Ibnu Hashim(أمير هاشم)
前往频道在 Telegram
"ألا لستُ للفردوسِ أهلا ولا أقوى على نار الجحيم فهبْ لي توبة واغفر ذنوبي فإنك غافر الذنب الأغامي"!!
显示更多📈 Telegram 频道 Ibnu Hashim(أمير هاشم) 的分析概览
频道 Ibnu Hashim(أمير هاشم) (@ibnuhashm) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 12 392 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 7 333,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 717 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 12 392 名订阅者。
根据 23 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -212,过去 24 小时变化为 -10,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 13.21%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.33% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 1 637 次浏览,首日通常累积 1 280 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 28。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“"ألا لستُ للفردوسِ أهلا ولا أقوى على نار الجحيم فهبْ لي توبة واغفر ذنوبي فإنك غافر الذنب الأغامي"!!”
凭借高频更新(最新数据采集于 24 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
12 392
订阅者
-1024 小时
-237 天
-21230 天
帖子存档
12 393
ሐቂቃ ቁም ነገር እናውራና ለምሳሌ አሜሪካ በኒውዮርክ የሚገኙትን መንትያ ሕንፃዎች አጋይቷል ብላ የምትወነጅለው ኡሳማ ቢን ላዲን የመጀመሪያ ትዳሩን የያዘው ገና በ17 ዓመቱ ነበር። ይህ ማለት ትዳር ለትግል ሕይወትም ሆነ ለማንኛውም ትልቅ ዓላማ መሳካት ምን ያህል ወሳኝ መሆኑን ማሳያ ነው።
እኔ እንደ ኡሳማ ቢን ላዲን ለሙስሊሙ ኡማ እና ለዲኔ በትልቁ ባልታገልም'ኳ ዕድሜዬ እየቆሰቆሰው ስለሚገኝ እና ለተሻለ ትግል ሲባል አሁን ላይ ማግባቴ ኸይር ነዉ ብዬ አስባለሁ። እስከ አሁንም ድረስ አግባ ብሎ የሚመክረኝ የቅርብ ሰው ስላጣሁ ነው እንጂ ፍላጎቱ ነበረኝ¡
ስለዚህ ባለፈው የነገርኳችሁን የቁርዓን ሒፍዙንና የመሳሰሉትን መስፈርቴን ለጊዜው ወደ ጎን ትታችሁ አሁን ላይ ዝም ብላችሁ ትንሽ ሻል የምትለዋን እህት ዳሩኝ። ከዚያ በኋላ በአሏህ ፍቃድ ያስቀመጥኩትን መስፈርት የምታሟላውን ሴት ደግሞ በሁለተኛዋ ሚስቴ በኩል ለማግኘት እሞክራለሁ¡
በነገራችን ላይ እስከዛሬ ድረስ ለኡማዉ በትንሹ አሳክቻቸዋለሁ ብዬ ከማስበዉ እያንዳንዱ ስኬቶች ጀርባ ሁልጊዜም ብርታት የምትሆን እና የምታግዘኝ አንዲት ልጅ ነበረች። አሏህ ይዘንላት።
ወደ ገደለዉ ስንገባ ጨከን ብላችሁ እኔ ላይ Invest አድርጉ ታተርፉብኛላችሁ¡
t.me/IbnuHashm
12 393
እንዲህ ያለ የቂል ተግባር በአደባባይ የሚፈፅሙት የሚመሩትን ሕዝብ ከመናቅ የሚመነጭ እንደሆነ እጠረጥራለሁ። ስንትና ስንት ያልተቀረፉ መሰረታዊ የሕዝብ ጥያቄዎች ያሉበት ተቋም ዝም ብሎ አንድ ሽልማት ተቀበልኩ በሚል ሰበብ ብቻ ልክ እንደ አዲስ ሙሽራ በአደባባይ ላይ በክፍት መኪና እየዞሩ ማሳየት ምን የሚሉት የብክነት እና የቅንጦት ተግባር ነው?
ይህ ነገር በአግባቡ ካለመሰልጠን እና የሀላፊነት ስሜት ከማጣት የሚመጣ ካልሆነ በስተቀር በሌላ በምንም ሊገለፅ አይችልም። በችግር እና በለቅሶ ውስጥ ባለ ማህበረሰብ ፊት እንዲህ በከንቱ ውዳሴ መፈንጠዝ የሕሊናም ተጠያቂነትን ያመጣል።
በግሌ እንዲህ ያለ የንቃተ ሕሊና ዝቅጠት የሚንፀባረቅበትን የይስሙላ ድራማ ስመለከት ይሸክከኛል። ምቾት እና ሰላምም ይነሳኛል። ኧረ ተው እናንተ ባክናችሁ አና ደንዝዛችሁ ማህበረሰቡንም አታደንዙዙት። ከፊት ለፊታችሁ ስንት ስራ ይጠብቃችኋል።
t.me/IbnuHashm
12 393
የሆ ጊዜ እኛ ሰፈር ተከራይተው የነበሩ የሆኑ ቤተሰቦች ነበሩና ከእነሱ ዉስጥ እጅግ የምወደው አንድ እኩያ ጓደኛዬ ነበረኝ። ከዛሬ 4 ወይም 5 ዓመት አካባቢ የሰሜኑ ጦርነት ወደ አማራ ክልል ገብቶ ኮምቦልቻን ሊወር ጥቂት ቀናት ሲቀሩት እሱና ቤተሰቦቹ ሁኔታው ስላሰጋቸው በጊዜ ወደ አዲስ አበባ ሸሽተዉ ነበር። እኔ ግን ከተማዋን ሳለቅ እዚያው ኮምቦልቻ ውስጥ ነበር ያሳለፍኩት። ከዛ በኋላ እሱ በዛው እንደሄደ ሳይመለስ ትምህርቱን እየተማረ ቀጠለ።
ከአራት ዓመታት በኋላ እሱና ቤተሰቡ ከአዲስ አበባ በመነሳት በድጋሚ እዚሁ እኛ ሰፈር መጥተው ቤት ተከራዩ። ከተከራዩ ገና አንድ ሳምንት'ኳ ሳይሞላቸው እኔን ሊዘይረኝ አሁን ከመሸ እኛ ቤት ብቅ አለ። ተቃቅፈን ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ ቁጭ ብለን የልብ የልባችንን አያወጋን ያንን ሁሉ የስደት ጊዜ አሳልፎ አሁን ላይ ትዳር ይዞ የሁለት ልጆች አባት መሆኑን አበሰረኝ።
የዚህን ጊዜ ይህንን ወሬ ከጎን ሆና ስትሰማ የነበረችው ኡሚ እንዴት ስታየኝ እንደነበረ ሱብሐን አሏህ የሚያስኝ ነዉ😁(በዉስጧ ይሄኔ አንት ግን ተቀምጠህ... እያለች ነዉ)
አሁን ቤቱ ልዳርህ ወይስ ራስህ ይዘሃት ትመጣለህ? በሚል ቀጭን ትዕዛዝ ተዉጧል😭 ከዚህ ሁሉ ጣጣ መዘየሩ ባይከፋ ምን አለ ኡሚ በሌለችበት ሰዓት ሆኖ ብቻዬን መጥቶ ቢዘይረኝ ኖሮ¡
t.me/IbnuHashm
12 393
ከሁለት ቀን በፊት፤ ከትናንት ወዲያ ምሽት ላይ ስለ ትዳር መስፈርቴ ያለኝን አመለካከት እና መስፈርቴ ምን እንደሆነ ሀሳቤን ለእናንተ አጋርቻችሁ ነበር።
እኔ ሀሳቡን ሼር ያደረኩት የራሴን መስፈርት ምን እንደሆነና ይህ አይነት ሰዉ የሚገኘዉ ለአሏህ ታማኝ ስንሆን እንደሆነ ለመግለጽ ብቻ ነበር።
አሁን ግራ የገባኝ፤ ሀሳቡን 17 ሰዉ ሁላ ሼር አድርጎታል። የእኔ ጥያቄ ለማን ነዉ ሼር ያደረጋችሁት? ለምንስ ምክንያት ነዉ ሼር ያደረጋችሁት? ግራ ገብቶኝ ነዉ። ሼሩ ለእናንተ ምን ጥቅም?(እኔ ሀሳቤን ለእናንተ ገለፅኩኝ እንጂ እንዲች አይነት ሚስት ፈልጉልኝ አላልኩም😁) ወይስ ከሀሳቤ ላይ ተመርኩዛችሁ እንዲች አይነት ሴት እያፈላለጋችሁልን ነዉ¿ እንዲህ ከሆነ በድብቅ አታድርጉት ግልፅ ንገሩኝ'ና አብረን እንፈልግ¡
ፅሑፉ ግን ለምን ሼር እንደተደረገ አሁንም አልገባኝም። ጥያቄ አለኝ መልስ እፈልጋለሁ።
t.me/IbnuHashm
12 393
በነገራችን ላይ የዚህን ሴሌብሬሽን ዜና በፀሐይ መማር ትወዳለች ትጠይቃለች ጥዑመ ዜማ ታጅቤ ነበር ያየሁት። የተሰማኝ ሥፍር ቁጥር የለሽ ደስታ እንባዬን አፍሶታል። መጅሊሳችን የዘመናት ጥያቄያችንን ፈቶ ከአትሌቶቻችን በላይ ኢትዮጲያን በዓለም አስጠርቶ ዳይመንዱን ይዞ ስለመጣ ተደምምያለሁ።
ፀሐይ መማር ስለምትወድ በጣም ደስተኛናት፤ መማር ከወደዳችሁ ተማሩሩ... የሚለው ስንኝ ላይ ስደርስ'ማ አልቻልኩም እዬዬን አቀለጥኩት¡
ጠቡን'ኮ ወገን ኧረ ቢስሚላህ😏
t.me/IbnuHashm
12 393
በዉቢቷ ወሎ ኮምቦልቻ ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም!
የአሊፍ በጎ አድራጎት ማህበር ተወዳጅ በሆነው ቁርዓናዊ ጉዞ ፕሮግራሙ ሁለተኛውን ዙር መድረኩን የልቤ ጠጋኝ በሚል መሪ ቃል እሁድ ሰኔ 21 ቀን አዘጋጅቷል። በዕለት ተዕለት የሕይወት ውጣ ውረድ እና ግርግር ውስጥ የደከመች ነፍስ የምታርፍበት፣ በዱንያ ፈተናዎች የተሰበረች ልብ የምትጠገንበት ልዩ የዳዕዋ ፕሮግራም ነው።
በዚህ መድረክ ላይ የልባችንን ቁስል በቁርዓን መመሪያ የምናክምበት ሲሆን ልብን በሚያርሱ እና በሚያረጋጉ ውብ ትምህርቶች የሚታወቀዉ ኡስታዝ ኑሩ ቱርኪ በአካል ተገኝቶ የልብን መዳኛ መንገዶች በቁርዓን ብርሃን ያሳየናል።
ሁላችሁም በዚህ ፕሮግራም ላይ በመገኘት የነፍስያችሁን ስንቅ እንድትሸምቱ አሊፍ በጎ አድራጎት ማህበር ጥሪውን ያቀርባል።
📌ቦታ:- ኻሊድ መስጅድ ፊት ለፊት ባዛር ግቢ
⏰️ ሰዓት:- ከ2:00 ጀምሮ
🗓 ቀን:- እሁድ ሰኔ 21 2018 ዓ.ል
ለበለጠ መረጃ:- 0914476787
t.me/IbnuHashm
12 393
ሚስት፦ ልጇን ልታስተኛ ወደ መኝታ ቤት ስትገባ
ባል፡- ምን ላግዝሽ
ሚስት፡- ጎሽ የኔ ጌታ ከፌስታል ውስጥ ድንች አውጣና ግማሹን ልጠህ ጣድልኝ
ባል፡- እሺ
t.me/IbnuHashm
12 393
የአሏህ መልእክተኛ ሱለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም ሶሐባዎቻቸውን አስከትለዉ ከመካ ወደ መዲና በገቡበት ወቅት በከተማይቱ ውስጥ በርካታ የአይሁድ ጎሳዎች ይኖሩ ነበር። በከተማይቱ የነበሩት አብዛኞቹ እንቅስቃሴዎችም የአይሁድንና የክርስትናን ቀኖና መሰረት ያደረጉ ነበሩ። ከዕለታት አንድ ቀን በከተማይቱ የሚኖሩ አይሁዳውያን ከወትሮው ለየት ባለ ሁኔታ ሁላቸውም ፆመኛ ሆነው አገኟቸዉ። ይህንን ያስተዋሉት ነቢም ወደ እነሱ ጠጋ በማለት ለምንድን ነው ዛሬ የፆማችሁት? ሲሉ ጠየቋቸው።
አይሁዳውያኑም መልሰው ይህ ለእኛ ታላቅ ቀን ነው፤ በዛሬዋ ቀን ጌታ ሙሳን ከፈርዖን ግፍ ድል አጎናፅፏቸዋል። እኛም ይህንን የድል ቀን በማሰብ ደስታችንን ለጌታ ለማድረስ እንፆማለን፤ ሙሳም ፁመውታል በማለት መለሱላቸዉ። በዚህ ጊዜ ነቢም ታላቁን ወንድማቸውን ነቢዩ ሙሳን አስታወሱ፤ የድሉ ቀንም ታያቸዉም። ከዚያም ለአይሁዳውያኑ ለሙሳ እኮ ከእናንተ ይልቅ እኔ ይበልጥ እቀርበዋለሁ በማለት መለሱላቸዉ። ወዲያውኑም ኡመታቸው ይህንን ቀን እንዲፆሙ አዘዙ።
በዚህን ጊዜ ሶሐባዎች በውስጣቸው ቅር ተሰኙ። ጎረበጣቸዉ። ምቾትም ነሳቸው። ወደ ነቢ በመቅረብ የአሏህ መልእክተኛ ሆይ! ይህ ቀን እኮ አይሁድና ክርስቲያኖች የሚያልቁት እና የሚፆሙት ቀን ነው፤ እኛም ልክ እንደነሱ አሥረኛውን ቀን ብቻ መፆማችን መመሳሰል አይሆንብንምን? በማለት ስጋታቸውን ለነቢ አቀረቡ።
ነቢም ቀጠል በማድረግ ለሶሓባዎቻቸዉ በሚቀጥለው ዓመት አሏህ ብሎ ከደረስኩኝ ከአይሁዶች ጋር ላለመመሳሰል ዘጠነኛውንም ቀን አብሬ እፆማለሁ በማለት መለሱላቸዉ። ከነገ ወድያ ዕለቱ አሹራ ነው።
t.me/IbnuHashm
12 393
የአሏህ መልእክተኛ ሱለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም ሶሐባዎቻቸውን አስከትለዉ ከመካ ወደ መዲና በገቡበት ወቅት በከተማይቱ ውስጥ በርካታ የአይሁድ ጎሳዎች ይኖሩ ነበር። በከተማይቱ የነበሩት አብዛኞቹ እንቅስቃሴዎችም የአይሁድንና የክርስትናን ቀኖና መሰረት ያደረጉ ነበሩ። ከዕለታት አንድ ቀን በከተማይቱ የሚኖሩ አይሁዳውያን ከወትሮው ለየት ባለ ሁኔታ ሁላቸውም ፆመኛ ሆነው አገኟቸዉ። ይህንን ያስተዋሉት ነቢም ወደ እነሱ ጠጋ በማለት ለምንድን ነው ዛሬ የፆማችሁት? ሲሉ ጠየቋቸው።
አይሁዳውያኑም መልሰው ይህ ለእኛ ታላቅ ቀን ነው፤ በዛሬዋ ቀን ጌታ ሙሳን ከፈርዖን ግፍ ድል አጎናፅፏቸዋል። እኛም ይህንን የድል ቀን በማሰብ ደስታችንን ለጌታ ለማድረስ እንፆማለን፤ ሙሳም ፁመውታል በማለት መለሱላቸዉ። በዚህ ጊዜ ነቢም ታላቁን ወንድማቸውን ነቢዩ ሙሳን አስታወሱ፤ የድሉ ቀንም ታያቸዉም። ከዚያም ለአይሁዳውያኑ ለሙሳ እኮ ከእናንተ ይልቅ እኔ ይበልጥ እቀርበዋለሁ በማለት መለሱላቸዉ። ወዲያውኑም ኡመታቸው ይህንን ቀን እንዲፆሙ አዘዙ።
በዚህን ጊዜ ሶሐባዎች በውስጣቸው ቅር ተሰኙ። ጎረበጣቸዉ። ምቾትም ነሳቸው። ወደ ነቢ በመቅረብ የአሏህ መልእክተኛ ሆይ! ይህ ቀን እኮ አይሁድና ክርስቲያኖች የሚያልቁት እና የሚፆሙት ቀን ነው፤ እኛም ልክ እንደነሱ አሥረኛውን ቀን ብቻ መፆማችን መመሳሰል አይሆንብንምን? በማለት ስጋታቸውን ለነቢ አቀረቡ።
ነቢም ቀጠል በማድረግ ለሶሓባዎቻቸዉ በሚቀጥለው ዓመት አሏህ ብሎ ከደረስኩኝ ከአይሁዶች ጋር ላለመመሳሰል ዘጠነኛውንም ቀን አብሬ እፆማለሁ በማለት መለሱላቸዉ። ከነገ ወድያ ዕለቱ አሹራ ነው።
t.me/IbnuHashm
12 393
ኢራን የጎል ክልሏን እንደ ሆርሙዝ ዘግታ አቻ ለአቻ ስትወጣ ሳዑዲ ግን...😭 አሁን ምን ይባላል ይሄ¿
እንዳዘምቱብኝ ደግሞ ስለ ኳስ ብቻ ነዉ ያወራሁት😁
t.me/IbnuHashm
12 393
ስለ ትዳር ከተነሳ አይቀር እንደ ፐርሰናል ''ከዚህኛው ቀጥሎ'' የማልደራደርበት ዋነኛው መስፈርቴ ቢኖር የቁርዓን ሐፊዝ መሆኗን ነው። ከዚህ ቀጥሎ ነው እንግዲህ ውበት፣ ሐያ፣ ሙያ፣ ኒቃብ የመሳሰሉት ሌሎች መስፈርቶች በየተራ የሚቀጥሉት። ዋናውና ከሁሉ በላይ የሚቀድመው ግን የቁርዓን ሐፊዝ መሆኗ የግድ ነው።
ለምን እንደሆነ ታውቃላችሁ? ትዳር ማለት ጊዜያዊ ስሜት ብቻ አይደለም፤ በትዳር ውስጥ ነገን የሚረከብ ትውልድን የመፍጠር እና የመቅረፅ ከባድ ሀላፊነት አለ። የእኔ ልጅ አቅሷን ነፃ ባያወጣ ቢያንስ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች መከታና አለኝታ እንዲሆን አጥብቄ እመኛለሁ። ይህ ዓይነቱ ስብዕና ያለው ልጅ ደግሞ የሚፈጠረው ልክ እንደ እንደ ሰላሐዲን አል አዩቢ እናት ማህፀኗ የተባረከ እና ልጇን በተርቢያ የምታንፅ እናት ስትኖር ነው። ለዚህ ደግሞ እሷ ራሷ በአሏህ ቃል የታነፀች መሆን ይኖርባታል።
ቁርዓንን የሐፈዘችና በውስጧ የአሏህን ቃል የተሸከመች ሴት ቀልቧ የተረጋጋ፣ ሥነ ምግባሯ ያማረ፣ አሏህን የምትፈራ ደግ ባልንጀራ ናት።
ስለዚህ እኔ ቁርዓን የሐፈዘችዉን ሴት ነዉ የማገባዉ። እንዲህ አይነቷ ሴት ደግሞ ለአሏህ ታማኝ እስከሆንን ድረስ ትገኛለች።
t.me/IbnuHashm
12 393
በነገራችን ላይ ይህቺ ልጅ ጋር በጣም ሷሂብ ሁነናል¡ በዲኗም ጥሩ ልጅ እንደሆነች ተነግሮኛል፤ ዝም ብላችሁ ዱዓ አድርጉ። አሁን የቀረኝ አባቷን ሂጄ ማሳመን ነዉ። ትንሽ ባለሀብት ነገር ነዉ እኔም ለክፉ አልሰጥም የምንግባባ ይመስለኛል😁 በዲንም በኩል ቢመጣ ለክፉ አልሰጥም፣ ፂምም አለኝ፣ መልክም ጠየም ያልኩም ነገር ነኝ ስለዚህ በሁሉም በኩል ቢመጣ ለክፉ የምሰጥ አይነት ሰዉ አይደለሁም ስለዚህ እሺ የሚል ይመስለኛል።
እምቢ ካለ ግን እዚህ ያሉትን ላጤ ሰራዊትን ነዉ አከታትዬ የምልክበት¡ የዛኔ እንግባባለን😎 ላጤዎች አላችሁ¿
t.me/IbnuHashm
12 393
በቅርቡ😑 እኔ'ማ ደግሼ ሰርግ ካላበለኋችሁ አሚር አይደለሁም¡ ባይሆን ወንድ ልጅ ላገባ ነዉ ካለ ምን አለዉ አይባልም፤ ተነሳሽነት ካለዉ በቂ ነዉ(ግልባጭ ለአባቷ¡)
በሌላ ግልባጭ ደግሞ እናንተ ለሰርጉ ስጦታ አዘጋጁ፤ ዝም ብሎ በልቶ መመለስ የለም¡ መጅሊስ፣ ፍሪጅ፣ ቲቪ፣ ላዉንደሪ ምን አምን ይዛችሁ ኑ¡ እኔ ተነሳሽነት ካለኝና እና ሚስት ይዤ ከመጣሁ በቂ ነዉ😁
ላጤዎች ይህንን ቪዲዮ አይታችሁ ይቁጫችሁ እስቲ¡ ባይሆን አደራችሁን ልጃገረድ አግቡ። እነርሱ አንደበታቸው ጣፋጭ፣ ማህፀናቸው ንፁህ፣ ቶሎ የማያረጁ፣ በትንሽ ነገርም የሚብቃቁ ናቸውና። (የአላህ መልእክተኛ የተናገሩት ኢብኑ ማጃህ እና በይሀቂ ዘግበውታል) ቁርዓን ሀፊዝም ብትሆን አይከፋም!
t.me/IbnuHashm
12 393
በነብዩሏህ ሙሳ ዐለይሂ ሰላም ዘመን አንዲት እናት ልጅ አጥታ፤ መዉለድ ተስኗት ወደ ነብዩሏህ ሙሳ ዐለይሂ ሰላም ዘንድ በጥልቅ ሐዘን ዉስጥ ሆና በመምጣት ''አንቱ የአሏህ ነብይ ሆይ! አሏህ ልጅ እንዲሰጠኝ ለምኑልኝ ጠይቁልኝ፤ ብቸኛ ሆንኩኝ'' በማለት አጥብቃ ጠየቀቻቸው።
ለሕዝባቸው አዛኝ የሆኑት ነብዩሏህ ሙሳም ዐለይሂ ሰላም ፍላጎቷንና የልቧን ስብራት ይዘው ወደ አሏህ ፊት በመቅረብ ጌታዬ! ይህች ምስኪን ባሪያህ ልጅ ትናፍቃለችና ለምን ልጅ አትሰጣትም? ብለው ጠየቁላት። አሏህም እሷ መሃን እንደሆነችና ልጅ መዉለድ እንደማትችል ነገራቸው።
ነብዩሏህ ሙሳም ዐለይሂ ሰላም የአሏህን ውሳኔ ይዘዉ ለሴትየዋ በነገሯት ጊዜ ያላት የመጨረሻ ተስፋ የተቋረጠባት መሰላት። ፈበከት ወዘሀበት በጣም አልቅሳና ተንሰቅስቃ ወደ ቤቷ ተመለሰች። ነገር ግን ማልቀሷ የጌታዋን እገዛ ከመፈለግ የመጣ እንጂ ከአሏህ ራሕመት ተስፋ ቆርጣ አልነበረም። ወደ ቤቷም ገብታ ማታም ጠዋትም እጆቿን ወደ ሰማይ እየዘረጋች እንባዋን እንደ ጎርፍ እያፈሰሰች አሏህን መማፀንና መለመን ጀመረች።
ከአንድ ዓመት በኋላ አሏህ ሱብሀነ ወተዓላ ድንቅ ስጦታን አበረከተላት፤ መሃን የተባለችው ፀንሳ አረገዘች፤ ወለደችም። በደስታ ተሞልታ ይህንን ተዓምር ለሙሳ ዐለይሂ ሰላም ልትነግራቸው ልጇን ታቅፋ እየበረረች ሄደች። ነብዩሏህ ሙሳ ዐለይሂ ሰላም ሴትየዋ ልጅ ታቅፋ በተመለከቷት ጊዜ በመገረም ወደ ጌታቸው ፊታቸውን አዙረው ጌታዬ! አንተ እሷን መሃን ናት፤ አትወልድም ብለኸኝ አልነበረምን? ታዲያ እንዴት ልትወልድ ቻለች? ብለው ጠየቁ።
ሁሉን ቻዩ የሆነዉ አሏህም ለሙሳ ዐለይሂ ሰላም እንዲህ የሚል ምላሽ ሰጣቸው። አንተ ሙሳ ሆይ! አንተ መሃን ነሽ አትወልጅም አልካት። እሷ ግን ከእኔ ተስፋ ሳትቆርጥ ጌታዬ ልጅ ስጠኝ እያለች ጠዋትም ማታም እያለቀሰች ለመነችኝ። በዚህን ጊዜ እጆቿን በባዶ ለመመለስ አፈርኩኝ፤ ልጅንም ሰጠኋት በማለት መለሰላቸዉ። ይህን በሰሙ ጊዜ ነብዩሏህ ሙሳ ዐለይሂ ሰላም እጅግ ተደነቁ።
ወዳጆቼ ወሏሂ... ዱዓ በጣም ሀይል ያለዉ መሣሪያ ነው። ቀደርን ሁሉ ይቀይራል። አንድ ሙዕሚን ከኢማኑ እና ከሶላቱ ቀጥሎ በዚህች ምድር ላይ ሊኖረው የሚችለው ትልቁ እና ውድ ሀብቱ ቢኖር ዱዓ ነው። ዶክተሮች አይቻልም ቢሉሽ አሏህ ግን ይቻላል ባይ ነው። ምንም አይቸግረዉም። ምክንያቶች ሁሉ ቢዘጉብህ ሰማያትንና ምድርን ያለ ምንም ዓምድ የገነባው አሏህ አዲስ መንገድ ይከፍትልሃል። ከአሏህ ራህመት ተስፋ አትቁረጡ። እንባውን አፍስሶ አሏህን የለመነ ባሪያ መቼም ቢሆን አፍሮ አያዉቅም።
t.me/IbnuHashm
12 393
በነብዩሏህ ሙሳ ዐለይሂ ሰላም ዘመን አንዲት እናት ልጅ አጥታ፤ መዉለድ ተስኗት ወደ ነብዩሏህ ሙሳ ዐለይሂ ሰላም ዘንድ በጥልቅ ሐዘን ዉስጥ ሆና በመምጣት ''አንቱ የአሏህ ነብይ ሆይ! አሏህ ልጅ እንዲሰጠኝ ለምኑልኝ ጠይቁልኝ፤ ብቸኛ ሆንኩኝ'' በማለት አጥብቃ ጠየቀቻቸው።
ለሕዝባቸው አዛኝ የሆኑት ነብዩሏህ ሙሳም ዐለይሂ ሰላም ፍላጎቷንና የልቧን ስብራት ይዘው ወደ አሏህ ፊት በመቅረብ ጌታዬ! ይህች ምስኪን ባሪያህ ልጅ ትናፍቃለችና ለምን ልጅ አትሰጣትም? ብለው ጠየቁላት። አሏህም እሷ መሃን እንደሆነችና ልጅ መዉለድ እንደማትችል ነገራቸው።
ነብዩሏህ ሙሳም ዐለይሂ ሰላም የአሏህን ውሳኔ ይዘዉ ለሴትየዋ በነገሯት ጊዜ ያላት የመጨረሻ ተስፋ የተቋረጠባት መሰላት። ፈበከት ወዘሀበት በጣም አልቅሳና ተንሰቅስቃ ወደ ቤቷ ተመለሰች። ነገር ግን ማልቀሷ የጌታዋን እገዛ ከመፈለግ የመጣ እንጂ ከአሏህ ራሕመት ተስፋ ቆርጣ አልነበረም። ወደ ቤቷም ገብታ ማታም ጠዋትም እጆቿን ወደ ሰማይ እየዘረጋች እንባዋን እንደ ጎርፍ እያፈሰሰች አሏህን መማፀንና መለመን ጀመረች።
ከአንድ ዓመት በኋላ አሏህ ሱብሀነ ወተዓላ ድንቅ ስጦታን አበረከተላት፤ መሃን የተባለችው ፀንሳ አረገዘች፤ ወለደችም። በደስታ ተሞልታ ይህንን ተዓምር ለሙሳ ዐለይሂ ሰላም ልትነግራቸው ልጇን ታቅፋ እየበረረች ሄደች። ነብዩሏህ ሙሳ ዐለይሂ ሰላም ሴትየዋ ልጅ ታቅፋ በተመለከቷት ጊዜ በመገረም ወደ ጌታቸው ፊታቸውን አዙረው ጌታዬ! አንተ እሷን መሃን ናት፤ አትወልድም ብለኸኝ አልነበረምን? ታዲያ እንዴት ልትወልድ ቻለች? ብለው ጠየቁ።
ሁሉን ቻዩ የሆነዉ አሏህም ለሙሳ ዐለይሂ ሰላም እንዲህ የሚል ምላሽ ሰጣቸው። አንተ ሙሳ ሆይ! አንተ መሃን ነሽ አትወልጅም አልካት። እሷ ግን ከእኔ ተስፋ ሳትቆርጥ ጌታዬ ልጅ ስጠኝ እያለች ጠዋትም ማታም እያለቀሰች ለመነችኝ። በዚህን ጊዜ እጆቿን በባዶ ለመመለስ አፈርኩኝ፤ ልጅንም ሰጠኋት በማለት መለሰላቸዉ። ይህን በሰሙ ጊዜ ነብዩሏህ ሙሳ ዐለይሂ ሰላም እጅግ ተደነቁ።
ወዳጆቼ ወሏሂ... ዱዓ በጣም ኃያል ያለዉ መሣሪያ ነው። ቀደርን ሁሉ ይቀይራል። አንድ ሙዕሚን ከኢማኑ እና ከሶላቱ ቀጥሎ በዚህች ምድር ላይ ሊኖረው የሚችለው ትልቁ እና ውድ ሀብቱ ቢኖር ዱዓ ነው። ዶክተሮች አይቻልም ቢሉሽ አሏህ ግን ይቻላል ባይ ነው። ምንም አይቸግረዉም። ምክንያቶች ሁሉ ቢዘጉብህ ሰማያትንና ምድርን ያለ ምንም ዓምድ የገነባው አሏህ አዲስ መንገድ ይከፍትልሃል። ከአሏህ ራህመት ተስፋ አትቁረጡ። እንባውን አፍስሶ አሏህን የለመነ ባሪያ መቼም ቢሆን አፍሮ አያዉቅም።
t.me/IbnuHashm
12 393
የድምፃችን ይሰማ ንቅናቄ ፈርጥ እና የሀሩን ሚዲያ መስራች እንዲሁም ዋና ሥራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ አብዱረሂም አህመድ ከብዙ ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ ወደ እናት ሀገሩ ኢትዮጵያ ተመልሷል።
አብዱረሂም አህመድ ብዙ ያልተነገረለት በድምፃችን ይሰማ ጊዜ ሙስሊሙ ማህበረሰብ መብቱን በሰላማዊ መንገድ እንዲያስከብር ካደረጉት ግንባር ቀደም የቁርጥ ቀን ልጆች መካከል አንዱ ነው። ከዚህም አልፎ የኡማው ድምፅ የሆነዉን ሐሩን ሚዲያን በመመስረት የሕዝብን ብሶት በማስተጋባት ለሙስሊሙ ማህበረሰብ ትልቅ ዉለታ የዋለ ወንድማችን ነዉ።
ወንድማችን አብዱረሂም አህመድ ለሀገርህ እንኳን በሰላም አበቃህ።
t.me/IbnuHashm
12 393
የድምፃችን ይሰማ ንቅናቄ ፈርጥ እና የሀሩን ሚዲያ መስራች እንዲሁም ዋና ሥራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ አብዱረሂም አህመድ ከብዙ ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ ወደ እናት ሀገሩ ኢትዮጵያ ተመልሷል።
አብዱረሂም አህመድ ብዙ ያልተነገረለት በድምፃችን ይሰማ ጊዜ ሙስሊሙ ማህበረሰብ መብቱን በሰላማዊ መንገድ እንዲያስከብር ካደረጉት ግንባር ቀደም የቁርጥ ቀን ልጆች መካከል አንዱ ነው። ከዚህም አልፎ የኡማው ድምፅ የሆነዉን ሐሩን ሚዲያን በመመስረት የሕዝብን ብሶት በማስተጋባት ለሙስሊሙ ማህበረሰብ ትልቅ ዉለታ የዋለ ወንድማችን ነዉ።
ወንድማችን አብዱረሂም አህመድ፤ ለሀገርህ እንኳን በሰላም አበቃህ።
t.me/IbnuHashm
12 393
የኢራንና የአሜሪካ ስምምነት በይፋ መተግበሩን ተከትሎ የነዳጅ ዋጋ ከአንድ በርሜል 120 ዶላር ወደ 77 ዶላር በከፍተኛ ሁኔታ ቀንሷል። በዚህም ምክንያት የዓለም ማርኬቶች እና የንግድ ዘርፎች ትልቅ እፎይታ አግኝተዋል። ሆርሙዝም ሊከፈት ስለሆነ ዓለም አቀፍ የመርከብ ኩባንያዎችም ወደ መደበኛ ሥራቸው እየተመለሱ ነው።
ነገር ግን በዚህ ስምምነት ምክንያት በሁለቱም ሀገራት ውስጥ የፖለቲካ ክፍፍል ተከስቷል።
በኢራን በኩል የኢራን ፖለቲከኞች ለሁለት ተከፍለዋል። ግማሹ እንኳንም ይሄ ጦርነት አበቃ ሀገራችን ካለችበት ማዕቀብና ቀውስ የምታገግምበት ዕድል ተገኘ በሚል እፎይታን ሲመርጥ ሁለተኛው ወገን ግን ይህ ጦርነቱ አላበቃም፤ ጠላቶቻችን ተሸንፈው ሳይሆን ተዘጋጅተው ለመመለስ ጊዜ እየገዙ ነው። ከሁሉም በላይ እስራኤል በዚህ ስምምነት ላይ አንድም ቦታ አልፈረመችም፤ እሷ እስካልፈረመች ድረስ ደግሞ ምንም ዓይነት የደህንነት ማረጋገጫ የለንም። ታዲያ ለምንድ ነው ለጠላቶቻችን ፋታ የምንሰጠው? የሚሉ ጠንካራ ሀሳቦችን እየሰጡ ነዉ።
በተመሳሳይ ሁኔታ በአሜሪካ በኩልም በዚህ ስምምነት የውስጥ ፍትጊያ ላይ ናቸዉ። የኮንግረሱ ግማሹ ወገን ትራምፕ ይህንን እርቅ ያደረገው የእውኑን ሰላም ፈልጎ ሳይሆን በመጪው ኖቬምበር ላይ ለሚካሄደው የሚድተርም ምርጫ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ሲል የፈጠረው ስልት ነው ብለው ይተቻሉ። በሌላ ወገን በኩል ያሉት ፖለቲከኞች ደግሞ እንዴት ለኢራን 300 ቢሊዮን ዶላር የጦርነት ካሳ እንሰጣለን? ከዚህ በላይ ደግሞ የሚደረግላቸው የማዕቀብ መላላት እና የሚለቀቅላቸው የታገደ ንብረት ኢራንን ከዚህ በኋላ ማንም ሀገር ሊገደባትና ሊያስቆማት ወደማይችልበት የሀያልነት ደረጃ ያሸጋግራታል። የኢራን ኒውክሌር ቦምብ መሰራትም አይቀሬ ነው፤ ስለዚህ እስካሁን ያደረግነው ጦርነት ሁሉ ትርጉም አልባ ነበረ በማለት ትራምፕን እየወቀሱት ነው።
በዚህ መሓል ሌላው የተጎዳው አካል የሩሲያ የነዳጅ ገበያ ነው። ጦርነቱ እንደተከፈተ የሩሲያ የነዳጅ ኩባንያዎች ስቶክ በጣም ናኝቶ ነበር። ሆርሙዝ በመዘጋቱ ምክንያት ገበያው ላይ ምንም ዓይነት ተፎካካሪ ስላልነበራቸው የራሳቸውን ነዳጅ በከፍተኛ ዋጋ ሲሸጡ ከርመዋል። አሁን ግን ከእርቁ በኋላ ሩሲያ ራሷን የዋጋ ቅናሽ ጦርነት ውስጥ አግኝታዋለች። ገዥ ለማግኘት ዋጋዋን እያረገፈች ግዙኝ ወደሚል የልመና ደረጃ ወርዳለች።
ለብዙ ጊዜ ኢራን እና ሩሲያ ማዕቀብ ያለባቸው ሀገራት በመሆናቸው ተመሳሳይ ገበያዎችን ለመሳብ ሻዶው ፕራይሲንግ ማለትም ከዓለም አቀፍ ገበያ በታች በሆነ ዋጋ ተደብቀው ይሸጡ ነበር። አሁን ግን ኢራን እገዳው ሙሉ በሙሉ ሲነሳላት የምታገኘው ቢሊዮን ዳላር ኢኮኖሚዋን አሁን ካለበት የደቀቀበት ሁኔታ አውጥቶ ወደ ከፍተኛ ደረጃ ሊያደርሳት እንደሚችል በርካታ የኤኮኖሚ ግምቶች እየተነገሩ ነው።
t.me/IbnuHashm
12 393
ሳዑዲ ከምዕራባዉያን ጋር ጦርነት ገጥማ ሉዓላዊነቷን እና ክብሯን እንደ ኢራን አስከብራ ቢሆን ኖሮ እስከ አሁን ዑስጣዞቻችንና መንጋዎቻቸዉ አያስቀምጡንም ነበር፤ እንደ አህያ ይዘሉብን ነበር🤦♂️ ባለፈዉ'ኳ በኳሱ ባንዲራዋን መሬት አላስነካችም ብለዉ ትልቅ ጀብድ እንደተሰራ ሲዘሉብን ነበር።
t.me/IbnuHashm
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
