1 084
订阅者
+524 小时
+107 天
+530 天
帖子存档
በአጫጭር ስልጠና ዘርፍ በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ለሚሰጡ ተቋማት የ2017 ዓ.ም በዝግጅት ምዕራፍ የትምህርትና ስልጠና ተቋማቱን አቅም ለመገንባት ያለመ የክትትልና ድጋፍ መርሃግብር ተካሄደ፤
በዚህም የድጋፍና ክትትል መርሃግብር የአጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት በዕቅድ መሠረት ስለመመራታቸው፤ በቂ የስልጠና ግብዓት ስለመኖሩ፤ የስልጠና ፍቃድ በተመለከተ በተሰጠው ፈቃድ ልክ እየሰሩ ስለ መሆናቸውና እንዲሁም የማሰልጠኛ ማንዋሎችና መሳሪያዎች በሚገባ መኖራቸውን ጨምሮ የአጠቃላይ ሰልጣኞችን መረጃ በማደራጀት እረገድ ያሉበትን ሁኔታ ለመመልከትና በቀጣይ በተከታታይ ድጋፍ የሚያገኙበትን አግባብ ለማመቻቸት ተችሏል፡፡
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደም እንደተናገሩት ይህ የድጋፍና ክትትል ልክ መደበኛ ስልጠና እንደሚሰጡ ተቋማት ሁሉ አጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማትም ዜጎችን በማሰልጠን የሚያበቁ ናቸው ስለሆነም ትምህርትና ስልጠና ተቋማቱን አቅም ለመገንባትና በቅርበት በመከታተል መደገፍ አላማው አድርጎ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 15/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በአጫጭር ስልጠና ዘርፍ በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ለሚሰጡ ተቋማት የ2017 ዓ.ም በዝግጅት ምዕራፍ የትምህርትና ስልጠና ተቋማቱን አቅም ለመገንባት ያለመ የክትትልና ድጋፍ መርሃግብር ተካሄደ፤
በዚህም የድጋፍና ክትትል መርሃግብር የአጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት በዕቅድ መሠረት ስለመመራታቸው፤ በቂ የስልጠና ግብዓት ስለመኖሩ፤ የስልጠና ፍቃድ በተመለከተ በተሰጠው ፈቃድ ልክ እየሰሩ ስለ መሆናቸውና እንዲሁም የማሰልጠኛ ማንዋሎችና መሳሪያዎች በሚገባ መኖራቸውን ጨምሮ የአጠቃላይ ሰልጣኞችን መረጃ በማደራጀት እረገድ ያሉበትን ሁኔታ ለመመልከትና በቀጣይ በተከታታይ ድጋፍ የሚያገኙበትን አግባብ ለማመቻቸት ተችሏል፡፡
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደም እንደተናገሩት ይህ የድጋፍና ክትትል ልክ መደበኛ ስልጠና እንደሚሰጡ ተቋማት ሁሉ አጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማትም ዜጎችን በማሰልጠን የሚያበቁ ናቸው ስለሆነም ትምህርትና ስልጠና ተቋማቱን አቅም ለመገንባትና በቅርበት በመከታተል መደገፍ አላማው አድርጎ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 15/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በአጫጭር ስልጠና ዘርፍ በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ለሚሰጡ ተቋማት የ2017 ዓ.ም በዝግጅት ምዕራፍ የትምህርትና ስልጠና ተቋማቱን አቅም ለመገንባት ያለመ የክትትልና ድጋፍ መርሃግብር ተካሄደ፤
በዚህም የድጋፍና ክትትል መርሃግብር የአጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት በዕቅድ መሠረት ስለመመራታቸው፤ በቂ የስልጠና ግብዓት ስለመኖሩ፤ የስልጠና ፍቃድ በተመለከተ በተሰጠው ፈቃድ ልክ እየሰሩ ስለ መሆናቸውና እንዲሁም የማሰልጠኛ ማንዋሎችና መሳሪያዎች በሚገባ መኖራቸውን ጨምሮ የአጠቃላይ ሰልጣኞችን መረጃ በማደራጀት እረገድ ያሉበትን ሁኔታ ለመመልከትና በቀጣይ በተከታታይ ድጋፍ የሚያገኙበትን አግባብ ለማመቻቸት ተችሏል፡፡
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደም እንደተናገሩት ይህ የድጋፍና ክትትል ልክ መደበኛ ስልጠና እንደሚሰጡ ተቋማት ሁሉ አጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማትም ዜጎችን በማሰልጠን የሚያበቁ ናቸው ስለሆነም ትምህርትና ስልጠና ተቋማቱን አቅም ለመገንባትና በቅርበት በመከታተል መደገፍ አላማው አድርጎ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 15/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
ማሳሰቢያ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተግባራዊ እያደረገ ያለው የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት መነሻና መዳረሻው የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ነው፡፡
በዘርፉ ባለፉት ሦስት ተከታታይ ዓመታት በተሰራው ጠንካራ የሪፎርም ሥራ በቴክኖሎጂ ጭምር በመታገዝ ህብረተሰቡን ካላስፈላጊ ወጪና እንግልት በመታደግ በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡ ይህ ሥራ አሁንም ተጠናክሮ እየቀጠለ ይገኛል፡፡
ነገር ግን ስምሪቱን በተመለከተ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ስምና አርማ እንዲሁም የከፍተኛ አመራሩን ስምና ምስል ጭምር በመጠቀም የተለያዩ ማስታወቂያዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በሕገወጦች በመዘዋወር ላይ ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ማስታወቂያዎች ሀሰተኛ መሆናቸው ታውቆ ሁሉም ላላስፈላጊ ወጪና እንግልት እንዳይዳረግ ጥንቃቄ እንዲያደረግ እናሳስባለን፡፡
የሥራ ስምሪቱን በተመለከተ አዳዲስ ነገሮች ሲኖሩ የተቋማችንን ይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያ ትስስርን ጨምሮ በሁሉም የሚደያ አማራጮች የምናሳውቅ ይሆናል፡፡
በሥራ ስምሪቱ ተጠቃሚ ለመሆን የሚፈልግ ማንኛው ሰው በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ (https://lmis.gov.et/auth) እንዲመዘገብ እና ህጋዊ አማራጮችን ብቻ በመጠቀም ደህንነቱ የተረጋገጠ የሥራ ስምሪት ተጠቃሚ እንዲሆኑ በድጋሜ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ
መስከረም 14/2017
በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE
ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols
ዋትስአፕ፡- https://whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y
ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+9
ብቃት እና ክህሎትን በመላበስ አደጋን ተከላክሎ ማሽከርከር ሚችል አሽከርካሪን ለማፍራት ትኩረት ሰቶ እየሰራ እንሚገኝ የድሬደዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አስታወቀ።
ኮሌጁ በማሽከርከር ሙያ ላይ ለሚገኙ አሽከርካሪዎች የመካኒክ አሽከርካሪ ስልጠና መስጠት ጀምሯል።
ስልጠናው በማሽከርከር ሙያ ላይ ያሉ አሽከርካሪዎች ያላቸውን ሞያዊ ክህሎት በማዳበር በሚያሽከረክሩ ጊዜ አደጋን ተከላክሎ እና የተሽከርካሪውን ፀባይ ተረድቶ ለማሽከርከር የሚያግዛቸውን መሰረታዊ ስልጠና ለመስጠት ታስቦ መዘጋጀቱ ነው የተጠቆመው።
በዚሁ ስልጠና ማስጀመሪያ ላይ የተገኙት የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን ኮሌጁ ከድሬደዋ ትራንስፖርት እና ሎጂስቲከስ ባለስልጣን እውቅናን በመውሰድ በማሽከርከር ሙያ አዳዲስ አሽከርካሪዎችን ባማፍራት ላይ እንዳለ አስታውሰው ይህንኑ በማሳደግ በአዲስ አበባ ብቻ ይሰጥ የነበረውን የአሽከርካሪ መካኒክ ስልጠና በሙያው ላይ ለሚገኙ መንጃፍቃድ ለያዙ ሹፌሮች ሙያቸውን የሚያዳብሩበት እና ዘመን የፈጠረውን የማሽከርከር ጥበብ እና የተሽከርካሪዎች ባህሪን ሚረዱበት ቀድሞ የተማሩበትን ማስታወሻ እንዲሁም ቀለል ያሉ የተሽከርካሪ ብልሽቶችን በራሳቸው መጠገን ሚያስችላቸውን አቅም ሚፈጥሩበትን ሙያ ለማስተማር ስልጠናው መዘጋጀቱን ጠቁመው ሰልጣኞችም ክህሎቱን ባግባቡ በመጨበጥ ብቁ አሽከርካሪ ለመሆን እንዲተጉ መልእክት አስተላልፈዋል።
ስልጠናው 110 ሰአት የሚሸፍን ሲሆን በዚህም የህይወት ክህሎት ቀላል የተባሉ የተሽከርካሪ ጥገና እንደሁም ያለፉ ትምህርቶቻቸውን ከአዲሱ አጣምሮ ሚያስገነዝቡ ስልጠናዎች ተካተውበታል።
በስልጠናው በመጀመሪያ ዙር 43 ተማሪዎች እየተከታተሉ ሲሆን በቀጣይ ሁሉም አሽከርካሪ በዚህ ስልጠና እንዲያልፍ በአነስተኛ ዋጋ ክህሎቱ እንደሚሰጠው ከአስተባባሪዎቹ ለመረዳት ተችሏል።
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ለ2017 የትምህርት ዘመን ለአቅመ ደካማ ተማሪዎች የሚሆን የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ ለአስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ አስረከበ።
በዛሬው ዕለት የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ እና በቢሮው የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ የሆኑት ክብርት ፈጡም መስጠፋ አማካኝነት ከአንድ መቶ በላይ ለሚሆኑ አቅመ ደካማ ቤተሰብ ተማሪዎች የትምህርት መርጃ ቁሳቁሶች ማለትም ደብተር ፣ ብዕር ፣ እርሳስ ለትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ለአቶ አቡበከር አዶሽ የድጋፍ ስጦታውን አስረክበዋል።
ክብርት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ የሥራና ክህሎት ቢሮ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ዘርፈ ብዙ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው ከዚህም ውስጥ ለቅመ ደካማ ወገኖች ቤት እንደ አዲስ መስራት፣ ዝቅተኛ ደሞዝ ላላቸው የቢሮው ሰራተኞች ቀጥተኛ የገንዘብ ድጋፍ እንዲሁም የደም ልገሳ መርሃ ግብሮች መከናወናቸውን አስታውሰዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ በትምህርት ቢሮ በመገኘት ላደረጉት ድጋፍ የትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አቡበከር አዶሽ ምስጋናቸውን በራሳቸውና በቢሮው ስም ያቀረቀረቡ ሲሆን በዚህ ተግባር ላይ ሁሉም ተሳታፊ በመሆን ለትውልድ ግንባታ የላቀ ኃላፊነታችንን በመወጣት አሻራችንን እናሳርፍ ሲሉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት (ዘገባ)
የትምህርት ቢሮ የህዝብ ግንኙነት (ፎቶ)
መስከረም 10/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ለ2017 የትምህርት ዘመን ለአቅመ ደካማ ተማሪዎች የሚሆን የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ ለአስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ አስረከበ።
በዛሬው ዕለት የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ እና በቢሮው የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ የሆኑት ክብርት ፈጡም መስጠፋ አማካኝነት ከአንድ መቶ በላይ ለሚሆኑ አቅመ ደካማ ቤተሰብ ተማሪዎች የትምህርት መርጃ ቁሳቁሶች ማለትም ደብተር ፣ ብዕር ፣ እርሳስ ለትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ለአቶ አቡበከር አዶሽ የድጋፍ ስጦታውን አስረክበዋል።
ክብርት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ የሥራና ክህሎት ቢሮ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ዘርፈ ብዙ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው ከዚህም ውስጥ ለቅመ ደካማ ወገኖች ቤት እንደ አዲስ መስራት፣ ዝቅተኛ ደሞዝ ላላቸው የቢሮው ሰራተኞች ቀጥተኛ የጀንዘብ ድጋፍ እንዲሁም የደም ልገሳ መርሃ ግብሮች መከናወናቸውን አስታውሰዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ በትምህርት ቢሮ በመገኘት ላደረጉት ድጋፍ የትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አቡበከር አዶሽ ምስጋናቸውን በራሳቸውና በቢሮው ስም ያቀረቀረቡ ሲሆን በዚህ ተግባር ላይ ሁሉም ተሳታፊ በመሆን ለትውልድ ግንባታ የላቀ ኃላፊነታችንን በመወጣት አሻራችንን እናሳርፍ ሲሉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 10/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ በመመዝገብ ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ይሁኑ
#የድሬዳዋ_አስተዳደር_የሥራና_ክህሎት_ቢሮ_አመራሮችና_ሠራተኞች_ደም_ለገሱ
የተለያዩ የማህበራዊ ኃላፊነቶችን በመወጣት የአስተዳደሩ ነዋሪ ተቋም መሆኑን በተግባር እያሳየ የሚገኘው ቢሮው በዛሬው ዕለትም አመራሩ እና ሠራተኛው በጋራ በመሆን የደም ልገሳ ፕሮግራም አካሂደዋል፡፡
ቢሮው በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የቢሮውን ማህበረሰብ በማስተባበር በተለይም በ2017 ሰባት የአቅመ ደካማ ወገኖችን ቤት በአዲስ አስገንብቶ ለማስረከብ የወሰደውን አገራዊ የመረዳዳትና የመተጋገዝ ኃላፊነት በመወጣት ላይ ይገኛል።
በዚህም ቀድሞውን በተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎች ላይ በመሳተፍ የሚታወቀው ቢሮው በዛሬው ዕለትም በቢሮው ቅጥር ጊቢ በተካሄደ የደም ልገሳ መርሃግብር በተለያየ ምክንያት ደም ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ከሰብዓዊነት የመነጨ አጋርነቱን አሳይቷል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 7/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ለእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ፥ እንኳን ለ1499ኛው የነቢዩ መሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) የልደት በዓል 'መውሊድ' በሰላም አደረሳችሁ። #መልካምበዓል!
Hordoftoota amantaa Islaamaa Baga Ayaana Mooyluuda Nabi Muhamad (SAW) kan bara 1499ffaa isiniin gahe. #AyyaanaGaarii!
Muslimiinta waxan ugu hambalyaynayaa maalinta dhalashada farxadeed ee mowlidka 1499aad ee nabigeena maxamed. #SanadWanaagsan.
+1
እንኳን ለ2017 አዲስ አመት በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን !
መጪው ዓመት የሰላም፤ የጤና፤ ፍቅር፤ የብልፅግና፤ የደስታና ፍሰሃ ዘመን እንዲሆንልን እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ!
አዲሱ ዓመት በአስተዳደራችን የከተማውንና የገጠሩን ነዋሪ ፍትሃዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ "ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ" መርህን ተከትለን የተጣለብንን ሰው ተኮር ተልዕኮ ከግብ ለማድረስ ቃልኪዳናችንን የምናድስበትና በትጋት ለመስራት ቁርጠኝነታችንን በቃልም በተግባርም የምናሳይበት ይሆናል።
በዓሉ የሰላም የፍቅር የአንድነት፣ የወንድ
ማማችነትና የእህትማማችነት እንዲሆን እየተመኘሁ በድጋሚ እንኳን አደረሳቹህ እላለሁ፡፡
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት
ቢሮ ኃላፊ
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
ትናንት አልቋል። ዛሬም እየተገባደደ ነው። ነገ ግን ገና አልተነካም። ነገን ለመጠቀም ታድያ ዛሬ መሥራት አለብን።
ሕዳሴ ግድብ፤ የገበታ ለሀገርና የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች፤ መንገዶችና ግድቦች፤ የተቋም ግንባታ ሥራዎች፤ አረንጓዴ ዐሻራና ኢትዮጵያ ታምርት፤ የኮሪደር ልማትና የሌማት ትሩፋት ፤ ዲጂታል ኢትዮጵያ እና የትምህርት ቤት ምገባ፤ ሀገራዊ ምክክርና የሽግግር ፍትሕ፤ ሌሎችም.. ነገን የተሻለ ለማድረግ የምንሠራቸው ናቸው።
የነገው ትውልድ እጅግ የተሻለች ኢትዮጵያን እንደሚረከብ ርግጠኞች ነን። ለነገ ዛሬ እየሠራን ነውና።
Kaleessi dhumeera. Har'is xumuramaa jira. Bor garuu ammayyuu hin tuqamne. Boritti fayyadamuuf garuu har'a hojjechuu qabna.
Hidhi Haaromsaa, piroojektoonni Maaddiin Biyyaafiifi Maaddiin Dhalootaaf, daandiiwwaniifi hidhawwan, hojiileen ijaarsa dhaabbilee, Ashaaraa Magariisaafi Itoophiyaan Haa Hoomishtu, Misoomni Kooriidariifi Maaddii Guutuun, Itoophiyaa Dijitaalofteefi sooruun manneen barnootaa, Mariin Biyyaalessaafi Haqni Cehumsaa, kanbiroonis... bor kan wayyu akka ta'uuf hojiilee hojjennudha.
Dhaloonni borii Itoophiyaa baay'ee wayyitu akka dhaalu kan mirkanaa'edha. Boriif har'a waan hojjetaa jirruuf.
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የ2017 አዲሱን አመት ምክንያት በማድረግ አነስተኛ ደሞዝ ላላቸው የተቋሙ ሰራተኞች የፍጆታ ዕቃ መግዣ የገንዘብ ድጋፍ አደረገ።
በድጋፍ ማድረግ መርሃግብሩ ላይ የተገኙት የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደገለፁት ቢሮው ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በዚህ ክረምት የአቀመ ደካሞችን ቤት እያደሰ እንደሚገኝ አስታውሰው ይህ ለቢሮው ሰራተኞች የተደረገውም ድጋፍ ተቋማዊ ጤናማ መስተጋብርን የሚያጎለብት በመሆኑ መሰል ተግባራትን ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።
የቢሮ ኃላፊው ለ2017 ዓ.ም የኢትዮጵያውያን አዲስ አመት የእንኳን አደረሳችሁ መልካም ምኞታቸውንና መልክታቸውን አስተላልፈዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጳጉሜ 4/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
⚠️ ድሬዳዋ ውስጥ ከሆናችሁ ⚠️
ቢዝነስዎን ስኬታማ ለማድረግ እንደግፍዎታለን!
በ https://forms.gle/34U9fXkRmPxyZzsT6 ተመዝግበው ቦታዎን ያሲዙ።
🗓️ መስከረም 09, 2017 ዓ.ም
🕒 ከጠዋቱ 3:00 እስከ 7:00 ሰዓት
📍 በኤም ኤም ሆቴል (MM Hotel), ድሬዳዋ
የመስራት ስራ ፈጠራ ፕሮግራም Info Session ጥቅሙ ምንድን ነው?
- መስራት ምን እንደሆነና ቢዝነስዎትን እንዴት እንደሚደግፍ ያውቃሉ፣
- ፕሮግራሙን እንዴት መቀላቀል እንደሚቻል ያውቃሉ፣
- ስለሚሰጡት ድጋፎች እና ለሚኖርዎት ጥያቄ መልስ ያገኙበታል።
- በቴሌግራም ቦት በኩል ለሚሰጥ ሥልጠና መመዝገብ ይችላሉ።
#መስራት #ስራፈጠራ #MesiratEthiopia #Entrepreneurship #Opportunity #GPM #Mesirat
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ በአስተዳደሩ ስር ከሚገኙ የከተማ እና የገጠር አንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያ ማስተባበሪያ አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሁለት ወራት የስራ አፈጻጸም ላይ ውይይት ተደረገ፡፡
በዚህም የውይይት መድረክ ላይ ማዕከላቱ ያከናወኗቸውን ተግባራት ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን በቀጣይም በመናበብ የአስተዳደሩን ነዋሪ ተደራሽና ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን በተጨባጭ ለመስራት አስፈላጊውን ትኩረት በመስጠትና ወደኋላ የቀሩ ተግባራትን መፈጸም ቅድሚያ እንዲሰጥና የሚታይ ውጤትና ለውጥ ለማምጣት ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራና የድጋፍና ክትትል ሥርዓቱም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ገልጸዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጳጉሜ 4/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
