ch
Feedback
ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

前往频道在 Telegram

📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623

显示更多
3 309
订阅者
-224 小时
-97
-3630
帖子存档
📖📖📖📖📖 #አፄ_ዘርዐ_ያዕቆብ_እና_ሥራዎቹ #አፄ_ዘርዐ_ያዕቆብ መንግሥት አጠቃላይ ቅጥር ግቢው በሁለት ዙር የተከበበ እና የታጠረ ሥፍራ ሲሆን፤ በአጥሩ ዙሪያም በቁጥር አሥራ ሦስት የሚደርሱ
📖📖📖📖📖 #አፄ_ዘርዐ_ያዕቆብ_እና_ሥራዎቹ #አፄ_ዘርዐ_ያዕቆብ መንግሥት አጠቃላይ ቅጥር ግቢው በሁለት ዙር የተከበበ እና የታጠረ ሥፍራ ሲሆን፤ በአጥሩ ዙሪያም በቁጥር አሥራ ሦስት የሚደርሱ የተለያዩ መጠሪያ ሥምና ተግባር(ግብር) ያላቸው በሮች (ዕድሞዎች) እናገኛለን። እነዚህ በሮች እያንዳንዳቸው የተለያየ ተግባር እና ስም ያላቸው ናቸው፡፡ ተግባራቸውን ወደ ኋላ የምናየው ሆኖ በስም ደረጃ ውድነሽ ደጅ፣ ጸር ዋጀት ደጅ፣ መርድ ደጅ፣ መጋረጃ ደጅ፣ መስቀል ደጅ፣ ውላጅ ደጅ፣ ግምጃ ማርያም ደጅ፣ ኢየሱስ ደጅ፣ ቁልፍ ደጅ በመባል ይታወቁ ነበር፡፡ በቤተ መንግሥቱ ውስጥ በርካታ ቤቶችና ድንኳኖች የነበሩ ሲሆን፤ የቀኝ በሀልቲሐት ቤት፣ የግራ በሀልቲሐት ቤት፣ የባሀልቲሐት ሽና ቤት፣ የንግሥቷ እናት ቤት፣ የዐቃቢ ሰዓት ቤት፣ የቀኝ ብሕትወደድ ቤት፣ የግራ ብሕትወደድ ቤት፣ የግብፅ ጳጳስ ቤት፣ የንጉሥ ዋና አዳራሽ ቤት፣ የሰቀላ (የጥበቃዎች ቤት፣ የአንበሶች ቤት፣ ከዚህ በተጨማሪ የቀኝ ጀጎላ ሦስት የተለያዩ ድንኳኖች(ደበና)ነበሩት፡፡ በመካከላቸው የተተከለው ድንኳን ዱለት ቤት፣ በቀኝ በኩል ያለው ግምጃ ድንኳን እና በግራ በኩል ያለው አቋት ግምጃ ድንኳን ተብሎ ይጠራ እንደነበረ ተዘግቦ ይገኛል።       [ከውስጥ ገጽ..] 🌿#ይህ የንጉሡ ዜና መዋዕል እኛ ዘንድ አለ! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖#ኦርቶዶክሳዊ_ቅዱሳት_ሥዕላት📖 #በዚህ_ክልስ_ዕትም ከቀደመው ዕትም አንጻር ተጨማሪ ሃሳቦችና ርእሶች ከአስረጂ ቅዱሳት ሥዕላት ተካትተውበት የተዘጋጀ ነው። በይበልጥ ቅዱሳት ሥዕላትን ስለሚያዘጋጁ
📖#ኦርቶዶክሳዊ_ቅዱሳት_ሥዕላት📖 #በዚህ_ክልስ_ዕትም ከቀደመው ዕትም አንጻር ተጨማሪ ሃሳቦችና ርእሶች ከአስረጂ ቅዱሳት ሥዕላት ተካትተውበት የተዘጋጀ ነው። በይበልጥ ቅዱሳት ሥዕላትን ስለሚያዘጋጁ ሠዓሊያን የትምህርት ዝግጅት ሒደት፣ የሚጠቀሙባቸው ቁሳቁሶች፣ የአሣሣል ቅደም ተከተሎችና ጥንቃቄዎች፣ ስለሚያጋጥማቸው ፈተናዎችና መፍትሔዎችቻውን አካቷል። በተጨማሪም በዚህ ዘመን የተለያዩ የሕንጻ ቤተ ፈተናዎችና ክርስቲያን አሠሪ ወይም እድሳት ኮሚቴዎች ከማማከርና በአካል ከመጎብኘት የሚታዩ ክፍተቶችን ከነመፍትሔዎቹ ቀርቧል። በተጨማሪም በዚህ ዘመን የሚታዩ የሌላ እምነት ሥዕሎችን እና ቅሰጣዎችን እንደ ንጽጽር ከሚገኙባቸው ደብራት በናሙና በማስረጃ ቀርቧል። 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📔#መድሎተ_ጽድቅ [በመምህር ያረጋል አበጋዝ] #መንፈስ_ቅዱስ በነቢይ ዳዊት አድሮ “ይትባረክ እግዚአብሔር አምላኪየ ዘመሀሮን ጸብአ ለእደውየ ወቀትለ ለአጻብእየ - ፈጣሪዬ እግዚአብሔር ለእጆቼ ሰልፍ
📔#መድሎተ_ጽድቅ [በመምህር ያረጋል አበጋዝ] #መንፈስ_ቅዱስ በነቢይ ዳዊት አድሮ “ይትባረክ እግዚአብሔር አምላኪየ ዘመሀሮን ጸብአ ለእደውየ ወቀትለ ለአጻብእየ - ፈጣሪዬ እግዚአብሔር ለእጆቼ ሰልፍን፣ ግራ ቀኝ ማማተብን፣ ለአእምሮዬ እቀውትን ለአንደበቴ መልስን የሰጠኝ ይክር ይመስገን ብሏል መዝ. 143፡1 “መድሎተ ጽድቅ - የእውነት ሚዛን በእጅህ አስጨብጦ፤ ቀዳሚውን፣ ማእከላዊውን፣ ደኃራዊውን፤ አማኒ፣ መናፍቅ፣ ተርጓሚ፣ ተቃዋሚ፣ አስተማሪ፣ ተከራካሪ የሚገናኝበት የምሥጢር ሜዳ ስለ ጻፍህ መንፈስ ቅዱስ በጥበቡ አሠርቶሃል፡፡ በተለይም ዛሬ በልቡናው ሳይሆን በሆዱ የሚያስብ አስተማሪ (ሰባኪ) ነኝ ባይ እንደ ተምች በወረደበት ጊዜ፣ በትረ ኖሎት ያዝን ባዮችም ከሜዳው ሸሽተው ከበጐች ተለይተው በትራቸውን በበትረ መንግሥት በቀየሩበት ጊዜ ይህን መጽሐፍ ማውጣትህ የተኙትን ያነቃል፣ እምነታቸው የዛገባቸውን ይወለውላል፣ መምሰል የማረካቸውና መሆን ያቃታቸውን ከቻሉ እንዲያስቡ ያደርጋል እላለሁ፡፡ ✍#የንታ_መምህር_ደጉ_ዓለም_ካሳ [የመጻሕፍት እና የቅኔ መምህር] #የንታ ያለምክንያት ይህን እንዳላሉ ልብ ልትል ይገባል!!ጊዜውን የሚዋጅ ይህን ምርጥ የጦር እቃ እነኾ..! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

🌹 #ተፈጸመ_ናሁ_ማሕሌተ_ጽጌ ❝የሚያብረቀርቅ ቀይና ነጭ ቀለም ያለው አርአያው የብር ዝንጒርጒር ጠቃጠቆ የኾነ ንጹሕ ተአምርሽ በወርቅ አምሳል የተሠራ ነው፤ እነሆ የተወደደ (መልካም) ማሕሌተ ጽጌ
🌹 #ተፈጸመ_ናሁ_ማሕሌተ_ጽጌ ❝የሚያብረቀርቅ ቀይና ነጭ ቀለም ያለው አርአያው የብር ዝንጒርጒር ጠቃጠቆ የኾነ ንጹሕ ተአምርሽ በወርቅ አምሳል የተሠራ ነው፤ እነሆ የተወደደ (መልካም) ማሕሌተ ጽጌ ደረሰ ተፈጸመ፤ የሰማይና የምድር ንግሥት ማርያም ሆይ የተወደደ ልጅሽ በጒያሽ (በዕቅፍሽ) እንዲጠጋ (እንዲደገፍ፣ እንዲንተራስ) በርሱ ዐማጽኚ፡፡❞ [አባ ጽጌ ድንግል ፦ማህሌተ ጽጌ] 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 የዓመት ሰው ይበለን። መልካም ዕለተ ሰንበት .! 📚ግዮን መጻሕፍት  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

❝ኢየሱስም ዘወር ብሎ ሁሉን ተመለከተ....❞ #ጌታችን ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ የሚሸጡ የሚለውጡትን ጠራርጎ እንዳስወጣ በወንጌላት ተጽፎ እናገኛለን:: ይህንን ከማድረጉ ከአንድ ቀን በፊት ያደረገው ግ
ኢየሱስም ዘወር ብሎ ሁሉን ተመለከተ....❞ #ጌታችን ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ የሚሸጡ የሚለውጡትን ጠራርጎ እንዳስወጣ በወንጌላት ተጽፎ እናገኛለን:: ይህንን ከማድረጉ ከአንድ ቀን በፊት ያደረገው ግን እጅግ የሚያስፈራ ነበር:: "ኢየሱስም ወደ ኢየሩሳሌም ወደ መቅደስ ገባ፤ ዘወር ብሎም ሁሉን ከተመለከተ በኋላ፥ ጊዜው መሽቶ ስለ ነበረ ከአሥራ ሁለቱ ጋር ወደ ቢታንያ ወጣ" ማር 11:11 መቅደሱ ውስጥ ያለነውን “የሚያየን አብ ብርሃን ከልጁ ጋር ቤተክርስቲያንን ከሚጎበኙ መላእክት ጋር አለ" #ልብ አድርጉ ገርፎ ከማስወጣቱ በፊት ወደ መቅደሱ ገብቶ፥"ዘወር ብሎ ሁሉን ከተመለከተ በኋላ "ወጣ ይላል:: ጌታ ሆይ ዛሬስ ወደ መቅደስ መጥተህ ዘወር ብለህ ባየህ ጊዜ ምን አይተህ ይሆን? ምን ምን አይተህ አዝነህ ይሆን? ዳግም ጅራፍህን ይዘህ እስክትመለስ ድረስ በምሕረትህ አስተካክለን:: መቅደስ ሰውነታችንን በኃጢአት ንግድ ያቆሸሽን የልባችንን ጽላት በጣዖት የተካን ከአፍኒን በላይ የተዳፈርንህ ከፊንሐስም _ በላይ የምግባር መብራታችንን አጥፍተን ደጅህን ያጨለምን እኛን ዘወር ብለህ አይተኸን ይሆን? አንተ ዘወር ብለህ አይተኸው በጸጸት እንዳለቅሰው እንደ ጴጥሮስ አድርገን:: "በሰውና በመላእክት ማኅበር መካከል ዕርቃኔን ቆሜያለሁና ማረኝ "የቤተ መቅደስህ ተክል ያደረግኸኝ እባክህን የውጪ ተክል አታድርገኝ" [ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ] [ከውስጥ ገጽ የተቀነጨበ] 📚ግዮን መጻሕፍት  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

✨✨✨ ❝በእርሱም ቁስል እኛ ተፈወስን።❞ ት/ኢሳይያስ ፶፫፥፭ እንኳን አደረሰን! ጥቅምት ፳፯ (መድኃኔዓለም ዓመታዊ ክብረ በዓል) እሱ ንፁህ፣ነውር የሌለበት ስለኛ የደም ዋጋ የከፈለልን፣ቸሩ መድኃኔዓ
✨✨✨ ❝በእርሱም ቁስል እኛ ተፈወስን።❞           ት/ኢሳይያስ ፶፫፥፭ እንኳን አደረሰን!        ጥቅምት      ፳፯ (መድኃኔዓለም ዓመታዊ ክብረ በዓል) እሱ ንፁህ፣ነውር የሌለበት ስለኛ የደም ዋጋ የከፈለልን፣ቸሩ መድኃኔዓለም ይክበር ይመስገልንል። #መድኃኔዓለም ጥቅምት 27 ቀን ቤተክርስቲያናችን የመድኃኔዓለምን የስቅለት በዓል በደማቁ ታከብራለች፤ይህም የለውጥ በዓል ነው፡፡ #ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደሙን ያፈሰሰው ስጋውን የቆረሰው አንዴ ብቻ ነው እርሱም መጋቢት 27 ቀን፤ ይህ ግን በዐቢይ ጾም ስለሚውል በዐቢይ ጾም ሀዘን እንጂ ደስታ ስለሌለና በዓል ማክበር ስለማይፈቀድ፤ወደ ጥቅምት 27 ተዛውሮ ደስ ብሎን እንድናከብረው ቤተክርስቲያን ስርዓት ሰርታልናለች፡፡ ከበዓሉ ረድኤት በረከት ይክፈለን። አሜን!🙏 📚ግዮን መጻሕፍት  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

#በቅርብ_ቀን_ይጠብቁ ‹‹ነገረ አበው ኢትዮጵያውያን›› የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አበው ሕይወትና ሥነ-ጽሑፋዊ ቅርስ #Ethiopian_Patrology አዘጋጅ #በኃይሉ #በቀለ ወል
#በቅርብ_ቀን_ይጠብቁ ‹‹ነገረ አበው ኢትዮጵያውያን›› የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አበው ሕይወትና ሥነ-ጽሑፋዊ ቅርስ #Ethiopian_Patrology አዘጋጅ #በኃይሉ #በቀለ ወልደጊዮርጊስ (MTh, MA) የዚህ ታላቅ ሥራ ዋና ዋና ገጽታዎች 1. ቀዳሚ ቃል: በመምህር በአማን ነጸረ (ደብተራ እና የሕግ ባለሙያ) የተጻፈለት ሲሆን የመጽሐፉን ጥልቀትና ፋይዳ ያብራራል። 2. የታላላቅ ምሁራን አስተያየትም ታክሎበታል: እነ መምህር ረዳት ፕሮፌሰር ቀሲስ ግርማ ባቱ እና ዶክተር አቤሰሎም ነቅዐ ጥበብ ለመጽሐፉ የሰጡት ገንቢ አስተያየት ለጥናቱ ጥራት ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል። 3. አንኳር ይዘቱ ደግሞ ይህን ይመስላል: መጽሐፉ ከሐዋርያዊ ዘመን ጀምሮ እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አበው የኖሩትን መንፈሳዊ ሕይወት፣ ያስተማሩትን ቀና የተዋሕዶ ትምህርት እና ቤተ ክርስቲያኒቱን ከኑፋቄ እንዴት እንደጠበቁት ይመረምራል። 4. ጥናቱ ነገረ አበው ኢትዮጵያውያን፣ የቅዱስ ያሬድ መለኮታዊ ዜማዎች፣ የዛግዌ ዘመን አበው ሥራዎች፣ የገዳማውያን ሊቃውንት ዘመን፣ የአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫና የዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ አስተዋጽኦዎች፣ የሀገር ውስጥ እና የውጭ የሃይማኖት ውዝግቦች፣ እና በዘመናዊቷ ኢትዮጵያ የአበው ትውፊት ቀጣይነት ባሉ ሰፊ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያተኩራል። 5. የታሪክ ዳሰሳው ደግሞ: በዐድዋ ድል የተመዘገበው ድል፣ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ራስ ገዝነት፣ እና የሃይማኖት አንድነትን የማምጣት ጥረቶች ከመጽሐፉ አንኳር ነጥቦች መካከል ናቸው። • የመጀመሪያ ዕትም: ፳፻፲፰ ዓ.ም. (2025 A.D.) #በቅርቡ_ገበያ_ላይ_ይጠብቁ!

🌹እመቤቴ ❝እኔ የተጠማሁ ነኝ ፤ አንቺ የወርቅ መቅጃ ነሽ ፤ልጅሽ የህይወት ውኃ ነው፡፡ እኔ ነጋዴ ነኝ ፤ አንቺ መርከብ ነሽ ፤ ልጅሽ ዕንቁ ነው። እኔ ገደል ተሻጋሪ ነኝ ፤ አንቺ ድልድይ ነሽ ፤
🌹እመቤቴእኔ የተጠማሁ ነኝ ፤ አንቺ የወርቅ መቅጃ ነሽ ፤ልጅሽ የህይወት ውኃ ነው፡፡ እኔ ነጋዴ ነኝ ፤ አንቺ መርከብ ነሽ ፤ ልጅሽ ዕንቁ ነው። እኔ ገደል ተሻጋሪ ነኝ ፤ አንቺ ድልድይ ነሽ ፤ ልጅሽ የደስታ ስፍራ ነው። እኔ ደሃ ነኝ ፤ አንቺ የክብር ማከማቻ ነሽ ፤ ልጅሽ የከበረ ጌጥ ነው። እኔ ቁስለኛ ነኝ ፤ አንቺ የመድኃኒት ብልቃጥ ነሽ ፤ ልጅሽ መድሃኒት ነው። እኔ እርቃኔን ነኝ ፤ አንቺ የሸማኔ ዕቃ ነሽ ፤ልጅሽ የማያረጅ ልብስ ነው።❞ 【አባ ጊዮርጊስ】 እንኳን አደረሰን!🙏 📚ግዮን መጻሕፍት  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

-----📖📖------ †ገድለ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ † መዘንጋታቸው እጅግ ከሚያስቆጭ ኢትዮጽያውያን አባቶች ትልቁን ሥፍራ እኒህ አባት ይወስዳሉ:: የማር ወለላን በሚያስንቅ ጣዕመ ሕይወታቸው ሃገ
-----📖📖------ †ገድለ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ † መዘንጋታቸው እጅግ ከሚያስቆጭ ኢትዮጽያውያን አባቶች ትልቁን ሥፍራ እኒህ አባት ይወስዳሉ:: የማር ወለላን በሚያስንቅ ጣዕመ ሕይወታቸው ሃገራችንን ያጣፈጡ: ብርሃን ሆነው ብዙ ቅዱሳንን የለኮሱ ታላቅ ጻድቅ ናቸው:: አባ መድኃኒነ እግዚእ የተወለዱት በ፲፫ኛው መቶ ክ/ዘመን አካባቢ ትግራይ [አዲግራት] ውስጥ ነው:: ወላጆቻቸውም ቀሲስ ሰንበትና ሒሩተ ማርያም ይባላሉ:: በደግነትም እጅግ የታወቁ እንደ ነበሩ ገድላቸው ይናገራል:: "መድኃኒነ እግዚእ" ማለት "ጌታ መድኃኒታችን ነው" ማለት ነው:: :: #የ፯ቱ እና የ፵፯ቱ ከዋክብት አስተማሪ: የአበው ፫ቱ ሳሙኤሎች [ዘዋልድባ: ዘጣሬጣና ዘቆየጻ] : የሌሎችም እልፍ አእላፍ ቅዱሳን አባት የሆኑት አባ መድኃኒነ እግዚእ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳሉ፤አራዊትን ገዝተዋል: በአንበሳ ጀርባ ላይ እቃ ጭነዋል:: ከረዥም የተጋድሎ ሕይወት በሁዋላም ኅዳር ፫ ቀን ዐርፈዋል:: እድሜአቸውም ፻፹ ነው:: " መድኃኒነ እግዚእ አቡነ መስተጋድል:: ምንኩስናሁ ምዑዝ ከመ ኮል:: በመንፈሰ ጸጋ ክሉል::" [መጽሐፈ ሰዓታት] # የታላላቅ አባቶች ገድል በእውነቱ በሊቃውንት ጉባኤ አባል በኾኑት በጥራት ሲዘጋጅ ያስደስታል። [መጋቤ ምሥጢር ፍሬ ስብሐት ዱባለን]፥እየመረቅን ገድሉን በመግዛት ገዳሙን እንርዳ ! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

--- #ዲያብሎስ የሚዋጋው ሁሉን ነው፡፡ በእግዚአብሔር ጸጋ በማደግ ላይ ያሉትን እንኳ ይዋጋል፡፡ እንዲያውም ውጊያው በእነርሱ ላይ ይበረታል፡፡ ስለሆነም ማንኛውም ሰው ራሱን ከውጊያዎቹ ነጻ ወይም የ
--- #ዲያብሎስ የሚዋጋው ሁሉን ነው፡፡ በእግዚአብሔር ጸጋ በማደግ ላይ ያሉትን እንኳ ይዋጋል፡፡ እንዲያውም ውጊያው በእነርሱ ላይ ይበረታል፡፡ ስለሆነም ማንኛውም ሰው ራሱን ከውጊያዎቹ ነጻ ወይም የበላይ አድርጎ የማሰብና ቸልተኛ መሆን የለበትም:: ንጉሥ ዳዊትን እናስታውስ! እርሱ ምንም አንኳ የእግዚአብሔር መንፈስ ቢያድርበትና በእግዚአብሔር የተቀባ ቢሆንም በዝሙት ወድቆ የከፋ ኃጢአትን ፈጽሞአል፡፡ በዚህም ዲያብሎስ ሁሉን እንደሚዋጋ እናስተውላለን:: «ባላጋራችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደ አንበሳ ይዞራል፤» (1ኛ ጴጥ 5÷8) ተብሎ ተጽፎአልና። ይህን ማለት ታዳኙን ለማጥመድ ያለ ማቋረጥ ይዞራል ማለት ነው:: በኢዮብ ታሪክ ውስጥ እንደምናነበው እግዚአብሔር ሰይጣንን «ከወዴት መጣህ›› ብሎ ሲጠይቀው እንዲህ በማለት ነበር በግልጽ የመለሰው:- ‹‹ምድርን ሁሉ ዞርኋት በእርሷም ተመላለስሁ፤» (ኢዮ 1፡7፤ኢዮ 2፡2) በማለት፡፡ በእርግጥም ይህ ዙረት የሚታደን ለመፈለግ ብሎም ለመጣል የሚደረግ ዙረት ነው፡፡ ዲያብሎስ የሚዋጋው ሰው በመንፈሱ ብርቱ ቢሆንም እንኳ ቶሎ አይተወውም፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለ ኃጢአት እንዲህ የሚል ቃል አለ:- «ወግታ የጣለቻቸው ብዙ ናቸውና፤እርሷም የገደለቻቸው እጅግ ብዙ ናቸው::» ምሳ 7:26:: ዲያብሎስ አሥራ ሁለቱን የጌታ ሐዋርያት ለመዋጋት እንኳ አላመነታም፡፡ ስለዚህ ውጊያም ጌታችን ለሐዋርያው ለቅዱስ ጴጥሮስ እንዲህ በማለት ነግሮታል፦ «ስምዖን፤ስምዖን ሆይ፦ ሰይጣን እንደ ስንዴ ሊያበጥራችሁ ለመነ፤እኔ ግን እምነትህ እንዳይጠፋ ስለ አንተ አማለድሁ፧ ...»ሉቃስ 22:31-32:: #ብፁዕ_አቡነ_ሺኖዳ_ሳልሳዊ [የዲያቢሎስ ዉጊያዎች] 📚ግዮን መጻሕፍት  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] https://t.me/GhionBookStore1623

💧#ዜና_መጽሐፍ #ሃይማኖታዊ_ገድል “ወንድማችን ዲ/ን ዘአማኑኤል ገና በወጣትነት ዕድሜው ሀሁ ብሎ ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ራሱን ያዘጋጀ፣ ለብዙ ወጣቶች አርኣያና ሞደል መኾን የሚችል፣ ብስለትን
💧#ዜና_መጽሐፍ #ሃይማኖታዊ_ገድል “ወንድማችን ዲ/ን ዘአማኑኤል ገና በወጣትነት ዕድሜው ሀሁ ብሎ ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ራሱን ያዘጋጀ፣ ለብዙ ወጣቶች አርኣያና ሞደል መኾን የሚችል፣ ብስለትን ከትሕትና አንድ አድርጎ የያዘ፣ ትጉህና ቅን፣ አርቆ አሳቢ የኾነ ድንቅ የቤተ ክርስቲያን ልጅ ነው። በዚህ የወጣትነት ዕድማው የሐዋርያው የቅዱስ ይሁዳን መልእክት መሠረት አድርጎ ስለሃይማኖታዊ ገድል በሁሉም የዕድሜ ደረጃ ላለነው በሚመጥን መልኩ አዘጋጅቶ አቅርቦልናል። የይሁዳ መልእክት አንድ ምዕራፍ ብቻ ያለው ሲሆን ዶግማና ቀኖናን በጠበቀ መልኩ በብዙ መንገድ ተንትኖ እና አብራርቶ ትልቅ መጽሐፍ አድርጎ ጽፎ እነሆ ይለናል። በእንድ ምዕራፍ ተነሥቶ ትልቅ መጽሐፍ መጻፍ እንደሚቻልም ሞዴል ኹኖ አሳይቶናል። በዚያ ላይ ወጣት እንደመሆኑ ብዙ ፍላጎቶች ያሉት ሲሆን ነገር ግን ራሱን ገዝቶ ከራሱ ይልቅ በተ ክርስቲያንን አስቀድሞ ይህን የመሰለ መንፈሳዊ ሥራ ሠርቶ ትውልድ ለሚታነጽበት ለቤተ ጉባኤ መስጠቱ ለቤተ ክርስቲያን ይበልጥ ያለውን አርቆ አሳቢነት ፍንትው አድርጎ ያሳየናል። ስለዚኸ ምእመናን ሆይ ይኸን መጽሐፍ ገዝተን በማንበብ ራሳችንን እንድናንጽበት ወዲኸም ት/ቤቱን እንድናግዝበት ለማለት እወዳለኹ። ✍️ሊቀ ሊቃውንት ትሕትና ተስፋዬ በሐይቅ እስጢፋኖስ አቡነ ኢየሱስ ሞዓ አንድነት ገዳም የኖኅተ ብርሃን ሸቱ ጉባኤያት መጻሕፍተ ትርጓሜ አዳሪ ት/ቤት የቅኔ፣ የአቡሻኸርና የ፬ቱ ጉባኤያት መጻሕፍተ ትርጓሜ ምስክር መምህር። 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

❖ በመከራ ውስጥ ካለችሁ የዮናስን ዓሣ ነባሪ አስታውሱ፤ ከፍራቻ ትገላገላገላላችሁ መከራው እግዚአብሔር ጸጋውን ሊያበዛላችሁ ስለፈለገ ያዘጋጀው ዓሣ ነባሪ እንደሆነ የምታውቁበት ጊዜ ይመጣል የዚህ ዓለ
በመከራ ውስጥ ካለችሁ የዮናስን ዓሣ ነባሪ አስታውሱ፤ ከፍራቻ ትገላገላገላላችሁ መከራው እግዚአብሔር ጸጋውን ሊያበዛላችሁ ስለፈለገ ያዘጋጀው ዓሣ ነባሪ እንደሆነ የምታውቁበት ጊዜ ይመጣል የዚህ ዓለም የባሕር ዓሣዎች ብዙ ስለሆኑ ስትዋጥ እንዳይከፋህ መጠንቀቅ ይኖርብሃል፤ የመጀመሪያው ባህታዊ ጻድቁ አባ ጳውሊ የተናገረውን መዘንጋት የለብህም "ከመከራ መራቅ የሚወድ ከእግዚአብሔር ይርቃል" ብሏል። ❖ በእውነት መከራ የጸሎት ትምህርት ቤት ነው፤ በመከራዬ ሳለሁ ወደ አምላኬ ጮኽሁ እርሱም ሰማኝ፤ በሲኦልም ሆድ ውስጥ ሆኜ ጮኽሁ ቃሌንም አደመጠ። 📖ዮናስ 2፥3 ✍️አቡነ ሽኖዳ ሳልሳዊ

❖ በመከራ ውስጥ ካለችሁ የዮናስን ዓሣ ነባሪ አስታውሱ፤ ከፍራቻ ትገላገላገላላችሁ መከራው እግዚአብሔር ጸጋውን ሊያበዛላችሁ ስለፈለገ ያዘጋጀው ዓሣ ነባሪ እንደሆነ የምታውቁበት ጊዜ ይመጣል የዚህ ዓለ
በመከራ ውስጥ ካለችሁ የዮናስን ዓሣ ነባሪ አስታውሱ፤ ከፍራቻ ትገላገላገላላችሁ መከራው እግዚአብሔር ጸጋውን ሊያበዛላችሁ ስለፈለገ ያዘጋጀው ዓሣ ነባሪ እንደሆነ የምታውቁበት ጊዜ ይመጣል የዚህ ዓለም የባሕር ዓሣዎች ብዙ ስለሆኑ ስትዋጥ እንዳይከፋህ መጠንቀቅ ይኖርብሃል፤ የመጀመሪያው ባህታዊ ጻድቁ አባ ጳውሊ የተናገረውን መዘንጋት የለብህም "ከመከራ መራቅ የሚወድ ከእግዚአብሔር ይርቃል" ብሏል። ❖ በእውነት መከራ የጸሎት ትምህርት ቤት ነው፤ በመከራዬ ሳለሁ ወደ አምላኬ ጮኽሁ እርሱም ሰማኝ፤ በሲኦልም ሆድ ውስጥ ሆኜ ጮኽሁ ቃሌንም አደመጠ። 📖ዮናስ 2፥3 ✍️አቡነ ሽኖዳ ሳልሳዊ

#እንኳን_አደረሰን ! #አቡነ_አረጋዊ_ዘደብረ_ዳሞ በሃገራችን ስም አጠራራቸው ከከበረ አባቶች አንዱ እኒህ ጻድቅ ናቸው:: ጻድቁ የተወለዱት በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን አጋማሽ ኣካባቢ ሲሆን ወላጆቻቸው ንጉሥ ይስሐቅና ቅድስት እድና ይባላሉ:: የተለወለዱበት አካባቢም ሮም ነው:: ስማቸው ብዙ ዓይነት ነው:: ወላጆቻቸው ዘሚካኤል ሲሏቸው በበርሃ ገብረ አምላክ ተብለዋል:: በኢትዮጵያ ደግሞ አረጋዊ ይባላሉ:: አቡነ አረጋዊ ምንም የንጉሥ ልጅ ቢሆኑም በልጅነታቸው መጻሕፍትን ተምረው ነበርና ጠፍተው ገዳም ገቡ:: በዚያም በገዳመ ዳውናስ (ግብጽ) የታላቁ ቅዱስ ጳኩሚስ ደቀ መዝሙር ሆነው ከነ አባ ቴዎድሮስ ጋር ሥርዓተ መነኮሳትን ተምረዋል:: ከመነኮሱ ከዓመታት በኋላም ወደ ሃገራቸው ሮም ተመልሰው በማስተማር 7 ያህል የቤተ መንግስት ሰዎችን ወደ ምናኔ ማርከዋል:: "የት ልሒድ" ብለው ሲያስቡም ቅዱስ መልአክ በክንፉ ጭኖ ወስዶ ኢትዮጵያን አሳያቸው:: ተመልሰውም ለ8 ባልንጀሮቻቸው "ሃገርስ ባሳየሁዋችሁ! ሐዋርያ ሳያስተምራት በሕጉ በሥርዓቱ ጸንታ የምትኖር" ብለው ከ8ቱ ጋር ወደ #ኢትዮዽያ መጡ:: በዚህ ጊዜም እናታቸው ቅድስት እድናና ደቀ መዝሙራቸው አባ ማትያስ አብረው ነበሩ:: ወደ ሃገራችን የመጡ በ470ዎቹ አካባቢ ሲሆን አልዓሜዳ በክብር ተቀብሏቸዋል:: በቤተ ቀጢን (አክሱም) ተቀምጠውም መጻሕፍትን እየተረጐሙ: ወንጌልን እየሰበኩ ቆይተዋል:: ለሥራ በተለያዩ ጊዜም አቡነ አረጋዊ በዓት ፍለጋ ብዙ ደክመዋል:: በመጨረሻ ግን ደብረ ዳሞን (ደብረ ሃሌ ሉያን) አይተው ወደዷት:: የሚወጡበት ቢያጡም ጅራቱ 60 ክንድ የሚያህል ዘንዶ ተሸክሞ ከላይ አድርሷቸዋል:: እንደ ወጡም "ሃሌ ሉያ ለአብ: ሃሌ ሉያ ለወልድ: ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ" ብለው ቢያመሰግኑ ከሰማይ ሕብስት ወርዶላቸው ተመግበዋል:: በዚህም ቦታዋ "ደብረ ሃሌ ሉያ" ተብላለች:: ጻድቁ ቦታውን ከገደሙ በኋላ ከተለያየ ቦታ መጥተው 6ሺ ያህል ሰዎች በእጃቸው መንኩሰዋል:: ምናኔን በማስፋፋታቸውና ሥርዓቱን በማስተማራቸውም "አቡሆሙ ለመነኮሳት ዘኢትዮዽያ-የኢትዮጵያ መነኮሳት አባት" ይባላሉ:: አቡነ አረጋዊ በሕይወታቸው ከተጋድሎ ባሻገር በወንጌል አገልግሎትና መጻሕፍትን በማዘጋጀትም ደክመዋል:: ቅዱስ ያሬድና አፄ ገብረ መስቀልም ወዳጆቻቸው ነበሩ:: በተራራው ግርጌ ያለችውን ኪዳነ ምሐረትን ለሴቶች ሲገድሟት ቀዳሚዋ መነኮስ እናታቸው ንግስት እድና ሁናለች:: ጻድቁ ንጹሕ ሕይወታቸውን ፈጽመው በተወለዱ በ99 ዓመታቸው በዚህ ቀን በገዳሙ በስተምሥራቅ አካባቢ ተሰውረው ብሔረ ሕያዋን ገብተዋል:: ጌታም 15 ትውልድን የሚያስምር የምሕረት ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል:: #ቅዱስ_ፊልጶስ_ሐዋርያ በዘመነ ሐዋርያት በዚህ ስም የሚጠሩ አባቶች 2 ነበሩ:: አንደኛው ከ12ቱ ሐዋርያት ሲቆጠር ዛሬ የምናከብረው ደግሞ ከ72ቱ አርድእት ይቆጠራል:: ቅዱስ ፊልጶስ ያደገው የኖረውም በቂሣርያ አካባቢ ሲሆን ባለ ትዳር የልጆች አባት ነው:: ጌታ ሲጠራው እንኩዋ 4 ደናግል ሴቶች ልጆች ነበሩት:: ከጌታ ሕማማት በፊት ተልኮ አስተምሯል:: ከበዓለ ሃምሳ በኋላም 7ቱ ዲያቆናት ሲመረጡ አንዱ እርሱ ነበር:: (ሐዋ. 6) በቅዱስ እስጢፋኖስ መሪነትም 8ሺውን ማሕበር አገልግሏል:: ቅዱስ እስጢፋኖስ ተገድሎ 8ሺው ማሕበር ሲበተንም ቅዱስ ፊልጶስ 4ቱን ልጆቹን አስከትሎ ወደ ሰማርያ ወርዷል:: በዚያም መሠሪ ስምዖንን ጨምሮ የሃገሪቱን ሰዎች አሳምኖ አጥምቁዋል:: መቼም ቢሆን እኛ #ኢትዮጵያውያን የማንዘነጋው ግን ጃንደረባውን ባኮስን ማጥመቁን እና ለሃገራችን የወንጌልን ብርሃን መላኩን ነው:: ጃንደረባው ቅዱስ ባኮስ ከጉዞ መልስ ትንቢተ ኢሳይያስን (ኢሳ. 53) ሲያነብ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ቀርቦ ምሥጢረ ሥጋዌን አስረድቶታል:: ሠረገላውም ቁሞለት ቅዱስ ባኮስን አጥምቆት ተነጥቆ ሔዷል:: (ሐዋ. 8:26) ቅዱስ ፊልጶስ በቀሪ ዘመኑ ከተባረኩ 4 ደናግል ልጆቹ ጋር ሲሰብክ ኑሮ በዚህች ቀን ዐርፏል:: #ቅዱስ_ገብረ_ክርስቶስ_መርዓዊ ሙሽራው ገብረ ክርስቶስ በሃገራቸው ልሳን 'አብደል መሲሕ' ይባላል:: ለቅዱስ ሙሴና ለሌሎችም ሙሽርነትን ትቶ መመነንን ያስተማረ እርሱ ነው:: አባቱ ታላቁ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ሲሆን እናቱ መርኬዛ ትባላለች:: የጻድቃን ትውልድ የተባረከ ነውና (መዝ. 111:1) ታላቁ አቡነ ኪሮስ አጐቱ ናቸው:: በአርማንያ: በእመቤታችን ቤተ ክርስቲያን ደጅ ለ15 ዓመታት ሲጋደል ወደ ወላጆቹ ሃገር ቁስጥንጥንያ ተመልሶ ለ15 ዓመታት ተፈትኗል:: ምንም የንጉሥ ልጅ ቢሆንም የአባቱ ባሮች በጥፊ ይመቱት: ጽሕሙን (ጺሙን) ይነጩት: ቆሻሻ ይደፉበት: ሽንታቸውንም ይሸኑበት ነበር:: ለእርሱ ወዳጆቹ ውሾች ነበሩ:: በአባቱ ደጅ ለ15 ዓመታት መከራን ከተቀበለ በኋላ "ጌታ ሆይ! የአባቴ አገልጋዮች በእኔ ላይ ያደረጉትን ሁሉ በደል አድርገለህ አትቁጠርባቸው" አለ:: በዚህች ቀን ሲያርፍም ጌታችን 7ቱን ሊቃነ መላእክት ከነ ሠራዊታቸው አስከትሎ ወርዶ በክብር አሳርጐታል:: አጠቃላይ የገድል ዓመታቱም 30 ናቸው:: #አምላከ ቅዱሳን ለእነርሱ ካደለው ፍቅራቸው ለእኛም አይንሳን:: በረከታቸውንም ያብዛልን:: 📚#ግዮን_መጻሕፍት

ስለ እርሱ አንብቡ "እግዚአብሔር በአሳባችሁ ውስጥ እንዲኖር ስለ እርሱ አብዝታችሁ "አንብቡ ። እርሱን ለማወቅ ስለ እርሱ "አንብቡ ። እርሱን ካላወቃችሁት እንዴት እርሱን ልትወዱት ትችላላችሁ ? ስለ
ስለ እርሱ አንብቡ "እግዚአብሔር በአሳባችሁ ውስጥ እንዲኖር ስለ እርሱ አብዝታችሁ "አንብቡ ። እርሱን ለማወቅ ስለ እርሱ "አንብቡ ። እርሱን ካላወቃችሁት እንዴት እርሱን ልትወዱት ትችላላችሁ ? ስለ እርሱ "አንብቡ ስታነቡ ግን በሳይንሳዊ ወይም በፍልስፍና ጠባይ አታንብቡ ወይም ደግሞ ስለ እርሱ ጥናታዊ ጽሑፍ ወይም ትምህርት ለመስጠት አታንብቡ ። ነገር ግን ወደ እርሱ ጥልቀት ለመግባት ወይም እርሱ ወደ እናንተ ጥልቀት እንዲገባ "አንብቡ። ለነፍሳችሁ ውድ የሆኑትን የእርሱን ባሕርያት ለማወቅ ስትሉ "አንብቡ ይህ እውቀት አሳባችሁ ከእርሱ ጋር እንዲጣበቅና ፍቅሩ ከእናንተ ልብ ጋር እንዲቀናጅ ያደርግላችኋልና ። ስለ ስምምነቱ ስትሉም "አንብቡ ። ከወደዱት ሰዎች ጋር ስላለው ግንኙነት በጠላቶቹ ላይ ስላለው አቋም ስትሉ "አንብቡ ! "እግዚአብሔር ቸር እንደ ሆነ ቀምሳችሁ ታዩ ዘንድ ስለ እርሱ "አንብቡ ። ታዲያ ንባባችሁ ለልባችሁ ምግብ እንዲሆን እንጂ እንዲሁ ተራ ንባብ እንዲሆን አትፍቀዱ ። ስለ እግዚአብሔር ብዙ ካነበባችሁ በእርሱ ዘንድ ያለውን ፍጹምነት በሙሉ ታገኛላችሁ ። ከወደዳችሁት ስለ እርሱ ማንበባችሁን ትቀጥላላችሁ ። እግዚአብሔር ስለ እርሱ የሚያነቡትን ስለ እርሱ ዜና የሚጠይቁትን ከእርሱ ታሪኮች መካከል አንዱን ለማወቅ የሚናፍቁትንና እርሱን የሚያደንቁትን ሰዎች ይወዳቸዋል ። ስለ እርሱ ከመጽሐፍ ቅዱስ ወይም ከአባቶች ብሒሎች ወይም ከቤተክርስቲያንና ከቅዱሳን ታሪክ ልታነቡ ትችላላችሁ ። በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ የእግዚአብሔር እጅ ለመዳሰስ ስትሞክሩ በጥበቡ በኃይሉና በርኅራኄው ውስጥ እንደምትወዱት ታውቃላችሁ ።   - አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ