1 084
订阅者
+524 小时
+107 天
+530 天
帖子存档
#ዜና | የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ በገጠር ሥራ እድል ፈጠራ ዙሪያ ከቢዮ አዋሌ ወረዳ እና ቀበሌ አመራሮች ጋር የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት አካሄደ።
የውይይት መድረኩ የቢዮ አዋሌ ገጠር ወረዳ አመራሮችን ጨምሮ ከ12ቱም ቀበሌ አመራሮች የተውጣጡ ተሳታፊዎችን ያካተተ ሲሆን በወረዳው ያሉትን ፀጋዎች በመጠቀም የኑሮ ሁኔታቸውን ለማሻሻል የታለመ ነው።
ቢሮው ከ2016 ጀምሮ በከተማ ወረዳዎች ላይ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን አከናውኖ ብዙ ውጤት ተገኝቷል፤ በ2017 የአስተዳደሩን ገጠር አካባቢ በተመሳሳይ ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በክህሎት መር ሥራ እድል ፈጠራ አቅዶ ወደ ስራ ገብቷል።
የከተማ ሥራ እድል ፈጠራ ሲመራበት የነበረው ሂደት ከገጠሩ አሰራር ጋር ሲነፃፀር በተለይ የቴክኒክና ሙያን አጣምሮ የመሄድ ክፍተት የሚታይበት ሲሆን አሁን ላይ ወጣቶችን በማሰልጠን ባሉበት ወረዳዎች ወደ ስራ ለማስገባት እየተሰራ ይገኛል።
የሥራ እድል ፈጠራ እና የብድር ምችችት በከተማ ወረዳዎች ላይ በሰፊው ብዙዎችን ተጠቃሚ ሲያደርግ መቆየቱን የገለፁት የሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ በገጠሩም ክፍል ወጥነት ባለው ደንብና መመሪያ እንዲጓዝ መፅደቁን ጠቁመዋል።
አያይዘውም የመድረኩ አላማ ከብድር ምችችት ሂደት ስርዓት በፊት አመራሩ ሊይዝ የሚገባውን ግንዛቤዎች ለማጎልበት እንደሆነ ገልፀዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ የገጠር ሥራ ዕድል ፈጠራ እንቅስቃሴን ለማነቃቃት በሥራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ በቢዮ አዋሌ ወረዳ ያካሄደው የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት በተቀሩት ሶስቱ ወረዳዎች ላይ እንደሚቀጥል ለማወቅ ተችሏል።
©️ #Diretv አማርኛ ጥቅምት 27/2017
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ2017 ዓ.ም የስልጠና ዘመን አዲስ ለተቀበላቸው ሰልጣኞች የህይወት ክህሎት ስልጠና መስጠ ጀመረ::
አዲስ ገቢ ሰልጣኞቹ በቀጣዮቹ 3ቀናት የህይወት ክህሎት(Life skill )ስልጠናውን እየወሰዱ እንደሚቆዩ የተገለፀ ሲሆን ይህ ስልጠናም ሰልጣኞች የቀጣይ ህይወታቸውን በእቅድ እዲመሩ እንዲሁም ራሳቸውን ፈልገው እንዲያገኙና ሚገጥማቸውን የተለያዩ ፈተናዎች በራስ መተማመን እንዲወጡ የሚያስችላቸውን ልምድ የሚያገኙበት ስልጠና ጭምር መሆኑም ተነግሯል::
ሰልጣኞቹ ይህን ስልጠና አጠናቀው ሲጨርሱ በእስተዳደሩ የሚገኙ የተለያዩ ፋብሪካዎችንና ድርጅቶችን ተዘዋውረው የሚጎበኙ ሲሆን ይህም በተሻለ ግንዛቤና መነቃቃት መደበኛ ስልጠናቸውን እንዲጀምሩ የሚያደርጋቸውም ይሆናል::
ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ጥቅምት 26/2017 ዓ.ም
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል የሆነው የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በዘንድሮ አመት 12ኛ ክፍልን አጠናቃችሁ የቴክኒክና ሙያ ስልጠናን ለምትፈልጉ በሙሉ አንጋፋው ኮሌጃችን በ12 የሙያ መስኮች ትምህርትና ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል በዘንድሮ አመትም ምዝገባ ላይ እንደሚገኝ በደስታ ያበስራል፡፡ ከነዚህ ሞያዎች መካከል electrical electronics technology departmentን በጥቂቱ እናስቃኛችሁ!!!!
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል የሆነው የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በዘንድሮ አመት 12ኛ ክፍልን አጠናቃችሁ የቴክኒክና ሙያ ስልጠናን ለምትፈልጉ በሙሉ አንጋፋው ኮሌጃችን በ12 የሙያ መስኮች ትምህርትና ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል በዘንድሮ አመትም ምዝገባ ላይ እንደሚገኝ በደስታ ያበስራል፡፡ ከነዚህ ሞያዎች መካከል automotive technology departmentን በጥቂቱ እናስቃኛችሁ!!!!
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ2017ዓ.ም የስልጠና ዘመን አዲስ ለተቀበላቸው ሰልጣኝ ተማሪዎች ኦረንቴሽን በመስጠት የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል አደረገ::
ሰልጣኝ ተማሪዎቹን ለመቀበል በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ በመገኘት መድረኩን ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ በቅድሚያ አዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎችን በኮሌጁ ለመሰልጠን እዚህ በመገኘታቸው እንኳን ደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን ወቅቱ ሚጠይቀውን ምርጫ መርጣችሁ በቴክኒክና ሙያ ተቋማት ለመሰልጠን ዘርፉን በመቀላቀላችሁ እጅግ እድለኞች ናችሁና እንኳን ደስ አላችሁም ብለዋል::
የኮሌጁ ዲን ቀጥለውም እንዳሉት በኮሌጁ በተለያዩ ሙያዎች ለመሰልጠን እዚህ የተገኛችሁ ወጣቶች አሁን የምትገኙበት እድሜ በራሳችሁ ውሳኔ ምትወስኑበት እድሜ ነውና ትክክለኛውን መንገድ በመምረጥ የወጣትነት እድሚያችሁን በአግባቡ በመጠቀም ለቀጣይ ህይወታችሁ ፍሬ የምታፈሩበት ሊሆን እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል::
እሁን ላይ የቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ራሱን ችሎ እስከ ከፍተኛው የትምህርት እርከን ድርስ ማሰልጠን እንደጀመረ የገለፁት የኮሌጁ ዲን አንድ ሰልጣኝ ከታች ከ ደረጃ 1(ሰርተፊኬት) ጀምሮ እራሱን እያሻሻለና እያበቃ እስከ ደረጃ 8(ዶክትሬት) ድረስ መድረስ እንደሚችልና መንገዱም የተመቻቸ መሆኑን ለሰልጣኞቹ ገልፀው ሰልጣኞችም ህንን ትልቅ አጋጣሚ በመጠቀም ለራሳቸውም ብሎም ለሀገራቸው የሚጠቅሙ ብቁ ዜጋ መሆን እንደሚጠበቅባቸው አፅዕኖት ሰተው ተናግረዋል::
የኮሌጁ ዲን በመጨረሻም በኮሌጁ የትኩረት ዘርፍ ተብለው የተያዙትና በዓለም ባንክ ፕሮጀክት ጭምር የሚደገፉ ሁለት ዘርፎች መኖራቸውን ገልፀው እነርሱም የማኑፋክቸሪንግ ዲፓርትመንት እና የኤክትሪካል/እሌክትሮኒክስ ዲፓርትመንት ናቸው ያሉ ሲሆን በእነዚህ ሁለት ዘርፎች ውስጥ ያሉ ሙያዎችን ለመሰልጠን የመረጡ ሰልጣኞችም ከምንም በላይ እድለኞች ያረጋቸዋል ብለዋል::
በመጨረሻም ሰልጣኝ ተማሪዎች በኮሌጁ የሚኖራቸው ቆይታንና የትምህርትና ስልጠናው ሂደት ምን እንደሚመስል በዝርዝር ገለፃ የተደረገላቸው ሲሆን በተጨማሪም ስልጠናቸውን አጠናቀው እስኪወጡ ድረስ በኮሌጁ ውስጥ በሚኖራቸው ቆይታ ወቅት የተቀመጠላቸውን መብትና ግዴታዎች ከወዲሁ እንዲያውቋቸው በትምህርትና ስልጠና አስተባባሪው በኩል ሰፊ ገለፃና ማብራሪያ ተደርጎላቸዋል::
ሰልጣኝ ተማሪዎቹ በቀጣዮቹ 3ቀናት በኮሌጁ በሚኖራቸው ቆይታ የህይወት ክህሎት(Life Skill) ስልጠና የሚወስዱ ሲሆን እሱን እንዳጠናቀቁ የትብብር ስልጠና የሚወጡባቸውን የተለያዩ እንዱስትሪዎችና ተቋማትን እንዲጎበኙ መርሃ-ግብር መያዙም ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ጥቅምት 25/2017 ዓ.ም
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
በ2017 ዓ.ም በኮሌጁ ሊሰሩ በታቀዱ ቴክኖሎጂዎች ላይ የውይይት መድረክ ተካሄደ::
በመድረኩ አሰልጣኝ መምህራን በበጀት አመቱ ሊሰሯቸው ያቀዷቸውን የቴክኖሎጂ አርዕስቶች ለጥናትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ክፍል በግልና ቡድን ባስገቡት መሰረት ስለሚሰሩት ቴክኖሎጂ ዝርዝር ገለጻ አድርገዋል::
በተጨማሪም በዕለቱ በቀረቡት የቴክኖሎጂ አርዕስቶች ላይ ከሚመለከታቸው ዲፓርትመንቶች እና ከክፍሉ ባለሙያዎች እንዲሁም አሰልጣኝ መምህራን ጋር በመሆን ከማህበራዊ ጠቀሜታ፣ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ፣ከአካባቢ ደህንነት እና ከቴክኖሎጂ አንጻር ገንቢ አስተያየት ተሰጥቶባቸው ወደ ቀጣይ ስራ እንዲገቡም የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ጥቅምት 24/2017 ዓ.ም
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኤጀንሲ በ2017 ዓ.ም በአስተዳዳር ደረጃ ለሚደረገው የቴክኖሎጂ ውድድር በሁሉም ወረዳዎች በኢንተርፕራይዝ የተመዘገቡ ሆነው የቴክኖሎጂ ስራ ያላቸውና ለመወዳደር የሚፈልጉ ኢንተርፕራይዞችና አንቀሳቃሾች እስከ ህዳር 20/2017 ዓ.ም ድረስ ቴክኖሎጂ ክፍል በአካል በመቅረብ ምዝገባ እንድታደርጉ እያሳወቅን የመ/ቤቱ አድራሻ ቢ-ካፒታል ሆቴል ጎን መሆኑን እናሳውቃለን ፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ
#ዜና | በሀገራችን የተንሰራፋውን ስራ አጥነት ለመቀነስ በሚደረገው ጥረት አጫጭር ስልጠናዎች ትልቅ ሚና እንዳላቸው ተገለፀ።
#Diretv አማርኛ ጥቅምት 24/2017
የአሰሊሶ ክላስተር በተለያዩ የሞያ ዘርፎች ላሰለጠናቸው ወጣቶች እውቅና ሰጥቷል።
ስልጠናው በምግብና በምግብ ነክ እንዲሁም በእንጨት ስራና በሌሎችም ሞያ ላይ ያተኮረ ሲሆን ያገኙትም የሞያ ስልጠና ለሶስት ወራት ያህል በአግባቡ በመውሰድ ላጠናቀቁ ለሰላሳ ወጣቶችም እውቅና ተሰጥቷል።
የአሰሊሶ ክላስተር ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አብዲ አብደላ ስራ አጥነትን በሀገራችን ለመቀነስ በተለያዩ የሞያ ዘርፎች የሚሰጡ ስልጠናዎች ወሳኝ መሆናቸውን ገልፀው ታዲያ በተለያዩ ጊዜዎች በምችችት የሚመጡ አጭጭር ስልጠናዎችን ወጣቶች እንዲጠቀሙበት ጥሪ አስተላልፈዋል።
ዛሬ በአሰሊሶ ክላስተር የወሰዱትን ስልጠና አጠናቀው እውቅና የተሰጣቸው ሰልጣኞች ወደ ስራ ለማሰማራት ሁኔታዎችን የማመቻቸት ስራዎች እንደሚሰሩም የገለጹት አቶ አብዲ ይህም ለሌሎች ወጣቶች መነቃቃት የሚፈጥር ነው ብለዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው አያይዘውም ይህን የአጭር ጊዜ ስልጠና እንዲያገኙ ከክላስተሩ ጋር በትብብር የሰሩትን አካላት ማለትም ወሊፍ በጎ አድራጎት ፣ የሥራና ክህሎት ቢሮን አመስግነዋል።
የአጭር ጊዜ ስልጠናውን የወሰዱ ወጣቶችም በቀሰሙት የሞያ ትምህርት ራሳቸው ለመለወጥ ጠንክረው እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።
©️ Dire Tv አማርኛ
በድሬዳዋ የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች ላይ የሚሰሩ የውጭ አገር ዜግነት ያላቸው ሰራተኞች ህጋዊነት የሚያረጋግጥ የቁጥጥር ስራ መሰራቱ ተገለጸ፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት በአዋጅ በተሰጠው ስልጣንና ኃላፊነት በአስተዳደሩ በሚገኙ ኢንደስትሪዎችና የግል ድርጅቶች ውስጥ በተለያዩ የሥራ መደብ ላይ ተቀጥረው የሚሠሩ የውጭ አገር ዜጎች ላይ ቁጥጥር አደረገ።
በዚህም መሰረት በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች ህጉን ተከትለው እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ማረጋገጥ ዋና አላማው ያደረገው ይህ ቁጥጥር አዋጅ ቁጥር 1156/2011 በአግባቡ ተፈጻሚነት፤ ወቅቱን ጠብቆ የታደሰ የመኖሪያ ፈቃድ መኖሩን፤ የፓስፖርት እና የስራ ፈቃድ እንዳላቸው፤ ለአገራችን ዜጎች በተገቢ መልኩ የእውቀት ሽግግር እያደረጉ መሆኑን እንዲሁም በሚሰሩበት ክልል/አስተዳደር ላይ የሥራ ግብር እየከፈሉ መሆኑን የማረጋገጥ ስራ ተሰርቷል፡፡
የአሰሪና ሰራተኛ ዘርፉን የሚመሩት አቶ መሀመድ ኢብራሂም ዜጎች ወደ ውጭ አገራት በመሄድ የመስራት መብት እንዳላቸው ሁሉ የውጭ አገራት ዜጎችም ወደ አገራችን በመምጣት በተለያዩ የሥራ መስኮች ላይ የመሥራት መብት እንዳላቸውና ሲሰሩ ሀገሪቱ ባጸደቀቻቸው የአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 መሠረት ተገቢውን ፎርማሊቲ እንዲያሟሉ የሚጠበቅ(የሚገደዱ) መሆኑን ገልጸዋል፤
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 21/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 በጀት አመት እቅድ እና የዝግጁነት ምዕራፍ አፈፃፀም ሪፖርት በተመለከተ የኮሌጁ ማህበረሰብ በተገኘበት የውይይት መድረክ አካሂዷል።
በመድረኩ በቅድሚያ በኮሌጁ የዝግጁነት ምዕራፍ ወቅት የተሰሩ ስራዎች አፈፃፀም የቀረበ ሲሆን በዋነኛነትም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የአለም አቀፍ የጥራት ደረጃ የሆነውን የISO 9001:2015 የጥራት አስተዳደር ስርዓት እውቅና ያገኘበትን የላቀ ትግበራ ያከናወነበት ምዕራፍም ነበር::
በተጨማሪም በዝግጁነት ምዕራፍ ወቅት እንደ ተቋም የ2017 በጀት ዓመት እቅድ ከዋና ስራ ሂደቶች ጀምሮ እስከ ፈፃሚው ድረስ የጠራ እቅድ ዝግጅት የተከናወነበት ወቅት ሲሆን እንዲሁም የአረንጏዴ አሻራ፣የደም ልገሳን ጨምሮ የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስና መሰል ትግበራዎችም በዝግጁነት ምዕራፍ ወቅት እንደተከናወኑ ለኮሌጁ ማህበረሰብ ሪፖርት ቀርቧል::
በመጨረሻም የ2017 በጀት ዓመት መሪ እቅድ ለኮሌጁ ማህበረሰብ የቀረበ ሲሆን የቀረበውን እቅድ መነሻ በማድረግም ከመድረኩ ተሳታፊዎች ሀሳብ ተሰቶበት ሰፋ ያለ ውይይትም ተደርጎበታል::
በማጠቃለያውም በተጠናቀቀው በጀት አመት የታዩ ጠንካራ አፈፃፀሞችን በማስቀጠል እንዲሁም በ2017 በጀት አመት የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ በጋራ መረባረብ እንደሚገባ ተገልፆ መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ጥቅምት 21/2017 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
