725
订阅者
+324 小时
+67 天
+5730 天
数据加载中...
吸引订阅者
九月 '24
九月 '24
+32
在0个频道中
八月 '24
+225
在0个频道中
Get PRO
七月 '240
在0个频道中
Get PRO
六月 '240
在0个频道中
Get PRO
五月 '240
在0个频道中
Get PRO
四月 '240
在0个频道中
Get PRO
三月 '240
在0个频道中
Get PRO
二月 '240
在0个频道中
Get PRO
一月 '240
在0个频道中
Get PRO
十二月 '23
+26
在0个频道中
Get PRO
十一月 '23
+14
在0个频道中
Get PRO
十月 '23
+809
在0个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 21 九月 | +1 | |||
| 20 九月 | +3 | |||
| 19 九月 | +2 | |||
| 18 九月 | +3 | |||
| 17 九月 | +1 | |||
| 16 九月 | +1 | |||
| 15 九月 | +2 | |||
| 14 九月 | +3 | |||
| 13 九月 | 0 | |||
| 12 九月 | +3 | |||
| 11 九月 | +1 | |||
| 10 九月 | +1 | |||
| 09 九月 | 0 | |||
| 08 九月 | +4 | |||
| 07 九月 | +2 | |||
| 06 九月 | +1 | |||
| 05 九月 | +1 | |||
| 04 九月 | 0 | |||
| 03 九月 | +2 | |||
| 02 九月 | 0 | |||
| 01 九月 | +1 |
频道帖子
#ስለ_ቅዱስ_ሚናስ
አዲስ ዝማሬ " ማር ሚና " ዘማሪት ሲሰተር ሕይወት ተፈሪ mar mina
Video ውን ከፈለጋችሁ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://youtu.be/IZc9_v6IxFU?si=-EAZm_XflLD1OlIG
https://t.me/BetMetsahfte
| 2 | ✝️ኅዳር_፱
✝️አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ኅዳር ዘጠኝ በዚህችም ቀን ሃይማኖታቸው የቀና 318ቱ_ቅዱሳን_አበው_ሊቃውንት_በኒቅያ አርዮስን ያወገዙበት ዕለት ነው፤ የእስክንድርያ አገር አርባ አንደኛ ሊቃ ጳጳሳት ቅዱስ_አባት_ይስሐቅ አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
ጉባኤ_ኒቅያ
ኅዳር ዘጠኝ በዚህችም ቀን የሦስት መቶ ዐሥራ ስምንት ኤጲስቆጶሳት ስብሰባ በኒቅያ ከተማ በጻድቅ ንጉሥ በቈስጠንጢኖስ ዘመን ሆነ። ከእርሳቸውም ጋራ አራቱ ሊቃነ ጳጳሳት አሉ እሊህም አባ እለእስክንድሮስ የእስክንድርያ አባ ዮናክንዲኖስ የሮሜ አገር አባ ሶል ጴጥሮስ የቊስጥንጥንያና የአንጾኪያም ሊቀ ጳጳሳት አባ ኤዎስጣቴዎስ ናቸው። ስብስባቸውም የሆነበት ምክንያት በእስክንድርያ አገር ቄስ ሁኖ ስለ ነበረው ስለ አር*ዮስ ነው። እርሱ ስቶ የክብር ባለቤት ወልድን በመለኮቱ ፍጡር ነው በማለቱ ነው።
ከእሊህም ቅዱሳን ተጋዳዮች አባቶች ከውስጣቸው እንደ ሐዋርያት ሙታንን ያስነሡ በሽተኞችን የሚፈውሱ ድንቆች ተአምራትን የሚያደርጉ አሉ ብዙ ዘመናትም ስለ ቀናች ሃይማኖት የተሠቃዩ አሉ። ከእርሳቸውም የእጃቸውንና የእግራቸውን ጥፍሮች ያወለቋቸው አሉ ዳግመኛም እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን የቆረጧቸው አሉ። ጥርሶቻቸውን የሰበሩአቸውና ጐናቸውን የሠነጠቋቸውም አሉ።
ከውስጣቸውም ስሙ ቶማስ የሚባል የሀገረ መርዓስ ኤጲስቆጶስ አለ ከሀድ*ያንም ሃያ ሁለት ዓመት አሥረው ርኅራኄ የሌለውን ሥቃይ አሠቃዩት በየዓመቱም ወደርሱ በመግባት ከሕዋሳቱ አንዱን ይቆርጣሉ እንዲሁም በማድረግ እጆቹን እግሮቹን ከንፈሮቹን አፍንጫውን ጆሮዎቹንም ቆርጠው ጨረሱ። ጥርሶቹንም ሰበሩ በእሳትም ተለብልቦ እንደ ጠቆረ ግንድ አደረጉት የርሱ ወገኖችም እንደሞተ አስበው እንደ ሌሎች ሰማዕታት በየዓመቱ መታሰቢያውን አደረጉ።
እሊህ አባቶችም ወደ ኒቅያ ከተማ በደረሱ ጊዜ ንጉሥ ቁስጠንጢኖስ ታላቅና ሰፊ የሆነ መሰብሰቢያ አዳራሽ አዘጋጀላቸው በውስጡም ለየአንዳንዳቸው ወንበሮችን አኖረ የእርሱንም ወንበር ከእነርሱ ወንበሮች ዝቅተኛ አደረገ መሳለምን በመርዓስ ኤጲስቆጶስ በቅዱስ ቶማስ ጀመረ ሰገደለት ሕዋሳቶቹ ከተቆረጡበት ላይ ተሳለመው። እንዲሁም አባቶችን ሁሉንም ተሳለማቸው። ከዚህም በኋላ በትረ መንግሥቱን ሰይፉን ቀለበቱን ሰጣቸውና እንዲህ አላቸው እነሆ አሁን በካህናት ሁሉና በመንግሥት ላይ ሃይማኖቱ እንደናንተ የቀና ከሆነ ታኖሩት ዘንድ ሃይማኖቱ የቀና ካልሆነ ግን ከምእመናን ለይታችሁ ታሳድ*ዱት ዘንድ ሥልጣንን ሰጠኋችሁ።
እነርሱም ሕግንና ሥርዓትን ሠሩ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በመካከላቸው ይቀመጥ ነበር ልቡናቸው በመንፈስ ቅዱስ የበራላቸው ሰዎች አይተውታልና በሚቆጥሩአቸው ጊዜ ግን ሦስት መቶ ዐሥራ ስምንት ቁጥር ሁነው ያገኙአቸዋል።
ከዚህም በኋላ ለካህናትና ለሕዝባውያን ለነገሥታት ለመሳፍንት ለሚገዙና ለሚሸጡ ነጋዴዎች ለድኆችም ለሽማግሎችና ለጐልማሶች ለሙት ልጆችም ለወንድና ለሴት ሥርዓትን ሠሩ። ከዚህም በኋላ ወልድ በመለኮቱ ከአብ ጋር ትክክል እንደሆነ እያስረዱ የቀናች ሃይማኖትን አስተማሩ የተረገመ አርዮ*ስንና በረከሰች ትምህርቱ የሚያምነውን አው*ግዘው ለዩ።
የሠሩዋት ያስተማሩዋትም የሃይማኖት ትምህርት ይቺ ናት እንዲህ ብለው ሁሉን በያዘ ሰማይና ምድርን የሚታይና የማይታየውን በፈጠረ በአንድ አምላክ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን። ዓለም ሳይፈጠር ከእርሱ ጋር በነበረ የአብ አንድ ልጁ በሚሆን በአንድ ጌታ በኢየሱስ ክርስቶስም እናምናለን።
ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ አምላክ የተፈጠረ ያይደለ የተወለደ በመለኮቱ ከአብ ጋር የሚተካከል። ሁሉ በርሱ የሆነ ያለ እርሱ ግን ምንም ምን የሆነ የሌለ በሰማይም ያለ በምድርም ያለ። ስለእኛ ስለ ሰው ስለ መዳናችን ከሰማይ ወረደ በግብረ መንፈስ ቅዱስ ከቅድስት ድንግል ማርያም ፈጽሞ ሰው ሆነ።
ሰው ሆኖ በጰንጤናዊ ጲላጦስ ዘመን ስለ እኛ ተሰቀለ ታመመ ሞተ ተቀበረም በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ በቅዱሳት መጻሕፍት እንደተጻፈ። በክብር ወደ ሰማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ ዳግመኛም ሕያዋንንና ሙታንን ይገዛ ዘንድ በጌትነት ይመጣል ለመንግሥቱም ፍጻሜ የለውም።
ከዚህም በኋላ የመንፈስ ቅዱስ ጠላት ስለሚሆን ስለመቅ**ዶንዮስ በቊስጥንጥንያ ከተማ መቶ ሃምሳው ኤጲስቆጶሳት በተሰበሰቡ ጊዜ ከዚህ የቀረውን ሠሩ። እንዲህም አሉ ጌታ ማሕየዊ በሚሆን ከአብ በሠረፀ በመንፈስ ቅዱስም እናምናለን እንሰግድለት እናመሰግነውም ዘንድ ከአብና ከወልድ ጋራ በነቢያት የተናገረ። ከሁሉ በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሰበሰብዋት በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም እናምናለን። ኃጢአትን ለማስተሥረይ በአንዲት ጥምቀትም እናምናለን ። የሙታንንም መነሣት የሚመጣውንም ሕይወት ተስፋ እናደርጋለን።
እሊህም አባቶቻችን ይችን የሃይማኖት ትምህርት ምእመናን ሁሉ በቀንም በሌሊትም በጸሎታቸው ጊዜ እንዲአነቡዋት በቅዳሴም ጊዜ እንዲጸልዩባት አዘዙ ወንዶችና ሴቶች ሽማግሎችና ልጆች አገልጋዮችም ሁሉ እንዲማሩዋት አዘዙ። ሠርተው ወስነው ለቤተ ክርስቲያን የሃይማኖትን ፋና ከአቆሙላት በኋላ ወደ የሀገራቸው በፍቅር አንድነት ተመለሱ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
ቅዱስ_አባት_ይስሐቅ
ዳግመኛም በዚህች ዕለት ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አርባ አንደኛ የእስክንድርያ አገር ሊቃ ጳጳሳት ቅዱስ አባት ይስሐቅ አረፈ።
ይህም ቅዱስ ቡርልስ ከሚባል አገር ነው ወላጆቹም እግዚአብሔርን የሚፈሩ እጅግም ባለጸጎች ናቸው ከረጅም ዘመንም በኋላ ይህን ቅዱስ በወለዱት ጊዜ በታላቅ ደስታ ደስ ተሰኙበት። ከዚህም በኋላ ያጠምቀው ዘንድ ወደ ኤጲስቆጶስ በአቀረቡት ጊዜ ኤጲስቆጶሱም ሲያጠምቀው በሕፃኑ ራስ ላይ የብርሃን መስቀልን አየ በዚያንም ጊዜ የሕፃኑን እጅ ይዞ በራሱ ላይ አኖረ። እንዲህም ብሎ ትንቢት ተናገረለት ይህ ሕፃን በእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ላይ ይሾማል አባቱንም እንዲህ አለው ይህን ልጅ ጠብቀው እርሱ ለእግዚአብሔር የተመረጠ መሣሪያ ይሆናልና።
ጥቂትም በአደገ ጊዜ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርትና ጽሕፈትን አስተማሩት የቅዱሳንንም ዜና የሚያነብ ሆነ ወላጆቹንም ትቶ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሔደ በአበ ምኔቱ በአባ ዘካርያስም ዘንድ መንኩሶ በገድል ተጠመደ።
በአንዲትም ዕለት አንድ ጻድቅ ሰው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አየው በእርሱም ላይ ይስሐቅ በክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ላይ ይሾም ዘንድ አለው ብሎ ትንቢት ተናገረ።
በዚያም ወራት ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሐንስ ጸሐፊ የሚሆነውና የሚረዳው ብልህ ሰው ፈለገ ስለ አባ ይስሐቅም ነገሩት እርሱም መልእክተኞችን ልኮ ወደርሱ አስመጣው ይጽፍለትም ዘንድ ደብዳቤ ሰጠው እርሱ ግን አባ ይስሐቅ እያወቀ ጽሕፈቱን አበላሽ ሊቀ ጳጳሳቱ እንዲተወውና ወደ አስቄጥስ ገዳም እንዲመለስ ነበር የዚህን ዓለም ክብር ይጠላልና።
ሊቀ ጳጳሳቱም እንዲተወውና እንዲአሰናብተው አውቆ ማበላሸቱን በአወቀ ጊዜ በጥሩ ጽፈሃል ከዚህም እንድትሔድ እኔ አልተውህም አለው አባ ይስሐቅም እንደማይለቀው አውቆ የሚያውቀውን ሁሉ ጥበቡን ያማረ ጽሕፈቱንም ገለጠለት ሊቀ ጳጳሳቱም በእርሱ እጅግ ደስ አለው ። | 92 |
| 3 | በአንተ ጨለማዬ በራ
ዘማሪ ገብረአምላክ ደሳለኝ
በአንተ ጨለማዬ በራ(2)
ተከፈተልኝ መንገዴ
ዋጋ አለው አንተን መውደዴ
አቀርባለሁኝ መዝሙር አቀርባለሁኝ ሽብሸባ
የክብር ንጉስ ሲመለክ የሰላም ንጉስ ሲገባ (2)
በሞት ጥላ በድቅድቅ ዓለም ኮብልዬ
ድምፁን ሰማሁ ልጄ ሆይ ሲለኝ ጌታዬ
እጁን ሳየው ይላወስ ጀመር አንጀቴ
የህማም ሰው ተስሎ ቀርቷል ከፊቴ
እውነተኛ ሀሰት የሌለው አዋጅ
መስቀሉ ላይ እዩት በደልን ሲዋጅ
ደሙ ነክቶህ ተከፍሎልሀል ተብዬ
ሰላም ገባሁ መድኃኒት ሆኖኝ ጌታዬ
ማምለጫዬ የተረፍኩብህ ከሞት
ማዕረጌ አጌጥኩኝ በአንተ ፍቅር
ፈላጊዬ ያኖረኝ በትከሻው
በጎ እድል ነው ለሰው ልጅ መጨረሻው
https://t.me/EthiopianOrthodoxTewahdoMezmurs | 107 |
| 4 | ✞ አብሰራ ገብርኤል
አብሰራ ገብርኤል ለማርያም
ወይቤላ (2) ትወልዲ ወልድ
ሚካኤል መላዕክ በክነፍ ፆራ
መንጦላዕት ደመና ሰወራ
ንፅህት በድንግልና አልባቲ ሙስና
ተወልደ ወልድ እምኔሐ
ትርጉም
ገብርኤል ማርያም አበሰራት አበሰራት
ወንድ ልጅም ትወልጃለሺ አላት
ሚካኤል መላዕክ በክንፋ ከለላት
የሰማይ መጋረጃውን ሸፈናት
ንፅህት ናትና በድንግልና (2)
ጥፋት የለባትምና ወንድ ልጅም ወልዳልናለችና
አዳም በጥፋቱ ከገነት ሲባረር
በሚካኤል ክንፎች ቀድሞ አይቶሽ ነበር
ሔዋንን ሲጠራት ሕይወቴ ነሽ አላት
እንደሚድን አውቆ ድንግል በአንች ምክንያት
ንፅህት ናትና በድንግልና (2)
ጥፋት የለባትምና ወንድ ልጅም ወልዳልናለችና
እግዚአብሔር የላከው የከበረው መላዕክ
ድንግል ሆይ ለክብርሽ ዐየን ሲንበረከክ
በፍቅር በትህትና በፍፁም ሰላምታ
የጌታ ሰው መሆን የነገረሽ በደስታ
ንፅህት ናትና በድንግልና (2)
ጥፋት የለባትምና ወንድ ልጅም ወልዳልናለችና
ደስተኛዬቷ ሆይ ደስ ይበልሽ ድንግል
የአብ ቃል ክርስቶስ ሥጋሽን ይለብሳል
አንቺም ትይዋለሽ ስሙን ኢየሱስ
መድኋኒት ነውና ለሥጋ ወነፍስ
ንፅህት ናትና በድንግልና (2)
ጥፋት የለባትምና ወንድ ልጅም ወልዳልናለችና
አንደ ኒቆዲሞስ ሳትከራከሪ
አንደ ዘኬርያስ ሳትጠራጠሪ
ይሁነኒ ብለሽ ቃልን ተቀበልሽ
ከፍጥረት ማነው አንቺ የሚመስልሽ
ንፅህት ናትና በድንግልና (2)
ጥፋት የለባትምና ወንድ ልጅም ወልዳልና
https://t.me/EthiopianOrthodoxTewahdoMezmurs | 100 |
| 5 | ✞ አብሰራ ገብርኤል
አብሰራ ገብርኤል ለማርያም
ወይቤላ (2) ትወልዲ ወልድ
ሚካኤል መላዕክ በክነፍ ፆራ
መንጦላዕት ደመና ሰወራ
ንፅህት በድንግልና አልባቲ ሙስና
ተወልደ ወልድ እምኔሐ
ትርጉም
ገብርኤል ማርያም አበሰራት አበሰራት
ወንድ ልጅም ትወልጃለሺ አላት
ሚካኤል መላዕክ በክንፋ ከለላት
የሰማይ መጋረጃውን ሸፈናት
ንፅህት ናትና በድንግልና (2)
ጥፋት የለባትምና ወንድ ልጅም ወልዳልናለችና
አዳም በጥፋቱ ከገነት ሲባረር
በሚካኤል ክንፎች ቀድሞ አይቶሽ ነበር
ሔዋንን ሲጠራት ሕይወቴ ነሽ አላት
እንደሚድን አውቆ ድንግል በአንች ምክንያት
ንፅህት ናትና በድንግልና (2)
ጥፋት የለባትምና ወንድ ልጅም ወልዳልናለችና
እግዚአብሔር የላከው የከበረው መላዕክ
ድንግል ሆይ ለክብርሽ ዐየን ሲንበረከክ
በፍቅር በትህትና በፍፁም ሰላምታ
የጌታ ሰው መሆን የነገረሽ በደስታ
ንፅህት ናትና በድንግልና (2)
ጥፋት የለባትምና ወንድ ልጅም ወልዳልናለችና
ደስተኛዬቷ ሆይ ደስ ይበልሽ ድንግል
የአብ ቃል ክርስቶስ ሥጋሽን ይለብሳል
አንቺም ትይዋለሽ ስሙን ኢየሱስ
መድኋኒት ነውና ለሥጋ ወነፍስ
ንፅህት ናትና በድንግልና (2)
ጥፋት የለባትምና ወንድ ልጅም ወልዳልናለችና
አንደ ኒቆዲሞስ ሳትከራከሪ
አንደ ዘኬርያስ ሳትጠራጠሪ
ይሁነኒ ብለሽ ቃልን ተቀበልሽ
ከፍጥረት ማነው አንቺ የሚመስልሽ
ንፅህት ናትና በድንግልና (2)
ጥፋት የለባትምና ወንድ ልጅም ወልዳልና
https://t.me/EthiopianOrthodoxTewahdoMezmurs | 88 |
| 6 | እንዲህ በአራት ነጥብ | ሊቀ-መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
እንዲህ በአራት ነጥብ ሊዘጋ ምዕራፉ እግዚአብሔር ሊያሸንፍ የእርሱ ሆኖ ሰልፉ መልካም ለመናገር አፉ ባይታደል
ይህን እስኪያይ ጠላት ምን አለ ዝም ቢል/2/
አዝ
መልካሙን ደብቆ ክፉን እያሳየ
ይለኝ ነበር ጠላት እግዚአብሔር ዘገየ
ግን ሁሉን በጊዜው ውብ አርጎ ሲሰራ አፍሯል ለዘላለም ደንቆት የእርሱ ስራ/2/
አዝ
በቃ ልጅ የለህም አትወልድም ሳራ ላይሰማህ እግዚአብሔር ቆመህ ብትጣራ እያለ ጠላቴ መስሎት ያሸነፈ
ይስሐቅ ተወለደ ያ ቀንም አለፈ/2/
አዝ
ፍፃሜዬን ሳያይ ገና ከጅምሩ
ጠላት በእርሱ ግምት ብዙ መናገሩ አስብሎታል ቴቄል ተቀይሮ ስሙ
የዘገየ መስሎ ጌታ በመቅደሙ/2/
አዝ
ድንጋይ ያሸከመን ውሃ ተሸከመ
ለኛ ቀን ወጣልን ለእርሱ ግን ጨለመ ገዳይ ቢዘገይም ሟች በመገስገሱ
ፈረሰኛው ሞተ እስከነፈረሱ/2/
አዝ
ቢመስለንም ሌቱ ፍፁም የማይነጋ
ተቆልፎ ሚቀር በሩ እንደተዘጋ
እርሱን ተስፋ አድርገው በአመንክበት ፅና ቀን አለው እግዚአብሔር ያደርግሃል ቀና/2/ | 82 |
| 7 | zamaarite_meretenashe_thelaahune_mirtnesh_tilahun_official_page_.m4a | 105 |
| 8 | ሙዳዬ መና
ክብረ ቅዱሳን ይእቲ ይእቲ ክብረ ቅዱሳን/2/ሙዳዬ መና ግሩም/3/
የቅዱሳኑ ክብር ነሽና
እንሰጥሻለን ቅኔ ምስጋና
የወለድሽልን የህይወት መና
ዝናብ ያለብሽ ታናሽ ደመና
ትህትና ልብስሽ ፍቅር ውበትሽ
ጽንስ ያዘልላል ሰላምታ ድመጽሽ
እሣቱን ወልደሽ እሣት ታቅፈሻል
ሳንዘምርልሽ መቼ ይመሻል
የጸሃይ መውጫ ምስራቅ ሆነሽ
ታላቁን ብርሃን አየንብሽ
አትጨልምም ህይወታችን
ልጅሽ ስላለ ጸሃያችን
ሰአሊለነ ሰላም ለኪ
ተማህጸነ በኪዳነኪ
ንኢ ርግብየ ምስለ ወልድኪ
ሰማይ ወምድር ያወድሱኪ
https://t.me/EthiopianOrthodoxTewahdoMezmurs | 95 |
| 9 | ❤️ምክንያት ስላለኝ ነው ❤️
=========//=========
ምክንያት ስላለኝ ነው የምዘምርልሽ
ምክንያት ስላለኝ ነው ቅኔ የምቀኝልሽ
አሁንም ይብዛልኝ ፍቅርሽ(፪)
ከዚህ በላይ እንዳመሰግንሽ
አውቃለሁ ከደጅሽ ምን እንዳገኘሁኝ
አስታውሰዋለሁ ሸክሜን እንደጣልኩኝ
የለመንኩሽ ሁሉ መቼ ከንቱ ቀረ
ሰይጣን ተመለሰ እንዳቀረቀረ
ጠላት ቢከፋውም ለአንቺ በመቆሜ
አደገድጋለሁ ደግሜ ደግሜ
አዝ===========
ልቤ አርፏል በአንቺ በእናቴ አማላጄ
እንቅፋት እሾሁ አይበቅልም በደጄ
በሚጣፍጥ ዜማ በኤፍሬም ውዳሴ
ሳሸበሽብልሽ ትረካለች ነፍሴ ጠላት
ቢከፋውም ለአንቺ በመቆሜ
አደገድጋለሁ ደግሜ ደግሜ
አዝ===========
ውለታ ያለበት የማይከፈል
ሲመሽም ሲነጋም ያመሰግናል
ማርያም ማርያም ይላል ምድርና ሰማዩ
በልጅሽ መከራ አልፎለት ገዳዩ
ጠላት ቢከፋውም ለአንቺ በመቆሜ
አደገድጋለሁ ደግሜ ደግሜ | 4 |
| 10 | ✞ይህቺን ዓመት ተወኝ✞
● መዝሙር ●
♡ዲያቆን ቀዳሜጸጋ ዮሐንስ♡
@orthodox_tewahdo30 | 132 |
| 11 | 🤲 ይህቺን ዓመት ተወኝ 🤲
ከዓመት እስከ ዓመት ፍሬን ሳላፈራ ደረቅ እንደሆንኩኝ
በራድ ወይም ትኩስ ሁለቱንም ሳልሆን እንዳው ለብ እንዳልኩኝ
አለሁኝ በቤትህ ለሙን መሬትህን እንዳጎሳቆልኩኝ
አውቃለሁ አምላኬ ፍሬን ለመቀበል እንዳመላለስኩህ
ዛሬም ሳላፈራ እሾህን አብቅዬ ደርቄ ጠበቅኩኝ
ያልተደረገልኝ ያላፈሰስክብኝ ያልሰጠኸኝ የለም ነገር ግን ይህ ሁሉ አላርምህ አለኝ አልለየኝም ከዓለም
የማትስለቸኝ ሆይ ተነስቼ እስክቆም እባክህ ታገሰኝ
የእኔን ክፋት ተወው መልአክህን ሰምተህ ይህቺን ዓመት ተወኝ
አውቃለሁ ታውቃለህ ቀጠሮን ሰጥቼ እንደማላከብር
ብዙ ጊዜ አቅጄ ብዙ ግዜ ዝቼ በወሬ እንደምቀር
ዘንድሮስ እንዳልኩኝ አምና ይኄን ጊዜ ሰምተኸኝ ነበረ
ምንም ሳልለወጥ ዘንድሮዬ አልፎ በአዲስ ተቀየረ
ፍሬ የማይወጣኝ እኔን በመኮትኮት እጆችህ ደከሙ
እኔ ግን አለሁኝ ዛሬም አልበቃኝም በኃጢአት መታመሙ
የቃልህን ውሃ በድንጋይ ልጅህ ላይ ሳትታክት ስታፈስ ዘመን ተቆጠረ
ወደ ልቤ ሳይሰርግ ሕይወቴን ሳይለውጥ
እንዳው ፈስሶ ቀረ
ቃልህን ጠግቤ እያገሳሁት ነው ሌሎች እስኪሰሙ
በቃልህ መኖር ግን አልያዝህ አለኝ ከበደኝ ቀለሙ
ብዙ ጥቅስ አገኘሁ ከቅዱስ መጽሐፍህ ገልጬ አይቼ
ከራሴ ላይ ብቻ አንድ ጥቅስ አጣሁኝ በበደል ተኝቼ
ውጤቴ ደካማ ትምህርት የማይሰርጸኝ ተማሪ ብሆንም
ይህቺን ዓመት ተወኝ ደግሞ ትንሽ ልማር ታገሰኝ አሁንም
እባክህ አልቆረጥ በቅዱስ መሬትህ ልቆይ ፍቀድልኝ
ያፈሩት ቅዱሳን የፍሬአቸው ሽታ መዓዛ እንዲደርሰኝ
የተሸከምከኝ ሆይ ዛሬም ተሸከመኝ አትሰልቸኝ አደራ
ማን ይታገሰኛል ጠላት እየሆንኩት አይሰሩ ስሰራ
አታውጣኝ ከቤትህ ብዙ ቦታ አልይዝም ፍሬ ስለሌለኝ
ስፍራ የማያሻኝ ቤት የማላጣብብ ፍሬ አልባ በለስ ነኝ
ቦታስ የሚይዙት ባለ ምግባሮቹ ቅዱሳንህ ናቸው
ልክ እንደ ዘንባባ የተንዠረገገ ተጋድሎ ጽድቃቸው
ከሊባኖስ ዝግባ እጅጉን የበዛ ገድል ትሩፋታቸው
እኔ አይደለሁም ቦታስ የምትይዘው ያንተው እናት ናት
ስሮቿ በምድር ጫፎቿ በሰማይ ሲደርሱ ያየናት
ይህቺን ዓመት ተወኝ ከስሯ እሆናለሁ ባፈራ ምናልባት
ይህቺን ዓመት ተወኝ እባክህ አምላኬ አንድ ዓመት ምንህ ናት
ሺ ዓመት አንድ ቀን አይደለም ወይ ለአንተ ዓመት ኢምንት ናት
ይኄ ዓመት አልፎ ዳግም ዓመት ስጠኝ እስከምልህ ድረስ
እባክህን ጌታ ይህቺን ዓመት ተወኝ የወጉን እንዳደርስ
መዝሙር
ዲያቆን ቀዳሜጸጋ ዮሐንስ
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
https://t.me/orthodox_tewahdo30
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯ | 127 |
| 12 | * ውዳሴ ማርያም እጮኻለሁ *
ውዳሴ ማርያምእጮኻለሁ
ድንግል እናቴን እጣራለሁ:
እንደ አባ ኤፍሬም ነይ ባርኪኝ
ወድሰኒ ልጄ በይኝ:
“ውዳሴ ማርያም” በሰርክ ጸሎት ላይ
”ውዳሴ ማርያም” ዜማ ስናደርስ:
“ውዳሴ ማርያም” ድንግል ትመጣለች
“ውዳሴ ማርያም” በቤተ መቅደስ:
“ውዳሴ ማርያም”የብርሃን ምንጣፍ
“ውዳሴ ማርያም” ከፊቷ ተነጥፏል:
“ውዳሴ ማርያም” ቅዱስ ኤፍሬም ታጥቆ
“ውዳሴ ማርያም” ያመሰግናታል
“ውዳሴ ማርያም” አባ ሕርያቆስ
“ውዳሴ ማርያም” ምስጋና ያደርሳል:
“ውዳሴ ማርያም” የቅዳሴው ዜማ
“ውዳሴ ማርያም” ልብን ይመስጣል:
“ውዳሴ ማርያም” በጎ ነገር ልቤ
“ውዳሴ ማርያም” አወጣ እያለ
“ውዳሴ ማርያም” ዳዊት በገናውን
“ውዳሴ ማርያም” እየደረደረ
“ውዳሴ ማርያም” የንጽሕናችን
“ውዳሴ ማርያም” መሰረት ነሽና
“ውዳሴ ማርያም” አንቺን ለማመስገን
“ውዳሴ ማርያም” ልቦናዬ ይብራ
“ውዳሴ ማርያም” ተፈስሒ ድንግል
“ውዳሴ ማርያም” ኦ ቤተ ልሔም
“ውዳሴ ማርያም” ካንቺ ተወለደ
“ውዳሴ ማርያም” መድኃኒዓለም
“ውዳሴ ማርያም” ቅዱሳኑ ሁሉ
“ውዳሴ ማርያም” ዙሪያሽን ከበዋል
“ውዳሴ ማርያም” ቅዱስ ጊዮርጊስም
“ውዳሴ ማርያም” ንዒ ድንግል ይላል
“ውዳሴ ማርያም” በወርቅ ዙፋን ላይ
“ውዳሴ ማርያም” ተቀምጠሽ ሳይሽ
“ውዳሴ ማርያም” ልቤ ተሰወረ
“ውዳሴ ማርያም” ድንግል በግርማሽ
@orthodox_tewahdo30 | 145 |
| 13 | የመስቀል ደመራ በዓል ታሪክና አከባበር
🌻✝️🌻✝️🌻✝️🌻
እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ መልካም በዓል 🙏✝️❤️ | 215 |
| 14 | ✞ 🌼 መስቀል አበባ 🌼 ✞
መስቀል አበባ ነህ ውብ አበባ
አደይ አበባ ነሽ ውብ አበባ/2/
መስቀል አበባ ተቀብሮ ሲኖር
አደይ አበባ ስነ ሥቅለቱ
መስቀል አበባ ዕሌኒ አገኘች
አደይ አበባ ደገኛይቱ
/አዝ✞✞✞✞✞
መስቀል አበባ ጥራጊ ሞልተው
አደይ አበባ አይሁድ በክፋት
መስቀል አበባ ጢሱ ሰገደ
አደይ አበባ መስቀል ካለበት
/አዝ✞✞✞✞✞
መስቀል አበባ ወንዙ ጅረቱ
አደይ አበባ ሸለቆው ዱሩ
መስቀል አበባ አሸብርቀው ደምቀው
አደይ አበባ ለአንተ መሰከሩ
@orthodox_tewahdo30 | 197 |
| 15 | 没有文字... | 153 |
| 16 | ✝️በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞🌻🌻
✝️እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ እና ለቅዱሳኑ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞
✝ ቅዱስ ዕፀ መስቀል
=>ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ቸር አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን ከሰማያዊ ክብሩ ወደ ምድር ወርዶ: በማሕጸነ #ማርያም_እግዝእት በኪነ ጥበቡ ተጸንሶ: በኅቱም ድንግልና ተወልዶ: በፈቃዱ መከራ መስቀልን ተቀብሎ:
¤ከግራ ቁመት:
¤ከገሃነመ እሳት:
¤ከሰይጣን ባርነት:
¤ከኃጢአት ቁራኝነትም አድኖናል::
✝️እምእቶነ እሳት ዘይነድድ አንገፈነ "እንዳለ ሊቁ::
+ምንም መስቀል በብሉይ የወንጀለኞች መቅጫ ሆኖ ቢቆይም እግዚአብሔር ለዓለም መዳኛነት የመረጠው ነውና ሕብረ ትንቢቶች ሲነገሩለት: በብዙ ሕብረ አምሳልም ሲመሰል ኑሯል:: ከተፈጥሯችን ጀምሮ ዓለም ራሷ አርአያ #ትዕምርተ_መስቀል ናት::
+እግዚአብሔር ለቃየን እንዳይገድሉት ከሰጠው ምልክት (ዘፍ. 4:15) ጀምሮ
¤#ይስሐቅ ሊሰዋ የተሸከመው እንጨት (ዘፍ. 22:6):
¤#ቅዱስ_ያዕቆብ ያያት የወርቅ መሰላል (ዘፍ. 28:12):
¤ያዕቆብ የዮሴፍን ልጆች የባረከበት መንገድ (ዘፍ. 48:14):
¤ባሕረ ኤርትራን የከፈለችው #የሙሴ_በትር (ዘጸ. 14:15):
¤#የናሱ_ዕባብ የተሰቀለበት እንጨት (ዘኁ. 21:8) ጨምሮ በርካታ ምሳሌዎች ለቅዱስ መስቀሉ መኖራቸውን መተርጉማን ተናግረዋል::
+#ቅዱስ_ዳዊትን የመሰሉ ነቢያት ደግሞ "ለሚፈሩሕ ከቀስት ያመልጡ ዘንድ ምልክትን ሰጠሃቸው" እያሉ መስቀሉን ከርቀት ተመልክተዋል:: (መዝ. 59:4)
+በሐዲስ ኪዳን ግን ምሳሌው ገሃድ ሆኖ: ጌታ በዕፀ መስቀል ላይ ተሰቅሎ ሥጋውን ቆረሰበት: ደሙን አፈሰሰበት: ዓለምንም አዳነበት:: ስለዚህም "#መስቀል_ብርሃን_ለኩሉ_ዓለም: #መሠረተ_ቤተ_ክርስቲያን" ተብሎ የሚመሰገን ሆኗል::
+#ቅዱስ_ያሬድ ሊቁ አክሎ "መስቀል መልዕልተ ኩሉ ነገር: ያድኅነነ እምጸር" ብሎ ጠላትን ማሳፈሪያ መሆኑን ይነግረናል:: #ብርሃነ_ዓለም #ቅዱስ_ዻውሎስም ስለ መስቀሉ አምልቶ አጉልቶ አስተምሯል:: መመኪያችን ነውና:: (1ቆሮ. 1:18, ገላ. 6:14)
+አንዳንዶቹ እኛን 'የተሰቀለውን ትታቹሃል' ይሉናል:: የተሰቀለውማ የጌቶች ጌታ: የነገሥታት ንጉሥ: የአማልክት አምላክ: ሁሉ በእጁ የተያዘ: #ኢየሱስ_ክርስቶስ ነውና ከኦርቶዶክስ በላይ የሚያመልክ በወዴት አለና::
+ነገር ግን መስቀሉን ንቆ የተሰቀለውን ማክበር አይቻልምና እኛ ለመስቀሉ የጸጋ ስግደትን እንሰግዳለን: እናመሰግነዋለን: እናከብረዋለን: ቤዛ: ጽንዕ: መድኃኒት: ኃይል እያልንም እንጠራዋለን:: አባቶቻችን በመስቀሉ ምርኩዝነት ማዕበለ ኃጢአትን: ባሕረ እሳትን ተሻግረዋል::
+በመስቀሉ ቢመኩ አጋንንትን ድል ነስተዋል:: ጠላትንም አሳፍረዋል:: እኛም በመስቀሉ አምነን ከብረን: ገነን እንኖራለን:: ተጠቅመንበታልና ከራሳችን ሕይወት በላይ ምስክርን አንፈልግም::
✝ በዓለ መስቀል
=>#መድኃኔ_ዓለም ክርስቶስ ካረገ ከዓመታት በሁዋላ አይሁድ በአንድ ነገር ተቸገሩ:: የክርስቶስን ሐዋርያት እያሳደዱ ቢገድሉም ከመስቀሉና ሥጋ ክርስቶስ አርፎበት ከነበረው ጐልጐታ ላይ የሚደረገውን ተአምር ግን መግታት አልተቻላቸውም::
+መቼም ለተንኮል አያርፉምና ቅዱስ መስቀሉን ሽፍቶቹ ከተሰቀሉባቸው ጋር ደርበው አርቀው ቀበሩት:: አካባቢው የጉድፍ መጣያ እንዲሆንም አዋጅ ነገሩ:: ለክፋት ሲሆን ተባባሪው ብዙ ነውና ለ270 ዓመታት ያህል ቆሻሻ ቢጥሉበት ተራራ ሆነ::
+ከዚህ ሁሉ ነገር በሁዋላ እናታችን ቅድስት #እሌኒ (ሔለና) በመንፈስ ቅዱስ አነሳሽነት: በቅዱስ #ኪራኮስ መሪነት: በቅዱስ #ሚካኤል ረዳትነት ደመራ አስደምራ: እጣን አጢሳ መካነ መስቀሉን አገኘች::
+መስከረም 17 ቀን የተጀመረው ቁፋሮ መጋቢት 10 ቀን ተጠናቆ: ንጹሕ መስቀሉ ወጥቶ ብርሃን በርቷል: ሙታን ተነስተዋል:: ከ10 ዓመት በሁዋላም የመስቀሉ ቤተ መቅደስ ታንጾ መስከረም 17 ቀን ተቀድሷል::
+ይህ ቅዱስ ዕፀ መስቀልም በደጉ #አፄ_ዳዊት ዘመን ወደ ሃገራችን መጥቶ: በጻድቁ #አፄ_ዘርዓ_ያዕቆብ አማካኝነት በደብረ ከርቤ (#ግሸን_ማርያም) ተለብጦ ተቀምጧል::
✝ ቅዱስ አውዶኪስ ቀሲስ
=>ይህ ቅዱስ ሰው ለቅዱስ መስቀሉ ከነበረው ፍቅር የተነሳ በብዙ ድካም ወደ #ኢየሩሳሌም በእግሩ ተጉዞ ነበር:: ከብዙ መንገደኞች ጋር በጐዳና ላይ ሳሉ ታዲያ አንድ አይሁዳዊ (ሰማርያዊ) ተቀላቀላቸው:: በወሬ በወሬ የት እንደሚሔዱ ሲጠይቃቸው "መካነ መስቀሉን ለመሳለም ወደ #ጐልጐታ ነን" አሉት::
+እሱ ግን ከት ብሎ ስቆ "እንዴት እንጨት ትሳለማላችሁ" በሚል አፌዘባቸው:: የፀሐዩ ሐሩር እጅግ ጠንቶ ነበርና ቅዱስ አውዶኪስ ኃይለ መስቀሉን ሊያሳይ ወደደ:: በመንገድም መርዝነት ያለው ውሃ ነበርና ቅዱሱ ቀርቦ ጸልዮ በመስቀሉ ባረከውና ፈጥኖ ወደ ጣፋጭነት ተቀየረ::
+ምዕመናኑ ደስ ብሏቸው ሲጠጡ ያ አይሁዳዊ 'እጠጣለሁ' ብሎ ቢቀርብ ወደ ነበረው ተመለሰበት:: 'በኮዳ የያዝኩትን እማልጠጣ' ብሎ ቢከፍተው ደግሞ ተልቶ አገኘው:: እጅግ ደንግጦ አለቀሰ:: በጣም ጠማው: ግን ምኑን ይጠጣ!
+አማራጭ ሲያጣ ወደ ቅዱስ አውዶኪስ ሒዶ እግሩ ላይ ወድቆ አለቀሰ:: በመስቀሉ ቢማጸን መራራው ጣፈጠለት:: በዚህ ምክንያትም ወደ ክርስትና ተመልሷል:: ቅዱሱ በመልካም ሽምግልና ሲያርፍ ውሃው የተቀየረበት ቦታ ላይ ቤተ መቅደስ ታንጾ በዚህ ቀን ተቀድሷል::
✝ ቅድስት ታኦግንስጣ
=>በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበረችው ሮማዊቷ እናት መንገድ ላይ ቁማ #ወንጌል ስታነብ በንጉሥ ወታደሮች ተማርካ ወደ #ሕንድ ተወስዳለች:: በዚያም በመስቀል አማትባ ሙት በማስነሳቷ የሃገሩ ሰው ወደ ክርስትና ከነ ንጉሡ ተመልሰዋል:: እርሷም ገዳም አንጻ: ደናግሉን ሰብስባ በንጽሕና ኑራለች:: በዚህ ቀን ዐርፋ ሲቀብሯት የብርሃን መስቀል መቃብሯ ላይ ተተክሏል::
=>አምላከ ቅዱሳን በኃይለ መስቀሉ: በሞገሰ መስቀሉ ይጠብቀን:: ከበረከቱ አሳትፎ በዓሉን የሰላም ያድርግልን::
✝️ መስከረም 17 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ዕፀ መስቀል
2.ቅድስት እሌኒ ንግስት
3.ቅዱስ ኪራኮስ አረጋዊ
4.ቅዱስ መቃርስ ሊቀ ዻዻስ
5.ቅዱስ አውዶኪስ ቀሲስ
6.ብጽዕት ታኦግንስጣ ሮማዊት
7.ቅዱስ ዲዮናስዮስ ሊቀ ዻዻሳት
✝️ ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት (ቀዳሜ ሰማዕት)
2.ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ (ወልደ ዘብዴዎስ)
3.ቅዱሳን አበው መክሲሞስና ዱማቴዎስ
4.አባ ገሪማ ዘመደራ
5.አባ ዸላሞን ፈላሢ
6.አባ ለትጹን የዋህ
7.ቅዱስ ኤዺፋንዮስ ሊቅ (ዘደሴተ ቆዽሮስ)
=>"የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና . . . መቼም አይሁድ ምልክትን ይለምናሉ:: የግሪክ ሰዎችም ጥበብን ይሻሉ:: እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን::"(1ቆሮ. 1:18-23)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
@orthodox_tewahdo30 | 141 |
| 17 | እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላምና በጤና አደረሳችሁ!!!
✝️🌼✝️🌼✝️🌼
@orthodox_tewahdo30 | 99 |
| 18 | 🕯መስከረም ዐሥራ ስድስት በዚች ቀን ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መቃብር ላይ ቤተ ክርስቲያን የታነፀችበትና የተቀደሰችበት ነው።እንኳን ለሁሉም በዛሬው እለት ታስበው ለሚውሉ ቅዱሳን መላእክት እና ሰማዕታት ጻድቃን ዓመታዊ እና ወርሃዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ🌻🌻
✝️አምላከ ቅዱሳን የኢየሩሳሌም ቤተ ክርስቲያንን ሰላምና ደስታ ያሳየን ከበዓላቱ ከሚገኘውም ጸጋ በረከት አይለየን::
@orthodox_tewahdo30
🕯🕯🕯 | 106 |
| 19 | ✝️ ✝️ ✝️
🌻 መስከረም ፲፮ [16]
✝ እንኳን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መቃብር ላይ ቤተክርስቲያን ለታነፀችበትና ለተቀደሰችበት በዓል፣ በኢየሩሳሌም አገር ንግሥት ዕሌኒ የገለጠቻቸው የከበሩ ቦታዎች ሁሉ ለተሠሩበትና ለከበሩበት በዓል (ለደመራ በዓል)ና በፋርስ ንጉሥ አሜኔሶር እጅ ተማርኮ ወደ ነነዌ አገር ለተወሰደ ከንፍታሌም ነገድ ለሆነ ለገባኤል ልጅ ለቅዱስ ጦቢት ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከቅዱሳን ከወርቅላ፣ ከስምዖን፣ ከመርቄኖስ፣ ከሐሊ፣ ከሮቂኖስ፣ ከሉክያኖስ፣ ከአርዝማኖስ፣ ከጴጥሮስ፣ ከሐና ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
🌼 #የዕለቱ_አንገርጋሪ፦ ሃሌ ሉያ "ዝኒ ኮነ በፈቃደ እግዚአብሔር ዝንቱ ኵሉ ኮነ ወአንቲኒ ታቦት እምኀበ መጻእኪ ወኀበኒ ተሐውሪ መድኃኒተ ኩኒ ታቦት ሕጉ ለንጉሥ ዐቢይ"። ትርጉም፦ የንጉሥ የሕጉ ታቦት መድኃኒትን ሁኚ በእግዚአብሔር ፈቃድ ሁሉ ሆነ፤ አንቺ ታቦት ከወዴት መጣሽ ወዴትስ ትሄጃለሽ።
🌼 "#ሰላም_ለጦቢት_መፍቀሬ_ምጽዋት_ዘተብህለ። እስመ ይገብር ምጽዋተ ወብዙኅ ሣህለ። እንዘ ምስለ ሕዝቡ ይሄሉ ሀገረ ነነዌ ማዕከለ። እምከመ ረከበ በእሴ ቅቱለ። እንበ ይቅብሮ አይጥዕም እክለ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የመስከረም 16።
🌼 #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ያበድሮን እግዚአብሔር ለአናቅጸ ጽዮን። እምኵሉ ተዓይኒሁ ለያዕቆብ። ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ ሀገረ እግዚአብሔር"። መዝ 86፥2-3 ወይም መዝ 50፥18-19። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 5፥13-17 ወይም ዮሐ 9፥1-12።
🌼 #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦"እቤ አዐቅብ አፋየ ከመ ኢይስሐት በልሳንየ። ወአንበርኩ ዐቃቤ ለአፉየ። ሶበ ይትቃወሙኒ ኀጥአን ቅድሜየ"። መዝ 38፥1-2 ወይም መዝ 50፥18-19። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 3፥10-18፣ ያዕ 1፥19-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 15፥13-21። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 9፥1-12 ወይም 10፥22-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቅዳሴ እግዚእነ ነው። መልካም የደመራ በዓል ለሁላችንንም ይሁንልን። | 125 |
| 20 | የሚፈልጉትን ስራ አሁን ይምረጡ | 153 |
