Pharmacist Voice ETH
前往频道在 Telegram
Your trusted source for verified health news and the latest pharmacy insights from Ethiopia and around the globe. We cut through the noise to bring you professional, evidence-based information and expert discussions. Promotion Dm 👉 @onlyGodgrace
显示更多7 350
订阅者
-724 小时
+277 天
+25730 天
帖子存档
7 347
በጤና ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መካከል በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈርሟል።
@pvethiopia
7 347
የፓኪስታን ልዑክ ከኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን በመገኘት ውይይት አደረጉ።
ሐምሌ 2/2018- አዲስ አበባ — በኢትዮጵያ የፓኪስታን ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ክቡር አቲፍ ሸሪፍ ምያን የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን በመገኘት ከባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሔራን ገርባ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገዋል።በውይይቱ ወቅት የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር የኢትዮጵያ መንግሥት የአገር ውስጥ መድኃኒት አምራቾች አቅምና ቁጥር ለማሳደግ ልዩ ትኩረት መስጠቱን ገልጸዋል።
ዋና ዳይሬክተሯ አክለውም መንግስት ለመድኃኒት ምርት ትኩረት ሰጥቶ ያዘጋጀው የቂሊንጦ ኢንደስትሪ ፓርክ ለውጭና ለአገር ውስጥ ባለሀብቶች ምቹ እንደሆነ አብራርተዋል። ባለሥልጣኑ መድኃኒቶችን እንዴት እንደሚመዘግብ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን፣ የተመዘገቡ መድኃኒቶችን ዝርዝር ለማስፋትና ኩባንያዎች ምርቶቻቸውን እንዲያስመዘግቡ የሚያስችሉ ቀልጣፋ አሰራሮች መኖራቸውን አስረድተዋል።
በኢትዮጵያ የፓኪስታን አምባሳደር ክቡር አቲፍ ሸሪፍ ምያን በበኩላቸው የፓኪስታን የመድኃኒት አምራች ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በመድኃኒት ዘርፍ ለመሰማራትና መዋዕለ ነዋያቸውን ለማፍሰስ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል። አምባሳደሩ አክለውም፣ በቀጣይ የፓኪስታኑ የምግብና የመድኃኒት ተቆጣጣሪ አካል ከኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ ስምምነት በመፈራረም አብሮ ለመሥራት ፍላጎት እንዳለው አምባሳደሩ አስረድተዋል።
በዚሁ የምክክር መድረክ ላይ በኢትዮጵያ የፓኪስታን ኤምባሲ የንግድና መዋዕለ ነዋይ ኃላፊ ባሲት ሰሊም ሻህ ተገኝተዋል።
7 347
👉 ጤና ምንስቴር በሚቀጥለው ሐምሌ ወር መጨረሻ ለሚሰጠው PHARMACY COC Exam Special tutorial እየሰጠን እንገኛለን።
👉 አሁኑኑ inbox ያድርጉና ይቀላቀሉን በቀላሉ ለፈተናው ይዘጋጁ👇👇👇👇
@TEMU24TSE
GRACE PHARMA Together We Can!
7 347
* የሀገር ውስጥ መድኃኒት ማምረት አቅም ወደ 45 ፐርሰንት ማሳደግ ተችሏል
* የዓለም የመድኃኒት ቁጥጥር ኤጀንሲ ኢትዮጵያን ማቹሪቲ ሌቭል ሦስት ብሏታል
ጠቅላይ ሚኒስቴር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
#Ethiopia | የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ፣ መንግሥት ለጤናው ዘርፍ በሰጠው ልዩ ትኩረት በሕክምና መሣሪያዎችና በመድኃኒት አቅርቦት ላይ ከፍተኛ መሻሻል መመዝገቡን ገልጸዋል።
እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጻ፣ መንግሥት በበጀት ዓመቱ ለመድኃኒት ግዢ ብቻ 70 ቢሊየን ብር ወጪ ያደረገ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም 4 ፐርሰንት ብቻ የነበረውን የሀገር ውስጥ መድኃኒት ማምረት አቅም ወደ 44 እና 45 ፐርሰንት ማሳደግ ተችሏል።
ይህም በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ጥቅም ላይ ከሚውሉት መድኃኒቶች መካከል ግማሽ ያህሉ እዚሁ በሀገር ውስጥ እንዲመረቱ በማድረግ ረገድ ትልቅ እመርታ መሆኑን አብራርተዋል።
በዘርፉ የተጀመሩ ሰፋፊ ሥራዎችን ለማጠናከርም የአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩትን ጨምሮ የተለያዩ የፋርማሲውቲካል ተቋማት የክትባት ምርትን ለመቆጣጠርና የመደገፍ አቅምን ለመፍጠር የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወኑ ይገኛሉ።
ከመድኃኒት አቅርቦት ባሻገር፣ ለሕክምና መሣሪያዎች ግዢ ከ60 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ መደረጉን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በርካታ ዘመናዊ መሣሪያዎች ወደ ሀገር ውስጥ እየገቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ ካላት ሰፊ የሕዝብ ቁጥር አንጻር የሁለትና የሦስት ሆስፒታሎችን አቅም በማሳደግ ብቻ ፍላጎትን ማሟላት እንደማይቻል ገልጸው፣ በአዲስ አበባ ባለፉት ጥቂት ወራት በርካታ የሕክምና ተቋማት መመረቃቸውንና በሚቀጥሉት ጥቂት ወራትም ሌሎች ተጫማሪ ተቋማት ለአገልግሎት ዝግጁ እንደሚሆኑ አስታውቀዋል።
ለአብነትም የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታልን በመጥቀስ፣ ተቋሙ ተጨማሪ የ1,000 አልጋዎች የመያዝ አቅም እንዲኖረው ተደርጎ በከፍተኛ ደረጃ መገንባቱን ገልጸዋል። ይሁን እንጂ አሁንም ያለው ፍላጎትና የተከማቸው የሕክምና ዕዳ ሰፊ በመሆኑ፣ በቀጣይነት ጠንካራና ተከታታይነት ያላቸው ሥራዎች እንደሚጠብቁ አስገንዝበዋል።
በፋርማሲውቲካል ዘርፍና በሆስፒታሎች ግንባታ እንዲሁም በቁጥጥር ሥርዓቱ ላይ በተከናወኑት ስኬታማ ሥራዎች ምክንያት፣ የዓለም የመድኃኒት ቁጥጥር ኤጀንሲ ኢትዮጵያን የብቃት ደረጃ ሦስት (Maturation Level 3) በሚል ዕውቅና መስጠቱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ይህ ደረጃ ጥቂት የአፍሪካ ሀገራት ብቻ የደረሱበት ሲሆን፣ ቀጣዩና ትልቁ ግብ ደረጃ አራትን ማሳካት ነው። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ የምታመርታቸው መድኃኒቶች ለዓለም አቀፍ የኤክስፖርት ገበያ ተቀባይነት እንዲኖራቸው ትልቅ በር የሚከፍት ነው።
በዘርፉ የታዩ ለውጦችና ዕድገቶች ተስፋ ሰጪ ቢሆኑም፣ ገና ብዙ የሚቀሩ ሥራዎች እንዳሉ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት በዓለም አቀፍ ደረጃ ሊወዳደሩ የሚችሉና እጅግ የጸዱ የሕክምና መስጫ ተቋማትን ለመገንባት በዕቅድ እየተሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።
በመጨረሻም የዜጎችን ጤና ከወረርሽኝ ለመጠበቅ የተከናወኑ የጤና ጥበቃ ሥራዎችን በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የወባ በሽታን ለመከላከል 14 ሚሊየን የሚጠጉ አጎበሮች በነጻ መሰራጨታቸውንና ወደ 3 ሚሊየን በሚጠጉ ቤቶች ላይ የፀረ-ወባ መርጨት ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪም በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በ58 ወረዳዎች የወባ መከላከያ ክትባት የመስጠት ሙከራ መጀመሩን ጠቁመዋል።
በጤና፣ በትምህርትና በአጠቃላይ በማኅበራዊ ዘርፍ የተጀመሩት ሥራዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚጠበቀውን ፍሬ እንዲያፈሩና ዘላቂ ውጤት እንዲያስመዘግቡ መንግሥት አበክሮ መስራቱን እንደሚቀጥልበት አስገንዝበዋል።
@pvethiopia
7 347
👉 ጤና ምንስቴር በሚቀጥለው ሐምሌ ወር መጨረሻ ለሚሰጠው PHARMACY COC Exam Special tutorial እየሰጠን እንገኛለን።
👉 አሁኑኑ inbox ያድርጉና ይቀላቀሉን በቀላሉ ለፈተናው ይዘጋጁ👇👇👇👇
@TEMU24TSE
GRACE PHARMA Together We Can!
7 347
የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተናን ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ለምትገኙ ተመዛኞች በሙሉ
____
የጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ለተመረቃችሁ ጤና ባለሙያዎች በነሀሴ ወር 2018 ዓ.ም የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና ለመስጠት በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡
ስለዚህም መረጃችሁን ወደ ሲስተም ያላስገባችሁ ነባር እና አዲስ ተመዛኞች ከሰኔ 30/2018 እስከ ሃምሌ 17/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ ይህንን https://hple.moh.gov.et/ ማስፈንጠሪያ/Link/ በመጫን የብሄራዊ መታወቂያ መለያ ቁጥር (National ID FAN 16 Digit) በማስገባት አስፈላጊ መረጃዎችን በማሟላት ለምዝገባ እንድትዘጋጁ እናሳስባለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
▪ ይህ መረጃን የማስተሳሰር ሂደት እንዳለቀ የፈተና ጣቢያ መረጣ ሂደት እንደሚቀጥል እናሳውቃለን፡፡
▪ በሰኔ 2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ተፈትናችሁ ያለፉችሁ ተመዛኞች የስም ዝርዝራችሁን በተማራችሁበት ተቋም አማካኝነት ወደ ሲስተም ማስጫን የሚጠበቅባችሁ መሆኑን እናሳስባለን።
ምንጭ፡- MoH
7 347
COC EXAM UPDATE !!!
በሰኔ 2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና የወስዳችሁ የጤና ሙያ ተመራቂዎችም የብቃት ምዘና ፈተናውን በሃምሌ ወር 2018 ዓ.ም መጨረሻ ለመስጠት በቅርብ ቀን ምዝገባ ስለምንጀምር ተመዛኞች አስፈላጊውን የትምህርት ማስረጃ እንድታሟሉ እና ለምዝገባ ራሳችሁን ዝግጁ እንድታደርጉ እናሳስባለን።
7 347
#COC Cutpoint #2018E.C
✅Pharmacy 43.7
✅Anesthesia 47.8
✅Public Health 42.8
✅Nursing 42.2
✅Laboratory 48.4
✅Midwifery 42.6
7 347
የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና ለወሰዳችሁ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ::
በሰኔ 2018 ዓ.ም የተሰጠውን የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና የወሰዳችሁ ተመዛኞች ከነገ ሰኔ 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ https://hple.moh.gov.et ላይ በመግባትና የብሔራዊ መለያ ቁጥር (FAN) እና Password በማስገባት የፈተና ውጤታችሁን መመልከት የምትችሉ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል።
በውጤታችሁ ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተመዛኞች ውጤት ከነገ ሰኔ 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት በአጭር ጥሪ ቁጥር 952 በሥራ ሰዓት በመደወል ሙሉ ስም፣ ዲፓርትመንት እና የተማራችሁበትን የትምህርት ተቋም ስም በማሳወቅ ጥያቄዎቻችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል።
የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተናውን ያለፋችሁ ተመዛኞች ከሰኞ ሐምሌ 06/2018 ዓ.ም ጀምሮ ስም ዝርዝራችሁ ወደ ክልል የሚላክ ስለሆነ፣ የሙያ ፍቃዳችሁን የ12ኛ ክፍል በተማራችሁበት ክልል ማውጣት ትችላላችሁ ተብሏል።
7 347
+2
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን የመድኃኒት እና የሕክምና መሣሪያዎች የላብራቶሪ ምርመራ ሥራዎቹን ይፋ አደረገ
********
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ እና በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶች እንዲሁም የሕክምና መሣሪያዎች ጥራት እና ደኅንነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የላብራቶሪ ምርመራ ሥራዎቹን ይፋ አድርጓል።
ባለሥልጣኑ በጉዳዩ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር እና የመስክ ምልከታ መርሐ ግብር ማዘጋጀቱንም አስታውቋል።
የሕብረተሰቡን ጤና በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅ የሕክምና ግብዓቶች ጥራት እና ፈዋሽነት ቀዳሚው ተግባር መሆኑን ባለሥልጣኑ ገልጿል፡፡
የተዘጋጀው መርሐ ግብር ጥራቱን ያልጠበቀ እና ሀሰተኛ መድኃኒት ወደ ሕብረተሰቡ እንዳይደርስ የሚያደርገውን የቁጥጥር ሥርዓት ይበልጥ ግልጽ ለማድረግ ያለመ እንደሆነ አስታውቋል።
ባለሥልጣኑ አሁን የጀመረው ይፋዊ የምክክር እና የመስክ ምልከታ መርሐ ግብር የቁጥጥር ሥርዓቱን ዘመናዊነት የሚያሳይ ነው።
ይህም በሀገራችን የጤናው ዘርፍ ላይ የሚታየውን የአቅርቦት ጥራት ችግር ለመቅረፍና በሕክምና መሣሪያዎች ላይ ያለውን ጥብቅ ቁጥጥር ይበልጥ እንደሚያጠናክረው ይጠበቃል።
በቶክ ሮች
7 347
+2
The 14th National and 1st International Antimicrobial Resistance (AMR) Day Commemorated in Debremarkos University
"The EPSA–Debre Markos Branch successfully organized an Antimicrobial Resistance (AMR) Awareness Seminar and Discussion Forum in a hybrid format (onsite & via Google Meet) to raise awareness about the growing threat of AMR, promote rational antimicrobial use, and highlight the vital role of pharmacy students in advancing public health. 🌍
The program opened with remarks from Mr. Abebaw, Head of the Pharmacy Department, followed by a presentation introducing the vision, structure, and objectives of EPSA. An insightful seminar on the pharmacological aspects of AMR was then delivered by Mr. Wubetu (pharmacologist)
The event was concluded with an engaging interactive discussion forum moderated by Mr. Abebaw and Mr. Wubetu, where both onsite and online participants shared valuable insights"
7 347
#COC_Examiner
COC ማለፊያ ነጥብ በየ አመቱ ወጥ አይደለም ይህም የሆነበት ምክንያት ማለፊያ ነጥቡ ሚወሰነው modified angoff method በመጠቀም ነው
modified angoff method ማለት በጤና ሚንስትር በተመረጡ subject experts ለያንዳንዱ ጥያቄ ከተማሪዎች ብዛት ስንቱን ይመልሳል ሚለውን ግምት በ% የሚያስቀምጡበት ነው
ለምሳሌ ሶስት የተመረጡ experts 100 የነርሲንግ ጥያቄን የወሰዱ ተማሪዎች ግምት ቢያስቀምጡ ለእያንዳንዱ ጥያቄ ከ100% ግምታቸውን ያስቀምጣሉ ለምሳሌ ለአንደኛው ጥያቄ ክብደት 85,80,80 በተከታታይ % በያስቀምጡ 85+80+80/3=0.816 የመጀመሪያው ጥያቄ ነጥብ ይሆናል
የመጨረሻው ውሳኔ ሁሉም ጥያቄዎች በተመሳሳይ መልኩ ከተሰሩ በኋላ አማካይ ተወስዶ ማለፊያ ነጥቡ ይወሰናል።
ለዚህ ማንም የአመቱን ማለፊያ ነጥብ አሁን ላይ በእርግጠኛነት ሊናገር አይችልም
source moh exam development administration group
7 347
ለብቃት ምዘና ፈተና ተመዛኞች በሙሉ
ጤና ሚኒስቴር ከሰኔ 17 እስከ 19/2018 ዓ.ም የሚሰጠውን የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና በ28 የፈተና ጣቢያዎች በጥሩ ሁኔታ እየተሠጠ ይገኛል፡፡
በዚህም መሠረት:-
1. የነገ 19/10/2018 ዓ.ም የፈተናው መርሃ-ግብር
- Pharmacy
- Anesthesia
- Dental Medicine
- Emergency and Critical Care Nursing
- Environmental Health
- Psychiatric Nursing
ሙያ ላይ የተመዘገባችሁ ተመዛኞች ምዘናው የጠዋቱ በ3 ሰዓት እንዲሁም የከሰዓቱ በ8 ሰዓት እንደሚጀመር አውቃችሁ ቀድማችሁ በፈተና ጣቢያ ተገኝታችሁ ምዘናውን እንድትወስዱ እያሳስባለን።
2. በተመሳሳይ መልኩ በሰኔ 2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና የወስዳችሁ የጤና ሙያ ተመራቂዎችም የብቃት ምዘና ፈተናውን በሃምሌ ወር 2018 ዓ.ም መጨረሻ ለመስጠት በቅርብ ቀን ምዝገባ ስለምንጀምር ተመዛኞች አስፈላጊውን የትምህርት ማስረጃ እንድታሟሉ እና ለምዝገባ ራሳችሁን ዝግጁ እንድታደርጉ እናሳስባለን። ( Exit Pass —-> Ready for COC )
@DODO_PHARMACY💊
