Minda Girma Law Office ምንዳ ግርማ ህግ ቢሮ 0910126619
前往频道在 Telegram
Welcome to Minda Girma Law Office Channel. ነፃ የህግ ምክር አገልገሎት እና ህግ- ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻነሉን ሰብስክራይብ በማድረግ ለሌሎችም ያጋሩ! Subscribe & share this channel using the link https://t.me/mindalaw for legal updates, case insights, and more. 📞0910126619 ጠበቃ እና የህግ አማካሪ
显示更多1 604
订阅者
无数据24 小时
-37 天
+530 天
帖子存档
1142_የኤሌክትሮኒክ_ደረሰኝ_ሥርዓት_አስተዳደር_መመሪያ_ቁጥር_1142_2018.pdf6.48 KB
1142_የኤሌክትሮኒክ_ደረሰኝ_ሥርዓት_አስተዳደር_መመሪያ_ቁጥር_1142_2018.pdf6.48 KB
1095-የፌዴራል-መንግስት-የንብረት-አስተዳደር-መመሪያ-ቁጥር-1095-2017 (1).pdf
የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሳባ የሕገ መንግሥት ትርጉም አያስፈልጋቸውም በማለት የወሰናቸው መዝገቦች ዝርዝር
ተ.ቁ መ. ቁጥር
1. 5477/13
2. 7565/15
3. 7756/15
4. 7761/15
5. 7899/15
6. 7972/15
7. 7975/15
8. 7978/15
9. 7991/15
10. 7999/15
11. 8009/15
12. 8010/15
13. 8012/15
14. 8013/15
15. 8014/15
16. 8016/15
17. 8017/15
18. 8020/15
19. 8032/15
20. 8037/15
21. 8041/15
22. 8054/15
23. 8072/15
24. 8078/15
25. 8083/15
26. 8086/15
27. 8095/15
28. 8110/15
29. 8114/15
30. 8102/15
31. 8201/16
32. 8210/16
33. 8212/16
34. 8222/16
35. 8229/16
36. 8422/16
37. 8430/16
38. 8431/16
39. 8437/16
40. 8438/16
41. 8440/16
42. 8448/16
43. 8510/16
44. 8512/16
45. 8518/16
46. 8525/16
47. 8535/16
48. 8552/16
49. 8568/16
50. 8589/16
51. 8598/16
52. 8615/16
53. 8626/16
54. 8663/16
55. 8683/16
56. 8703/16
57. 8730/16
58. 8735/16
59. 8750/16
60. 8794/16
61. 8800/16
62. 8892/16
63. 8895/16
64. 8907/16
65. 9136/17
66. 9424/17
67. 9544/17
68. 9551/17
69. 9744/17
70. 9750/17
71. 9837/17
72. 10052/17
73. 10226/18
74. 10452/18
75. 10737/18
76. 10740/18
77. 10748/18
78. 10881/18
79. 10924/18
80. 11149/18
81. 11426/18
82. 11087/18
ማስፈቀጃ
83. 10803/18 ፈቃድ አላገኘም
*ማስታወሻ*
1. ቁጥራቸው የቅርብ ጊዜ የሆኑት ጉዳዮች ቀድመው የታዩበት ምክንያት በጉባዔው መመሪያ መሰረት ቅድሚያ አግኝተው ምርመራቸው የተጠናቀቀ (የወንጀል፣ የአካል ጉዳተኞች፣ የአሰሪና ሰራተኛ፣ ከፍ/ቤት ሪፈራል የተላኩ፣ የታገዱ መዝገቦች መሆናቸውን እየገለፅን ከዚያ ውጭ ያሉት ግን እንደ አመጣጥ ቅደም ተከተላቸው የተስተናገዱ ናቸው፡፡
2. ከላይ የተዘረዘሩትን ውሳኔዎች የውሳኔ ግልባጭ ከሁለት ሳምንት በኋላ በጉባዔው ፅ/ቤት በመቅረብ ማግኘት የሚቻል መሆኑን እንገልፃለን፡፡
መረጃው የሕገ መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ጽ/ቤት ነው
ቅፅ 22 ሰ/መ/ቁ 137545 በወንጀል የተከሰሰ ሰው የግል ተበዳይን በመከላከያ ምስክርነት ያቀረበና የግል ተበዳይም ድርጊቱ ያለመፈጸሙን በመግለጽ የምስክርነት ቃል የሰጠ ከሆነ ዓ/ህግ የግል ተበዳይ የምስክርነት ቃል በደላላ ወይም በጥቅም የተገኘ መሆኑን ለማረጋገጥ እስከ አልቻለ ድረስ ተከሳሽ ክሱን አልተከላከለም ሊባል የማይገባ ስለመሆኑ፡፡
+3
በፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ያለዎትን ጉዳይ በተመለከተ በአካል መምጣት ሳይጠበቅብዎ መከወን የሚችሏቸው ጉዳዮችና አማራጮች፤
✍️የቀጠሮ ቀን ማወቅ፣
✍️ክርክሩ ያለበትን ደረጃ ማወቅ፣
✍️ጉዳይዎን መከታተል፣
✍️ዝርዝር የዕለት ቀጠሮ ማየት፣
ሲፈልጉ የመዝገብ ቁጥር ወይም የተከራካሪ ወገኖችን ስም በማስገባት መፈለግ የሚችሉባቸው አማራጮች፤ እንዲሁም የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የታተሙ የሰበር ዉሳኔዎች ቅጂ፣ የድምጽ ቅጂ እና ሌሎችም አገልግሎቶችን ለማግኘት ሲፈለጉ የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ፤
1) የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መተግበሪያን (Application) "Federal Supreme Court" ብለው ከ App Store ወይም ከ Play store ላይ በማውረድ፣
2) በፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ድረ-ገጽ fsc.gov.et/ ላይ በመግባት፣
3) በነጻ የስልክ ጥሪ መስመራችን 992 በመደበኛዉ የስራ ሰዓት በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፣
4) አጠቃላይ ከተቋሙ የሚወጡ የተለያዩ መረጃዎች በፍጥነት እንዲደርስዎ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችንን ይከተሉ፡፡
👉ፌስቡክ ↠ https://web.facebook.com/FSCEthiopia
👉ትዊተር (ኤክስ) ↠ https://x.com/federalsupreme1
👉ሊንክድኢን ↠ https://tinyurl.com/supereme-court-of-ethiopia
👉ቴሌግራም ↠ https://t.me/fscethiopiaPR
👉ዋትስአፕ ↠ https://tinyurl.com/fscethiopia
👉ዩቲዩብ ↠ https://www.youtube.com/@fscethiopia
👉ቲክቶክ ↠ https://tiktok.com/@federal.supreme.court
የመጽሐፍ ማየስ / Book Review
ርዕስ: የአእምሯዊ ንብረት ሕግ
ደራሲ: ዳዊት በዛብህ
ገምጋሚ: ካሴ መልካም
ይህ ግምገማ የዳዊት በዛብህን 281 ገፅ ያለውን “የአእምሯዊ ንብረት ሕግ” መፅሐፍ ያስተዋውቃል። መፅሐፉ የፈጠራ፣ የቅጂ መብት፣ የንግድ ምልክት፣ የንግድ ሚስጥር፣ AI እና ዓለም አቀፍ የአእምሯዊ ንብረት ክርክሮችን ከኢትዮጵያ ሕግ ጋር በማያያዝ የሚዳስስ የሕግ ሙያ መፅሐፍ ነው።
🔗 ሙሉውን ያንብቡ፦
https://abyssinialaw.com/blog/intellectual-property-book-review-by-kassie-melkam
የሰ|መ|ቁ 47800
“በመሰረቱ የፈቃድ ወይም የፎርም ጉድለት ያለበት ውል ሕጉ መብት በሚሰጠው ሰው የይፍረስልኝ ጥያቄ ሲቀርብበት ፈራሽ እንደሚሆን በመርህ ደረጃ በሕጉ በግልጽ የሰፈረ ጉዳይ ነው፡ በመሆኑም ውሉ በሚፈፀምበት ወቅት ጉድለት የነበረበት መሆኑ ከተረጋገጠ ውሉ እንዲፈርስና ባለጉዳዮች ወደነበሩበት ሁኔታ እንዲመለሱ ማዘዝ ከፍርድ ቤት የሚጠበቅና ሕጉም የሚያዘው መርህ ነው፡፡ (የፍትሐብሔር ሕግ ቁ.1815 ይመለከታል) ሆኖም ይህ ተዋዋዮችን ወደነበሩበት የመመለስ መርህ ተፈፃሚ ማድረግ የማይቻል ከሆነ ወይም ለአንደኛው ተዋዋይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያስከትል ከሆነ ውሉን ለመፈፀም የተከናወኑ ተግባራት ፀንተው እንደሚቆዩ የፍትሐብሔር ሕግ አንቀጽ 1817 በግልጽ ደንግጎታል፡፡ በመሆኑም ፍርድ ቤቱ ውሉ ሲመሰረት ጉድለት የነበረበት መሆኑን ቢያረጋግጥም ውሉን ማፍረስ የማይቻል ወይም ለአንደኛው ወይም ለሁሉም ወገን ከፍተኛ ጉዳት የሚያስከትል መሆኑን በሂደት ከተረዳ ተዋዋይ ወገኖች ወደነበሩበት ሊመለሱ አይገባም በማለት ትእዛዝ ሊሰጥ ይችላል፡ ይህ ትርጉም ይህ የሰበር ችሎት በሌሎች በርካታ ጉዳዮችም የተከተለው ነው፡፡
አሁን በቀረበልን ጉዳይም ፍ/ቤቱ የተከተለው ይህን መርህ ነው። ውሉ ሲመሰረት ጉድለት እንደነበረበት አረጋግጧል፡፡ በሌላ በኩል ውሉ በ1992 ዓ.ም ከተፈፀመ በኋላ በመልስ ሰጪ በኩል ተጨማሪ ንብረት የታከለበት መሆኑን ግንዛቤ ውስጥ አስገብቷል፡ አመልካችም በሰበር አቤቱታቸው ጭምር በተሸጠው ንብረት ላይ ተጨማሪ ግንባታ የተካሄደበት መሆኑን አይክዱም:: ሁኔታው ይህ ከሆነ ደግሞ ፍ/ቤቶች የውሉ መፍረስ የሚያስከትለው ጉዳት በዝርዝር ገልጸው ውሉን ከማፍረስ ይልት ፀንቶ እንዲቆይ ማዘዛቸው የሕጉን አንቀጽ 1817 መንፈስና ግልጽ ቃል የተከተለ እንጂ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተሰራበት ውሳኔ ሰጡ ለማለት የሚያበቃ ሆኖ አላገኘነውም" ::
Repost from Minda Girma Law Office ምንዳ ግርማ ህግ ቢሮ 0910126619
212950_በወንጀል_የተከሳሽ_ድርሻ_በዓህግ_ምስክሮች_ላይ_ጥርጣሬ_መፍጠር_ስለመሆኑ_1.pdf2.91 KB
Repost from Minda Girma Law Office ምንዳ ግርማ ህግ ቢሮ 0910126619
ሰ/መ/ቁጥር - 219887 ታህሳስ 25 ቀን 2015 ዓ.ም
አንድ ሰው ሁለት ሚስቶችን ያገባ እንደሆነ እና ጋብቻው በሞት ወይም በሌላ ህጋዊ ምክንያት የፈረሰ እንደሆነ እና ከሁለቱ ሚስቶች አንደኛዋ ንብረቶቹን በማፍራት ሂደት የተለየ አስተዋጽኦ ያደረገች መሆኑን ያረጋገጠች እንደሆነ ከተፈራው ንብረት ግማሽ ድርሻ የሚገባት ሲሆን፣ የሌላኛዋ ተጋቢ ከባል ጋር ግማሹን ትካፈላለች።
በእርግጥ ሟች ሁለት ሚስቶች ኖረውት የሞተ እንደሆነ ሁለቱ ሚስቶች የንብረቱን ድርሻ ግማሹን ለሁለት ሊካፈሉ እንደሚገባ የፌዴራል ጠቅሊይ ፍርድ ቤት በሰ/መ/ቁጥር 24625 ላይ ውሳኔ ሰጥቷል። በሌላ በኩል በሰ/መ/ቁጥር 45548 ላይ (ቅጽ 13 ላይ እንደታተመው) አንድ ሰው ሁለት ሚስቶች ያሉት እንደሆነ ንብረቶቹን በማፍራት ረገድ ከሚስቶቹ አንደኛዋ ሚስት ከሌላኛዋ የተሻለ አስተዋጽኦ ያደረገች መሆኑ የተረጋገጠ እንደሆነ ባደረገችው አስተዋጽኦ ልክ ልትካፈል ትችላለች የሚል ሃሳብ መነሻ በማድረግ ባል ንብረቱን በሚያፈራበት ጊዜ ከእርሱ ጋር በትዳር የነበረች ሚስት ንብረቱን በማፍራት ረገድ በቀጥታ አስተዋጽኦ እንዳደረገች ግምት ተወስዶ ከንብረቱ ግማሹን ድርሻ የማግኘት መብት እንዳላት እና በአንፃሩ በቀጥታ አስተዋጽኦ ያላደረገች ሚስት ከባል ድርሻ ግማሹን የማግኘት መብት ብቻ ያላት ስለመሆኑ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡ በሰ/መ/ቁጥር 50489 (ቅጽ 11 እንደታተመው) ጨምሮ በሌልች በርካታ መዛግብት ላይም ይህንኑ የሚያጠናክር ውሳኔ ሰጥቷል።
አግባባዊ የመድኃኒት አጠቃቀም ቁጥጥር መመሪያ ቁጥር 1138/2018
Rational Medicine Use Control Directive No. 1138/2026
#ተጨማሪ
የጉምሩክ አዋጁ ያሻሻላቸው ተጨማሪ ጉዳዮች ምንድናቸው?
አስመጪዎችና ላኪዎች በባህር እንዲሁም በየብስ የሚያስገቧቸው ዕቃዎች በመጋዘን የሚቆዩበት ጊዜ ከ15 ወደ 45 ቀናት ፣ በአየር የሚገቡ ደግሞ ከ10 ወደ 30 ቀናት እንዲያድግ ተደርጓል።
በተጨማሪም አስመጪዎች በአንድ ዲክላራሲዮን ላስገቧቸው ዕቃዎች ሙሉ ቀረጥ በአንዴ ለመክፈል የገንዘብ እጥረት ካጋጠማቸው፣ ቀረጥ የከፈሉበትን የዕቃ መጠን ብቻ ለይተው በክፍልፋይ እንዲያወጡ የሚፈቅድ አዲስ አሰራር ተዘርግቷል።
የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማገዝም፣ ሶፍትዌር ወደ አገር ሲገባ የሚታሰበው ቀረጥ በውስጡ ባለው መረጃ ዋጋ ላይ ሳይሆን፣ ሶፍትዌሩ በተጫነበት መሣሪያ (Carrier Medium) ዋጋ ላይ ብቻ እንዲሆን ተወስኗል።
የውጭ ምንዛሬ ተመን አወሳሰን ላይም የቀረጥ ስሌት የሚከናወነው ዲክላራሲዮኑ በጉምሩክ ተመዝግቦ ተቀባይነት ባገኘበት ቀን ብሔራዊ ባንክ በሚያወጣው ጠቋሚ (Indicative) የምንዛሬ ተመን መሠረት እንዲሆን ተደንግጓል።
በገዥና በሻጭ መካከል ግንኙነት ባለበት ሁኔታ ደግሞ፣ አስመጪው ዝምድናው በዋጋው ላይ ተጽዕኖ አለማሳደሩን ማረጋገጥ ካልቻለ ጉምሩክ የቀረበውን ዋጋ ውድቅ የማድረግ ሥልጣን ተሰጥቶታል።
ረቂቅ አዋጁ ኮንትሮባንድ ለመከላከል የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን ለመደበቅ ተብለው ተሻሽለው የተሠሩ ወይም ከፍተኛ መጠን ያለው የኮንትሮባንድ ዕቃ የጫኑ ተሽከርካሪዎች፣ የዕቃው ዋጋ ግምት ውስጥ ሳይገባ በቀጥታ እንዲወረሱ ይደረጋል።
በኮንትሮባንድ ተግባር ላይ የተገኘ እንስሳ ባለቤት፣ የእንስሳውን ወቅታዊ የገበያ ዋጋ 100 በመቶ እኩል የገንዘብ መቀጫ እንዲከፍል ተደንግጓል።
በተጨማሪም መረጃ ለሚሰጡ እና ለሚተባበሩ አካላት የገንዘብ ወሮታ እንዲከፈል የተወሰነ ሲሆን፣ ከኮንትሮባንድ ዕቃ ሽያጭ የሚገኘው ገቢም ለኮሚሽኑ አቅም ግንባታ እንዲውል ይደረጋል።
ሌላው፣ አንድ አስመጪ በጉምሩክ ውሳኔ ላይ ቅሬታ ካለው ይግባኝ ማለት የሚችለው፣ ክርክር የተነሳበትን ቀረጥና ታክስ 50 በመቶ አስቀድሞ መክፈሉ ሲረጋገጥ ብቻ ነው።
በተጨማሪም አስመጪዎች ለጉምሩክ የሚሰጡት የዋጋ መረጃ እንደ ምስጢር ተጠብቆ እንዲቆይ ሕጋዊ ዋስትና ተሰጥቷል። መረጃው ሊገለጽ የሚችለው ለፍርድ ቤት ክርክር ሲፈለግ ብቻ ይሆናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
የኮንትሮባንድ እቃዎችን ጭኖ የተገኘ የጭነት ተሽከርካሪ ተወርሶ ለመንግሥት ገቢ እንዲደረግ የሚያዘው አዋጅ በነገው ዕለት ይጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
የኮንትሮባንድ ወንጀል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየረቀቀና በአገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያሳድረው ጉዳት እየከፋ በመምጣቱ፣ለሕገ-ወጥ ንግድ ማጓጓዣነት የሚያገለግሉ ተሽከርካሪዎች በቀጥታ እንዲወረሱ የሚደነግግ አዲስ የአዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረቡ ይታወቃል።
ቀደም ሲል በአዋጅ ቁጥር 1160/2011 በተደረገ ማሻሻያ፣ የተሽከርካሪ ባለቤቶች በወንጀሉ በቀጥታ ካልተሳተፉ ንብረታቸው ከመወረስ ይልቅ 100,000 (መቶ ሺህ) ብር ብቻ ተቀጥተው ንብረታቸውን እንዲረከቡ ይፈቀድ ነበር።
ይሁን እንጂ ይህ አሰራር ኮንትሮባንዲስቶች የተቀመጠውን ቅጣት እንደ ቀላል የሥራ ማስኬጃ ወጪ በመቁጠር የሕገ-ወጥ ንግዱ ይበልጥ እንዲጧጧፍ በር መክፈቱን የተሻሻለው አዋጅ ይገልጻል።
በተጨማሪም ወንጀሉ አሁን ላይ እጅግ የረቀቀ መልክ በመያዙ:-
• ኮንትሮባንዲስቶች መንገድ በሌለባቸው አካባቢዎች በከፍተኛ ፍጥነት የሚሽከረከሩ፣
• ለመለየት የሚያዳግቱ መደበቂያ አካላት የተገጠሙላቸው አልፎ ተርፎም ጎማቸው በጥይት ቢመታ እንኳ እንዳይቆሙ የሚያስችል የጥይት መከላከያ የገጠሙላቸው ተሽከርካሪዎችን በመጠቀም ላይ መሆናቸው ይገልጻል።
ይህንን ተግዳሮት ለመፍታት አዲሱ ረቂቅ አዋጅ ጥብቅ ማሻሻያዎች አድርጓል።
በእዚህም መሰረት ማንኛውም ተሽከርካሪ የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን ለመደበቅ እንዲያስችል ሆኖ የተሠራ፣ የተለወጠ ወይም መደበቂያ አካል የተገጠመለት ሆኖ ከተገኘ በቀጥታ ይወረሳል።
አንድ ተሽከርካሪ የጫነው የኮንትሮባንድ ዕቃ መጠን የገንዘብ ሚኒስቴር በሚያወጣው መመሪያ ከተቀመጠው ገደብ በላይ ከሆነ፣ የዕቃው ግምታዊ ዋጋ ከግምት ውስጥ ሳይገባ ተሽከርካሪው ተወርሶ ለመንግስት ገቢ ይደረጋል።
አዋጁ የባለቤቶችን መብት ግምት ውስጥ በማስገባት፣ ተሽከርካሪው ከመወረሱ በፊት ባለቤቱ ጉዳዩን እንዲያውቀውና ተሽከርካሪው ጥቅም ላይ ስለዋለበት ሁኔታ ማስረጃዎችን በማቅረብ ራሱን እንዲከላከል ዕድል እንደሚሰጠውም በድንጋጌው ላይ ተመልክቷል።
@SM
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
