316
订阅者
无数据24 小时
无数据7 天
-830 天
帖子存档
316
ቅምሻ ፪ - ከአሐቲ ድንግል
ድንግል ማርያም እግዚአብሔር ስለመረጣት ነው ንጽሕት የሆነችው ወይስ ንጽሕት ስለሆነች ነው እግዚአብሔር የመረጣት?
አንዳንዶች ስለ ድንግል መመረጥ ሲነገር ሲሰሙ ሲመርጣት ላትመረጥ ነውን? እርሱ ጠበቃት እንጂ እርስዋ ምን አደረገች ሲሉ ይሰማሉ። እግዚአብሔር ሰለመረጣት ነው ንጽሕት የሆነችው የሚለው አደገኛ ክህደት ነው። ለምን ቢሉ እግዚአብሔር ለሰው ልጅ የሰጠውን ነፃ ፈቃድ የሚንድ ነውና። ዳግመኛ እርሷ እግዚአብሔር ስለመረጣት ብቻ ከሆነ ንጽሕት የሆነችው እያንዳንዱ ሰው ንጹሕ የማይሆነው እግዚአብሔር ስላልመረጠው ነው ወደሚል የቅድመ ውሳኔ ክህደት የሚያመራ ጠማማ መንገድ ነው።
እንዲህ ከሆነ ደግሞ በዓለም ላይ ለሚሠሩ የርኩሰትና የአመፅ የበደል ውድቀቶች ሁሉ ተጠያቂው እግዚአብሔር እንጂ ሰው አይደለም ብሎ እግዚአብሔርን መሳደብ ነው። ምክንያቱም እግዚአብሔር የመረጠው ብቻ ንጹሕ ከሆነ ሁሉም የመንጻት ሥልጣን ካልተሰጠው በበደለኛነት ዘመናቸውን የፈፀሙ ሰዎች ተጠያቂ መሆን የለባቸውም፤ ከኃጢአት ለመንጻት ቢፈልጉ እንኳን አልተመረጡምና አይችሉም ማለት ነዋ! እንዲህ ከሆነ ሰዎች ሁሉ ሊድኑ እና እውነቱን ወደ ማወቅ እንዲደርሱ የሚወድ እግዚአብሔር (ጢሞ. ፪፥፫) ፈቃዱ ወዴት አለ? እርሱ የመረጣቸው ብቻ የሚነጹ ከሆነ ባልመረጣቸው ላይ ለምን ይፈርድባቸዋል? ፈታሒ በጽድቅነቱስ ወዴት አለ?
ነገር ግን ርቱዕ የሆነው የሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን የቀና የጸና አስተምህሮዋ እንዲህ አይደለም። እግዚአብሔር ሰዎችን ፍጻሜያቸውን አስቀድሞ አይቶ ይመርጣል እንጂ ወስኖ መርጦ የፈጠረው ሰው የለም። በወንጌል የእግዚአብሔር መንግስት በመካከላችሁ ናት ማለቱም ሰው ለመዳን የሚያስችለው ለመምረጥ የሚያበቃው ኃይል በእጁ እንዳለ ሲያጠይቅ ነው። በስሙ ለሚያምኑ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው የተባለውም ለዚህ ነው። በስሙ ለሚያምኑ የተሰጣቸው ስልጣን የተባለው ለመዳንም ላለመዳንም የሰው ነፃ ፈቃድና ልጅነት እንደተሰጠ ሲያስረዳ ነው። እግዚአብሔር ወደ አቤልና ወደ መስዕዋቱ ተመለከተ የተባለውም አቤል የልቡን ቅንነት የመስዕዋቱን መበጀት ስሙርነት አይቶ ተመልክቶ አቤልን ተቀበለው እንጂ አቤል እንዲያ እንዲሆን አድርጎ ወሰኖ መርጦ አልፈጠረውም። በአንፃሩ ወደ ቃየልና መስዕዋቱ አልተመለከተም ማለት የቃየልን የልቡን ጥመት አየና የመስዕዋቱን አለመበጀት አይቶ አልተቀበለውም ነገር ግን እግዚአብሔር ለክፋት ወስኖ አልፈጠረውም። እግዚአብሔር ሲኦል የሚገቡ ሰዎች እንዳሉ አውቆ ሲኦልን አዘጋጀ እንጂ ሲኦል በሚገቡ ሰዎች ላይ አስቀድሞ እንዲገቡ አድርጎ ወስኖ አልፈጠረም።
እናቱ ድንግል ማርያምን ከእናቷ ማሕፀን መርገም እንዳይኖርባት የጠበቃት እርሱ ነው ቅድመ ዓለም የአምላክ እናት እንድትሆን የመረጣትም እርሱ ነው። ነገር ግን ፍፃሜዋን በነፍስ በስጋ በአፍኣ ንጽሕት እንድትሆን አውቆ መረጣት እንጂ እርሱ ሰለወሰነ የጠበቃት የመረጣት አይደለችም። በዘመኗ ሁሉ በቅድስናዋ ተሸልማ እንደምትኖር አውቆ ከመርገም አነጻት፥ ኖሮባት አይደለም እንዳይኖርባት ጠበቃት እንጂ!
መንፈስ ቅዱስ ጠበቃት አነፃት መባሉም ፍፃሜዋን አይቶ መርገም እንዳይኖርባት ጠበቃት ማለት ነው እንጂ በዓለም ኃጢአት እንዳትሰራ ከለከላት ማለት አይደለም። ንጹህ ሆኖ መፈጠርማ አዳምም ተፈጥሮ ነበር በተፈጥሮ የተሰጠውን ንጹህ ጠባይ በቅድስና መጠቀም አልተቻለውም እንጂ እርሷ ግን ንጽሕናን ቅድስናን ደራርባ ይዛ ተገኝታለችና በዛው ድንግልናዋ ለአምላክ እናትነት በቃች። የሕይወት ፍሬን አፈራችበት እንዲመርጣት እግዚአብሔርን የሳበ በአምላክ ዘንድ ሞገስን የያዘ ንጽሕና ይዛ ተገኝታለችና እንድትመረጥ ሆና ተገኝታለች። ንጹሃንን ለክብር መምረጥማ ለፈጣሪ ድንቅ አይደለም ከእርስዋ ይልቅ ጠላቶቹን እኛን በደሙ ፈሳሽነት ይቅር ማለቱ አይደንቅምን?.......(ቀጣዩን መጽሐፉን ገዝተው ያንብቡ)
(ከርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን ግርማ አሐቲ ድንግል ገፅ 272-277 ላይ የተቀነጨበ)
https://t.me/dn_mezmur
316
👉ንጽሐ ሥጋ
(ጽማሜ፣ ልባዌ፣ ጣዕመ ዝማሬ)
👉ንጽሐ ነፍስ
(አንብዕ፣ ኩነኔ፣ ፍቅር፣ ሑሰት)
👉ንጽሐ ልቡና
(ንጻሬ መላእክት፣ ተሠጥሞ ብርሀን፣ ከዊነ እሳት)
316
የአዳም በደል ውጤት
አዳም የቤተ ፈት ኀዘን አላገኘውም። ቤተ ፈት ይህን ጊዜ እበላ ፤እጠጣ፤እከብር ነበርኩ ዛሬ ግን አጣሁ ነጣሁ ተዋረድኩ ብሎ ነውና። አዳም ግን አትብላ ያለኝን ዕፀ በለስ ቀጥፌ፤ ሕጉን ተላልፌ፤ እምነቴን አጉድዬ ፣ፈጣሪዬን አሳዘንኩት ብሎ የው እንጂ በገነት አደርገው የነበረው ተድላ ደስታ ቀረብኝ ብሎ አይደለም።
"ለአዳም ስለ ኃጢአቱ ከማልቀስ በስተቀር ሌላ ሐሳብ አልነበረውም የለውምም "።
ምንጭ፦
መቅድመ ወንጌል
ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ
Deacon Mezmur Niguse
https://t.me/dn_mezmur
316
ዲያብሎስ በተተናኮላት ሰውነት ላይ የእግዚአብሔር ጥበብ አታድርም።በኃጢአት በተገዛ ሰውነትም አታድርም።
Dewcon Mezmur
https://t.me/dn_mezmur
316
እመቤታችን
ከልጅሽ ከወዳጅሽ ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ለምኝልን። ኃጢአታችንን ያስተሠርይልን ዘንድ።
ለሰው ኃጢአቱ ከተሠረየለት ሌላ አይሻምና።
"ጸጋሰ ሥርየተ ኃጢአት ይእቲ" እንዲል።
Deacon Mezmur
https://t.me/dn_mezmur
316
+++በዕለተ ሐሙስ የተፈጠሩ ፍጥረታት ስማቸውና ምሳሌያቸው+++
በዕለተ ሐሙስ "ለታውጽእ ባሕር ኩሎ ዘመደ ዓሳት ወኩሎ ዘቦ ተሐዋስያነ ላዕሌሁ መንፈሰ ሕይወት" ባለ ጊዜ በልብ የሚሳቡ ፣በእግር የሚሽከረከሩ፣በክንፍ የሚበሩ በደመ ነፍስ ሕያዋን ሆነው ጸንተው የሚኖሩ ሦስት አሥራወ ፍጥረታት ተገኝተዋል።
ከእነዚህም ዕለቱን ወጥተው በረው በረው የሄዱ አሉ፣ ከዚያው የቀሩም አሉ። ዕለቱን ወጥተው በረው በረው የሄዱ የኢጥሙቃን(ያላመኑ) ከዚያው የቀሩ የጥሙቃን (ያመኑ) የምዕመናን ምሳሌ ነው።
+++ ወባረኮሙ ለኩሎሙ በአሐቲ በረከት ይላል ብሎ ዕለቱን ወጥተው በረው በረው የሄዱ ተመስጦተ ጸጋ ያላቸው የሰማዕታት፣በልብ የሚሳቡ የሰብአ ዓለም፣በእግር የሚሽከረከሩ ከገድል ወደ ገድል ከትሩፋት ወደ ትሩፋት የሚሉ የጻድቃን፤ ዕለት የእመቤታችን፣ባሕር የጥምቀት ምሳሌ ነው።
አንድም ዕለቱን ወጥተው በረው በረው የሄዱ ኅድግዎ ወመንንዎ ለዝ ዓለም ብለው ዳዋ ጥሰው፤ጤዛ ልሰው፤ድንጋይ ተንተርሰው ፣ግርማ ሌሊቱን፣ጸብዓ አጋንንቱን ታግሰው የሚኖሩ የባሕታውያን ምሳሌ፤ ከዚያወ የቀሩ ሃይማኖት ተምረው፣ምግባር ሠርተው፣አስራት በኩራቱን አውጥተው በሕገ እግዚአብሔር ጸንተው የሚኖሩ የምዕመናን ምሳሌ ፣ባሕር የማየ ገቦ ምሳሌ።
አንድም በክንፍ የሚበሩ የፍጽማን ምዕመናን ፣በእግር የሚሽከረከሩ የማዕከላውያን ምዕመናን፣በልብ የሚሳቡ የወጣኒያን ምዕመናን ምሳሌ ነው።
ስታነቡት ያልገባችሁ ካለ በውስጥ መስመር ማናገር ትችላላችሁ!!
@mezwell
ምንጭ፦ ኦሪት ዘፍጥረት ትርጓሜ፤ ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ
Deacon Mezmur Niguse
https://t.me/dn_mezmur
316
"ፈቀደ እግዚእ ያግዕዞ ለአዳም"
አምስት ሺ አምስት መቶ ዘመን ወደ ሲኦል ተግዞ ፤ በግብርናተ ዲያብሎስ ተይዞ ይኖር የነበረ አዳምን ነጻ ሊያወጣው ወደደ።
ምነው አመስግነኝ ብትለው ወደ ጌታ ሄደ? ቢሉ፦ መክበሪያዋን ሲሻ ነው። ከዚያ ቅዱስ ሉቃስን ታኦፊላ መኮንነ እስክንድሪያ ይለዋል። በቅዱስ ሉቃስ ስብከት ያመነ ነው። ዜና ሐዋርያትን ጻፍልኝ ቢለው፦ መክበሪያቸውን ሲሻ " እምጊዜ ዕርገቱ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘአኀዘ ይግበር ወይምሀር" ብሎ ከጌታ ዕርገት ጀምሮ እንደጻፈለት። ጌታንስ ይሁን አዳምን ስለምን አነሣው? ቢሉ፦ አዳም አባቷ ነውና ነገር ከሥሩ ውኃ ከጥሩ እንዲሉ ከጥንት ጀምሮ ተርኮ ለመናገር። አንድም አስከትላው መጥታ ነበርና ቢያየው አነሣው።
"ኁዙነ ወትኩዘ ልብ"
"ኁዙነ ልብ ወትኩዝ"ሲል ነው። እንዲህ አይነት ቅጽል ለመጽሐፍ ልማድ ነው። "ስመ ወግብረ ወልድ ተምያጠ ወተውላጠ ህላዌያት ጽጌያተ በፍሬያተ ትሩፋን"እንዳለው ያለ ነው።
አምስት ሺ አምስት መቶ ዘመን አዝኖ፣ተክዞ፣ቆዝሞ ይኖር የነበረ አዳምን ነጻ ሊያወጣው ወደደ። አዳም የቤተ ፈት ኃዘን አላገኘውም። ቤተ ፈት ይህን ጊዜ እበላ፣እጠጣ፣እከብር ነበርኩ ዛሬ ግን አጣሁ፣ነጣሁ፣ተዋረድኩ ብሎ ነውና። አዳም ግን አትብላ ያለኝን ዕፀ በለስ ቀጥፌ፣ሕጉን ተላልፌ፣እምነቴን አጉድዬ ፈጣሪየን አሳዘንኩት ብሎ ነው እንጂ ፣በገነት አደርገው የነበረው ተድላ ደስታ ቀረብኝ ብሎ አይደለም። "አልቦቱ ካልዕ ኅሊና ለአዳም ዘእንበለ ብካይ ላዕለ ኃጢአቱ" እንዲል። አንድም ይህንን ለጌታ እየሰጡ ይተረጉሙታል፦አምስት ሺ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም ያዘነ የተከዘ ሆኖ አዳምን ነጻ ሊያወጣው ወደደ። "ተከዘት ነፍስየ እስከ ለሞት" እንዲል።
"ወያግብኦ ኃበ ዘትካት መንበሩ"
ወደ ቀደመ ክብሩ፣ወደ ቀደመ ማዕረጉ፣ወደ ቀደመ ቦታው ይመልሰው ዘንድ ወደደ።
ቦታ ቢሉ ገነት ፤ ክብር ቢሉ ልጅነት ነው። ይህም የዕርቅ ምልክት ነው። ንጉሥ ሎሌውን የተጣላው እንደሆነ ቤቱን፣ንብረቱን፣ርስቱን፣ጉልቱን ይወርስበታል። ሰናፊል አትታጠቅ፣ዘንግ አትያዝ፣ከከተማ አትውጣ፣ከአደባባይ አትቀመጥ ብሎ ሥርዓት ይወስንበታል(ያጸናበታል)። በታረቀው ጊዜ ግን ቤትህን፣ንብረትህን፣ርስትህን፣ጉልትህን መልሼልሃለሁ፣ እንደ ልብህ ውጣ ግባ ብሎ ነጻነቱን እንዲፈቅድለት።
አንድም "ወደ ቀደመ ጌትነቱ ይመልሰው ዘንድ ወደደ"
መንበረሂ ሶበ ሰመይከ ለብዎ ለመንበር" እንዲል።
"ሰአሊ ለነ ቅድስት"
ሰአሊ ለነ ቅድስትን ቅዱስ ኤፍሬም አልተናገረውም። ቅዱስ ያሬድ ለዜማ ማቅኛ አድርጎ ተናግሮታል። ይኸውም ሊታወቅ ከሀገራቸው ከመጽሐፋቸው ቢፈልጉ ፤ከቃላቸው ቢጠይቁ አይገኝም። ቅዱስ ያሬድም ከአፍአ አምጥቶ ከልቡናው አቅንቶ አልተናገረውም። "ሰአሊን" ሰአለ ካለው፤ "ቅድስትን" ቀደሰ ካለው ግሥ አምጥቶ ተናግሯታል እንጂ።
አምስት ሺ አምስት መቶ ዘመን በግብርናተ ዲያብሎስ ተይዞ፤ ወደ ሲኦል ተግዞ ይኖር የነበረ አዳምን ነጻ ሊያወጣው ከወደደ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና፤ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን፣ክብሩን እንዳይነሣን ለምኝልን። አእምሮውን ጥበቡን በልቡናችን ሣይልን አሳድሪልን።
(ውዳሴ ዘሰኑይ ትርጓሜ )
አሜን አሜን አሜን
ዲ/ን መዝሙር ንጉሴ
ኢትዮጵያ
27-01-17 ዓ.ም
https://t.me/dn_mezmur
316
+ አንድ ሱፉን ግጥም አድርጎ የለበሰ ሰውዬ አንዲትን ሕፃን መንገድ ላይ ጠራት
"ሚጣ በምድር ላይ ለዘላለም መኖር ትፈልጊያለሽ?" አላት
"ሰማይና ምድር እኮ ያልፋሉ እንዴት ለዘላለም ልኖር እችላለሁ?" አለችው
"አይ ሚጣ እግዚአብሔር እኮ ሰማይ ዙፋኔ ነው ምድርም የእግሬ መረገጫ ነው ብሎአል:: ሰማይና ምድር ካለፉ እግዚአብሔር የት ይሔዳል?" አላት ፈገግ ብሎ
ሚጣ አልተቸገረችም
"ሰማይና ምድር ሳይፈጠሩ ወደነበረበት ቦታ ይሔዳል" አለችው።
ዲ/ን መዝሙር
2017 ዓ.ም
https://t.me/dn_mezmur
316
+ ልጅሽ ደጅ ላይ ቆሟል +
ከመስከረም 26-እስከ ሕዳር 6 ባሉ አንድ ቅዳሜ ማታ ከ3 ሰዓት በኋላ ማሕሌተ ጽጌን ለመቆም ወደየካ ደብረ ሳሕል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን እየሄድኩ ነው . . . መንገዱ ጭር ብሏል፤ አንድ ሱቅ ላይ ግን ደምበኛ (ገዢ) ቆሟል፤ እኔ መንገዴን እየቀጠልኩ ነው፡፡ ደንበኛው ቀጥ ብሎ ወደኔ መጣ እና ‹‹አባ ይበርኩኝ?›› አለኝ። ‹‹ካህን አይደለሁም›› አልኩት፣ በለበስኩት ነጠላ ጋቢና በእጄ የያዝኩት የጸሎት መጽሐፍ ወደ ቤተ ክርስቲያን እንደምሄድ አውቆ ነው፡፡ ‹‹አውቃለሁ›› አለኝ እና ‹‹ወደየትኛው ቤተ ክርስቲያን ነው የምትሄደው?›› ጠየቀ መለስኩለት፤ ‹‹እባክህን ልሸኝህ?›› አለኝ አዲስ ቪ 8 መኪና እያሳየኝ፣ ‹‹ብዙም ሩቅ ስላልሆነ በእግሬ ነው የምሄደው›› አልኩት . . .
ግለሰቡ የጠጣ ይመስላል፣ በእርግጥም የመጠጥ ሽታ ሸትቶኛል፤ በእጁ ፓኬት ሲጋራ ይዟል፣ ከሱቁ ሲመጣ ከፓኬቱ ውስጥ አንዱን አውጥቶ ከንፈሩ ላይ አድርጎ ነበር ሲቀርበኝ በጣቶቹ መሃል ያዘው፣ ምልከታዬን አስተውሎ ነው መሰለኝ የያዘውን ሲጋራ በሙሉ ጣለና በእግሩ ረጋገጠው፡፡ ‹‹አክሊለ ጽጌ ማርያም ቀጸላ መንግሥቱ ለጊዮርጊስ ልትል ነው አይደል?›› አለኝ
ከዚህ ንግግር በኋላ ስካሩ ሙሉ ለሙሉ ሲጠፋ በግልጽ ይታያል፡፡ ሁሉንም የመኪናውን በሮች ከፈተና ‹‹እንዲናፈስ ፈልጌ ነው . . . በሲጋራና በመጠጥ ሽታ የታጠነ መኪና ውስጥ እንዳትገባ›› አለኝ፤ በግርምት ቆምሁ፤
‹‹እባክህ አሁን እንሂድ?›› የጋቢናውን በር ብቻ ትቶ ሌሎቹን ዘጋጋና መኪናውን ለመንዳት ተዘጋጀ፤ በእምነት ገባሁና ተቀመጥኩ። መንገድ ስንጀምር በጣም ባዘነ ድምጸት
‹‹ሽሮ ሜዳ ነው ያደግሁት . . . ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን . . . ጽጌን በፍቅር ቆሜ ነው ያደግኩት . . . ለረጅም ዓመታት . . . አክሊለ ጽጌ ብዬ . . . ክበበ ጌራ ወርቅ ብዬ ›› ዓይኖቼን ከመንገዱ ነቅዬ ወደርሱ ሳዞር መንታ መንታ ሆነው የሚወርዱ እንባዎቹን ይጠርጋል፤ ምን ማለት እንዳለብኝ አላውቅም መስማት ብቻ
‹‹ዲግሪዬን ከያዝኩ በኋላ አንድ ዓለም አቀፍ ኤን ጂ ኦ ገባሁ . . . በከፍተኛ ደመወዝ በቃ ከቤተ ክርስቲያን ጋር ተለያየሁ. . . አልሳለም፣ ኪዳን አላደርስ፣ አላስቀድስ፣ አላድር፣ አላነግስ ከሀገር ሀገር መዞር ከጓደኞቼ ጋር መጠጣት፣ ሲጋራ ማጨስ . . . ይኸውልህ ሚስትና ልጆች እያሉኝ ነው እዚህ ያገኘኸኝ፣ የመጠጥና የሲጋራ ጓደኞቼ በልጠውብኝ ነው ያገኘሁህ. . . ውስኪአቸውን ይዘው እየጠበቁኝ ነው ›› ያለቅሳል፣ እንባዎቹን ይጠርጋል፤ ግን በሥርዓት ረጋ ብሎ ይነዳል፤ መናገሩን ይቀጥላል
‹‹ተረጋግቼ ማሰብ አልፈልግም . . . ምክንያቱም ከተረጋጋሁ ልጅነቴን ማሰብ እጀምራለሁ . . . ልጅነቴን ማሰብ ከጀመርሁ ቤተ ክርስቲያንን ማሰብ እጀምራለሁ . . . ደጀ ሰላሟን ማሰብ እጀምራለሁ. . . መቅደሷን ማሰብ እጀምራለሁ፣ . . . የዕጣኑን ሽታ ማሰብ እጀምራለሁ . . . ማልቀስ እጀምራለሁ . . . ፍቅሯን አስባለሁ . . . የጸናጽሉ፣ የከበሮው ድምጽ ይሰማኛል፣ በመሃል ሰይጣኔ ይመጣና እውነቴን ነው ስጠራው ነዋ የሚመጣው. . . ለጓደኞችህ ደውል ይለኛል . . . በመጠጥ ራስህን ደብቅ ይለኛል እታዘዘዋለሁ ልጆቼንና ሚስቴን ጥዬ እወጣለሁ››
አሁን ወደ ቤተክርስቲያን ታጥፈናል፤ ወደ ግቢው የሚያስገባ በር ጋር ስንደርስ ቆመ፣ ወደውስጥ ለመግባት በሮቹ የተከፈቱ ቢሆንም አልገባም፤
‹‹ወደውስጥ ገብተህ ትንሽ ቆይተህ አትሄድም?›› አልኩ ሀዘኑ ተጋብቶብኝ ‹‹አልገባም ግን ድሮ የሚወድሽ ልጅሽ ደጅ ቆሟል በላት›› አለና ሳግ ተናንቆት መሪውን ተደግፎ ድምጽ አሰምቶ አለቀሰ፣ ቅዱስ ጴጥሮስ ለምን እንዳለቀሰ፣ እንዴት እንዳለቀሰ በዓይኔ ያየሁ መሰለኝ፤
‹‹እባክህን ግባና አልቅስ›› አልኩ፣ የቻለውን ያህል አልቅሶ እንዲወጣለት ፈለግሁ፣
‹‹ማን . . . እኔ? አልገባም ግን ንገርልኝ አሁንም ይወድሻል በልልኝ . . . እዚህ በር ላይ ቆሟል በልልኝ›› አለኝ፣ እያለቀሰ ወረድሁ
ቅዱስ ዳዊት ‹‹በኃጥአን ድንኳኖች ከመቀመጥ ይልቅ በእግዚአብሔር ቤት እጣል ዘንድ መረጥሁ›› መዝ 84፣10 ያለው ለምን እንደሆነ ይበልጥ ገባኝ። ሳላውቀው የእኔም እንባ መንገዱን ጀምሯል፤ ‹‹ማን ስለሆንኩ ነው እንዲህ በፍቅርህ የተሸከምከኝ››አልኩ አምላኬን፣
በላዔ ሰብዕ ትዝ አለኝ በልጅነቱ የሚያስታውሳትን የድንግልን ድንቅ ስሟን ሲሰማ ከክህደት እንደተመለሰና ለመዳን ምክንያት እንደሆነችው፡፡ እናም ‹‹በልጅነቱ ይወድሽ የነበረውን ልጅሽን አስቢው ከልጅሽ ዘንድ አሳስቢለት›› አልኳት
ዲ/ን አብርሃም ይኄይስ እንደጻፈው
https://t.me/dn_mezmur316
"የእመቤቴ ምስጋና እንደ ሰማይ ኮከብ፤ እንደ ባሕር አሽዋ በዝቶልኝ እንደ ምግብ ተመግቤው፣ እንደ መጠጥ ተጥቼው፣ እንደ ልብስ ተጎናጽፌው ምነው በኖርኩ እያለ ሲመኝ ይኖር ነገር።
(ቅዱስ ኤፍሬም እመቤታችንን ለማመስገን ሲመኘው የነበረ ቃል)
ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ
እኛስ በውሎአችን ምን እንመኛለን።
ዲ/ን መዝሙር
26-01-17 ዓ.ም
https://t.me/dn_mezmur
316
ወደ ምስራቅ ተመልከቱ የሚለው የዲያቆኑ ትእዛዝ
1. ወደ እመቤታችን ራሳችሁን መልሱ
2. ወደ ኢየሩሳሌም
3. ወደ ቅዱስ ወንጌል
4. ወደ ቀራኒዮ ተመልከቱ
ይህንና የመሳሰሉትን ትርጉሞች ይይዛል።
ዲ/ን መዝሙር
25-01-17 ዓ.ም
316
“ብዙ ኀዘን የማያቋርጥም ጭንቀት በልቤ አለብኝ" አለ ቅዱስ ጳውሎስ ለሮሜ ሰዎች።
ለተወሰነ ጊዜ ፤ ታይቶ በሚጠፋ ሰዓት ሳይሆን ሁልጊዜ በጭንቀት መኖሩን ለሮሜ ሰዎች ገለጠላቸው። የማያቋርጥም ጭንቀት ከማያቋርጥ ወይም መፍትሔ ከሌለው ችግር የሚመጣ ነው።
— ሮሜ 9፥1-2
https://t.me/dn_mezmur
316
የኦሪት ዘፍጥረት ታሪክ በአጠቃላይ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ጉዳዮች ላይ የሚያነጥን ነው። ስለዚህ ቢያንስ በቀን አንድ ታሪክ ለማንበብ ሞክሩ።
የፍጥረት አጀማመር
አዳምና ሔዋን
የሰው ውድቀት
ቃየልና አቤል
ከአዳም እስከ ኖኅ
የጥፋት ውሃ
እግዚአብሔር ከኖኅ ጋር የገባው ቃል ኪዳን
የኖኅ ልጆች ትውልድ
ከሴም እስከ አብራም
የአብራም መጠራት
አብራም በግብጽ አገር
የአብራምና የሎጥ መለያየት
አብራም ሎጥን መታደጉ
አግዚአብሔር ለአብራም የገባው ቃል ኪዳን
አጋረና እስማኤል
የግዝረት ኪዳን
ሦስቱ እንግዶች
አብርሃም ስለሰዶም ማለደ
ሰዶምና ገሞራ ጠፉ
ሎጥና ሴት ልጆቹ
አብርሃምና አቤሜሌክ
የይሥሐቅ መወለድ
የአጋርና የእስማኤል መባረር
አብርሃም ተፈተነ
የናኮር ልጆች
የሣራ ሞት
የይሥሐቅና የርብቃ ጋብቻ
የአብርሃም መሞት
የእስማኤል ልጆች
ያዕቆብና ኤሳው
ይሥሐቅና አቤሜሌክ
ይስሐቅ ያዕቆብን ባረከው
ያዕቆብ ወደ ላባ ሸሸ
ያዕቆብ በቤቴል ያየው ሕልም
ያዕቆብ መስጴጦምያ ደረሰ
ያዕቆብ ልያንና ራሔልን አገባ
የያዕቆብ መንጎች መብዛት
ያዕቆብ ከላባ ቤት ኮበለለ
ላባ ያዕቆብን ተከታተለው
ያዕቆብ ወንድሙን ኤሳውን ሊገናኝ ተዘጋጀ
ያዕቆብ ከእግዚአብሔር ጋር የገጠመው ትግል
የያዕቆብና የኤሳው መገናኘት
የያዕቆብ ልጅ ተደፈረች
ያዕቆብ ወደ ቤቴል ተመለሰ
የራሔልና የይስሐቅ መሞት
የዔሳው ዝርያዎች
የኤዶም ነገሥታት
የዮሴፍ ሕልሞች
ወንድሞቹ ዮሴፍን ሸጡት
ይሁዳና ትዕማር
ዮሴፍና የጵጥፈራ ሚስት
የመጠጥ አሳላፊውና የእንጀራ ቤቱ
የፈርዖን ሕልም
ዮሴፍ በግብጽ ተሾመ
የዮሴፍ ወንድሞች ወደ ግብጽ ሄዱ
የዮሴፍ ወንድሞች ዳግመኛ ወደ ግብፅ መሄዳቸው
የብር ዋንጫ በስልቻ
ዮሴፍ ለወንድሞቹ ራሱን ገለጠ
ያዕቆብ ወደ ግብፅ ሄደ
የራቡ ዘመንና የዮሴፍ አመራሪ
ምናሴና ኤፍሬም
ያዕቆብ ልጆቹን ባረከ
የያዕቆብ መሞት
ዮሴፍ ወንድሞቹን እንደማይቀበላቸው አረጋገጠ
የዮሴፍ መሞት
316
የኢትዮጵያ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ስአት አቆጣጠር
፨ የመስከረም ወር ቀኑ 12 ሰአት ለሊቱ 12 ሰአት ነው ።
፨ የጥቅምት ወር ቀኑ 11 ሰአት ለሊቱ 13 ሰአት ነው ።
፨ የህዳር ወር ቀኑ 10 ሰአት ለሊቱ 14 ሰአት ነው ።
፨ የታህሳስ ወር ቀኑ 9 ሰአት ለሊቱ 14 ስአት ነው ።
፨ የጥር ወር ቀኑ 10 ሰአት ለሊቱ 14 ሰአት ነው ።
፨ የየካቲት ወር ቀኑ 11 ሰአት ለሊቱ 13 ሰአት ነው ።
፨ የመጋቢት ወር ቀኑ 12 ሰአት ለሊቱ 12 ሰአት ነው ።
፨ የሚያዝያ ወር ቀኑ 13 ሰአት ለሊቱ 11 ሰአት ነው ።
፨ ግንቦት ወር ቀኑ 14 ሰአት ለሊቱ 10 ሰአት ነው ።
፨ የሰኔ ወር ቀኑ 15 ሰአት ለሊቱ 9 ሰአት ነው ።
፨ የሐምሌ ወር ቀኑ 14 ሰአት ለሊቱ 10 ሰአት ነው ።
፨ የነሃሴ እና ጳጉሜ ወር ቀኑ 13 ሰአት 11 ሰአት ነው ።
፨ ምንጭ አቡሻክር - ስንክሳር
https://t.me/dn_mezmur
316
የጽድቅ ስሜት
የጽድቅ ስሜት ነው ያለን እንጂ ጽድቅ የለንም።
ይኽ ብዙዎቻችን የምንኖርበት ድባብ ነው። ቤተ ክርስቲያን ስለምንሄድ ፣ እጣን ስለምንታጠንን፣ መስቀል ስለተሳለምን ስላስቀደስን ስለዘመርን ፣ ከሰዎች ጋር ፈገግ እያልን ስለተሳሳምን የጽድቅ ስሜቶቻችን ይፈጠራሉ።
ቤት ስንመጣ ቤታችን ቅዱሳት ስእላት አሉ፣ አለባበሳችን ነጠላችን ከቤተ ክርስቲያን ጋር ያያዝነው ስለኾነ ይኽ የጽድቅ ስሜት አለ። ጓደኞቻችን ስለ ቤተ ክርስቲያን የሚያወሩ ናቸው። ግን እውን ይኽ የጽድቅ ስሜት ከፍሬያችን ከሥራችን የመነጨ ነው ወይስ ክፉን ድርጊት እንደምንጠላው እንደምንጠነቀቀው በምናደርገው ትግል የተሰማን ነው?
መስቀል አክብረናል። ልብሳችንን ለብሰናል በዓል ደርሰን ተመልሰናል። ግን በሕይወታችን አንድ ሰው እንኳ ሲሰድበን ታግሰናል? ለአንድ ሰው እንኳ የመዳን ምክንያት ኾነናል። ጌታ ከእኔ የሚፈልገው ፍሬ ይኽንን ነው ብለን የምናደርገው አለ? ታድያ የጽድቅ ስሜቱን የፈጠረው ምንድነው? ያደረግናቸው የሰቀልናቸው ስእላት አለባበሳችን በስሜት ብቻ ሊገሉን አይደል? ይኽ የጽድቅ ስሜት ብቻ ከምን መጣ? መልሱን ፈልጉ። ከፍሬያችን ከኾነ ትክክል ነው። ካልኾነ ግን ሩቅ መንገድ ሄደን እንፈትሽ። ጽድቅን ወደ ባሕርያችን ማስገባት የግድ ይኾናል። ግር የሚል ከኾነ አትድከሙ እለፉት።
ንዋይ ካሳሁን
https://t.me/dn_mezmur
316
ለአደባባይ በዓላት ‹‹በሰላም ተከብሮ ዋለ›› የዜና ርእስ ባይሆን
(በአማን ነጸረ)
እንደ መስቀልና ጥምቀት ያሉ የአደባባይ በዓላት ሲደርሱ ስለበዓሉ ትርጉምና አከባበር ከሚነገረው ይልቅ ስለ ፀጥታና ሰላም የሚነገረው ዜና መበርከት ይጨንቃል፡፡ በዓላት በተጋነነ የፀጥታ ድባብ (securitization) ሲያልፉ ያፍናል፡፡
እንደ ሚዲያ፣ ዜናዎቹ የበዓሉን ትርጕም አጉልተው የሰላሙ ነገር ንዑስ ርእስ ቢሆን ጥሩ ነው፡፡ የፀጥታና ሰላም ሰበካው፣ የማስጠንቀቂያው ጋጋታ ለበዓሉ ገጽታ የስጋት ጥላ ያላብሳል፡፡ መስቀል የጥል ግድግዳ የፈረሰበት የሰላም ምልክት ነው፡፡ ‹‹ትእምርተ ሰላምነ›› እንለዋለን፡፡ በዚያ መንፈስ ቢታይ እንወዳለን፡፡
--
የአደባባይ በዓላት ሲደርሱ ‹‹ወቅታዊ ጉዳይ›› እየተባለ ወጣቶችን በየጣቢያው ማቆያዎች አስሮ ለማቆየት የትኛው ሕግ እንደሚፈቅድ አልተገለጠልንም፡፡ ስጋት ካለ ማሳወቅ፣ መምከር፣ ባስ ካለም አስጠንቀቆ መልቀቅ ያንጻል፡፡ ከዚያ ባለፈ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በሌለበት አደገኛ ልማድ እየሆነ የመጣው ‹‹ወቅታዊ ጉዳይ›› በሚል ሰበብ የሚደረግ እስር የሕግም የሞራልም ድጋፍ የለውም፡፡ ለበዓሉ አክባሪዎች ሕሊናን ይረብሻል፡፡
--
አሁንም፡- ‹‹በሰላም ተከብሮ ዋለ›› ዜና ባይሆን ደስ ይለናል፡፡ ‹‹በመላ ኢትዮጵያና ኦርቶዶክሳውያን ባሉበት ሁሉ በታላቅ ድምቀት ተከበረ›› እንዲባል ነው የምንፈልገው፡፡ በዓልን በሰላም ማክበር ዜናም ሆነ ሰበር ዜና አይደለም፡፡ ለሺህ ዓመታት በጨዋነት ሲከበር ኖሯል፣ ይኖራልም፡፡
--
ሀባ ሰላማ ለሀገሪትነ ኢትዮጵያ
በአማን ነጸረ
https://t.me/dn_mezmur
