4 005
订阅者
无数据24 小时
-97 天
-8030 天
帖子存档
4 005
ገራሚው ሚስጥር
ክፍል 2
ቀና ስል ልጅቷ የለችም በጣም ደነገጥኩ እዚ ሰፈር ከመጣች ጊዜ ጀምሮ ከዚ ቦታ ተነስታ አይቻት አላውቅም እዚ የመጣችው የዛሬ 3ወር አካባቢ ነው ከዛ ጊዜ ጀምሮ ሁሌ አያታለሁ አሁን ግን የለችም አላውቅም በጣም ተጨነኩ ምን ሆና ይሆን እንዴት ዛሬ ከዚ ቦታ ተነሳች ብዬ ማሰብ ጀመርኩ ለካ ለኔ አልታወቀኝም እነሱ ፊት ነው የቆምኩት ከሀሳቤ የነቃውት "ምነው ቺኳ ችግር አለ "ሲለኝ ነው እ ብዬ ለመመለስ ስንተባተብ ሌላኛው ልጅ ደሞ
"ኧረ መደንበር ምንሼ ፎንቃ ያዘሽ እንዴ ከማናችን ነው" አለኝ ምን እንደምለው ሳስብ መጀመሪያ ያወራኝ ልጅ
"አንተ አሁን ማነው ከኛ ፎንቃ ሚይዘው"ብሎ ጠየቀው
"እና ስትደነባበር ነዋ' አለው በዚ ሰአት እኔም ስለ ልጅቷ ልጠይቃቸው አስቤ
ይቅርታ እዚ ጋ ብቻዋን ምትቀመጠው ልጅ የት ሄደች"አልኳቸው
"እኛም አላየናትም በምን ሰአት እንኳን ከዚ እንደሄደች" አለኝ በዚ ጊዜ በጣም ደነገጥኩ ከዚ ተነስታ ማታቅ ልጅ እነሱ እንኳን ሳያያት ወዴት ሄደች ልጆቹን አመስግኜ ወደ ቤቴ ሄድኩ
ከሀሳቤ ግን ልትወጣ አልቻለችም ማረገው ሳጣ አሁን መታ ከሆነ ልያት ብዬ ከቤት ልወጣ በሩን ስከፍት "በሰላም ነው ሰሊ በዚ ሰአት" አለችኝ ፀሀይ ስልኬን አውጥቼ ሳየው ለ 4 ሩብ ጉዳይ ይላል በሩን ዘግቼ ወደ ቤት ገባው ግን መረጋጋት አቃተኝ ቢጨንቀኝ ፀሀይን ጠራዋት ፀሀይ ማለት ሰራተኛችን ናት እቤት ውስጥ እኔ ብቻ ነው ምኖረው ቤተሰቦቼ ወንድሜ ውጪ ወስዶቸዋል እኔም ፕሮሰስ ተጀምሮልኛል ከፀሀይ ጋ እንደ እህት ነን 3 አመት አብራን ቆይታለች "አቤት ሰላም "ብላ ገባች እኔም ቀጥታ
"እዚ እታች የጎዳና ልጆቹን ታቂያቸዋለሽ"
አልኳት
"አዎ ምነው አለችኝ"
"እሺ ብቻዋን ምትቀመጠው የነበረችው በቅርቡ የመጣችው ዝምተኛዋንስ"ስላት ወዲያው" ሀናን ነው" አለችኝ
"ስሟ ሀና ነው እንዴ"አልኳት ወድያው ደንገጥ ብላ
"እ እ አዎ ባለፈው የሆኑ ሰውዬ ሀናሲሏት ሰምቻለሁ" አለችኝ አሁን ግራ ገባኝ በሷ ባህሪ ያውም ወንድ ጠርቷት "ግን ምነው አለችኝ" እኔም "አይ ዛሬ እዛ ቦታ ላይ የለችም" አልኳት እሷም ደንግጣ "ወዴት ትሄዳለች" አለችኝ
"አላውቅም እኔም እሱ ነው የጨነቀኝ" አልኳት
"ቆይ ግን አንቺ ለምን ተጨነቅሽ" አለችኝ
"አላውቅም ግን ሁሌ ስለማያት ዛሬ ስትጠፋ ጨነቀኝ በዛ ላይ ላወራት ነበር" አልኳት የሷም መልስ እንደ ጓደኛዬ ያምሻል ሚለውን ጠብቄ ነበር እሷ ግን በተቃራኒው "እኔም ላወራት እየፈለኩ ዝም ምለው ፈርቼ ነው" አለችኝ
በጣም ደስ አለኝ ይሄ ሀሳብ እኔ ጋ ብቻ አይደለም ያለው
"ግን የለችማ አልኳት"
"እሱስ አዎ ግን የትም አትሄድም አንቺ አትጨነቂ አሁን ተኚ መሽቷል" ብላኝ ወጣች
እኔም ፊቴን ታጥቤ አልጋዬ ውስጥ ገባው የትላንትም እንቅልፍ ስላለ ወዲያው እንቅልፍ ወሰደኝ...
ክፍል 3
ይ
ቀ
ጥ
ላ
ል
እንደዚ አይነት ታሪክ ከፈለጉ join
https://t.me/kebrarr
4 005
ገራሚው ሚስጥር
ክፍል 2
ቀና ስል ልጅቷ የለችም በጣም ደነገጥኩ እዚ ሰፈር ከመጣች ጊዜ ጀምሮ ከዚ ቦታ ተነስታ አይቻት አላውቅም እዚ የመጣችው የዛሬ 3ወር አካባቢ ነው ከዛ ጊዜ ጀምሮ ሁሌ አያታለሁ አሁን ግን የለችም አላውቅም በጣም ተጨነኩ ምን ሆና ይሆን እንዴት ዛሬ ከዚ ቦታ ተነሳች ብዬ ማሰብ ጀመርኩ ለካ ለኔ አልታወቀኝም እነሱ ፊት ነው የቆምኩት ከሀሳቤ የነቃውት "ምነው ቺኳ ችግር አለ "ሲለኝ ነው እ ብዬ ለመመለስ ስንተባተብ ሌላኛው ልጅ ደሞ
"ኧረ መደንበር ምንሼ ፎንቃ ያዘሽ እንዴ ከማናችን ነው" አለኝ ምን እንደምለው ሳስብ መጀመሪያ ያወራኝ ልጅ
"አንተ አሁን ማነው ከኛ ፎንቃ ሚይዘው"ብሎ ጠየቀው
"እና ስትደነባበር ነዋ' አለው በዚ ሰአት እኔም ስለ ልጅቷ ልጠይቃቸው አስቤ
ይቅርታ እዚ ጋ ብቻዋን ምትቀመጠው ልጅ የት ሄደች"አልኳቸው
"እኛም አላየናትም በምን ሰአት እንኳን ከዚ እንደሄደች" አለኝ በዚ ጊዜ በጣም ደነገጥኩ ከዚ ተነስታ ማታቅ ልጅ እነሱ እንኳን ሳያያት ወዴት ሄደች ልጆቹን አመስግኜ ወደ ቤቴ ሄድኩ
ከሀሳቤ ግን ልትወጣ አልቻለችም ማረገው ሳጣ አሁን መታ ከሆነ ልያት ብዬ ከቤት ልወጣ በሩን ስከፍት "በሰላም ነው ሰሊ በዚ ሰአት" አለችኝ ፀሀይ ስልኬን አውጥቼ ሳየው ለ 4 ሩብ ጉዳይ ይላል በሩን ዘግቼ ወደ ቤት ገባው ግን መረጋጋት አቃተኝ ቢጨንቀኝ ፀሀይን ጠራዋት ፀሀይ ማለት ሰራተኛችን ናት እቤት ውስጥ እኔ ብቻ ነው ምኖረው ቤተሰቦቼ ወንድሜ ውጪ ወስዶቸዋል እኔም ፕሮሰስ ተጀምሮልኛል ከፀሀይ ጋ እንደ እህት ነን 3 አመት አብራን ቆይታለች "አቤት ሰላም "ብላ ገባች እኔም ቀጥታ
"እዚ እታች የጎዳና ልጆቹን ታቂያቸዋለሽ"
አልኳት
"አዎ ምነው አለችኝ"
"እሺ ብቻዋን ምትቀመጠው የነበረችው በቅርቡ የመጣችው ዝምተኛዋንስ"ስላት ወዲያው" ሀናን ነው" አለችኝ
"ስሟ ሀና ነው እንዴ"አልኳት ወድያው ደንገጥ ብላ
"እ እ አዎ ባለፈው የሆኑ ሰውዬ ሀናሲሏት ሰምቻለሁ" አለችኝ አሁን ግራ ገባኝ በሷ ባህሪ ያውም ወንድ ጠርቷት "ግን ምነው አለችኝ" እኔም "አይ ዛሬ እዛ ቦታ ላይ የለችም" አልኳት እሷም ደንግጣ "ወዴት ትሄዳለች" አለችኝ
"አላውቅም እኔም እሱ ነው የጨነቀኝ" አልኳት
"ቆይ ግን አንቺ ለምን ተጨነቅሽ" አለችኝ
"አላውቅም ግን ሁሌ ስለማያት ዛሬ ስትጠፋ ጨነቀኝ በዛ ላይ ላወራት ነበር" አልኳት የሷም መልስ እንደ ጓደኛዬ ያምሻል ሚለውን ጠብቄ ነበር እሷ ግን በተቃራኒው "እኔም ላወራት እየፈለኩ ዝም ምለው ፈርቼ ነው" አለችኝ
በጣም ደስ አለኝ ይሄ ሀሳብ እኔ ጋ ብቻ አይደለም ያለው
"ግን የለችማ አልኳት"
"እሱስ አዎ ግን የትም አትሄድም አንቺ አትጨነቂ አሁን ተኚ መሽቷል" ብላኝ ወጣች
እኔም ፊቴን ታጥቤ አልጋዬ ውስጥ ገባው የትላንትም እንቅልፍ ስላለ ወዲያው እንቅልፍ ወሰደኝ...
ክፍል 3
ይ
ቀ
ጥ
ላ
ል
እንደዚ አይነት ታሪክ ከፈለጉ join
https://t.me/kebrarr
4 005
ገራሚው ሚስጥር
ክፍል 1
ከስራ ስወጣ በእግሬ ወደ ቤት የመሄድ ልምድ አለኝ ታክሲ ስለማይኖር አይደለም እና ቅርብ ስለሆነም ነው አትበሉኝ በርግጥ ሩቅ አይደለም ግን ቅርብም ሚባል አይደለም ብቻ ግን ወደኛ ቤት ሚወስደው አስፓልት ስር የጎዳና ተዳዳሪዎች ይኖራሉ ግን ሁሌም ከሌሎቹ ተለይታ ብቻዋን ምትቀመጥ ሌሎቹ ሲለምኑ እሷ ምንም ማትል የጎዳና ተዳዳሪ ሁሌ አያለሁ ሁላችንም የጎዳና ተዳዳሪዎችን እንፈራቸዋለን እኔንም ጨምሮ ግን ደሞ እሷን ሳያት ለምን እንደሆነ ባላውቅም ታሳዝነኛለች ብዙ ነገር መናገር ፈልጋ ሰው ያጣች ይመስለኛል ግን አንድ ማላውቀው ስሜት እንዳወራት ገፋፋኝ ምንም ብል ውስጤን ማሸነፍ አቃተኝ በመጨረሻም ነገ ላወራት ወሰንኩ እንዴት እንደማወራት ሀሳብ ሳወጣ ሳወርድ እንቅልፍ ወሰደኝ የማይነጋ የለም ነጋ ግን ማታ 9:00 ሰአት ስለተኛው ደካክሞኛል ለመነቃቃት ሻወር ወስጄ ቡና ጠጥቼ ከቤት ወጣው ሰርቢሳችንን ጠብቄ ወደ ስራ ሄድኩ ስመለስ እንጂ ስሄድ በሰርቪስ ነው ምሄደው ምን እንደሆንኩ ባላውቅም ስራዬን በስራት መስራት አቃተኝ እዛው ማውቃት ጓደኛዬ በዚ ሁኔታ አይታኝ ስለማታውቅ በግርምት
"ቆይ አንቺ ሰላም ነሽ "አለችኝ
ምነው "አልመስልም"ብዬ መለስኩላት
"ኧረ በጭራሽ እኔ ማውቃት ሰሊ እቺ አይደለችም ችግር አለ እንዴ" አለችኝ
"ባክሽ ምንም አልሆንኩም ማታ አምሽቼ ስለተኛው ይሆናል" አልኳት አሁን የበለጠ ተገረመች ምክንያቱም ሌላ ቀን በ እንቅልፍ እንደማልደራደር ታውቃለች
አሁን ደሞ የበለጠ ምን እንደሆንሽ ማወቅ ፈለኩ" አለችኝ ፈገግ ብላ "ባለፈው ያሳየውሽ ልጅ እሷን ላወራት አስቤ ነበር ግን እንዴት እንደማወራት ግራ ገባኝ"አልኳት
"ማንን ነው ያሳየሽኝ" አለች
"ያቺ ጎዳና ላይ ብቻዋን ምትቀመጠው ልጅ ናታ" አልኳት
"እና ምን ሆነች"
"ምንም ግን ላወሪያት አስቢያለሁ"
"እንዴት አበድሽ እንዴ ጭራሽ የጎዳና ሰው ላውራ ትይ ጀመር" አለችኝ
"እንዴ ምን ችግር አለው"
"አንቺ አብደሻል ሰላም ሙች የሆነ የሆንሽው ነገርማ አለ" ብላኝ ትታኝ ሄደች እንደምንም ስራዬን ሰርቼ 11:00 ሰአት ሲል ወጣው ላውራት ይቅር አላውራት እያልኩ ሳስብ ቆይቼ በመጨረሻም ላወራት ወስኜ ወደ ጎዳና ተዳዳሪዎች ቀረብኩ አንገቴን ደፍቼ ስለነበር ማንንም አላየሁም ድንገት ቀና ስል ግን ልጅቷ...
ክፍል 2
ይ
ቀ
ጥ
ላ
ል
እንደዚ አይነት ታሪክ ከፈለጉ join
4 005
እንደምታፈቅረኝ አይኗ ላይ አውቅባታለሁ... እንስፍስፍ ናት።ለሰአታት እንኳ ተራርቀን ስንገናኝ ለወራት የተጠፋፋን ያህል ጥምጥም ትልብኛለች። ሁሉ ነገሯ እውነት ነው ...ማስመሰል አታቅም ፤እንደውም አንዳንዴ እንደት ትንሽዬዋ ልጃችን የምታየኝ ይመስለኛል።ስትንከባከበኝ አትሰለችም።ከፍቷት እንዳያት አትፈልግም!!ሳቋን እንጂ እንባ እና ህመሟን እንደሸሸገቺኝ ነው...
አመመሽ እንዴ??ደና ነሽ??እላታለሁ የሷ መልስ ሁሌ ደና ነኝ ነው።ግንኮ ውሸቷን እንደሆነ አውቅባታለሁ ብዙ ጊዜ በለሊት ተነስታ ሽንት ቤት ስታቃስት ደርሼባታለሁ።ጭራሽ ሰውነቷ እየመነመነ እየጠቋቆረች ስትመጣ ሀኪም ቤት እንድንሄድ ብለምናትም መልሷ እንደተለመደው ደና ነኝ ብቻ ነው
አንድ ቀን ግን ለስራ በጠዋት ስነሳ አጠገቤ አጣኋት። ብዙ ጊዜ ቀድማኝ ስለምትነሳ አልገረመኝም..እየጠራኋት ጓዳ ብሄድ መኝታ ቤት ብገባ የልጃችን ቤት ብፈልጋት የለችም። ቤቱ ፀጥ ብሏል የቀረኝ ሽንት ቤት ነበርና ወደዛው ሳመራ ሽንትቤቱ ገርበብ ብሎ ታየኝ ብዙም ሳይቆይ ትከሻዬ እየከበደኝ በሩን እንደከፈትኩት ፍቅሬ ተዘርራ አየኋት ።በቅፅበት በድን ሆኜ ወደመሬት ተንሸራተትኩና ቶሎ ቶሎ እጠራት ጀመርኩ ሰውነቷን እየናጥኩ ልቀሰቅሳት ሞከርኩ እሷ ግን ቀድማኛለች ሞታለች።ምን አመመሽ ምን ቸገረሽ ምን ልሁንልሽ ሳልላት ሳላስታምማት ጥላኝ ጠፍታለች....
ፍቅርዬን ከቀበርኳት ሳምንት በኋላ ቤቱ በድኖ ሲያበድነኝ ለመፅናናት መፅሀፍ ቅዱሴን ገለጥኩ... የመጀመርያ ገፅ ላይ ብጣሽ ወረቀት ተቀምጣለች ደብዳቤውን አነበው ገባሁ...
የኔ ውድ ባል እባክህ አትዘንብኝ ህመሜን ላንተ ከነገርኩህ ቀድመከኝ ትሞታለህ።እየተደበቅኩህ ህክምና ስከታተል ነበር ግን አልሆነም ሞት ግድ ነው...ለኔ ህይወት ማለት ሳቅህን ማየት ነው ።መታመሜን አውቀህ ብሞት ኖሮ ሞቴ እረፍ ሳይሆን ስቃይ ነው!!እንባህን ማየት ሲኦልን የማየት ያህል ያስፈራኛል...
የኔ ውድ እኔ ብሞት እንኳ አለሁ ምክንያቱም አንተና ልጄ ሁለተኛ ነብሴ ናችሁ።እድሜ አጉድሎኝ ህይወትህን ስላጎደልኩብሽ ይቅር በለኝ...እንደገና 10ሬ ብፈጠር ማገባው አንተን ነው...የኔ ውድ ባል አደራ ራስህን አበርታ የሚል ነበር
በቃ ተለያየን
ደራሲ ቅድስት ቢቂላ ✍️
