Mark Tech Info | Mark Technology Information
前往频道在 Telegram
Buy ads: https://telega.io/c/MarkTechInfo ለአስተያየት ፣ ጥቆማ ፣ ለማስታወቂያ እና ለጥያቄዎች በዚህ ያናግሩን። 👇👇👇👇👇👇👇👇 @MarkTechInfoBot
显示更多6 218
订阅者
-324 小时
-337 天
-31730 天
帖子存档
❗️በአሜሪካ አስተማሪዎች CHAT-GPT እየተጠቀሙ መሆኑ ተቃውሞ አስነሳ
በአሜሪካ ተማሪዎች የትምህርት ክፍያቸውን እንዲመለስላቸው እየጠየቁ ነው ምክንያቱም መምህራን ጽሑፎችን ለማዘጋጀትና ለመፈተሽ ቻትጂቲፒ እንደሚጠቀሙ ተደርሶበታል።
ይህ በተማሪዎች ዘንድ ተቃውሞ አስነስቷል፣ ተማሪዎች ለቻትጂፒቲማ አስተማሪ ሳያስፈልጋቸው በራሳቸው በነፃ መማር እንደሚችሉ ይናገራሉ።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
❗️የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለሚወሰዱ ተማሪዎች የሞዴል ፈተና እየተሠጠ መሆኑ ተገለጸ።
ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚወሰዱ ተማሪዎች ቅድመ ዝግጅት ሥራ እንዲሰሩ እና ተማሪዎች 'ምን ያህል ተዘጋጅተዋል?' የሚለውን ለማወቅ፤ በክልል እና በሀገር ደረጃ የሞዴል ፈተና እየተሠጠ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል።
በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ይልቃል ወንድሜነህ ለአሐዱ እንደተናገሩት፤ የሞዴል ፈተናው የሚሰጠው ተማሪዎች ከዋናው ፈተና በፊት የዝግጅት ደረጃቸውን እንዲገመግሙ ለመርዳት ነው።
"ፈተናው ተማሪዎች ጠንካራና ደካማ ጎናቸውን እንዲለዩ፣ ጊዜያቸውን በተሻለ ሁኔታ እንዲቆጣጠሩ እና ከፈተና ጋር የተያያዘ ጭንቀትን እንዲቀንስ ያስችላቸዋል" ሲሉም ተናግረዋል።
እንዲሁም ሊያጋጥሟቸው ስለሚችሉት ጥያቄዎች አወቃቀር እና አስቸጋሪነት እራሳቸውን እንዲያውቁ ጠቃሚ ዕድል ይሰጣቸዋል።
ሞዴል ፈተናው በክልልም ሆነ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጥ ሲሆን፤ ይህም ተማሪዋቹ ምን ያህል ብቁ ናቸው የሚለውን ትክክለኛ ግምገማ እያስገኘ ነው ተብሏል።
እንዲህ ያለው ሁሉን አቀፍ የዝግጅት ስልት በሀገር አቀፍ ፈተና የተማሪዎችን አጠቃላይ ውጤት ለማሻሻል ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
የ2017 ትምህርት ዘመን የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ከሰኔ 23 ጀምሮ እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ፤ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል።
አገልግሎቱ በወረቀት የሚፈተኑ እና በበይነ መረብ የሚፈተኑ ተፈታኞች እንደሚያካትት ተገልጿል።
የፈተናው ይዘት በተማሪው መጽሐፍ ላይ ያተኮረ በመሆኑ፤ እያንዳንዱ ተፈታኝ በትምህርት ቤቱ የተማረበትን የተማሪ መጽሐፍ መሠረት አድርጎ ሊዘጋጅ እንደሚገባ አስተላልፏል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
❗️በናይጄሪያ በተሰጠ ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና 80 በመቶ ያህል ተማሪዎች መውደቃቸው አነጋጋሪ ሆኗል።
ፈተናውን የሚያዘጋጀው አካል ችግሩ በቴክኒክ ብልሽት ምክንያት የተፈጠረ እንደሆነ ቢያስታውቅም ተማሪዎች ግን በፈተናው ወቅት ኮምፒዩተሮች ወደ ፈተናው ስርዓት ለመግባት መቸገራቸው፣ ጥያቄዎቹ በኮምፒዩተሮቹ መስኮት ላይ ለመታየት በጣም መዘግየታቸውና የኃይል መቆራረጥ ዋነኞቹ ምክንያቶች ናቸው ብለዋል፡፡
የፈተናው ውጤት ይፋ ከሆነ በኋላ አንዲት የ19 ዓመት ተማሪ ሕይወቷን ማጥፋቷ በመላው ሀገሪቱ ሰፊ ተቃውሞ እንዲነሳ አድርጓል፡፡
ለሁለተኛ ጊዜ ፈተናውን የወሰደችው ተማሪዋ ባለፈው ዓመት ከማለፊያው በ7 ነጥብ ብቻ ዝቅ ብላ የነበረ ቢሆንም በዚህኛው ዓመት እጅግ ዝቅ ያለ ውጤት ማምጣቷ ነው የተገለጸው፡፡
ለፈተና ከቀረቡት 1.9 ሚሊየን ተማሪዎች አራት መቶ ሺ ብቻ ማለፊያ ውጤት ያመጡ ሲሆን በቅርብ ዓመታት ከታዩ አስከፊ ውጤቶች አንዱ ነው ተብሏል፡፡ አብዛኞቹ ተማሪዎች ጥቂት የማይባሉ ጥያቄዎችን ኮምፒዩተሩ ስለማያሳይ በመረበሻቸው ውጤታቸው መበላሸቱን ገልጸዋል፡፡
የፈተናው አዘጋጅ አካል ኃላፊ በሀገሪቱ ከነበሩት የፈተና ማዕከላት በ157ቱ የተፈተኑ 380 ሺህ ተማሪዎች ከነገ ጀምሮ ፈተናውን እንደ አዲስ መውሰድ እንደሚችሉ በሀገሪቱ ቴሌቪዥን ቀርበው ሕዝቡን እያነቡ ይቅርታ በጠየቁበት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል ያለው የቢቢሲ ዘገባ ነው፡፡
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
+5
❗️ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና ውጤትን ከዓምናው የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ዘርፈ ብዙ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ ።
የሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ በዛሬዉ እለት በክልሉ ዘንድሮ የ12ተኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና አስፈታኝ ከሆኑ የግልና የመንግስት ትምህርት ቤቶች ከኦንላይን ፈተና አሰጣጥን አስመልክቶ ስልጠና ሰጠ ።
በስልጠናው መድረኩ ተገኝተው መክፈቻ ንግግር ያደረጉ የሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ጌቱ ነገዎ እንደተናገሩት ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎችን ለማብቃት በኦንላይን ለመፈተን ብቁ እንዲሆኑ ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናቀቅ ይገባል ።
ሃላፊው አክለውም ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና ውጤትን ከዓምናው በተለየ መልኩ ለማሻሻል የቀረውን የትምህርት ክፍለ ጊዜን በአግባቡ በመጠቀም ተማሪዎችን ቅዳሜን ጨምሮ በበይነ መረብ መፈተንን ልምምድ እንዲያደርጉ ከማድረግ አንፃር የበኩላቸውን እንዲወጡ ማድረግ ይጠበቃል ።
በመቀጠልም ዘንድሮ የሁለተኛ ክፍል ሀገራዊ ተፈታኝ ተማሪዎች በበይነ-መረብ ሲፈተኑ ምንም አይነት ችግር እንዳይፈጠር በጥንቃቄ ስራዎችን ለማከናወን በሁሉም የመንግስት እና የግል ትምህርት ቤቶች ርዕሰ መምህራን ጋር አሞላልን በተመለከተ አጭር ስልጠና መሰጠቱን ያመለከተችው የሙያ ፍቃድ እና ምዘና ዳይሬክቶሬት ወጣት ዙኽራ ሙኽታር ገልፃለች ።
በመጨረሻም ኦንላይን ፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ስልጠናውን የሰጠዉ የየኮምፒውተር (ICT) ዳይሬክቶሬት አቶ ፈርሃን አህመድ ነው ።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
❗️በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና አመርቂ ውጤት ለማስመዝገብ የሚያስችለንን ቅድመ ዝግጅት እያደረገን ነው ሲሉ ተፈታኝ ተማሪዎች ገለጹ።
የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሀምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።
በመላ ሀገሪቱም ከ600 ሺህ በላይ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተናውን በወረቀት እና በበይነ መረብ እንደሚወስዱ የወጣው ፕሮግራም ያሳያል።
ኢዜአ ለሀገር አቀፍ ፈተናው እየተደረጉ ያሉ ቅድመ ዝግጅቶችን አስመልክቶ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች እና የትምህርት ቤት ርዕሰ መምህራን አነጋግሯል።
በኮከበ ፅባህ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ አብርሃም ሠላምነህ በብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ጥሩ ውጤት በማስመዝገብ ወደ አዲስ የትምህርት ምዕራፍ ለመሻገር ሰፋ ያለ ዝግጅት እያደረኩ ነው ብሏል።
በተለይም ለፈተናው የሚረዱትን መጽሀፍት እንዲሁም በበይነ መረብ አማካኝነት አጋዥ የሆኑ ግብዓቶችን በማንበብ ላይ እንደሚገኝ ነው ያብራረው።
ሀገር አቀፍ ፈተናው ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የተማርናቸውን ርዕሰ ጉዳዮች የሚሸፍን በመሆኑ ይህን ታሳቢ ያደረገ የአጠናን ዘዴ በመጠቀም እየተዘጋጀሁ እገኛለሁ ያለችው ደግሞ በዚሁ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪ የሆነችው ዳናት ባህሩ ናት።
በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ ሼርድ ካምፓስ የ12ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው አማኑኤል ታሪኩ በበኩሉ፥ ውጤታማ በመሆን ህልሙን እውን ለማድረግ በትምህርቱ ላይ ጠንክሮ እየሰራ መሆኑን ተናግሯል።
ይህንን ጥረት ከግብ ለማድረስም በቀጣይ ወር በሚሰጠው ሀገር አቀፍ ፈተና ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ ከዚህ ቀደም የተማራቸውን ትምህርቶች ወደ ኋላ መለስ ብሎ በመከለስ ላይ እንደሚገኝ ተናግሯል።
ሌላኛዋ የካምፓሱ ተማሪ ሰሎሜ ታደሰ በፈተናው ውጤታማ እንድንሆን መምህራኖቻችን ጥያቄዎችን እንድንሰራ በማድረግና በሌሎች በሚያስፈልጉን ነገሮች እየደገፉን ይገኛሉ ብላለች።
ፈተናው እየተቃረበ በመምጣቱ በእውቀትም በስነ-ልቦናም ብቁ ለመሆን ጥረቷን እንደምታጎለብት ገልፃለች።
ተማሪ አማኑኤል በበኩሉ፥ተፈታኞች ራሳቸውን በሚገባው ልክ በማዘጋጀትና በመፈተሽ ለላቀ ውጤት ዝግጁ መሆን አለባቸው ሲል ጥሪውን አቅርቧል።
የኮከበ ፅባህ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ደለለኝ አስማረ በበኩላቸው፥ ትምህርት ቤቱ በዘንድሮ ዓመት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና 632 የቀን 63 የማታ ተማሪዎችን ያስፈትናል ብለዋል።
ትምህርት ቤቱም ተፈታኝ ተማሪዎች ለፈተናው በሚፈለገው ደረጃ እንዲዘጋጁ ለማድረግ የማጠናከሪያ ትምህርት እንዲወስዱ እና ተፈታኞች በግቢው እያደሩ ማጥናት የሚችሉበት ሁኔታ ማመቻቸቱን ተናግረዋል።
ተፈታኝ ተማሪዎቹ በወረቀት እና በበይነ መረብ የሚፈተኑ መሆናቸውን በማንሳት በተለይም በበይነ መረብ ለሚፈተኑ የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች በኮምፕዩተር ልምምድ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ ሼርድ ካምፓስ ምክትል ርዕሰ መምህር አብርሃም ድሪባ፥ ካምፓሱ በሀገር አቀፉ የ12ኛ ክፍል ፈተና 80 ተማሪዎችን እንደሚያስፈትን አስታውቀዋል።
ተማሪዎቹም ለረጅም ዓመታት በትምህርት ዓለም ያደረጉት ጉዞ ፍሬያማ እንዲሆን የተለያዩ ሞዴል ፈተናዎችን እየወሰዱ እንደሚገኙ አንስተው፥ ይህም እስከ ፈተናው መዳረሻ ይቀጥላል ነው ያሉት።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
+3
❗️የትግራይ ብሔራዊ ክልል በ2017 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል በበይነ መረብ የሚፈተኑ ተማሪዎች ልምምድ ሲያደርጉ - አዲግራት ዩኒቨርሲቲ
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
❗️የ2017 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ፈተናን በወረቀት ለሚፈተኑ ተፈታኞች
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ከቀድሞው የተሻሻለ የመልስ መስጫ ወረቀት ለተፈታኞች ምቹ በሆነ ዲዛይን በአዲስ መልክ አዘጋጅቷል፡፡ ስለሆነም ተፈታኞች ማድረግ ስለሚገባቸው ጉዳዮች ማስገንዘብ በማስፈለጉ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን ከ608 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለመውሰድ መመዝገባቸው ተገለጸ!
በ2017 የትምህርት ዘመን ከ608 ሺህ በላይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ መመዝገባቸውን የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አስታወቀ፡፡የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ለኢፕድ እንዳስታወቁት፤ መልቀቂያ ፈተና የፈተና ስርቆትና ኩረጃ በሚቀንስ መልኩ በወረቀት እና በበየነ መረብ ይሰጣል።
በወረቀት የሚፈተኑት መሰረተ ልማት ያልተሟላባቸው፤ ኮምፒውተር እና ኢንተርኔት ኮኔክሽን በበቂ ባላገኙ አካባቢዎች የሚገኙ ተፈታኞች መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ዋና ዳይሬክተሩ፤ በበየነ መረብ የሚሰጠው ፈተና እየጨመረ በመሄድ ላይ መሆኑን ጠቁመው፤ ወደፊት ሙሉ በሙሉ ፈተናውን በበየነ መረብ ለመስጠት እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡
በአሁኑ ጊዜ የፈተና ዝግጅቱ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን በመግለጽ፤ ፈታኞችን የመመልመል፤ የተመለመሉት ወደዬመፈተኛ ጣቢያው እንዲሰማሩ የማድረግ ዝግጅት እየተካሄደ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡በአማራ ክልል ባለው ግጭት ሳቢያ በርካታ ት/ቤቶች የዘንደሮውን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና እንደማያስፈትኑ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ እየሩስ መንግሥቱ በቅርቡ ገልጸዋል።
በክልሉ በአጠቃላይ 685 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንደሚገኙ የገለጹት ኃላፊዋ ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት የዘንድሮውን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና የሚያስፈትኑ ትምህርት ቤቶች 470 ብቻ ናቸው ብለዋል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ምን ያህል ተማሪዎች ይወስዳሉ?
👉በአገር አቀፍ ደረጃ 608 ሺህ 588 ተማሪዎች የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለመውሰድ ተመዝግበዋል
🟢 የተፈጥሮ ሳይጓስ ———309,547
🔵 የማኅበራዊ ሳይንስ ——— 299,041
👉150 ሺህ ተማሪዎች በኦላይን (በይነ መረብ) ፈተናቸውን ይወስዳሉ
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
Enjoy our content? Advertise on this channel and reach a highly engaged audience! 👉🏻
It's easy with Telega.io. As the leading platform for native ads and integrations on Telegram, it provides user-friendly and efficient tools for quick and automated ad launches.
⚡️ Place your ad here in three simple steps:
1 Sign up
2 Top up the balance in a convenient way
3 Create your advertising post
If your ad aligns with our content, we’ll gladly publish it.
Start your promotion journey now!
Enjoy our content? Advertise on this channel and reach a highly engaged audience! 👉🏻
It's easy with Telega.io. As the leading platform for native ads and integrations on Telegram, it provides user-friendly and efficient tools for quick and automated ad launches.
⚡️ Place your ad here in three simple steps:
1 Sign up
2 Top up the balance in a convenient way
3 Create your advertising post
If your ad aligns with our content, we’ll gladly publish it.
Start your promotion journey now!
❗️በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና 608 ሺህ ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ/ም የሚሰጠው አገር አቀፍ ፈተና ላይ 608 ሺህ ተማሪዎች ይቀመጣሉ ተብሎ ነው የሚጠበቀው።
ፈተናው በወረቀት እና በበየነ መረብ ይሰጣል።
ፈተናውን በወረቀት የሚወስዱ ተማሪዎች እንደ ቀደሙት ዓመታት ሁሉ ሙሉ በሙሉ ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ገብተው ይወስዳሉ።
ፈተናውን በበይነ መረብ የሚወስዱት ደግሞ ፦
- በዩኒቨርሲቲዎች፣
- በመንግስት እና በግል ትምህርት ቤቶች፣
- በጤና እና መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆች
- በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ውስጥ ባሉ ኮምፒዩተሮች ይፈተናሉ። ተማሪዎቹ ግቢ ማደር ሳይጠበቅባቸው ከቤታቸው እየተመላለሱ ነው ፈተናውን የሚወስዱት።
በበይነ መረብ የሚሰጠው ፈተና በሁለት ዙር ሲሆን ይህም የሆነው በበይነ መረብ የመፈተን አቅምን እና የተፈታኝ ተማሪዎችን ቁጥር ለመጨመር እንዲሁም ያለውን የመሰረተ ልማት አቅም ለማሳደግ እንደሆነ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ለኤፍ ኤም ሲ በሰጠው ቃል አስረድቷል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
+1
‼️የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆኗል።
የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና መቼ ይሰጣል ?
✅ በወረቀት ፈተናቸውን የሚወስዱ ተፈታኞች ፦ ሰኔ 23 ፣ ሰኔ 24 እና ሰኔ 25/2017 ዓ/ም
✅ በበየነ መረብ (ኦንላይን) /ፈተናቸውን የሚወስዱ የ1ኛ ዙር ተፈታኞች ፦ ሰኔ 23 ፣ ሰኔ 24 እና ሰኔ 25/2017 ዓ/ም
✅ በበየነ መረብ (ኦንላይን) /ፈተናቸውን የሚወስዱ የ2ኛ ዙር ተፈታኞች ፦ ሰኔ 26 ፣ ሰኔ 27 እና ሰኔ 30/2017 ዓ/ም
የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና መቼ ይሰጣል ?
✅ በወረቀት ፈተናቸውን የሚወስዱ ተፈታኞች ፦ ሐምሌ 1 ፣ ሐምሌ 2 እና ሐምሌ 3/2017 ዓ/ም
✅ በበየነ መረብ (ኦንላይን) /ፈተናቸውን የሚወስዱ የ1ኛ ዙር ተፈታኞች ፦ ሐምሌ 1 ፣ ሐምሌ 2 እና ሐምሌ 3/2017 ዓ/ም
✅ በበየነ መረብ (ኦንላይን) /ፈተናቸውን የሚወስዱ የ2ኛ ዙር ተፈታኞች ፦ ሐምሌ 4 ፣ ሐምሌ 7 እና ሐምሌ 8/2017 ዓ/ም
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ይዘጋጁ!
የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈታና ተፈታኝ ተማሪ ከሆኑ ከታች የተቀመጠውን ሊንክ በመጫን ለፈተና በቂ ዝግጅት ለማድረግ የሚያስችሉ ትምህርቶችን ማግኘት ይችላሉ።
በትምህርት ሚኒሰቴር የተዘጋጁ የሁሉም ትምህርት አይነቶች የቲቶርያል ቪዲዮዎችን ለማግኘት 👇
https://examinfo.moe.gov.et/guides
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
" በአሰቃቂ ሁኔታ ነው ዶርም ውስጥ በጩቤ ተወጋግቶ የተገደለው " - ተማሪዎች
➡️ " ሕይወቱን ለማትረፍ ርብርብ ቢደረግም ሳይሳካ ቀርቷል። ጥቃት አድራሹ ተማሪ በቁጥጥር ስር ውሏል " - ዩኒቨርሲቲው
የአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ተማሪው ዶርም ውስጥ መገደሉን ተማሪዎች ገለጹ።
ዩኒቨርሲቲው ጥቃት አድራሹ ተማሪ እንደሆነና በቁጥጥር ስር እንደዋለ አሳውቋል።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የጫሞ ካምፓስ ተማሪዎች ፥ በጫሞ ካምፓስ ዛሬ ጠዋት ላይ ብሎክ 9 የወንዶች ዶርም ውስጥ አንድ ተማሪ በጩቤ ተወጋግቶ በአሰቃቂ ሁኔታ መገደሉን ገልጸዋል።
ተማሪዎቹ " እዚህ ካምፓስ ውስጥ መወጋት የተለመደ ከሆነ ሰነባብቷል " ያሉ ሲሆን ዩኒቨርስቲው በግቢ ውስጥ የሚፈጸሙ ተግባራትን ስሙን ለመጠበቅ ሲል መሸፋፈን ትቶ ለተማሪዎቹ ደህንነት ዋስትና እንዲሰጥ አሳስበዋል።
ተማሪዎች ባለው ነገር ስጋት ላይ እንደወደቁና መፍትሔ እንዲሰጣቸው ፤ ደህንነታቸውም በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲረጋገጥ ጠይቀዋል።
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ምን አለ ?
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተማሪው ግድያ አረጋግጦ የሀዘን መግለጫ ዛሬ ምሽት አውጥቷል።
ዩኒቨርሲቲው " የሥነ- ትምህርትና ሥነ-ባህርይ ሳይንስ ትምህርት ቤት የሳይኮሎጂ ትምህርት ክፍል የ2ኛ አመት ተማሪ የሆነው ናትናኤል ፀጉ አሰፋ ከጓደኛው ጋር በተፈጠረ የግል ፀብ በደረሰበት ጥቃት ዛሬ ጠዋት ሚያዚያ 28 ቀን 2017 ዓ/ም ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል " ብሏል።
" ሕይወቱን ለማትረፍ በአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ከፍተኛ ርብርብ ቢደረግም ሳይሳካ በመቅረቱ ማምሻውን 12:30 ላይ ሕይወቱ አልፋል " ሲል ገልጿል።
ጥቃቱም ያደረሰው ተማሪ በቁጥጥር ስር ውሎ አስፈላጊው ምርመራ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጾ የሕግ ሂደቱን በመከታተል ውሳኔውን ተከታትሎ በአጭር ጊዜ ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ቃል ገብቷል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️ዶርም ውስጥ በጩቤ...
ዛሬ ጠዋት በአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ጫሞ ካምፓስ አንድ የሁለተኛ ዓመት ተማሪ ዶርም ውስጥ እጅግ ሰቅጣጭ በሆነ መልኩ በጩቤ ተወግቶ ህይወቱ ማለፉን ከዩንቨርሲቲው ተማሪዎች ሰምተናል።
የግቢው ተማሪዎች ካምፓሱ ላይ ተማሪ ሲወጋ ይህ የመጀመሪያው አለመሆኑንና መወጋጋትም የተለመደ እየሆነ ነው ዩንቨርሲቲውም የተማሪዎቹን ደህንነት ለመጠበቅ ጠንካራ ስራ እየሰራ አይደለም ሲሉ ስጋታቸውን አጋርተውናል።
ከደቂቃዎች በፊት የአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ የሚከተለውን የሃዘን መግለጫ አውጥቷል👇
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥነ- ትምህርትና ሥነ-ባህርይ ሳይንስ ትምህርት ቤት የሳይኮሎጂ ትምህርት ክፍል የ2ኛ አመት ተማሪ የሆነው ናትናኤል ፀጉ አሰፋ ከጓኛው ጋር በተፈጠረ የግል ፀብ በደረሰበት ጥቃት ዛሬ ጠዋት ሚያዚያ 28 ቀን 2017 ዓ/ም ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል:: በመሆኑም ሕይወቱን ለማትረፍ በአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ከፍተኛ ርብርብ ቢደረግም ሳይሳካ በመቅረቱ ማምሻውን 12:30 ላይ ሕይወቱ አልፏል።
አደጋውን ያደረሰው ተማሪ በቁጥጥር ስር ውሎ አስፈላጊው ምርመራ እየተደረገ የሚገኝ ሲሆን ዩኒቨርሲቲው የሕግ ሂደቱን በመከታተል ውሳኔውን ተከታትሎ በአጭር ጊዜ ለሕዝብ ይፋ ያደርጋል::
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተማሪ ናትናኤል ከዚህ አለም በሞት መለየት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰቡ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም ለመላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ሁሉ መፅናናትን ይመኛል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
DV 2026 ውጤት ይፋ ሆነ‼️
መልካም እድል ለውድ ኢትዮጵያውያን!
በፈረንጆቹ 2026 ወደ አሜሪካ ለመሄድ እድላቸውን ለመሞከር ባለፈው ዓመት (October 2 to November 7, 2024) ለDV ሎተሪ የተመዘገባችሁ ውድ ኢትዮጵያውያን በሙሉ፣ ዛሬ የአሜሪካ መንግስት በይፋ የDV 2026 እድለኞችን ዝርዝር ይፋ አድርጓል!
ውጤቱን ለመመልከት ምንም አይነት ክፍያ አይጠየቅም። የአሜሪካ መንግስት ይፋዊ ድረ-ገጽ ላይ በመግባት በቀጥታ ማረጋገጥ ትችላላችሁ።
ይህ ነው ይፋዊው ድረ ገጽ፡ https://dvprogram.state.gov/ESC/
ይህንን ሊንክ በመጠቀም እድላችሁን ገብታችሁ ተመልከቱ!
ውጤቱ የወጣላችሁ እድለኞች እስከሚቀጥለው ዓመት መስከረም ወር ድረስ አስፈላጊውን የኢሚግሬሽን ሂደቶች አጠናቃችሁ ወደ አሜሪካ መግባት ይኖርባችኋል። አለበለዚያ ያገኛችሁት እድል ይሰረዛል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
"ልጄ የተገረፈችው በኤሌክትሪክ ገመድ ነው"
እግረኛው የተሰኘ ሚድያ ሰሞኑን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚገኝ አንድ ትምህርት ቤት የቤት ስራ አልሰራሽም በሚል በጭካኔ የተገረፈችው የሁለተኛ ክፍል ተማሪ እናት ጋር ቆይታ አድርጎ ነበር። ሚድያው በህፃኗ ተማሪ ላይ ስለደረሰው ግርፋት እና ጉዳዩ አሁን ስላለበት ሁኔታ ጠይቋታል።
የተማሪዋ እናት ስለ ተፈጠረው ክስተት እንዲህ ብላለች 👇
"ልጄ የተገረፈችው በኤሌክትሪክ ገመድ ነው። በ50-60 ተማሪዎች ፊት በአራት ተማሪ አስይዛ ነው የገረፈቻት። ልጄን ማሳድገው ብዙ መከራ ስቃይ አይቼ ነው። ልጄ በጣም ተጎድታብኛለች። ከፍቶኛል። አሁን እያሳከምኳት ነው። መምህርቷም በህግ ጥላ ስር ውላ የፍርድ ሂደት ላይ ነን። ማክሰኞ የፍርድ ቤት ቀጠሮ አለን።"
👉 ሚድያውም በተጨማሪም ስለ ቤተሰቡ የኑሮ ሁኔታም ጠይቋት ነበር ...
"ሁለት ልጆች አሉኝ። ሶስት ሺህ ብር ቤት ተከራይቼ ነው የምኖረው። አንድ ጀሪካን ውሃ በ5ብር ገዝቼ 20ብር በመሸጥ ነው ህይወትን የምገፋው። በቀን ውስጥ ሁለትም፣ ሶስትም፣ አራትም ጀሪካን ውሃ ልሸጥ እችላለሁ አንዳንድ ቀን ውሃ ወረፋ ላላገኝም እችላለሁ።ውሃውን የማመጣው ንጋት 11 ሰዓት ከቤት ወጥቼ ራቅ ያለ አካባቢ በመሄድ እስከ 4 ሰዓት ወረፋ ጠብቄ ነው።"
"ባለቤቴ ወዛደር ነው። በቀን 50ብር ...ያገኘውን ያህል ይሰራል። አንዳንዴ ባዶ እጁንም ሊመጣ ይችላል።"
👉ሚድያው በመጨረሻም መምህርቷ ምን ማለት ትፈልጊያለሽ የሚል ጥያቄ ቀርቦለት ነበር...
"ምንም ልላት አልችልም። ብቻ ግን በዚህ ልክ ያስጨከናት ከኔ ጋር ያለ የግል ጉዳይ ይኖራት እንደሆን ማወቅ ነው ምፈልገው ብላለች።"
📌 የተማሪ ሀያት አህመድ እናት ወላጆች ልጆቻችሁን ተከታተሉ! ስትል የመጨረሻ መልዕክቷን አስተላልፋለች።
===================
በዚህ አጋጣሚ ይህችን እናት እና ቤተሰቡን መርዳት የምትፈልጉ ከላይ በተያያዘው አድራሻዋ በኩል ልታግዟት ትችላላችሁ 🙏
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
