ch
Feedback
በወላይታ አከባቢ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ማህበር

በወላይታ አከባቢ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ማህበር

前往频道在 Telegram

እውነተኛ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ድምፅ!! በዚህ የቴሌግራም ቻናል የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ዶግማን፡ቀኖናን እና ትውፍትን የጠበቁ ስርዓተ አምልኮ ትምህቶች እና ዝማሬዎች ይቀርቡበታል!!!

显示更多
326
订阅者
无数据24 小时
无数据7 天
无数据30 天
帖子存档
#ታላቅ_መንፈሳዊ_ጉባኤ በወላይታ ሀ/ስብከት በቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ቤተክህነት ጦቂሳ ቅ/ኪዳነ ምህረት ቤ/ያን #በብዙ_ፈተና_ያለፈችው_ተአምረኛዋ_የጦቂሳ_ኪዳነ_ምህረት_ቤተክርስቲያ_ጥሪ!! ለጦቅሳ ቅ/ኪዳ
#ታላቅ_መንፈሳዊ_ጉባኤ በወላይታ ሀ/ስብከት በቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ቤተክህነት ጦቂሳ ቅ/ኪዳነ ምህረት ቤ/ያን #በብዙ_ፈተና_ያለፈችው_ተአምረኛዋ_የጦቂሳ_ኪዳነ_ምህረት_ቤተክርስቲያ_ጥሪ!! ለጦቅሳ ቅ/ኪዳነ ምህረት ምዕመናንና በአጠቃላይ በመላው ዓለም አቀፍ ላሉ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች በሙሉ ታላቅ ደስታ የሆነውን ድንቅ ታምር ታዩ ዘንድ በዕለቱ በቦታው በመገኘት ሁላችሁም እንዲትባረኩ በጦቅሳ በኪዳኔ ምህረት ስም ታላቅ ጥሪ ተደርጎላቿል!! ታህሳስ 14,2016 ዓ/ት #መቅረት_የለበት!!! #ሼር_በማድረግ_ለሁሉም_አጋሩ🙏 👉የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif 👉ልንኩን በመጫን የፈስ ቡክ ፔጃችንን ቤተሰብ ይሁኑ https://www.facebook.com/teka132 #followlikecommentandshare

የመንፈስ ቅዱስን ምግብን የጠገበ ፤ ከመጻሕፍት ኹሉ ትርጓሜያተ ድርሰትን ያሰባሰበ፤ ሃሌ ሉያ በሚል ምስጋና የኢትዮጵያ አገርን በጥዑም ማሕሌትና በማያምር ምስጋና ያስጌጠ፤ የመለኮት ቃልን በላይዋ ላይ
የመንፈስ ቅዱስን ምግብን የጠገበ ፤ ከመጻሕፍት ኹሉ ትርጓሜያተ ድርሰትን ያሰባሰበ፤ ሃሌ ሉያ በሚል ምስጋና የኢትዮጵያ አገርን በጥዑም ማሕሌትና በማያምር ምስጋና ያስጌጠ፤ የመለኮት ቃልን በላይዋ ላይ እንደ ንጹሕ የወርቅ ሻሻቴ ያፈሰሰ ለኾነ ለካህኑ ለቅዱስ ያሬድ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮጊስ ዘጋስጫ

🔔ከ125k ተከታዮች በላይ ያሉበት የወላይታ አከባቢ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ማህበር የተሰኘው የፈስቡክ ግሩፕ ስለተጠለፈብን በግሩፉ የሚለጠፉ መረጃዎች ከይኛ እንዳልሆነ እንዲታውቁ እናሳስባለን!!
🔔ከ125k ተከታዮች በላይ ያሉበት የወላይታ አከባቢ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ማህበር የተሰኘው የፈስቡክ ግሩፕ ስለተጠለፈብን በግሩፉ የሚለጠፉ መረጃዎች ከይኛ እንዳልሆነ እንዲታውቁ እናሳስባለን!!!

Wolqaama metuwa paaciya xooniida geeshshatusi

#በወላይታው ሀ/ ስብከት ኪንዶ ኮይሻ ወረዳ ቤተ ክህነት በሌ መንበረ ፀሐይ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ከተካኸደው ታላቅ መንፈሳዊ ጉባዔ በከፍል 💕🙏💕
+3
#በወላይታው ሀ/ ስብከት ኪንዶ ኮይሻ ወረዳ ቤተ ክህነት በሌ መንበረ ፀሐይ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ከተካኸደው ታላቅ መንፈሳዊ ጉባዔ በከፍል 💕🙏💕

#ሥላሴ የመመኪያ ዘውዳችን ነው። #ሥላሴ የክብር ልብሳችን ነው። #ሥላሴ ከጠላት ዲያብሎስ ጋር ስንዋጋ የጦርነት ልብሳችን ነው። #ሥላሴ በጠላታችን ላይ የአሸናፊነት ሰይፍ ነው። #ሥላሴ ለወገባችን የኃይል ትጥቅ ነው። #ሥላሴ በፊታችን መመኪያ ጋሻ ነው። #ሥላሴ ለእግሮቻችን ከመሰናክል የሚታደገን የብርሃን ጫማ ነው። #በሥላሴ ፊት ተጠግተን እንመሸጋለን። #በሥላሴ አምባ ላይ ተቀምጠን ከጠላታችን እንሰወራለን። #በሥላሴ አምባም ከሰማይ ከይሲ ሰይጣን ጠላትነት እንድናለን። #በሥሉስ_ቅዱስ ክንፈ ረድኤት ስንጠለል። የእግዚአብሔር መልዐክ በዙሪያችን ይሰፍራል። መጽሐፈ ሜላድ

#የዕርዳታ_ጥሪ ለእናንተ ለደጋግ ኢትዮጵያዊያን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ያን በጎፋ እና ባስኬቶ ሀ/ስብከት ከሳውላ ከተማ ፥ ከሳውላ ከተማ በ7 ኪሎ ሜተር ዕርቀት ላይ የሚገኘው የሱሳ አቡነ
#የዕርዳታ_ጥሪ ለእናንተ ለደጋግ ኢትዮጵያዊያን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ያን በጎፋ እና ባስኬቶ ሀ/ስብከት ከሳውላ ከተማ ፥ ከሳውላ ከተማ በ7 ኪሎ ሜተር ዕርቀት ላይ የሚገኘው የሱሳ አቡነ ተክለ ሐይማኖት ቤ/ያን ስሆን ታቦተ ሕጉ ከስር በፎቶ በሚትከለመቱት መቃኞ ውስጥ ነው ያለው።   በቤተክርስትያኗ በጣም ጥቅት ምዕመናኖች ናቸው ያሉና ሕንፃ ቤተክርስትያን እየተሰራ በአቅም ውስንነት በመንገድ ቆሟል😢😢  ስለዚህ በመላው ዓለም ያላችሁ ውድ የተዋህዶ ልጆች ሁላችንም ባለን አቅም ደግፈን የቤተክርስትያኑ ግንባታ እንዲቀጥልና በቶሎ እንድጠናቀቅ እንድንረባረብ በአቡነ ተክለሐይማኖት ስም ጥሪ እያቀረባ ይገኛሉ!!! ⭕ውድ የእግዝአብሔር ቤቸሰቦች ሁላችንም እጃችንን እንዘርጋ!!! ✅የባንክ አካውንት:-1000294080507 የሱካ አቡነ ተክለ ሐይማኖት ለበለጠ መረጃ ይህን ስልክ ቀጥር ተጠቀሙ👇 0921005345 0916758820 0926288175 #ሼር_በማድረግ_ለሁሉም_አጋሩ🙏 ⚡️የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ 👉👉 https://t.me/httplif👈👈 👉ልንኩን በመጫን የፈስ ቡክ ፔጃችንን ቤተሰብ ይሁኑ https://www.facebook.com/teka132

በወላይታው ሀገረ ስብከት ኪንዶ ኮይሻ ወረዳ ቤተ ክህነት በሌ መንበረ ፀሐይ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ጉባዔ በከፍል 💕🙏💕:: ሼር......
+2
በወላይታው ሀገረ ስብከት ኪንዶ ኮይሻ ወረዳ ቤተ ክህነት በሌ መንበረ ፀሐይ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ጉባዔ በከፍል 💕🙏💕:: ሼር......

🎤ታላቅ በሆነው እምነትሽ ታመንኩኝ ካለሽበት ገስግሼ መጣሁኝ እናቴ ክብርሽን አንግሼ ሆንኩኝ እንደ ሕፃን ታድሼ እናቴ ቅድስት አርሴማ ዝናሽ ለዓለም ተሰማ የሰማእቷ በረከቷ አይለየን 🎤 አሜን🙏

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ስድስት በዚህች ቀን ሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያኗ የከበረበትና የሥጋዋ ፍልሰት የሆነበት ፤ ከእርሷ ጋር የተገደሉ የሃያ ሰባ
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ስድስት በዚህች ቀን ሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያኗ የከበረበትና የሥጋዋ ፍልሰት የሆነበት ፤ ከእርሷ ጋር የተገደሉ የሃያ ሰባት ደናግልም የሥጋቸው ፍልሰት የሆነበት ነው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአማላጅነቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን።

“ እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት ኩነኔ የለባቸውም ፣ እንደ መንፈስ ፈቃድ እንጂ እንደ ሥጋ ፈቃድ አይመላለሱምና ” (ሮሜ 8፡1) በክርስቶስ ኢየሱስ መኖር ምን ማለት ነው? ➽ እርሱ እንደተመላለሰ መመላለስ ማለት ነው! በእርሱ እኖራለሁ የሚል ክርስቶስ እንደተመላለሰ ይመላለስ ዘንድ ይገባዋል" 1ዮሐ2:6 ፡፡ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ እንደሚነግረን በክርስቶስ ነው ያለሁት ኩነኔ ወይም ፍርድ የለብኝም የሚል አካል ክርስቶስ ኢየሱስ መድኃኒታችን እንደተመላለሰ ሊመላለስ ይገባዋል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ በሥጋዌ ወራት እንዴት ይመላለስ እንደነበር ለመረዳት አራቱን ወንጌላት ማንበብ በቂ ነው!! ➲ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር ህይወቱ በሥጋ ማርያም ተገልጦ ሳለ እንደሰውነቱ ሲፆም ሲጸልይ ሲሰግድ ሲመጸውት በኃጢአት እንኳ የሚከሰው ሳይኖር ንጹሕ ሆኖ እንደተመላለሰ በተሰጠን የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ልንኖር ይገባል !! በእርሱ እኖራለው ኩነኔ የለብኝም ብሎ መፎከር ሳይሆን በእርሱ ለመኖራችን ማረጋገጫ የሆነውን እርሱ እንደተመላለሰ በቸርነቱ ልንመላለስ ይገባል!! ➧ ቅዱስ ሥጋውን መብላት ክቡር ደሙን መጠጣት! ‹‹ሥጋዬን የሚበላ ደሜን የሚጠጣ በእኔ ይኖራል እኔም በእርሱ እኖራለው ››ዮሐ6፡ 56 ጌታችን ኢየሱስ በወንጌል ከእርሱ ጋር የምንኖርበትን መንገድ ሲነግረን " ሥጋዬን የበላ ደሜን የጠጣ" በማለት ነው፡፡ በክርስቶስ መኖር ማለት ሥጋውን መብላት ደሙን መጠጣት እንደሆነ ከጌታ ንግግር እንረዳለን፡፡ሥጋውን ሳይበሉ ደሙንም ሳይጠጡ እንዲሁ በክርስቶስ ነው ያለሁት ኩነኔ የለብኝም ቢሉ ራስን ማሞኘት ይሆናል፡፡ሥጋውና ደሙ ምን ማለት እንደሆነ ራሱ ጌታችነን በምሴተ ሐሙስ በአላዛር ቤት " ይህ ሥጋዬ ነው ይህ ደሜ ነው" ማቴ26: በማለት አስረድቷል፡፡ይህንም መነሻ በማድረግ በጌታ ቃል ሥጋውነን መብላት ደሙን መጠጣት ከእርሱ ጋረር መሆን ማለት እንደሆነ እንረዳለን!!ለዚህ ክብር ጌታ ያብቃን!አሜን!! በክርስቶስ ያመኑ ብቻ ያለ መልካም ምግባር እና ያለ ቅዱስ ቁርባን ኲነኔ ወይም ፍርድ የለባቸውም ማለት ሳይሆን በክርስቶስ አምነው እርሱ እንደተመላለሰ የሚመላለሱ ኲነኔ የለባቸውም ማለት ነው። ክርስቶስ በዚህ ምድር እኛን ለማዳን በሥጋ በተመላለሰበት ወራት ተጠምቋል ጾሞአል ሰግዷል ጸልዮአል ..... በተጨማሪም ቅዱስ ቁርባንን ሰጥቶናል ይህ ሁሉ እንዴት መመላለስ እንዳለብን እኛን ለማስተማር ነው ስለዚህ በክርስቶስ የሆኑት ኲነኔ የለባቸውም ማለት እሱን አምነው እሱ እንዳሳያቸው የሚመላለሱ ኲነኔ የለባቸውም ማለት እንጂ አምነው ግን ኃጢአት የሚሰሩ ኲነኔ የለባቸውም ማለት እንዳይደለ ልንረደ ይገባል !! ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በእርሱ እንድንኖር በጸጋው ይርዳን አሜን!!

በዓታ ለእግዘትነ ማሪያም በወላይታ ሀ/ስብከት በማዮ ደ/ም/በአዓታ ለማርያም ደብር እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ዓመታዊ ክብረ በዓል በደማቅ ተከብሮ ውሏል። ለአመቱ
+2
በዓታ ለእግዘትነ ማሪያም በወላይታ ሀ/ስብከት በማዮ ደ/ም/በአዓታ ለማርያም ደብር እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ዓመታዊ ክብረ በዓል በደማቅ ተከብሮ ውሏል። ለአመቱ በሰላም ታድርሰን💕🙏💕 #followlikecommentandshareሼር_በማድረግ_ለሁሉም_አጋሩ

እንኳን አደረሳችሁ 👉መልካም በዓል💕🙏💕
+1
እንኳን አደረሳችሁ 👉መልካም በዓል💕🙏💕

† በጾም ሦስት ነገሮችን ! " በጾም ሰዓታችሁ ጊዜም ይኹን በሌላ ጊዜ ሦስት ነገሮችን በሕሊናችሁ ትይዙ ዘንድ እንመክራችኋለን፡፡ እነርሱም 1. ክፉ ከመናገር መከልከልን ፣ 2. ማንንም ሰው እንደጠላት ከማየት መቆጠብንና 3. እንደልምድ አድርጋችሁ ከያዛችሁት መሐላ ትርቁ ዘንድ ! በአጨዳ ላይ ያለ ገበሬ እህሉን ከማሳው በአንዴ እንደማይሰበስብ ነገር ግን በጥቂት በጥቂቱ እንደሚሰበስብ ኹሉ እኛም እነዚህን ምክሮች ተግባራዊ በማድረግ በዚህ የጾም ወቅት ልንለማመዳቸው እና መልካም ልምዶቻችን ልናደርጋቸው ይገባናል፡፡ እንዲህ በማድረጋችንም በቀላሉ መንፈሳዊ ጥበብን ገንዘብ ማድረግ ይቻለናል፡፡ በዚህም ዓለም ሳለን መልካም ተስፋ ያለውን አዝመራ እናፈራለን። በሚመጣውም ዓለም በክርስቶስ ፊት ያለፍርሐት በደስታ ተሞልተን እንድንቆም ይረዱናል፡፡ ለዚህ የሚያበቃንን ጸጋ አግኝተን የክብሩ ወራሾች ያድርገን፡፡ " [ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ] ሼር በማድረግ ለሌሎች አጋሩ!!

በወላይታ ሀ/ ስብከት በዳሞት ጋሌ ወረዳ ቤተክህነት ውስጥ የሚገኘው አዴ ዳሞታ #ቅዱስ_ኤልያስ_ቤተክርስቲያን 4 አባወራዎች ብቻ ናቸው ያሉት በአከባቢው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ባለመኖሩ ብዙዎች ጠፍተዋል😢 በአሁን ሳት ብዝዎች አሁን እየተሰራ ያለው ህንፃ ቤ/ያን ተስፋ አድርገው የቤተክርስቲያኗን ማለቅ  እየጠበቁት ስለሆነ ሁላችንም ተረባርበን የማስፈፀም የሐይማኖታዊ ግዴታ አለብን!!! ስለሆነም በመላው ዓለም ላይ ያላችሁ ውድ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች በሙሉ አቅማችሁ የፈቀደው ለዝህች ቤ/ያን  በመስጠት የቅዱስ ኤልያስ በረከት እንዲታገኙ በቅዱስ ኤልያስ ስም እንጠይቃለን!!! «1000481955835» አዴ ዳሞታ ቅዱስ ኤልያስ ቤተክርስቲያን በጥር ወር ታቦተ ህጉን ለማስገባት ህንፃ ቤተክርስቲያኑን ለመጨረስ አግዙን እያሉ ይገኛሉ 🙏 #ሼር_በማድረግ_ለሁሉም_አጋሩ🙏 👉የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ 👉👉 https://t.me/httplif👈👈 👉ልንኩን በመጫን የፈስ ቡክ ፔጃችንን ቤተሰብ ይሁኑ https://www.facebook.com/teka132 #followlikecommentandshare

በወቅታወ ጉዳይ ዙሪያ ከቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ በስመአብ፣ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤ አሜን፡፡ በወቅታዊ ጉዳዮች ከቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ “ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ፥ ወይስ ጭንቀት፥ ወይስ ስደት፥ ወይስ ራብ፥ ወይስ ራቁትነት፥ ወይስ ፍርሃት፥ ወይስ ሰይፍ ነውን? ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን፥ እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን” ሮሜ 8፡35-36 ቤተ ክርስቲያን ልዩ ልዩ ጸዋትወ መከራን፣ ሞትንና ስደትን፣ የመቀበል ታሪኳ ዛሬ የተጀመረ ባይሆንም በአሁኑ ጊዜ የሰው ልጅ  ይኽንና መሰል መተኪያ የሌለው ሕይወት የሚያጠፋና ሥጋት ላይ የሚጥሉ ተፈጥሮአዊ፣ ሰብዓዊ ክብሩን የሚያራክስ ተግባራት እንዳይደገሙ ለማድረግ በሚጥርበት ዓለም ችግሩ በተለይም በሀገራችን እየተባባሰ መቀጠሉ እጅግ ያሳስበናል፡፡ በአርሲ ዞን በሹርካ ወረዳ ሶሌ ሚካኤል፣ በዲገሎ ማርያም፣ በሮቤ እንደቶ ደብረ ምጥማቅ ማርያም አብያተ ክርስቲያናት ላይ በተለያዩ ጊዜያት ሠላሳ ስድስት፣ እንዲሁም በሶሌዲገሉና ጢጆለቡ በተባሉ ቀበሌዎች ሃያ ስምንት ኦርቶዶክሳዊያን ከየቤታቸው ተለቅመው ሰማዕትነትን ሲቀበሉ ከእነዚህም ሰባቱ ሴቶችና ሃያ አንዱ ወንዶች ናቸው፡፡ በዚህ ጥቃት የሰባ ዓመት አዛውንትና የሃያ ስምንት ቀን ጨቅላ ሕጻናት ይገኛሉ፡፡ ከጥቂት ቀናት በፊትም በዲገሉ ማርያም ቤተክርስቲያን አምስት ምእመናን ሰማዕት ሲሆኑ የሦስት ምእመናን ቤት ተቃጥሏል። በሮቤ አንዲቶ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም አጥቢያ በዓለ ድንግል ማርያምን አክብረው በመመለስ ላይ የነበሩ ሦስት ኦርቶዶክሳዊያን ጨለማን ተገን ባደረጉ ገዳዮች ሰማዕትነት የተቀበሉ መሆኑን ከሀገረ ስብከቱ ሪፖርት ደርሶን ከሐዘናችን ገና ሳንጽናና ይባስ ብሎ በማዕከላዊ ጐንደር ሀገረ ስብከት የጐንደር ዓቢየ እግዚእ ኪዳነ ምሕረት የአቋቋም መምህር የሆኑት መምህር ፍሥሐ አለምነው ባልታወቀ ግለሰብ በድንጋይ ተወግረው መገደላቸው እና ኅዳር 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ከሌሊቱ 11፡00 ላይ የማዕከላዊ ጐንደር ዞን ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ የሆኑት በኲረትጉሃን ዘርዓዳዊት ኃይሉ ባልታወቁ ግለሰቦች በጥይት ተመተው መገደላቸው በእጅጉ ከማዘናችንም በላይ የጉዳዩን አሳሳቢነት የሚያረጋግጥ አድራጐት ሆኗል፡፡  በዚህ መግለጫ በቅርብ የተፈጸመውን ለማቅረብ ተሞከረ እንጅ ተመሳሳይ ግድያና፣ ስደት፣ የንብረት ውድመትና መፈናቀል የየዕለት ዜናችን ከሆነ ሰንብቷል፡፡ ለአብነትም ያህል በወለጋ፣ በጐንደር፣ በጐጃም፣ በወሎ፣ በሰሜን ሸዋ፣ በመሳሰሉት እየተፈጸመ ያለው ድርጊት መንግሥትና ሕገ መንግሥት ባለበት ሀገር፣ የውጭ ወራሪና ድንበር ተሻጋሪ ጠላት ሳይኖርብን፣ እርስ በርሳችን በምናደርገው መጠፋፋት፣ ሃይማኖት ተኮር ጥላቻዎች፣ የንፁሐን ሕይወት መቀጠፉና የሀገርን ሀብት መውደሙ እኛንም ሆነ በመላው ዓለም መፍቀሬ ሰብእ የሆኑ የሰብዓዊ ክብር አስጠባቂ ተቋማትን ሳይቀር ማሳዘኑ ቀጥሏል፡፡  ይህ ሁኔታ በታሪክ ከመመዝገቡ በላይ የዜጎች በሕይወት የመኖር፣ ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሶ የመሥራት፣ የአካልና የንብረት ደኅንነታቸው መጠበቅ፣ የሃይማኖትና የእምነት ነፃነት መከበር፤ የዜጎች ሁለንተናዊ ደኅንነት የመጠበቅና የማስጠበቅ ግዴታ ያለባቸውን አካላት በሙሉ በምድርም ሆነ በሰማይ ተጠያቂ የሚያደርግ ጉዳይ ነው፡፡ እየተፈጠረ ባለው አስከፊ መከራ፣ በጭካኔ የተሞላ ድርጊት፣ ኃላፊነትና ተጠያቂነት ማጣት የዜጎችን ሕይወት፣ አካልና ንብረት፣ የእምነት ተቋማትን፣ መተኪያ የሌላቸው የተፈጥሮና ሰው ሠራሽ ቅርሶችና መስሕቦችን ሲያወድም፣ በሀገር ሁለንተናዊ ደኅንነትና በሕዝቦች ትሥሥር ላይ የፈጠረው አለመተማመን በቀላሉ የማይመለስ አደጋ ነው፡፡  ይኽ እንደተጠበቀ ሆኖ ከተከሰተው ረሀብ፣ ድርቅ፣ የኑሮ ውድነትና ሥራ አጥነት በተጨማሪ በየቦታው በተፈጠሩ አለመረጋጋቶችና ግጭቶች ምክንያት በርካቶች ቀያቸውን ለቀው፣ መነኰሳት ገዳማትን ትተው ተሰደዋል፤ ወላድ እናቶች፣ ሕሙማንና አረጋውያን በሕክምና እጦት እያለቁ ነው፣ ሕፃናትና ወጣቶች ከጤናማ እድገትና ከትምህርት ገበታ ተደናቅፈዋል፣  በመሆኑም ፩. ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ከግጭትና ከጦርነት፣ ከርስ በርስ መገዳደል ወጥተው በውይይትና በምክክር፣ በኃላፊነትና በተጠያቂነት ስሜት የታላቋን ሀገር መልካም ስምና ክብር እንዲሁም የዜጎቿን ሁለንተናዊ ደኅንነት የመጠበቅና የማስጠበቅ ተግባር ቅድሚያ እንዲሰጡ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡   ፪. በቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ንፁሐን ምእመናንና ተቋማት ላይ ያተኮሩ ጥቃቶች  በአስቸኳይ እንዲቆሙ፣ መንግሥትና የሚመለከታችሁ ሁሉ ዋስትና እንድትሰጡ፣ ወንጀል ፈጻሚዎችም ለፍርድ እንዲቀርቡ፣ ድርጊቱንም መላው ዓለም እንዲያወግዘው ቋሚ ሲኖዶስ በአጽንዖት ይጠይቃል፡፡  ፫. ከቤተ ክርስቲያን አልፎ የሀገርና የዓለም ሀብት የሆኑ ቅዱሳን መካናት፣ እንደ ዝቋላ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፣ ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም፣ አሰቦት ደብረ ወገግ አቡነ ሳሙኤል ገዳም እና አካባቢው፣ ደብረ ሮሐ ቅዱስ ላሊበላ ገዳምና አካባቢው የመሳሰሉ ሁሉ ታላላቅ አድባራትና ገዳማት አደጋ የተጋረጠባቸው በመሆኑ ልዩ ጥበቃ እንዲደረግላቸው እናሳስባለን። ፬. በመጨረሻም በየቦታው የሚያጋጥሙ ተመሳሳይ ጥቃቶችን ለማስቀረት ይቻል ዘንድ የሚመለከታቸው አካላት ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት በመስጠት ለቅድመ ወንጀል መከላከል ሥራ ቅድሚያ በመስጠት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እያሳሰብን ለቅድመ ወንጀል መከላከል ሥራው መሳካትም  በየደረጃው ያላችሁ አህጉረ ስብከት የስጋት መረጃዎችን ለሚመለከተው ሁሉ በማሳወቅ ግዴታችሁን እንድትወጡ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡      ልዑል እግዚአብሔር አምላካችን ለሞቱት የተዋሕዶ ኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን አስበ ሰማእትታን እንዲከፍልልን፣ ለወገኖቻቸው ሁሉ መጽናናት እንዲሰጥልን፣ ስለስሙና ስለሰብዓዊ ማንነታቸው በመከራና ሥጋት ወስጥ ለሚገኙ ወገኖቻችን ሁሉ ጽናቱንና ብርታቱን እንዲሰጥልን፣ አጥፊዎችን እንዲገስጽልን፣ ስደትና አለመረጋጋትን እንዲያርቅልን፤ የሀገራችንን አንድነትና ሰላም፣ የቅድስት ቤተክርስቲያንን ሕልውና እንዲጠብቅልን የአምላካችን የልዑል እግዚአብሔር ቅዱስ ፈቃዱ ይሁንልን፡፡                 ወስብሐት ለእግዚአብሔር