Mark Tech Info | Mark Technology Information
前往频道在 Telegram
Buy ads: https://telega.io/c/MarkTechInfo ለአስተያየት ፣ ጥቆማ ፣ ለማስታወቂያ እና ለጥያቄዎች በዚህ ያናግሩን። 👇👇👇👇👇👇👇👇 @MarkTechInfoBot
显示更多6 218
订阅者
-324 小时
-407 天
-33730 天
帖子存档
ማስታወቂያ
ለትምህርት ማህበረሰቡና ለባለድርሻ አካላት በሙሉ
በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፉ በተዘጋጁ ረቂቅ ደንብና መመሪያዎች ላይ አስተያየት እንድትሰጡ ስለመጠየቅ፤
1. በትምህርት ሚኒስቴር የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የራስ-ገዝነት የሽግግር መመሪያ https://forms.gle/KiRAQn6kjsZ6yymt6
2. የራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ የመንግስት ጥቅል የበጀት ድጋፍ ለመደንገግ የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ https://forms.gle/YEsQJwjE3wYUypJz6
3. በትምህርት ሚኒስቴር ለመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራር አሰያየምን ለመደንገግ የወጣ መመሪያ
https://forms.gle/HLqZm83W2ANMWMLt5
ይመዝገቡ!
የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና ምዝገባ ማክሰኞ መጋቢት 15/2018 ዓ.ም ከቀኑ 11:30 ይጠናቀቃል፡፡
በድጋሜ በግላችሁ የምትፈተኑ ተፈታኞች https://register.eaes.et ላይ በመግባት መመዝገብ ይኖርባችኋል።
ተፈታኞች በተሰጠው የጊዜ ገድብ ውስጥ እንዲመዘገቡ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳስቧል።
https://t.me/Grade12results
የኢድ እንግዳ
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር #INSA ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ፤ የ2018 ዓ/ም የኢድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡
ክብርት ዋና ዳይሬክተሯ በቆይታቸው የሥራና የአመራር ሕወታቸውን፤ አጠቃላይ ከሕይወት ጉዟቸው ጋር በማዋዛት ጥሩ ቆይታ አድርገዋል፡፡
ክብርት ዋና ዳይሬክተሯ ያደረጉትን ቆይታ የኢድ አልፈጥር ዕለት ዓርብ መጋቢት 11/2018 ዓ/ም በኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ከቀኑ 5:00 ላይ እንዲከታተሉ እንጋብዛለን፡፡
https://www.facebook.com/share/p/16ym2hr6Km/
የረመዳን ወር ከዒባዳው ጎን ለጎን በርካታ የማይረሱና አዝናኝ ገጠመኞች
የሚስተናገዱበት ወቅት ነው። በተለይ በቤተሰብ እና በጓደኛ መሃል የሚፈጠሩ አንዳንድ ኩነቶች ሁልጊዜም ፈገግ ያሰኛሉ። ከአነዚህም መካከል ጥቂቶቹ እነሆ፦
1. "የእንቅልፍ ልብ" የሱሁር ግብዣ
አንድ ሰው ሱሁር ለመብላት ተነስቶ ገበታ ላይ ቁጭ ይላል። ነገር ግን እንቅልፍ ገና ስላልለቀቀው፣ ማንኪያውን ይዞ አይኑን እንደጨፈነ "ቢስሚላህ" ብሎ መብላት ይጀምራል። ትንሽ ቆይቶ ሲነቃ ግን እየበላ ያለው ባዶ ሰሃን መሆኑን ወይም ጉርሻው አፉ ጋር ሳይሆን አፍንጫው ጋር መድረሱን ሲያይ በራሱ መሳቁ አይቀርም።
2. "ፈጣኑ" ሰዓት አቆጣጠር
አንዳንዴ ለኢፍጣር ጥቂት ደቂቃዎች ሲቀሩ ረሃቡና ጥማቱ ይበረታል። በዚህ ሰዓት በየደቂቃው ሰዓት ማየት የተለመደ ነው። "አምስት ደቂቃ ቀረው" ተብሎ ታይቶ፣ ረጅም ሰዓት ያለፈ መስሎን በድጋሚ ስናይ ግን ያለፈው አንድ ደቂቃ ብቻ መሆኑን ስንረዳ የሚፈጠረው የ"ትዕግስት መፈተን" ስሜት አስቂኝ ነው።
3. የህፃናት "የቆላ ጾም"
ህፃናት ለመጾም ያላቸው ጉጉት በጣም ደስ ይላል። ጠዋት ላይ "እኔም እጾማለሁ" ብለው ይጀምሩና ቀትር ላይ ሲርባቸው "እኔ የቆላ ጾም ነው የምጾመው (ምሳ በልቼ የምቀጥለው)" ይላሉ። ማታ ኢፍጣር ላይ ግን ከሁሉም ቀድመው ገበታው ላይ ተገኝተው "ጾሜን ፈታሁ" ሲሉ ማየቱ በጣም ያዝናናል።
መልካም በዓል!
🌙🌙🌙እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የደስታ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ። መልካም በዓል!"☪️💡💡
ለትምህርት ቤቶችን አዲሱ ደንብ‼️
ህግ የጣሰ የግል የትምህርት ተቋም የገቢውን 35 በመቶ ለመንግስት እንዲያስረክብ የሚገደድበት ደንብ ወጣ ‼️
በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የግል ትምህርት ተቋማት በመንግስት ያልተገመገሙ መጻሕፍትን ሲጠቀሙ ወይም ሲሸጡ ከተገኙ፣ ከአጠቃላይ ወርሃዊ ገቢያቸው ላይ 35 በመቶ የሚሆነውን ለመንግስት ገቢ እንዲያደርጉ የሚያስገድድ አዲስ ደንብ መዘጋጀቱን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።
ይህ "ለአንድ ጊዜ ብቻ" ተግባራዊ የሚደረግ የገንዘብ ቅጣት፣ በትምህርት ጥራት ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በህግ ለማስተካከልና ተጠያቂነትን ለማስፈን የታለመ መሆኑ ተገልጿል።
ረቡዕ መጋቢት 9 ቀን 2018 ዓ.ም ለባለድርሻ አካላት ውይይት የቀረበው ይህ ደንብ፣ በተለይ ጥብቅ የሆኑ የቁጥጥር ድንጋጌዎችን ይዟል።
ከመጽሐፍ አጠቃቀም ባለፈ፣ የትምህርት ተቋማቱ ከከተማዋ ትምህርት ቢሮ አሰራር ውጪ "የማጠናከሪያ ትምህርት" (Tutorial) ሲሰጡ ከተገኙም ተመሳሳይ የ35 በመቶ የገቢ ቅጣት ይጠብቃቸዋል።
ደንቡ "የማጠናከሪያ ትምህርት" የሚለው በክረምት ወይም ከትምህርት ሰዓት ውጪ የሚሰጡ ስልጠናዎችን ሲሆን፣ እነዚህም በተማሪዎችና በወላጆች ፈቃደኝነት ላይ ያልተመሰረቱ ከሆኑ ተቋማቱን ለከፍተኛ ቅጣት ይዳርጋቸዋል።
ይህም ትምህርት ቤቶች ካልተገባ የትርፍ ፍለጋ ሩጫ እንዲታቀቡ ለማድረግ ታስቦ የተቀረጸ መመሪያ ነው።
ሌላው ከፍተኛ ቅጣት የሚያስከትለው ጥፋት፣ ትምህርት ቤቶች ከእውቅና ፈቃዳቸው በላይ "የተማሪ ቁጥር" አጭቀው ሲገኙ ነው።
አግባብ ካለው አካል ከተሰጠው ደረጃና እርከን ውጪ ተማሪ ይዞ የሚገኝ ማንኛውም የትምህርትና ስልጠና ተቋም፣ የገቢውን 35 በመቶ ቅጣት እንዲከፍል ይገደዳል።
በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የሚገኙ ተቋማት ደግሞ የሰልጣኞችን መረጃ በጥራትና በጊዜው ካላስገቡ፣ ከወርሃዊ ገቢያቸው 20 በመቶውን ለመንግስት እንዲያስረክቡ ደንቡ ያዝዛል።
ይህ አዲሱ ደንብና አብሮት የቀረበው መመሪያ፣ ተቋማቱ የተገኘባቸውን ጥፋት እንዲያስተካክሉ እስከ ሁለት ሳምንት የሚቆይ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እንደሚሰጥ ይደነግጋል።
በዚህ የጊዜ ገደብ ውስጥ ማስተካከያ ያላደረጉ፣ በተደጋጋሚ ጥፋት የሚፈጽሙ ወይም የሚሰጣቸውን ግብረ-መልስ የማይቀበሉ ትምህርት ቤቶች፣ እስከ "ዕውቅና ፈቃድ መሰረዝ" የሚደርስ ጠንካራ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው ኢትዮጵያ ኢንሳይደር በዘገባው አመልክቷል።
እርምጃውን የመውሰድ ሙሉ ስልጣንም ለአዲስ አበባ ከተማ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ተሰጥቷል።
ይህ አዲስ መመሪያ በተለይ የግል ትምህርት ቤቶች ላይ ከፍተኛ ጫና ሊፈጥር እንደሚችል የሚገመት ሲሆን፣ የትምህርት ተቋማትና የሙያ ብቃት ምዘና ላይ የሚሳተፉ አካላት መብትና ግዴታንም በዝርዝር አካቷል።
ለአንድ ጊዜ ብቻ ተግባራዊ የሚደረገው ይህ የገቢ 35 በመቶ ቅጣት፣ ተቋማቱ ከትምህርት ጥራትና ከአሰራር ደንቦች ጋር ተስማምተው እንዲሰሩ ለማስገደድ የተቀመጠ ጠንካራ የቁጥጥር ስልት መሆኑን ዘገባው አመልክቷል።
https://t.me/Grade12results
guys the GIVEAWAY It hasn't stopped and don't stop to participate. still you guys have chance to win the 500 birr - 2000 birr so do your thing
let's go family
https://t.me/Grade12results
https://t.me/Grade12results
የዒድ አልፈጥር በዓል አርብ (ጁምዓ) ይውላል።
ዛሬ የሸዋል ወር ጨረቃ ባለመታየቷ 1447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል ከነገ ወዲያ አርብ (ጁምዓ) ተከብሮ ይውላል።
ዒድ ሙባረክ !
#Haramain
https://t.me/Grade12results
https://t.me/Grade12results
https://t.me/Grade12results
ከእናንተ የሚጠበቀዉ እዚህ ቻናል ላይ ዒድ አል-ፊጥር በዓልን በማስመልከት 50 ሰዉ እስከ 200 ሰዉ እዚህ ቻናል ላይ add ✅️ ላደረጉ እና channel joine ላስደረጉ ከ 500 ብር 💶 እስከ 2000 ብር💶 ይሸለሙ 🎉🎉🎉 ማን ያዉቃል አንቺ / አንተ ልትሆን ትችላላቹ 💪 የሞከረ ይሸለማል 😉 እንዳይረሳ ለመሸለም ከ 50 እስከ 200 ሰዉ add ማደረግ የግድ ነዉ
ያደረጋቹትን በማስረጃ screenshot በማድረግ በዚ @grade12resultsbot መላክ ትችላላቹ
መልካም በአል መልካም እድል ኢድ አለዳህ
https://t.me/Grade12results
ሰላም ቤተሰቦች ኢድ አለዳን በማስመልከት GIVEAWAY 🎁 ይዘን መጣንላቹ አዎ ለእናተ 🫵
ከእናንተ የሚጠበቀዉ እዚህ ቻናል ላይ ዒድ አል-ፊጥር በዓልን በማስመልከት 50 ሰዉ እስከ 200 ሰዉ እዚህ ቻናል ላይ add ✅️ ላደረጉ እና channel joine ላስደረጉ ከ 500 ብር 💶 እስከ 2000 ብር💶 ይሸለሙ 🎉🎉🎉 ማን ያዉቃል አንቺ / አንተ ልትሆን ትችላላቹ 💪 የሞከረ ይሸለማል 😉 እንዳይረሳ ለመሸለም ከ 50 እስከ 200 ሰዉ add ማደረግ የግድ ነዉ
ያደረጋቹትን በማስረጃ screenshot በማድረግ በዚ @grade12resultsbot መላክ ትችላላቹ
መልካም በአል መልካም እድል ኢድ አለዳህ
@Grade12results
@Grade12results
@Grade12results
ሰላም ቤተሰቦች GIVEAWAY 🎁 ይዘን መጣንላቹ
ከእናንተ የሚጠበቀዉ እዚህ ቻናል ላይ ዒድ አል-ፊጥር በዓልን በማስመልከት 50 ሰዉ እዚህ ቻናል ላይ add ላደረጉ እና channel joine ላስደረጉ ከ 50 ብር እስከ 200 ብር የሞባይል ካርድ ይሸለሙ 🎉🎉🎉 ማን ያዉቃል አንቺ / አንተ ልትሆን ትችላላቹ 💪 የሞከረ ይሸለማል 😉
@Grade12results
@Grade12results
@Grade12results
የህክምና ዶክተር እና ፓይለት በመሆን የመጀመሪያዋ ኢትዮጵያዊት ሴት
በአንድ ሰው ሁለት ዓለማት የህክምና ጥበብን እና የሰማይ ላይ ንግሥናን አስተሳስራ የያዘችው የዶ/ር መቅደስ ብርሃኑ ታሪክ መላው ኢትዮጵያውያንን የሚያኮራ ደማቅ ታሪክ ሆኖ ተመዝግቧል።
ዶ/ር መቅደስ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ትምህርት ቤት በመመረቅ የህክምና ዶክተር መሆን የቻለች ሲሆን፣ በዚህ ብቻ ሳትወሰን የልጅነት ህልሟን እውን ለማድረግ በኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ የፓይለት ስልጠናዋን (MPL) በስኬት አጠናቃለች።
በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ በረዳት አብራሪነት (First Officer) እያገለገለች የምትገኘው ዶ/ር መቅደስ፣ በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመርያዋ ሴት ሀኪም እና የንግድ አውሮፕላን አብራሪ በመሆን አዲስ ምዕራፍ ከፍታለች። ይህ አስደናቂ ስኬቷ ለማንኛውም ሰው በተለይም ለሴት እህቶቻችን "የማይቻል ነገር የለም" የሚል ትልቅ ትምህርት የሚሰጥና የፅናት ተምሳሌት የሆነ ታሪክ ነው።
ዶ/ር መቅደስ ብርሃኑ በምድር ላይ የሰውን ህይወት ለመታደግ በነጭ ጋውን፣ በሰማይ ላይ ደግሞ የሀገርን ባንዲራ አንግቦ ለሚበረው አየር መንገድ በፓይለት ዩኒፎርም ደምቃ የታየች የኢትዮጵያ ኩራት ነሽና ትልቅ አድናቆት ይገባሻል ሲል ወርልድ ፕረስ ከ5 ዓመታት በፊት ካወጣው መረጃ ዶች ኤችዲ ተመልክቷል።
ዶች ኤችዲ
#TAKEN_FROM_MATRIC_EXAM
Choose the word with correct spelling.
🥰. Receive
🙏. Recceive
❤️. Reseive
🤩. Resieve
React To The Right Answer.
http://t.me/Grade12results
#NationalExamrenews
ትምህርት ሚኒስቴር ፤ " የዚህ አመት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና መቶ በመቶ በበይነ መረብ ይሰጣል " አለ።
በዚህ ዓመት የሚሰጠውን የ2018 የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና መቶ በመቶ በበይነ መረብ ለመስጠት የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ " በዚህ ዓመት የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና መቶ በመቶ በበይነ መረብ ይሰጣል " ሲሉ ተናግረዋል።
ይህን ያሉት በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የግማሽ ዓመት አፈፃፀም መድረክ ላይ ተገኝተው ነው።
ባለፉት ሁለት ዓመታት ፈተናው በወረቀትና በበይነ መረብ ሲሰጥ እንደነበር አንስተው በዚህ ዓመት የሚሰጠውን ማጠናቀቂያ ፈተና ሙሉ በሙሉ በበይነ መረብ ለመስጠት የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ለዚህም የተለያዩ ግብዓቶች ለክልሎች ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው በፈተና ጣቢያዎች በቂ የኢንተርኔት አቅርቦት እንዲኖር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመነጋገር ይሰራል ብለዋል።
ክልሎች በዚህ ሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮች እንዳይኖሩ በቂ ኮምፒዩተር ፣ ኔትዎርክና አማራጭ የሀይል አቅርቦት እንዲኖር ልዩ ትኩረት ሰጥተው መዘጋጀት እንዳለባቸው አሳስበዋል። ለተማሪዎችም በቂ ሥልጠና መስጠት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የክልልና ከተማ መስተዳድሮች ይህንን አውቀው አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የዲጅታል ትምህርትና አይሲቲ ሥራ አስፈፃሚ ዘላለም አሰፋ (ዶ/ር) ፤ ተማሪዎች የሚለማመዱባቸው ሞዴል ፈተናዎች በበቂ ሁኔታ የተጋጁ መሆኑን ገልጸዋል።
" ተማሪዎች አስቀድመው እንዲለማመዱና ሥልጠና እንዲያገኙ ማድረግ ይገባል " ብለዋል።
@Grade12results
@Grade12results
#TAKEN_FROM_MATRIC_EXAM
Choose the word with correct spelling.
❤️. Necessety
🥰. Neccssity
🙏. Necessity
🤩. Necesety
React To The Right Answer. t.me/Grade12results
#እጅግ_ቀላል_የማትሪክ_ጥያቄ
What’s___ she asked when she saw our anxious faces.
🤩. Up
🥰. On
🙏. About
❤️. Out
React To The Right Answer.
t.me/Grade12results
2018 ተፈታኞች ለ entrance exam matinat ስጀምሩ ለራሳችሁ ፈተናው ቀላል እንደሆነ አሳምኑት እንደኛ አክብዳቹ ካሰባቹ ለማጥናት ባሰባቹ ቁጥር ጭንቀት ይይዛቹሃል እኛ ሄደን ስንፈተን ነው ያመነው ፈተናው ከምናስበው በላይ ቀላል ነው class final ከምንፈተነው ራሱ ይቀላል እና እናንተ ይሄን ካወቃቹ እንደእኛ ምንም ሚያስተሽናቹ ነገር ሊኖር አይገባም ስታጠኑ ደሞ relax አያረጋቹ አጥኑ. እኛ በዚህ misunderstanding ብዙ ነገር አተናል ይሄን አወቀን ቢሆን ኖር ያለቴንሽን አጥንተን አሁን ከሰራነው በላይ እንሰራ ነበር. ይሄን ክረምት bio, chem,phy, math 9-10 short note አውጥታቹ ጨርሱ 11-12 ደሞ እየተማራቹ እስከ ሞዴል ከቻላችሁ cover አርጉ note ስታወጡ short ለማረግ ሞክሩ coz ሲታዩት /ስታነቡት ትንሽ ነው እያላችሁ በቀላሉ ትይዛላችሁ ex እኔ grade 12 bio በ 20 ልሙጥ ሉክ ከሆአላ እና ከፊት ከነስእሉ ነው የያዝኩት እኔ note ሳወጣ competency ላይ ሚጠይቀውን ነበር እሱን መልስ በሚመስል መልኩ ለያንዳንዱ competency note ሳወጣ የነበረው. English ደሞ አንብቦ ፈተና መስራት ለኔ ሞኝነት ነው እኔ ያረኩት በ ትርፍ ሰዓት english movie አይ ነበር እና ethiomatric በስልክ ከ 2007-2016 የ 10 ክፍል matric, 11-12 matric እና 9-12 entrance exam ሁሉንም ደጋግሜ ሰርቻለው just ትንሽ አነበብኩ more ግን ከ ጥያቄ ጋር familiar ሆንኩኝ እና grammar ብትረሱ እንኩዋን ከጥያቀ ጋር ከመላመዳቹ ብዛት ትክክለኛውን መልስ sense ማረግ ትቺላላችሁ እና በዚህ way ከሁሉም የሰራሁት English new specially passage ማታ ማታ ዓመቱን ሙሉ English አልጋየ ላይ ተኚቼ ስሰራ ነበር. Math እና physics ብዙ ጥያቄ ስሩ physics እንደ ድሮ አይደለም concept ማምጣት ጀምረዋል እና በደንብ ለመረዳት ሞክሩ math ጥያቄ በደንብ ስሩ text book በደንብ ሰርታቹ entrance ተለማመዱ እና reference book ጭራሽ ባታዩ ጥሩ ነው text እራሱ ከበቂ በላይ ነው. እኔ አንድም reference book አልጠቀምኩም. እና sat practice አርጉ. የራሳችሁን ድሮ የሚታውቁትን የንባብ መንገድ ተጠቀሙ. ከ social media( except tg and you tube for educational purpose) ራቁ. በሞደል ፈተና result እንዳትደናገጡ coz entrance ከሞዴል ቀላል ነው. Spiritually መጠንከር የሚፈልግ ጊዜ ስልሆነ church/ mosque ሂዱ ክዱስ መፃፍ አንብበው /ዱአ አርጉ /ፀልዩ." እና የሰራነውን የሚባርክ እንጂ የሚነሳ ፈጣሪ የለም እና የቻላቹትን ያክል ስሩ በጎደለው ፈጣሪ ይሞላል. መልካም ጥናት ይሁንላችሁ...
@Grade12results
@Grade12results
MegaMind Academy
https://megamindacademyhub.com/
check it this web helps you to beat your goal
also this web developed by grade 12 students that so check it 👌
@Grade12results
@Grade12results
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
