ch
Feedback
MTULSU(Mizan Tepi University Law students Union👩‍🎓👨‍🎓

MTULSU(Mizan Tepi University Law students Union👩‍🎓👨‍🎓

前往频道在 Telegram

A channel that aims to connect MTU law students of all years with a sense of unity and to exchange information. contact us Dawit Amanuel(MTULSU president) 👉0983225745 Dirshaye kida (Vice president) 👉 0965754565 Please join and Invite others too @MTULSU

显示更多
557
订阅者
无数据24 小时
+37
+2530
帖子存档
Repost from MTU School of Law
Dear Students, Congratulations on your outstanding achievement in the National Moot Court Competition! Securing 3rd place at
+1
Dear Students,   Congratulations on your outstanding achievement in the National Moot Court Competition! Securing 3rd place at a national level is no small feat—it reflects your hard work, dedication, critical thinking, and advocacy skills. You’ve made your university proud and set an inspiring example for your peers. This success is not just a trophy or a title; it’s a stepping stone toward a bright legal career and a testament to the power of preparation and teamwork. Keep pushing forward, continue sharpening your legal minds, and never stop striving for excellence. This is just the beginning—greater victories await you! With pride and encouragement, Abdurrahman Seid Lecturer, Mizan-Teppi University School of Law

9ኛው አገር አቀፍ የምስለ ችሎት ውድድር በባህር ዳር ዩንቨርሲቲ አሸናፊነት ተጠናቀቀ (10/09/2017 ዓ.ም) የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ከሚዛን ቴፒ ዩንቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 9ኛው አገር አቀፍ የምስለ ችሎት ውድድር በባህር ዳር ዩንቨርሲቲ አሸናፊነት ተጠናቀቀ፡፡ በዕለቱ የእንኳን ደህና መጣቹህ ንግግር ያደረጉት የሚዛን ቴፒ ዩንቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዜዳንት ዶ/ር ተፈራ ጌታቸው በንግግራቸው ለምስለ ችሎቱ መሳካት ሌት ተቀን የደከሙ የህግ ትምህርት ቤት አባላት፣ ኮንሰርቲም አባላት፣ ተወዳዳሪዎች፣ ዳኞችና የዩንቨርሲቲው ማህበረሰብን በማመስገን የቀጠሉ ሲሆን በተለይ የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለፕሮግራሙ የጀርባ አጥንት ሆኖ ስላገዘን ምስጋና ይገባዋል ብለዋል፡፡ የእለቱን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በሚንስቴር ዴዔታ ማዕረግ የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ክቡር አቶ ምትኩ ማዳ እንደዚህ አይነት ውድድሮች ተማሪዎች በክፍል ንድፈ ሃሳብ የቀሰሙትን ዕውቀት በውድድሩ ላይ በመሳተፍ ተግባራዊ እንዲያደርጉ ያግዛቸዋል ያሉ ሲሆን በዚህም የተሳታዎችን ብዛት ከ8 ወደ አስራ ሁለት ከፍ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል፡፡ ምስለ ችሎት ውድድር የሕግ ተማሪዎች ከትምህርታቸው መጠናቀቅ በኋላ በተግባር በሚሰማሩባቸው የሕግ ሙያ ዘርፎች ብቁ የህግ ባለሙያ እንዲሆኑ የተግባር ትምህርት ነው ያሉት አቶ ምትኩ በመሆኑም በውድድሩ የተለያዩ ክህሎቶችን በተለይም የጥናትና ምርምር የጥሁፍ ዝግጅትና በቃል የመከራከር ክህሎችን ለማዳበር ያግዛቸዋል ብለዋል፡፡ ለተሳታፊዎች የተሰማቸውን ሥሜት ያስተላለፉት የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳት ክቡር ዶክተር ዋቆ ገዳ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው ይህን ውድድር ከፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር በማዘጋቱ ደስተኛ መሆኑን በመናገር ለሁሉም የምስለ ችሎት ተዋናዮች ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የእለቱ የክብር እንግዳና የፌደራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ክቡር አምባሳደር ደግፌ ቡላ   በበኩላቸው ለውድድሩ ታዳሚዎች ባስተላለፉት መልዕክት ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ፕሮግራሙ በተሳካ መልኩ ማዘጋጀት በመቻሉ ምስጋናቸውን በመቸር ንግግራቸውን የቀጠሉ ሲሆን ተማሪዎች በንድፈ ሀሳብ ያገኙትን እውቀት ወደ ተግባር ለመለወጥ እንደነዚህ አይነት መድረኮች ጥሩ አጋጣሚዎች እንደሆኑ ጠቁመዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት የሚሰራቸውን አንኳር ተግባራት ለተሳታፊዎቹ የማሳወቅ ሥራ የሰሩት ክቡር አምባሳደሩ ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምሮችን ማካሄድ፣ የፍትሕ ዘርፉ ተዋናዮችን አቅም ግንባታ ሥራ መስራት፣ የፍትሕና ሕግ ማሻሻያዎችን መደገፍና የሃገሪቱ የሕግና ፍትሕ መረጃ ቋት ሆኖ ማገልገል የፌዴራል ህግና ፍትህ ኢንስቲትዩት ወደፊትም ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በትብብር መስራቱን ይቀጥላል ብለዋል ። በ9ኛው ምስለ ችሎት ውድድር ባህር ዳር ዩንቨርሲቲ 1ኛ፣ ሰላሌ ዩንቨርሲቲ 2ኛ እና አዘጋጁ ሚዛን ቴፒ ዩንቨርሲቲ 3ኛ በመውጣት ያጠናቀቁ ሲሆን  የምስለ ችሎት (Moot Court) ውድድር አሸናፊ ዩኒቨርሲቲዎች፣ ተማሪዎች፣  ዳኞች፣ ተሳታፊ ዩኒቨርሲቲዎች እና የፕሮግራም አስተባባሪዎች የተዘጋጀላቸውን የዋንጫ፣ የመዳሊና የሰርተፊኬት ሽልማት ከእለቱ የክብር እንግዳ እና ከሌሎች አመራሮች ሽልማቶች ተቀብለዋል ። Federal Law and Justice Institute የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት @MTULSU

9ኛው አገር አቀፍ የምስለ ችሎት ውድድር በባህር ዳር ዩንቨርሲቲ አሸናፊነት ተጠናቀቀ
+8
9ኛው አገር አቀፍ የምስለ ችሎት ውድድር በባህር ዳር ዩንቨርሲቲ አሸናፊነት ተጠናቀቀ

ለመላው የዩኒቨርሲቲያችን ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ደስ ያላችሁ።።። የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ህግ ትምህርት ቤት ከፌደራል ፍትህ እና ህግ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ከአርብ ግንቦት 8 ቀን 2017 ጀ
+2
ለመላው የዩኒቨርሲቲያችን ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ደስ ያላችሁ።።።  የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ህግ ትምህርት ቤት ከፌደራል ፍትህ እና ህግ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር  ከአርብ  ግንቦት 8 ቀን 2017 ጀምሮ እስከ ዛሬ  እሁድ ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ ሲካሄድ የቆየው 9ኛው ዙር ሀገር አቀፍ የህግ ትም/ት ቤቶች የምስለ ችሎት ውድድር ፍጻሜውን ያገኘ ሲሆን። በውድድሩ ላይ 12 ዪኒቨርሲቲይዎች ተሳትፈዋል የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲን በመወከል የተወዳደረው ቡድን 1.ፋሲል ዘለቀ 2.ፈቲያ ኑረድን እና 3.ወርቁ ማስሬ    2nd running up team (3ኛ ደረጃን በመያዝ የውድድሩ አሸናፊ ሁነዋል።) የሚዳሊያ እና ሰርተፍኬት ተሸላሚም ሁነዋል። ለመላው የዩኒቨርስቲያችን ማህበረሰብ ፣ለህግ ትምህርት ቤት ማህበረሰብ እንድሁም ለተወዳዳሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን።🥰🥰🥰 የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ህግ ተማሪዎች ህብረት 👇👇👇 @MTULSU

የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ህግ ትምህርት ቤት ከፌደራል ፍትህ እና ህግ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ከአርብ ግንቦት 8 ቀን 2017 ጀምሮ እስከ ዛሬ እሁድ ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም በሚዛን ቴፒ ዩ
+1
የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ህግ ትምህርት ቤት ከፌደራል ፍትህ እና ህግ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር  ከአርብ  ግንቦት 8 ቀን 2017 ጀምሮ እስከ ዛሬ  እሁድ ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ ሲካሄድ የቆየው 9ኛው ዙር ሀገር አቀፍ የህግ ትም/ት ቤቶች የምስለ ችሎት ውድድር ፍጻሜውን አግኝቶል ። በውድድሩ ላይ 12 ዪኒቨርሲቲይዎች የተሳተፉ ሲሆን።የውድድሩ የመጨረሻ ውጤትም የሚከተለው ነው። 👉National champion Team/የውድድሩ አሸናፊ ቡድን ባህርዳር ዩኒቨርስቲ ሁኖል 1.ቤተልሔም  ገበየሁ ጸጋነህ 2.ዮናስ ሙጨ ዳኘ 3.እዮብ  ይመች 👉Best Runner Up Team (2ኛ ደረጃን) የያዙት ሰላሌ ዩኒቨረሲቲ ናቸው 1.ሄርሜላ መስፍን 2 ሀዴሳ መረከቡ 3.አብዲ ረታ 👉Second runner up team(3ኛ ደረጃን የያዙት) ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ሰሆን 1.ፋሲል ዘለቀ ዘውደ 2.ወርቁ ማስሬ አበበ 3. ፈቲያ ኑረድን መሃመድ 👉Best Memorial Applicant   ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ 👉Best Memorial Respondet winner         ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ 👉Best orator of the preliminary round competition እዮብ  ይመች ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ 👉Best Femal orator of the preliminary round Competition ቤተልሔም  ገበየሁ ጸጋነህ ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ 👉Best orator of the final round competition competition እዮብ  ይመች ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ህግ  ተማሪዎች ህብረት 👇👇👇 @MTULSU

9ኛው ሀገራዊ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ህግ ተማሪዎች የምስለ ችሎት ( Moot Court) ውድድር ዛሬ በሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተጀመረ ። */** ሚቴዩ፣ ግንቦት 8/2017 ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲና
+9
9ኛው ሀገራዊ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ህግ ተማሪዎች የምስለ ችሎት ( Moot Court) ውድድር ዛሬ  በሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተጀመረ ። */** ሚቴዩ፣ ግንቦት 8/2017 ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲና የፌደራል የህግና ፍትህ ኢንስቲትዩት በመተባበር ያዘጋጁት 9ኛው ሀገራዊ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ህግ ተማሪዎች የምስለ ችሎት ( Moot Court) ውድድር  ዛሬ የተጀመረ ሲሆን እንግዶችን የዩኒቨርስቲው ከፍተኛ አመራሮች ዶ/ር ግርማ ጥላሁን የጥናትና ምርምር ማህበረሰብ ጉድኝት ም/ፕሬዚዳንትና የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ተወካይ ፣ዶ/ር ተረፈ ጌታቸው የአካዳሚክ ጉ/ምክትል ፕሬዝዳንት እንዲሁም ኢ/ር ይደግ ማሞ የአስተዳደር ልማት ም/ፕሬዚዳንት ተቀብለዋቸዋል ። ውድድሩ የፊታችን እሁድ ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም ፍጻሜውን የሚያገኝ ሲሆን  አሸናፊ የሚሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች እንዳስመዘገቡት ውጤት  የሰርተፍኬት ፤ የሜዳሊያና  የዋንጫ ተሸላሚዎች እንደሚሆኑም ታውቋል ። በዘንድሮው አገራዊ ምስለ ችሎት ውድድር ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ 12 ዩኒቨርሲቲዎች ማለትም አርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ ፣ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፣ ደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ ፣ድሬ ዳዋ ዩኒቨርሲቲ ሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ፣ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፣ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲና ወሎ ዩኒቨርሲቲ ይሳተፋሉ ። Mizan-Tepi University Light of the green Valley! 👇👇👇👇 @MTULSU

ለሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ  በሙሉ 9ኛውን ሀገር አቀፍ የህግ ትም/ት ቤቶች የምስለ ችሎት ውድድር የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ህግ ትምህርት ቤት ከፌደራል ፍትህ እና ህግ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር  ከአርብ  ግንቦት 8 ቀን 2017 እስከ እሁድ ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ የሚካሄድ መሆኑን ስንገልጽ በታላቅ ደስታ ነው። ይህ ታላቅ ዝግጅት በመላው ኢትዮጵያ ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ የህግ ተማሪዎችን በማሰባሰብ እያንዳንዳቸው ዪኒቨርሲቲያቸውን ወክለው የህግ እውቀታቸውን እና የክርክር ክህሎታቸውን የሚያሳዪበት ነው። እያንዳንዱ ዩኒቨርሲቲ በሦስት የሕግ ተማሪዎች የሚወከሉ ሲሆን። ዩኒቨርሲቲያችንም እንደ አዘጋጅ ዩኒቨርሲቲ ጎበዝ በሆኑ ሶስት የህግ ተማሪዎች ተወክሏል።የሀገር አቀፍ የምስለ ችሎት  ውድድር ማዘገጀት ለዩኒቨርሲቲያችን ትልቅ ስኬት ነው  ተማሪዎቻችን ካሸነፉልን ደግሞ ሌላ ታላቅ ድል እና ስኬት ነው።ስለዚህ ሁላችሁም የዩኒቨርስቲያችን ማህበረቦች እንድትመጡ እና   በውድድሩ ላይ  የወደፊት እጩ ድንቅ የህግ ባለሙያዎች የሚፈለሙበት የውድድር መድረክ ላይ እንድታደሙ እያልን። የውድድሩ አጠቃላይ መርሐግብር፡ ዓርብ ግንቦት 8 ቀን 2017፡ የመጀመሪያ ዙር ውድድር(preliminary Round) ቦታ: በአዲሱ ህንፃ (Complex Building) ውስጥ በሚገኙ ስድስት(6) በተመረጡ ክፍሎች ውስጥ ውድድሩ ይጀምራል። ሁሉም የዩኒቨርሲቲያችን ተማሪዎች(Remedial, Freshman, Seniors &Gc,)፣ መምህራን፣ የአስተዳደር ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ሁላችሁም ተገኝታችሁ ውድድሩን ይታደሙ የህግ እውቀተዎን ያስፉ ተወዳዳሪዎቻችንን ይደግፉ። ቅዳሜ፣ ግንቦት 9፣ 2017፡- የሩብ ፍፃሜ እና የግማሽ ፍፃሜ ውድድሮች በኮምፕሌክስ ህንጻ ውስጥ ባሉ ተመሳሳይ ክፍሎች ውስጥ ይካሄዳሉ። እሑድ ግንቦት 10 ቀን 2017፡ የመጨረሻው ዙር ውድድር  በዋናው ካምፓስ የመመረቂያ አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል። ከፍተኛ ቡድኖች ለሻምፒዮንሺፕ ሻምፒዮንነት የሚፋለሙበት የውድድሩ ፍጻሜም ይሆናል።የመዝጊያ ስነስርአቱም አሁድ በዚሁ በመመረቂያ አዳራሽ የሚካሄድ ይሆናል። የሚዛን ቴፒ ዩንቨርስቲ ለዚህ ትልቅ ውድድር  በሶስት  የህግ ተማሪዎች የሚወከል ይሆናል። የእርስዎ መገኘት እና ድጋፍ ቡድናችንን ውድድሩን እንድያሸንፍ ከማነሳሳት በተጨማሪ ስለ ህጋዊ ተግባራት እና የውድድር ተሟጋችነት ያለዎትን ግንዛቤ የሚያበለጽጉበት እንድሁም ልምድ የሚያገኙበት በመሆኑ በዚህ ሀገር አቀፍ የምስለ ችሎት ውድድር ላይ መሳተፍ ለሁሉም የዩኒቨርሲቲያችን ማህበረሰብ  ትልቅ እድል ነው። ሁሉም የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት - ተማሪዎች፣ መምህራን፣ የአስተዳደር ሰራተኞች እና ሰራተኞች በዚህ አስደናቂ ዝግጅት ላይ እንድትገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ዪኒቨርሲቲያችንን የወከሉ ተማሪዎቻችንን ለማበረታታት ኑ እንሰባሰብ እና ይህን ውድድር ታሪካዊ እና  የማይረሳ ተሞክሮ እናድርገው። ውድድሩ እንዳያመልጥዎት!  አርብ  ግንቦት 8 2017/ እስከ ግንቦት 10/2017 ዓ.ም የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ቤት © የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች ህብረት 👇👇👇 @MTULSU

Meeting for Moot Court Competition Bailiffs This is a reminder for those listed above to serve as bailiffs for the 9th Nation
Meeting for Moot Court Competition Bailiffs This is a reminder for those listed above to serve as bailiffs for the 9th National Moot Court Competition at Mizan Tepi University. We will have a meeting today at 8:00 AM in the Dean's office of the School of Law. SCHOO OF LAW!!

ማስታወቂያ ለሁሉም የግቢያችን ተማሪዎች በሙሉ ከዚህ በሗላ የሚቀሩ የ2017 አካዳማክ ካሌንደር ክንውኖች ። 1. ተመራቂ ያልሆኑ ተማሪዎች ማጠቃለያ ፈተና (final Exam) 18-26/09/2017ዓ.
+2
ማስታወቂያ ለሁሉም የግቢያችን ተማሪዎች በሙሉ ከዚህ በሗላ የሚቀሩ የ2017 አካዳማክ ካሌንደር  ክንውኖች ። 1. ተመራቂ ያልሆኑ ተማሪዎች ማጠቃለያ ፈተና (final Exam) 18-26/09/2017ዓ.ም 2.ተመራቂ ያልሆኑ ተማሪዎች ከግቢ የሚወጡበት 27-28/09/2017ዓ.ም 3. ሀገራዊ የሪሚድያል ፈተና የሚሰጥበት 24-30/09/2017ዓ,ም 4. የሪሚድያል ተማሪዎች ከግቢ የሚወጡበት 1-2/10/2017ዓ.ም 5. ሀገራዊ መውጫ ፈተና የሚሰጥበት 2-10/10/2017ዓ.ም 6.የ2017 የምረቃ ስነ-ስርዓት 14-15/10/2017ዓ.ም 7. ተመራቂ ተማሪዎች ከግቢ የሚወጡበት 16-17/10/2017ዓ.ም 8.የ12ተኛ ክፍል ተፈታኞች መግቢያ 22/10/2017ዓ.ም 9.የ12 ክፍል ፈተና የሚሰጥበት 25-30/10/2017ዓ.ም 👇👇👇👇 @MTULSU

Last Mock-Exam Schedule 2017 EC (2).xlsx0.12 KB

Call for Bailiff To all 4th and 5th Year LL. B Students of Mizan Tepi University It is with a great pleasure that the school of Law of Mizan Tepi University announces its desire to select qualified students from 4th and 5th year and assign them as bailiff (time keeper) on the 9th Ethiopian Law Schools Moot Court Competition to be held at Mizan Tepi University in collaboration with the Federal Law and Justice Institute from 08-10/08/2027 E.C. Thus, those students who fulfill the below specified criteria are cordially invited to apply in person to the School of Law within 4 days from the announcement of this call (till Friday) Eligibility: 👉4th or 5th year law students from accredited universities 👉Punctual, responsible, and committed to upholding courtroom discipline 👉Prior exposure to moot court activities or legal event coordination is a plus Roles and Responsibilities: 👉Maintain courtroom order and manage session timing 👉Support judges and teams during oral rounds 👉Ensure procedural compliance and efficient round transitions 👉Serve as the liaison between the bench and participants For more information, please contact Mrs. Rozina(school of law deen) ©School of law For more information Please join out community 👇👇👇 @MTULSU