1 092
订阅者
+324 小时
+247 天
+2030 天
帖子存档
የዜጎችችን ተጠቃሚነት መሰረት ያደረጉ ተግባራትን በቅንጅት ለመስራት ጥረት ይደረጋል
''አቶ ሮቤል ጌታቸው የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ሃላፊ''
የድሬደዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የ2015 ዓም ሪፓርት እና የ2016 ዓም ረቂቅ ዕቅድ ላይ ከሰራተኞችና ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል
በውይይት መድረኩ የቢሮው ሃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በ2015 በጀት አመት እንደ ቢሮ ጠንካራ አደረጃጀት እንዲኖር እንዲሁም በተቀናጀ እቅድ ለመመራት የተደረገው ጥረት በጠንካራ ጎን የሚጠቀስ መሆኑን ጠቁመዋል።
ቢሮው በ2015 ዓም የስራ ዘመን የሚከናወኑ ተግባራትን እቅድ ከፈፃሚ ባለሞያዎች እንዲሁም ከዘርፉ ጋር በቀጥታ ከሚገናኙ ባለድርሻ አካላት ጋር ሰፊ ውይይት አድርጎ ወደ ተግባር መግባቱን አውስተው በስሩ ባሉ የስራ መስኮች በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤት መመዝገባቸውን ገልፀዋል ።ከዚህ ውስጥ በፌደራል ደረጃ ጭምር እውቅና ያገኙ ብሎም እንደ ተሞክሮ የሚጠቀሱ አፈፃፀሞች መኖራቸውን አቶ ሮቤል አብራርተዋል።
በመድረኩ የተጠናቀቀው በጀት አመት እቅድ አፋፃፀም ሪፖርት እንዲሁም የቀጣዩ በጀት አመት እረቂቅ እቅድ ቀርቦ በባለሙያዎች ባለድርሻ አካላት ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል በዚህም በዘርፉ የዲጂታላይዜሽን ስራን ማጎልበት÷የቢሮው እቅድ ከፌደራል እቅድ ጋር አጣጥሞ ማስኬድ÷ ከስራ እድል ፈጠራ እንዲሁም ከቴክኖሎጂ ልማት ጋር ተያይዞ የተጠናከረ ስራን ማከናወን እንደሚገባ ተመላክቷል።
ለስራ ውጤታማነት ወሳኝነት ያላቸውን የሰው ሃይልን ከማሟላትና ከሰው ሃይል ልማት ብሎም ከግብአት አቅርቦት ጋር ያሉ ክፍተቶች መቅረፍ ፣ ከቴክንኒክና ሙያ ዘርፍ አንፃር ከሃብት ማፈላለግና መጠቀም ጋር የተገኙ መልካም ውጤቶችን ማጠናከር እንደሚያስፈልግም ተገልፃል።
በገጠሩ የማህበረሰብ ክፍል የስራ እድል ፈጠራን ከማስፋፋት አኳያ ከሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀናጅቶ የመስራት ፣ በአጫጭር ስልጠና ለገጠሩ ወጣትና ማህበረሰብ የሰራ ክህሎትና የስራ ሞያብቃትን ማሻሻል የሚያስችሉ ተግባራት መታቀድ እነደሚገባቸውም ተጠቁሟል።
ከስራ እድል ፈጠራ ጋር ተያይዞ የመስሪያና የመሸጫ ቦታ ምችችት ማድረግ ፣የብድር ዋስትና ድጋፍ አሰጣጥን ቀልጣፋ አሰራር እንዲኖር ማድረግ በ2016 ዓም ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ ጉዳዮች ሊሆኑ እንደሚገባ በውይይቱ ተመላክቷል።
የስራላይ ደህንነትን በተመለከተ የሰራተኛ ደህንነትና ጤናን ለማስጠበቅ ጥብቅ የሆነ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንዲሁም ቀጣይነት ያለው ግንዛቤ መፍጠር ፣የፆታ ተሰትፎ እንዲዳብር ማድረግ፣ የህገወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል ከሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ መስራት እንደሚገባ የተገለፀ ሲሆን ተግባራት የለውጥ ስራዎችን መሰረት ያደረጉ ኢንዲሆኑ ማጠናከር ይገባል የሚሉ ሃሳብና አስተያየቶች በውይይቱ ተነስቷል።
በመድረኩ ለተነሱ ሃሳብና አስተያየቶች ማብራሪያ የሰጡት የቢሮ ሃላፊው አቶ ሮቤል ጌታቸው ውይይቱ የተለያዩ አካላት የተሳተፉበት መሆኑና ሰራተኛው የሚታዩ ክፍተቶችን በግልፅ አንስቶ መወያየት ያስቻለ በመሆኑ ውጤታማ ነው ብሎ መገምገም ይቻላል ብለዋል ።
የቢሮ ሃላፊው አክለውም ከስነ ምግባር ጋር ያሉ ችግሮችን ህጋዊ ማእቀፍን በተከተለ መንገድ የማያዳግም እርምጃ እንደሚወሰድ የገለፁ ሲሆን በጥቅሉ ህዝብን መሰረት ያደረጉ የህዝብን ጥቅም ማስጠበቅ የሚያስችሉ ስራዎች እንደሚከናወኑ አስረድተዋል።
በአጠቃላይ የስራ እድል ፈጣራን ማስፋት ፣ብቁ የሰለጠነ የሰው ሃይል ማፍራት፣ከስራ ስምሪት ደህንነትና የሞያ ብቃት ምዘና ማዘመን ብሎም ቀልጣፋና ግልፅ አሰራርን ማስፈን በ2016 በጀት አመት በይበልጥ ትኩረት እንደሚሰጠው አመላክተዋል።
©️ የድሬዳዋ መንግስት ኮምኒኬሽን
የ2015 ዓ.ም የስራ ዕድል ፈጠራ እንዲሁም "ብቃት" የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም የስራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሄደ፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በውስጡ ከሚገኙ ዘርፎች የስራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት አንዱ ሲሆን በዚህም የአስርና የአምስት ዓመት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ መነሻ በማድረግ ለዜጎች የስራ እድልን በመፍጠር አሁን ያለውን የሥራ አጥ ቁጥር ለመቀነስና የስራ ባህልን በማጎልበት የሚያስፈልጓቸውን የሙያና የክህሎት ስልጠናዎች ወስደውና ወደ ስራ እንዲሰማሩ በማመቻቸትና ራሳቸውን ከስራ አጥነት እንዲያላቅቁ በማድረግና በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡
በዚህም የሚመለከታቸው የቢሮው አመራርና ባለሙያዎች እንዲሁም የወረዳ ስራ ክህሎት ማስተባበሪያዎች በተገኙበት በ2015 በጀት አመት አጠቃላይ የስራ ዕድል ፈጠራ በተለይም በብቃት ፕሮግራም የተሰሩ ስራዎች አፈጻጸም ላይ ሁሉም የወረዳ አንድ ማዕከላት አፈጻጸማቸው ቀርቦ ሰፊ ውይይት በማድረግ በቀጣይ በአጭር እና በረጅም መሰራት በሚገባቸው ስራዎች ላይ መወያየትና መግባባት መፍጠር ተችሏል፡፡
በመድረኩም ላይ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በቢሮ እና በአንድ ማእከላቱ መናበብ የተሰሩ መልካም ስራዎችን አበረታተው በቀጣይ በተለይ የአካባቢ ፀጋዎችንና ዕድሎችን በየሴክተሩ የመለየት ሥራ በአስተዳደሩ ውስጥ በሶስቱ ዋና ዋና የስራ እድል የመፍጠሪያ የስራ ዘርፎች ማለትም በግብርና በኢንዱስትሪ እና በአገልግሎት ዘርፍ ስራ ፈላጊዎችን ከማሰማራት አንጻር የአካባቢ ጸጋ ናቸው ተብለው የታመነባቸውን የጸጋ አይነቶች እና የመስሪያ ቦታዎችን የመለየት ስራን አጠናክሮ በመስራት ተጨባጭ ስራዎችን መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
በተለይም ዋነኛ ችግር ሆኖ እየመጣ ያለውን የፋይናንስ እና የመስሪያ ቦታ ችግርን በፍጥነት መፍታት በጣም አስቸኳይ እንደሚሆንና ለዚህም ዘለቄታዊ መፍትሄ ለመስጠት የሚመለከታቸው የአስተዳደሩ ባለድርሻ አካላት አዳዲስ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥና የሚፈጠሩ የስራ እሎች ዘለቄታቸውን እና አስተመማኝነታቸውን ከማረጋገጥ አኳያ የየእለት ድጋፍ እና ክትትሎችን አጠናክሮ መቀጠል ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ በቢሮው የስራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አሚን አብዱላሂ ገልጸዋል፡፡
የስራ ክህሎትና ቴክሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 28/2015 ዓ.ም
ሐረር
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
