ch
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

前往频道在 Telegram
1 064
订阅者
-224 小时
-77
+130
帖子存档
‹‹ዴሞክራሴያዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት›› #ዜና | የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሰልጣኝ ተማሪዎች ዴሞክራሴያዊ መግባባ ለህብረ ብሔራዊ አንድነት በሚል መሪ ቃል 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔርና ብሔረሰቦች ቀን አከበሩ፡፡ አገራችን ኢትዮጵያዊ በርካታ ብሔር እና ብሔረሰቦች በመቻቻል እና በመፈቃቀር በአንድነት አብረው ለዘመናት እየኖሩባት የምትገኝ ታላቅ አገር ነች።ትንሿ ኢትዮጵያ ከተማችን ድሬዳዋም ሁሉም ብሔሮችና ብሔረሰቦች ተከባብረውና ተዋደው የሚኖሩባት ለሌሎችም ከተሞች እንደ ሞዴል የምትታይ ከተማ ነች ያሉት በበዓሉ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ኢ/ኤ/ቴ/ሽግግር ም/ዲን የሆኑት ወይዘሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ ም/ዲኗ አያይዘውም ኮሌጃችን ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች እንዲሁም ከተለያዩ ብሄሮችና ብሔረሰቦች የተውጣጡ ሰልጣኞች ለስልጠና የሚመጡበት ኮሌጅ እንደ መሆኑ መጠን ሰልጣኞቻችንም ይህን የብሄሮች ስብጥር እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም አንዱ የሌላውን ባህል የሚማርበት እንዲሁም ቋንቋ፣ባህልና እሴቶቻቸውን የሚለዋወጡበት እንዲህ አይነት መድረኮች ያስፈልጉናል ብለዋል፡፡ በመጨረሻም ብሔርና ብሔረሰቦች ቀን ስናከብር ሁሉን አቅፋ የሰበሰበችንን ሀገራችንን ለመለወጥ በአንድነት ተግተን ልንሰራና አገራችንንም በጋራ በመሆን ለማሳደግ ቃል የምንገባበት ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡ በ1987 የፌዴራል ህገመንግስት የፀደቀበትን ቀን ምክንያት በማድረግ በየአመቱ የኢትዮጵያን ብሄሮች፣ብሄረሰቦች እና ህዘቦች ቀን በዓል ለ20ኛ ጊዜ እየተከበረ ይገኛል። ከዚህ ቀደም የኮሌጁ ማህበረሰብ አሰልጣኝ መምህራኖችና የአስተዳደር ሰራተኞች በጋራ በመሆን ማክበራቸው የሚታወስ ነው፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር 29/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ ለወቅታዊ ትኩስ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መረጃ You tube: Dire Dawa Polytechnic College(DDPTC) Facebook: https://web.facebook.com/Dire Dawa Polytechnic College Regional Flagship TVET Institute Telegram: t.me/Dire Dawa Polytechnic College TikTok: tiktok.com/@diredawapolytechnicollege Facebook (https://web.facebook.com/Dire)

#የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተማሪዎች የብሔር ብሔረሰቦች ቀን አከባበር
#የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተማሪዎች የብሔር ብሔረሰቦች ቀን አከባበር

ክቡር የአስተዳደራችን ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር፥ ከሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ጋር በመሆን፥ በድሬዳዋ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅ የሚገኘውን የምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ልህቀት ማዕከል 2ኛ ምዕራፍ የግንባታ ሂደት ጎብኝተዋል።

"በመደመር መንግስት እይታ፤ የዘርፎች እምርታ" በሚል መሪ ሀሳብ ትላንት የጀመረው 3ኛ ዙር የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክሀሎት ቢሮ ብልጽግና ህብረት የመንግስት ሰራተኞች የብልጽግና ፓርቲ አባልት ስልጠና ተጠናቀቀ። ትላንትና እና ዛሬ በቀረቡት በመደመር መንግስት የግብርና እና የኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን እንዲሁም የከተማ ልማትና የቱሪዝም እምርታዎች ዙሪያ የተዘጋጁ ሰነዶች ቀርበው ውይይት የተካሄደባቸው ሲሆን የፓርቲው አባላትም የተለያዩ ጥያቄዎችን አንስተው ከመድረክ ሰፋ ያለ ምላሽ እና ማብራሪያዎች ተሰጥቶባቸዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 27/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

"በመደመር መንግሥት እይታ፣ የዘርፎች እምርታ" በሚል መሪ ቃል የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ብልጽግና ህብረት 3ኛ ዙር የብልፅግና ፓርቲ አባላት ስልጠና መካሄድ ጀመረ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 26/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

"ተግዳሮቶችን በመቋቋም የኤች አይ ቪ ኤድስ ምላሽን በዘላቂነት እናረጋግጥ" በሚል መሪ ቃል በአለም ለ38ኛ ጊዜ በሀገራችን ለ37ኛ ጊዜ የሚከበረውን የዓለም ኤድስ ቀን የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች በፓናል ውይይት አከበሩ። በፓናል ውይይቱም የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭትን በመቆጣጠር ሂደት ተግዳሮቶችን በመለየት መቋቋም የሚያስችል የሚከሰቱትንም ቸግሮች መቅረፍ እንዲቻል ታላሚ ያደረገ ሲሆን ለዚህም ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትብብርና በሃላፊነት መስራት እንዳለባቸው ተመላክቷል፡፡ የኤች አይ ቪ ስርጭት አሁንም እጅግ አሳሳቢ በሆነ ደረጃ ላይ የሚገኝ መሆኑንና ከዚህም ጋር በተያያዘ በበሽታው የሚፈጠረው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና  ከፍተኛ መሆኑን ነው፤ በመሆኑም የፓናሉ ተሳታፊዎች በየአካባቢያቸው የሚመለከቷቸውን ለቫይረሱ ተጋላጭ የሚያደርጉ ጉዳዮችን አንስተዋል። በማጠቃለያውም ቢሮው በዋናነት ከወጣቶች ጋር የሚገናኝ እንደመሆኑ መጠን ተጋላጭነታቸውን በመቀነሱ ረገድ ከዋና ስራ ጎን ለጎን ትኩረት ተሰጥቶት ሊሰራ እንደሚገባ መግባባት ተፈጥሯል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 25/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በብራንዲንግ እና አድቨርታይዚንግ ላይ በድሬዳዋ አስተዳደር ለሚገኙ 30 ኢንተርፕራይዞች ስልጠና ተሰጠ፡፡ በስልጠናው ተሳታፊ የሆኑ ኢንተርፕራይዞች በአስተዳደሩ የሚገኙና ምርታማነታቸው እንዲሁም ከፍተኛ የማደግ አቅም እንዳላቸው የተመሰከረላቸው ሲሆኑ ምርትና አገልግሎታቸውን በዘመናዊና በተሻለ አቀራረብ በማዘጋጀት በአገር ዓቀፍ አልፎም በአለም ዓቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሆነው እንዲወጡ የሚያስችላቸውን ግንዛቤ እንዲጨብጡ አስችሏል፡፡ በዚህም የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ባህላቸውን እንዲያሳድጉና በዲጂታል ገበያው በተለይም ሉሲ ማርኬት ላይ ተቀላቅለው ተደራሽነታቸውን እንዲያሰፉ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ትኩረት ሰጥቶ ተከታታይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝና በቀጣይም አጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ሀ/ማርያም እና የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ አብራርተዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 25/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በእጀ ወርቆች የተመረተ ልዩ ልዩ ቦርሳዎችን፣ባህላዊና ዘመናዊ ልብሶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ታገኛላችሁ ምርቶቻችን 💼 በቆዳ ውጤቶች የተማሪ ቦርሳ፣የላፕቶፕ ቦርሳ፣የሴቶች ቦርሳ፣ዋሌት፣ቀበቶ 👗 በአልባሳት የሠራተኞች የደንብ ልብስ፣ጋውን፣የ ሰራተኞች ቱታ፣የባህል አልባሳት፣የስፖርት ቁምጣ እና ቲሸርት፣የህትመት ቲሸርቶች፣ስካርፕ እንዲሁም ዘመናዊ አልባሳትን በትእዛዝ እናመርታለን በቡድን ለሚመጡ ደንበኞች ልዩ ቅናሽ እናደርጋልን፡፡ጥራትና ቅልጥፍና መለያች ነው ይምጡ ይዘዙን አድራሻችን ከድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ወደ ኤርፖርት በሚወስደው መንገድ 150 ሜትር ላይ እንገኛለን

ኤስ.ኦ.ኤስ ወጣቶችን በተለያዩ ፕሮጀክቶች በማቀፍ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያደርግ የአምስት ዓመት ፕሮጀክት ሊተገብር ነው ። ግሪን ግሮውዝ - ወጣቱን ለብሩህ መፃሄ ማብቃት("Green Growth - Empowering Youth for a green future") የተባለውን ፕሮጀክት ስራ ለማስጀመር ኤስ ኦ ኤስ ( sos ) ህጻናት መንደር ከባድርሻ አካላት ጋር ውይይት አድርጓል። ግሪን ግሮውዝ ከ 2ሺ400 በላይ ወጣቶችን የስራ ዕድል ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮጀክት የስራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በፕሮጀክት ውይይቱ ላይ እንደገለጹት እንደ ግሪን ግሮውዝ ያሉ በተለይ ወጣቶችን የስራ ዕድል ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶች እንደ አስተዳደር ከፍተኛ የሆነውን የወጣት ሥራ አጥነት ቁጥር የሚያቃለሉ ናቸው። ኤስ ኦ ኤስ ህፃናት መንደር ከዚህ በፊትም መሰል ፕሮጀክቶችን በመቅረፅ ከቢሮው ጋር መስራታቸውን አስታውሰው አሁንም ቢሮው በፕሮጀክቱ የሚታቀፉትን ከ 2ሺ 4 መቶ በላይ ወጣቶችን በቴክኒክና ሞያ ኮሌጅ በሞያና በክህሎት በማስልጠን የስራ ምችችት በማድረግ ከsos ( ኤስ ኦ ኤስ ) ህጻናት መንደር ጋር ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል ። የኤስ ኦ ኤስ (sos) ህጻናት መንደር የድሬዳዋ ቅርንጫፍ የፕሮጀክቶች አስተባባሪ አቶ ሚካኤል ስንታየሁ እንደገለጹት ወጣቶችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ በማድረግ መጪ ጊዜያቸውን ብሩህ ለማድረግ የሚተገበረው ፕሮጀክት ለአምስት ዓመታት የሚቆይ ነው። ፕሮጀክቱንም ተግባራዊ ለማድረግ ቀደም ሲል ከባለድርሻ አካላት ጋር የመግባቢያና የትብብር ፊርማ መፈራረም መቻሉን ጠቁመዋል። ከፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ወጣቶች መካከል 60 በመቶው ሴቶች እንደሚሆኑ የተገለጸ ሲሆን አካል ጉዳተኞች ደግሞ 5 በመቶ የተጠቃሚነት ድርሻ እንደሚኖራቸው ነው የታወቀው። በማስጀመሪያ መድረኩ ላይ ከዚህ በፊት በጥናት የተሰሩ ፕሮጀክቶች ተሞክሮ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። ©️ DireTvአማርኛ | ህዳር 25 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ