎላይተቶ ሌምሱዋ - የወላይትኛ ምሳሌያዊ ንግግሮች ከአማርኛ ትርጉሞች ጋር
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
ፍትሀ ብሔር - Ethiopian Civil Code (Amharic)
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
ትንንሽ Trauma በትልቅ trauma ማዳን!
ኤልያስ ሽታኹን
የነካኃቸው አበቦች እሾህም ነበራቸው።
ያምራሉ ያደማሉ።
ከሁሉ ነገር ርቄ የራሴን ቤት ከሰራሁ ዓመታት ሆነውኛል።
ቤቴ ያፈሳል ግን ይደብቀኛል።
ካባ ደርቡልኝ ሙግት የለኝም።
ዙፋን አልሻም።
ጥግ ካገኘሁ እፍ እፍ ብዬ መሬቱ ላይ መደላደል አውቅበታለሁ።
ትህትናን አላውቀውም። ሀበሻ ትህትናን Abuse ሲያርገው አይቻለው። መቻልህን ደካማ ጎን ያረገዋልና።
በጥርስ ማልቀስ በዐይን መሳቅ ተለማመድኹ።
የማጣውን አጥቼ
የሚቀበረውን አፈር አልብሼ
(አንድ ሁሁት ወዳጆቼን)
የሚታመመውን መድኃኒት ፈልጌለት
የሚታሰረውን ወዳጄን ባልታገልለት ጸልዬለት
(*Belay Bekele Weya እግዚአብሔር ይጠብቅህ።)
መኖር ከስሩ እስስኪገነድሰኝ አለሁ።
ለደስታዬም ለሀዘኔም ድንኳን ትከሉልኝ አልልም።
ለሻማዬ አለሁለት።
የመገኘቴን ዋጋ አስሉልኝ ብዬ አላውቅም።
በሰው ልብ ስንት አወጣለሁ አልልም።
ስለክብር የልመና ቃል የለኝም።
እንዲሁ አመሰግነዋለሁ ጠባቂዬን።
በመከራ መሐል ስለማገኛት " ትንሽ እረፍት " እንዲሁ ደስ ይለኛል እንጂ ሰው መሆንስ ጓዙ ብዙ ነው።
የመኖር አንጻር በየት ነው።
በማን በኩል የታየው ነው ህይወት።
ከህመሜ ድኜ አይደለም።
ትንንሽ ሀዘኖቼን በትልልቅ ሀዘኖች ተክቼ ነው።
የማትፈጽመውን ተስፋ አትስጥ!!!!
በአንድ ቅዝቃዜው ባየለበት የክረምት ወራት አንድ ባለጠጋ አንድን ድሃ ሽማግሌ ከበሩ ደጃፍ ቆሞ ያገኘውና፣ "በዚህ ቅዝቃዜ ለብርድ የሚሆን ልብስ ሳትለብስ እንዴት ብርዱን ተቋቋምከው?" ሲል ይጠይቀዋል።
ድሃው ሽማግሌም፣ " መብረዱን ይበርደኛል፤ ነገር ግን የምደርበው ልብስ ስለሌለኝ ብርዱን እችለዋለሁ " ሲል ይመልሳል። ባለጠጋውም ድሃውን ሽማግሌ፣ " ቆይ ጠብቀኝ ወደ ቤት ገብቼ የምትለብሰው ይዤልህ መጣለው" ይለውና ወደ ቤቱ ይገባል። ድሃው ሽማግሌም በደስታ ስሜት ከበሩ ደጃፍ ሆኖ መጠባበቅ ይጀምራል።
ባለጠጋው ሰው ወደ ቤት ከገባ በኋላ በሌሎች ጉዳዮች ይዋከብና ድሃውን ሽማግሌ ይረሳዋል። በነጋታው ጥዋት ከእንቅልፉ ሲነሳ ግን ድሃውን ሽማግሌ ያስታውሰውና ሊፈልገው ወደ ውጪ ሲወጣ፣ ድሃው ሽማግሌን በቅዝቃዜው ምክንያት ሞቶ በድኑን ያገኘዋል። ነገር ግን ሽማግሌው ከመሞቱ በፊት ለባለጠጋው ሰው በብጣሽ ወረቀት እንዲህ የሚል ማስታወሻ ጽፎለት ነበር፣
"የምለብሰው ልብስ ባልነበረኝ ጊዜ ቅዝቃዜውን የምቋቋምበት ብቃት ነበረኝ። ነገር ግን አንተ የምለብሰውን እንደምታመጣልኝ ቃል ስትገባልኝ፣ በቃልህ ላይ ተስፋዬን አደረኩ፤ በዚህም ምክንያት ቅዝቃዜውን የመቋቋም አቅሜን አጣሁ።"
የታሪኩ ዘላቂ ትምህርት፦ " የማትፈጽመውን ነገር ቃል አትግባ! ቃል መግባትህ ለአንተ ትልቅ ነገር ላይሆን ይችላል፤ ቃል ለምትገባለት ሰው ግን ሁሉ ነገሩ ሊሆን ይችላል።
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
