ch
Feedback
ማኅበረ ቅዱሳን አዳማ ማዕከል ሕዝብ ግንኙነት

ማኅበረ ቅዱሳን አዳማ ማዕከል ሕዝብ ግንኙነት

前往频道在 Telegram
405
订阅者
+124 小时
+67 天
+3130 天

数据加载中...

标签云
无数据
有任何问题?请刷新页面或联系我们的客服
进出提及
---
---
---
---
---
---
吸引订阅者
九月 '24
九月 '24
+19
在0个频道中
八月 '24
+35
在0个频道中
Get PRO
七月 '24
+7
在0个频道中
Get PRO
六月 '24
+11
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+16
在0个频道中
Get PRO
四月 '24
+11
在0个频道中
Get PRO
三月 '24
+11
在0个频道中
Get PRO
二月 '24
+15
在0个频道中
Get PRO
一月 '24
+20
在0个频道中
Get PRO
十二月 '23
+374
在0个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
21 九月+2
20 九月+1
19 九月+1
18 九月+2
17 九月0
16 九月+1
15 九月+1
14 九月+1
13 九月0
12 九月+1
11 九月+1
10 九月0
09 九月+1
08 九月+1
07 九月0
06 九月+2
05 九月+1
04 九月+2
03 九月0
02 九月+1
01 九月0
频道帖子
"Guyyaa Beellame Jiraati Ni Dhufa" #"ቀን ቀጥሯልና ይመጣል" በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ወርኃዊ ጉባኤ ዛሬ ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ በአዳማ ማዕከል ጽ/ቤት ይከናወናል:: እርሶም ሌ
"Guyyaa Beellame Jiraati Ni Dhufa" #"ቀን ቀጥሯልና ይመጣል"  በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ወርኃዊ ጉባኤ ዛሬ ከቀኑ  8:00 ሰዓት ጀምሮ በአዳማ ማዕከል ጽ/ቤት ይከናወናል:: እርሶም ሌሎችን በመጋበዝ እንዲገኙ በልዑል እግዚአብሔር ስም እናሳስባለን:: #ማኅበረ ቀዱሳን አዳማ ማዕከል አባላት እና ወረዳ ማስተባበሪያ::

2
https://youtu.be/Canxw3ZDSVQ?si=7f_CKUlaJQ7blTaz
524
3
没有文字...
657
4
Qophiin/Waraabbin Boruu Meedaa Jalqabamee Jiraa .+2
Qophiin/Waraabbin Boruu Meedaa Jalqabamee Jiraa .
224
5
没有文字...
182
6
没有文字...
612
7
#Guyyaa 5 Qofa Hafe Maqaa Abbaa Kan Ilmaa Kan Hafuura Qulqulluu Waaqa Tokko Ameen *BORUU Meedaa* Marsaa 2ffaa Sagantaan Walta
#Guyyaa 5 Qofa Hafe Maqaa Abbaa Kan Ilmaa Kan Hafuura Qulqulluu Waaqa Tokko Ameen *BORUU Meedaa* Marsaa 2ffaa Sagantaan Waltajjii Gaaffii Fi Deebii Kallattii “BORUU MEEDAA” Jedhamu  marsaa 2ffaan mata duree "Bu'uurri Kiristaanummaa eenyu? fi Gaaffiwwan Dubbii Kiristoos Irratti ka'an kanneen biroo" Jedhuun Waldaa Qulqullootaa Wiirtuu Adaamatti Afaan Oromootiin Qophaa’eera!   Waltajjii Gaaffii fi deebii kanarratti Kallattiin  Argamtanii gaaffii akka gaafattanii fi deebii gahaa akka argattan affeeramtaniittu. Guyyaa:- 22/7/2016 B.G Sa'aatii:- 7:30 irraa eegalee Qoph:- Kutaa Olaanaa Tajaajila  Miidiyaa Wiirtuu Adaamaa Iddoo:- Galma Biyyaa Lallaba Shawaa Bahaa በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ፭ቀን ብቻ ቀረው #''ቦሩ ሜዳ''   ፪ኛ ዙር ቦሩ ሜዳ  የፊት ለፊት የጥያቄ እና መልስ መርሐ ግብር ለ2ኛ ጊዜ በአፋን ኦሮሞ በአዳማ ማዕከል ተዘጋጀ፡፡ “የክርስትና መሠረቱ ማን ነው?” እና ሌሎች የነገረ ክርስቶስ ጥያቄዎችን  በቦሩ ሜዳ የፊት ለፊት የጥቄ እና መልስ መድረክ ላይ  ተገኝተው እንዲጠይቁ እና መልስ እንዲያገኙ ተጋብዘዋል፡፡ ቀን፡- መጋቢት 22/2016 ዓ.ም  ሰዓት፡- ከቀኑ 7፡30 ጀምሮ አዘጋጅ፡ አዳማ ማዕከል ሚዲያ አገልግሎት ዋና ክፍል ቦታ:-በም/ሸዋ ሀ/ስብከት አዳራሽ
517
8
没有文字...
274
9
https://youtu.be/fYEnN1t_zXo
404
10
没有文字...
187
11
በርካታ ልንመልሳቸው የሚከብዱብን ጥያቄዎች፣ ልናስተካክላቸው የሚገቡ ብልሽቶች፣ ልንሞላቸው የሚገቡ ጎደሎዎች እንዲሁም ልንጠግናቸው የሚገቡ ስብራቶች አሉብን፡፡ በብዙ መልኩ ከተቀበልነው አጉድለናል፣ ለክብሯ የሞቱላትን ቤተ ክርስቲያን ተረክበንና ለክብራችን ስንል ዝቅ እንድትል ምክንያት ሁነናል፡፡ ለጥቅሟ ሲሉ በታሰሩላት አባቶችና እናቶች ቦታ ተቀምጠን ለጥቅማችን ስንል ልእልናዋን አስደፍረናል፤ እንድናገለግላት ተመርጠን አገልግይን ብለናታል፤ ወይም ተገልጋይ ሆነንባታል፤ የተሰበሰቡትን እየበተንን፣ የተከበሩትን እያቃለልንና የታፈሩትን እያስደፈርን ቤተ ክርስቲያኗን ሸክሟን በማቅለል ፋንታ ሸክም ሆነንባታል፡፡ ዶግማዋ እየተሸራረፈ፣ ቀኖናዋ እየተጣሰ፣ መታፈር መከበሯ ቀርቶ የውስጥም የውጭም ጠላት በዝቶባት፣ የዜና ማሟሟቂያ የውሬ ማድመቂያ፣ የልጆቿ ማሸማቀቂያ፣ የጠላቶቿ መሳለቂያ የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለልጆቻችን እናወርሳለን? ወይስ በቀደመ ገናንነቷና ክብሯ እናሸጋግራተለን? የሚለው ለነገ የማይባል የቤት ሥራችን ነው፡፡ አሁን ላይ የቤተ ክርስቲያኗ ተግዳሮት በጣም ዘርፈ ብዙ መሆኑ ለማንም የተደበቀ አይደለም፡፡ ከምንም በላይ ተሰሚነቷን፣ ተከባሪነቷን፣ ሉዓላዊነቷን መመለስ የታፈረችና የተከበረች ማድረግ፣ አጥር እንደ ሌለው ቤት ማንም አልፎ ሄያጅ፣ ዘው ብሎ የሚገባባትና የፈለገውን የሚፈጽምባት፣ ቤተ ክርስቲያን ለልጆቻችን ላለማውረስና የትውልድ ባለዕዳ ላለመሆን አብዝተን መትጋት አለብን፡፡ በኦሪት ዘጸአት ላይ ያለውን ታሪክ እናስታውስ፡፡ ‹‹እግዚአብሔርም እንዲህ አለ፤ በግብጽ ያለውን የሕዝቤን መከራ በእውነት አየሁ፤ ከአስገባሪዎቻቸውም የተነሣ ጩኸታቸውውን ሰማሁ፤ ሥቃያቸውንም አውቃለሁ›› (ዘጸ. ፫፥፯) በዘመናችን ክርስቲያኖች ካስገባሪዎቻቸው የተነሣ መከራቸው በዝቷል፡፡ ደማቸውን በከንቱ የሚያፈሱ፣ ሀብት ንብረታቸውን የሚዘርፉባቸው፣ መድረሻ እንዲያጡ በሜዳ ተበትነው እረኛ እንደሌላቸው በጎች እንዲቅበዘበዙ የተደረገበት ወቅት መሆኑንና በጥቅሉ ቤተ ክርስቲያን በስደት ላይ ያለችበት መሆኑን ማንም አይዘነጋውም፡፡ ከገዥዎቻቸውና ከአስገባሪዎቻቸው የሚታደግ፣ ባሕርን ከፍሎና ደመና ጋርዶ የሚያሻግር፣ ነጻ ሆኖ ነጻ የሚያወጣ ሙሴ መሆን ከቤተ ክርስቲያን አባቶችና አገልጋዮች አሁን ይጠበቃል፡፡ ያለበዚያ አደራውን መብላት ነው፡፡ ክፉ ገዥዎች ሕዝቡን ሊለቁት ይገባል፤ ብዙዎቹን በዘረኝነት፣ በቋንቋ፣ በፖለቲካ አመለካከት፣ በልዩ ልዩ ሁኔታ፣ ግማሾቹን በኃይል ተብትበው ይዘዋቸዋል፡፡ ያገለግሉት ዘንድ ደግሞ እግዚአብሔር ይፈልጋቸዋልና፤ ሙሴን ሆኖ መገኘት በፈርኦን ፊት በድፍረት ቆሞ ያገለግሉት ዘንድ እግዚአብሔር ይፈልጋቸዋልና ሕዝቡን ልቀቅ፡ ብሎ መናገር እውነተኛ ሙሴ መሆን አሁን ያስፈልጋል፡፡ (ዘጸ.፭፥፩) ምክንያቱም በደሙ የዋጃት ቤተ ክርስቲያን በደሙ የዋጃቸው ምእመናን ናቸውና፡፡ ቤተ ክርስቲያን ስደቷ እንዲቆም፣ መከራዋ ዳርቻ እንዲኖረው፣ የሀገር ባለውለታነቷ ተዘንግቶ እየደረሰባት ላለው መከራና ስደት ማብቂያና መቋጫ እንዲኖረው፣ አንድነቷን የሚፈታተኗት ኃይሎች አደብ እንዲገዙ፣ እንደ ወርቅ የነጻው፣ እንደ ዕንቁ የሚያበራው ዶግማዋና ቀኖናዋ ለነገው ትውልድ ተጠብቆ ይተላለፍ ዘንድ ከምንም በላይ የተሰሚነትና ቅቡልነት ደረጃዋን ለማሳደግ ብዙ ሥራዎች መሥራት ይገባናል፡፡ የነገዋ ቤተ ክርስቲያን በክብረ ክህነት፣ በክብረ ምንኩስና፣ በምእመናን መንፈሳዊ ሕይወት፣ በመልካም አስተዳደር ረገድ፣ በሀብትና ንብረት አስተዳደርና በሰው ኃይል ስምሪት፣ በጋብቻ ሕይወትና በሕፃናት አስተዳደግ እንዲሁም በወጣቶች ሕይወት፣ በወንጌል አገልግሎትና በዓለም አቀፍ ግንኙነት፣ በመንፈሳዊና በቁሳዊ ልማት ረገድ፣ ማኅበራዊ ተሳትፎዋ የጎላ፣ ተጽእኖ ፈጣሪነቷ ታላቅ እንደ ጥንቱ እንዲሆን፣ ተነጋግረው ብቻ ሳይሆን በዐይን ጥቅሻ የሚግባቡ አባቶች፣ አገልጋዮች እንዲሁም ምእመናን እንዲኖሯት ከፍተኛ ሥራ መሥራት ከዚህ ትውልድ ይጠበቃል፡፡ ቤተ ክርስቲያንን ከእነ ክብሯ ለልጆቻችን ለማስተላለፍ አዲስ ነገር መፍጠር የሚጠበቅብን አይደለም፡፡ ትናንትን ለመመለስ፣ የአባቶቻችንን መንገድ ብቻ መፈተሽ፣ የጥንካሬያቸው ምክንያት ምን እንደነበር መረዳት፣ ቤተ ክርስቲያንን ገናና ያደረጓት፣ ታፍረው ተከብረው ያስከበሯት፣ “ምን ቢያደርጉ፣ እንዴት ቢሠሩ፣ ምን ዓይነት ሰብእናን ቢላበሱ ነው” ብሎ መጠየቅ፣ መልሱንም ከታሪካቸው ከገድላቸው መረዳት ብቻ በቂ ነው፡፡ በእኛ እምነት ቤተ ክርስቲያንን ያተለቃት፣ ያገዘፋት፣ የታፈረች የተከበረች ያደረጋት፣ በጨለማው ዓለም ውስጥ የምትበራ ድንቅ ፋኖስ ያደረጋት ዋና ነገሮች አልጫውን የሚያጣፍጥ፣ ጨለማውን የሚያበራ ድንቅ የሆነ የቅድስና ሕይወት ያላቸው አባቶችና እናቶች የነበሩ መሆኑ ነው፡፡ እነዚህ የቤተ ክርስቲያን ብርሃን የነበሩ አባቶቻችን ደግሞ ክብራቸውና ቅድስናቸው ከክብረ ክህነትና ክብረ ምንኩስና የሚመነጭ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን በዘመናችን የተፈተነችውና ከቀደመ ልዕልናዋ ዝቅ ያለችው ክብረ ክህነትና ክብረ ምንኩስና በገጠመው ተግዳሮት ነው ብሎ መናገር ድፍረት አይሆንም፡፡ የነገዋ ቤተ ክርስቲያን ከፍ ያለች እንድትሆን፣ የቀደመ ተወዳጅነቷን፣ ተሰሚነቷን፣ ተከባሪነቷንና ተገዳዳሪነቷን ለመመለስ ብዙ ሥራዎችን መሥራት የሚጠበቅብን መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ነገር ግን ከሁሉም ሥራዎች የሚቀድሙ፣ ለሁሉም ሥራዎች መሠረትና መሥሪያ ሆነው የሚያገለግሉ ናቸው ብለን የምናምንባቸው ነገሮች ክብረ ክህነትና ክብረ ምንኩስና ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡ የቤት ሥራዎቻችን መሆን ሲችሉ ነው፡፡ እነዚህ ሁለት ዐበይት ጉዳዮች ትናንት ለነበረችው፣ ቤተ ክርስቲያን የቅድስና፣ የክብር፣ የልዕልና፣ የመታፈር የመከበር ምንጭ ምክንያት እንደነበሩ፣ እንዚህ ሁለት የቤተ ክርስቲያን ቁልፍ ጉዳዮች ተግዳሮት ሲገጥማቸው ቤተ ክርስቲያን ተግዳሮት እንደገጠማት ፈተና ውስጥ መግባቷን መረዳት አይከብድም፡፡ ስለሆነም ከዛሬዋ ከፍ ያለች፣ ቤተ ክርስቲያን ነገ እንድትኖረን ሐዋርያዊ የሆነው የክህነት ቅብብሎሽና የምድር መላእክት የሰማይ ሰዎች ያስባለው ምንኩስና ወደ ክብሩ ወደ ታሪኩ ሊመለስ ግድ ይላል፡፡ ውድ አንባብያን! የክብረ ክህነትንና ምንኩስናን ምንነትና ለነገዋ ቤተ ክርስቲያን እንዴት መተላለፍ እንዳለበት በቀጣይ ክፍሎች ይዘን እንቀርባለን፤ ቸር እንሰንብት! Join @mkpublicrelation
465
12
"ነገን ዛሬ እንሥራ!" ክፍል ሁለት ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? ባለፈው ሳምንት ‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ›› በሚል ርእስ ባቀረብንላችሁ ጽሑፍ ቤተ ክርስቲያን ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዴት እ
"ነገን ዛሬ እንሥራ!" ክፍል ሁለት ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? ባለፈው ሳምንት ‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ›› በሚል ርእስ ባቀረብንላችሁ ጽሑፍ ቤተ ክርስቲያን ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዴት እየተላለፈች ወደ እኛ እንደደረሰችና እኛም እንዴት ከአባቶቻችንና እናቶቻችን እንደተረከብናት በጥቂቱ የዳሰስንበትን ክፍል አድርሰናችኋል፡፡ በዚህ በክፍል ሁለት ደግሞ ከክፍል አንድ የቀጠለውንና “ቤተ ክርስቲያንን እኛስ እንዴት ለቀጣዩ ትውልድ እናስተላልፋት?፡ የሚለውን ክፍል ይዘንላችሁ ቀርበናል፤ መልካም ንባብ! ቤተ ክርስቲያንን እንዴት እናስተላልፋት? ቤተ ክርስቲያን እንዲሁ አልጋ አልጋ በሆነ ሁኔታ ወደ እኛ እንዳልደረሰች በክፍል አንድ አይተናል፡፡ ራሳቸውን የካዱና ሁለንተናዊ ሕይወታቸውን ለቤተ ክርስቲያን ክብር አሳልፈው የሰጡ አባቶች ለዚህ ትውልድ በቅብብሎሽ ያደረሷትን ቤተ ክርስቲያን እኛ የዛሬዎቹ ትውልዶችስ እንዴት ለማስተላለፍ ለማውረስ አስበናል? አባቶቻችን ካወረሱን አጉድለን ወይስ አትርፈን ነው የምናስተላልፋት? ክብረ ክህነትን አጎድለን ነው፤ ወይስ አሙልተን? ክብረ ምንኩስናንስ? የምእመናንስ ቁጥር ጨመርን ወይስ ቀነስን? ዶግማ ቀኖናዋንስ ሸራረፍን ወይስ ጠብቀን ዘለቅን? መታፈርና መከበሯንስ ጨመርንላት? ወይስ አጎደልነባት?
403
13
ቁም ነገሩ የዛሬዋ ቤተ ክርስቲያን ለነገው ትውልድ በምን ሁኔታ ነው የምትተላለፈው? ትውልዱስ እንዴት ነው የሚቀበላት? እኛ የዛሬዎቹ ትውልዶችስ እንዴት ለማስተላለፍ ለማውረስ አስበናል? አባቶቻችን ካወረሱን አጉድለን ወይስ አትርፈን ነው የምናስተላልፋት? የሚሉ ጥያቄዎች መጠየቅ ያለባቸው ናቸው፡፡ ከላይ እንደጠቀስነው ቤተ ክርስቲያን (ምእመኑን፣ ጉባኤውን ወይም አንድነቱን እና ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑን እስከ ሥርዓትና ትውፊቱ) በጥቅል ቤተ ክርስቲያን ብለን ወስደን እንዴት ተቀበልናት እንዴትስ እናስተላልፋት የሚለውን ሐሳብ ማንሳት አስፈላጊ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያንን እንዴት ተቀበልናት? አባቶቻችን ቤተ ክርስቲያን እንድትሰፋ፣ ዶግማና ቀኖናዋ እንዲጠበቅ፣ ምእመናን ወንጌል ሰምተው፣ ሃይማኖትን ጠብቀው፣ ምግባር ትሩፋት ሠርተው፣ በንስሓ በሥጋ ወደሙ ተጠብቀው መንግሥቱን ርስቱን እንዲወርሱ፣ ጉባኤው ሰፍቶ፣ አንድነቱ ጸንቶ አንዲኖር፣ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያንም በዓለም እንድትታነጽ፣ ጉባኤም እንዲ ሠራባት፣ ምእመናንም እንዲገለገሉባት ለማድረግ አገልግሉኝ ሳይሉ አገልግለው፣ ለራሳቸው ክብር ሳይሆን ለቤተ ክርስቲያን ክብር፣ ለራሳቸው ምቾት ሳይሆን ለምእመናን ምቾት፣ ለራሳቸው ሥጋዊ ጥቅም ሳይሆን ለቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ ጥቅም በትጋት ሠርተው አልፈዋል፡፡ ‹‹ስለዚህም አንታክትም፤ ነገር ግን የውጭው ሰውነታችን ቢጠፋ እንኳን የውስጡ ሰውነታችን ዕለት ዕለት ይታደሳል›› እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ ስለ ቤተ ክርስቲያን ስለ ወንጌል የማይታክቱ፣ አደራ ጠባቂ አደራ አስጠባቂ አባቶች ቤተ ክርስቲያንን እስከ ክብሯ ከትውልድ ትውልድ እያሸጋገሩ ከዚህ ትውልድ አድርሰዋታል፡፡ (፪ኛ ቆሮ. ፬፥፲፮፡) ሃይማኖት ለማጽናት፣ ምግባር ለማቅናት፣ ቤተ ክርስቲያንን ለማስፋት፣ ምእመናንን ለማብዛት፣ መናፍቃንን /ከሐድያንን ለመለየት፣ ሕግና ሥርዓት ለማውጣትና ለማስፈጸም በአጠቃላይ የቤተ ክርስቲያንን ሁለንተናዊ ጥቅም ለማስጠበቅ መብቷን ለማስከበር አስተምህሮዋን ለማስፋት እና ለማስቀጠል የጥረት የሚያደርጉ አባቶች በየዘመኑ ስለነበሯት ነው፡፡ በደሙ ለዋጃት ቤተ ክርስቲያን፣ በደሙ ለዋጃቸው ምእመናን /ለመንጋው/ እንዲሁም ለራሳቸው እንዲጠነቀቁ አደራ የተሰጣቸው ባላደራ ናቸውና የአደራቸውን አላጓደሉም፡፡ (ሐዋ.ሥራ ፳÷፳፰) አባቶቻችን ቤተ ክርስቲያንን ከእኛ ለማድረስ ብዙ መከራን ተቀብለዋል፡፡ መከራው የጀመረው ገና ከሐዋርያት ዘመን ነው፡፡ ገና ከጅምሩም ነው፡፡ ‹‹በኢየሩሳሌም ባለችው ቤተ ክርስቲያን ላይ ታላቅ ስደት ሆነ›› ብሎ መጽሐፍ እንደነገረን (የሐዋ.ሥራ ፰፥፩)፡፡ ይህም የቅዱስ እስጢፋኖስን በድንጋይ ተወግሮ መሞት የጉባኤውን መበተን፣ በቤተ ክርስቲያን ላይ የደረሰውን ስደትና ሥቃይ የሚያስታውስ ቃል ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን በትውልድ ቅብብሎሽ ስትመጣ እንዲሁ አይደለም የሚባለውም ለዚህ ነው፡፡ ብዙዎች በድንጋይ ተወግረው፣ በእሳት ተቃጥለው፣ በምሳር ተወግተው፣ በሰይፍ ተቀልተው፣ በገደል ተወርውረው በእስራት፣ በእርዛት፣ በረኃብ በጽም ተፈትነው ያቆዩን ናት ለማለት ነው፡፡ (ገድለ ሐዋርያት) ከሐዋርያት ዘመንም በኋላ በሐዋርያት አበውም በሊቃውንትም ዘመን የቤተ ክርስቲያን ጉዞ አልጋ በአልጋ እንዳልነበር የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ምስክር ነው፡፡ ጥርሱ እንደወለቀው፣ ጺሙ እንደተነጨው፣ ፊቱ እንደተጸፋው እንደ ዲዮስቆሮስ፣ በፓትርያሪክነት ዘመኑ አምስት ጊዜ እንደተጋዘው አትናቴዎስ፣ ንግሥቲቱን በመዝለፉ፣ ሥርዓት አልበኛ ካህናትና ጳጳሳትን ከሹመታቸው በመሻሩ በስደትና በመከራ ሕይወቱ እንዳለፈው እንደ ዮሐንስ አፈወርቅ ያሉ አባቶችን ስናስብ ቤተ ክርስቲያንን ወደ እኛ ለማሸጋገር የተከፈለው ዋጋ ይገባናል፡፡ (የሃይማኖተ አበው ትርጓሜ መቅድም/የቤ ክርስቲያን ታሪክ) በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ከመርቅያን ንጉሥና ከብርክልያ ንግሥት፣ መከራን ተቀብሏል፡፡ በጉባኤ ኬልቄዶን የተነሣውን ምንፍቅና በመቃወሙ፣ የሊቀ ጳጳሱን ደብዳቤ ባለ መቀበሉ፣ ንግሥቲቱና ደንገጡሮቿ ፊቱን ጸፍተው ጺሙን ነጭተው ጥርሱን ሰብረው ወደ ግዞት እንደላኩት የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ያስረዳል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅም ሰነፍና ሥርዓት አልበኛ ካህናትንና ጳጳሳትን በመሻሩ፣ ከተማ ለከተማ የሚዞሩ መነኮሳትን በመገሠፁ፣ በሚሠሩት ግፍ ንግሥቲቱንና ባለ ሥልጣናቱን በድፍረት በመገሠፁ መከራ ደርሶበታል፤ በግፍም በግዞት ሞቷል፡፡ (የቤተ ክርስቲያን ታሪክ/ግንቦት ፲፪ ስንክሳር፣ ሰማዕትነት አያምልጣችሁ) ይህም ለራስ ክብር ሳይሆን ለቤተ ክርስቲያን የተደረገ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን በዘመነ ሰማዕታት፣ ከዚያ በኋላም ሆነ በፊት እስከ ዛሬዋ ዕለት ቤተ ክርስቲያን እንድትቀጥል፣ ዘመናትን ተሻግራ ሙሽራዋ ክርስቶስ እስኪመጣ ተከብራ ትጠብቀው ዘንድ፣ ትውልዱ በየዘመኑ የበረከት ፍሬዋን ይመገብ ዘንድ፣ የጸጋ ግምጃዋን ይለብስ ዘንድ፣ የአጋንንትና ክፉ ሰዎችን ውጊያ የተዋጉላት ለክብሯና ለህልውናዋ ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡላት፣ ብርቱ የማይታክቱ አገልጋዮች፣ መሪዎች፣ አማኞች ስለ ነበሯት መሆኑን እንረዳለን፡፡ (፪ኛ ቆሮ. ፬፥፩) ጠፍር ታጥቀው፣ ጥሬ ቆርጥመው፣ ውኃ ጠጥተው፣ ሰሌን አንጥፈው፣ ማቅ ለብሰው ቤተ ክርስቲያንን የጠበቋት ክፉ ቀንን ያሳለፏት፣ የዚህ ዓለም ሀብት፣ ሹመት ሽልማት፣ ሥጋዊ ደማዊ ጥቅም ያላበላሻቸው አባቶቻችንና እናቶቻችን ብዙ የብዙ ብዙ ነበሩ፡፡ ‹‹የቀረውንም ነገር ሳልቆጥር ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ዐሳብ ነው›› እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ የወንጌል አለመሰበክ፣ የምእመናን አለ መብዛት፣ የቤተ ክርስቲያን አለ መስፋት፣ የዕለት ዕለት ዐሳብ ሸክም የሆነባቸው፣ እየሠሩ የማይደክሙ፣ ትጉሃን ጽኑዓን አባቶቻችንና እናቶቻችን ለእኛ አደረሱልን፡፡ (፪ኛ ቆሮ.፲፩፥፳፰) በዚህም የተነሣ ዳር ደንበሯ ሰፍቶ፣ ምእመኖቿ በዝተው፣ አጥር ቅጥሯ ተከብሮ፣ ጉባኤዋ ሰፍቶ፣ መንፈሳዊ ሀብት ንብረቷ ፋፍቶ ደርጅቶ፣ ክብሯ ገናንነቷ ዓለምን ናኝቶ፣ ለወዳጅ ትምክሕት፣ ለጠላት ኀፍረት ቁጭት ፈጥሮ፣ በየአህጉሩ ያለች ገናና ቤተ ክርስቲያንን አስረከቡን፤ እኛም ተረከብን፡፡ ውድ የዚህ ጽሑፍ ተከታታዮች! አምላካችን ቢፈቅድ በሕይወትም ብንኖር ክፍል ሁለትን ይዘንላችሁ እንቀርባለን፤ ቸር እንሰንብት!
462
14
‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ!›› ክፍል አንድ ቤተ ክርስቲያን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደሙ ዋጅቶ የመሠረታት፣ በክርስቶስ ክርስቲያን ለተባልን በሙሉ መሰብሰቢያችን የተቀደሰች ቤታችን ናት፡፡
‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ!›› ክፍል አንድ ቤተ ክርስቲያን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደሙ ዋጅቶ የመሠረታት፣ በክርስቶስ ክርስቲያን ለተባልን በሙሉ መሰብሰቢያችን የተቀደሰች ቤታችን ናት፡፡ ቤተ ክርስቲያን ስንልም ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን፣ የክርስቲያን ወገን፣ የምእመናን አንድነት ወይንም ማኅበረ ምእመናን እያንዳንዱን ማለታችን ነው፡፡ (የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ቁጥር ፩) ውድ አንባብያን! የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ስለ ቤተ ክርስቲያን ምንነት፣ ታሪክ ወዘተ መተንተን አይደለም፡፡ የነገዋ ቤተ ክርስቲያን ምን መምሰል አለባት? እንዴትስ ለትውልዱ እስከ ክብሯና ግርማ ሞገሷ ትሻገር? የሚለውን አሳሳቢ ጉዳዮችን መዳሰስ ነው እንጂ፡፡ ትውልድ ጅረት ነው፡፡ አንድ ትውልድ አልፎ ሌላ ትውልድ ይተካል፡፡ አንዱ አልፎ ሌላው ሲተካ ግን ተተኪው ትውልድ በቅብብሎሽ የሚተላለፉ ነገሮችን እየተቀበለና እየጨመረባቸው እንደ ዘመኑና እንደ ወቅቱ እያሳደጋቸው፣ እርሱም በተራው ለሌላው ትውልድ እያወረሳቸው ይተላለፋሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያን ከትውልድ ወደ ትውልድ በበርካታ ትውልዶች ቅብብሎሽ ከዛሬው ትውልድ ከደረሱ ሀብቶች ዋናዋ ናት፡፡ ሀብት ብዙ ወገን ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ሀብተ ሥጋና ሀብተ ነፍስን የምታሰጥ ናት፡፡ በተጋድሎ በጠንካራ ሥራ፣ በብዙ ውጣ ውረድ ደምና ላብ ፈስሶበት የተገነባን ሀብት የተቀበለ ትውልድ ብቻውን ተጠቅሞ ጨርሶ ለተተኪው ትውልድ በተለይ መንፈሳዊ ውርስ ሳያተርፉ መሄድ ዕዳና በደል ነው፡፡ ይህ ሀብት የምንጠቀመው ብቻ ሳይሆን የምናስተላልፈው አደራ ጭምር ነው፡፡ አባቶቻችን ይህን አደራ አላፋለሱም፡፡ ቤተ ክርስቲያንን ከተቀበሉት አብልጠው፣ ከተጠቀሙት አትርፈው ከጥፋትና ከብክነት ጠብቀው ከእኛ ዘመን ያደረሱልን መተኪያ የሌላት መንፈሳዊ ሀብታችን ናት፡፡
429
15
አደራ አለብኝ! በሚል መሪ ቃል ሁለተኛው ዙር አለማቀፍ የድህረ ግቢ ጉባኤ ምሩቃን መርሐግብር መጋቢት 08/2016 ዓ.ም በአዳማ ማዕከል ተካሄደ። በመርሐ ግብሩ ላይ በመጋቤ አዲስ ቀሲስ ቴድሮስ ትምህ+3
አደራ አለብኝ! በሚል መሪ ቃል ሁለተኛው ዙር አለማቀፍ የድህረ ግቢ ጉባኤ ምሩቃን መርሐግብር መጋቢት 08/2016 ዓ.ም በአዳማ ማዕከል ተካሄደ። በመርሐ ግብሩ ላይ በመጋቤ አዲስ ቀሲስ ቴድሮስ ትምህርተ ወንጌል የተሰጠ ሲሆን የበገና አገልግሎት በማዕከሉ ዘማሪያን ቀርቦ የልምድ ልውውጥ ያደረጉልን ወንድማችን ዶ/ር ሽመልስ( የማዕከለሉ ልማት ተቋማት ተጠሪ )እና እህታችን ወ/ሮ ቤዛዊት ለማ ነበሩ። ይህ ጉባኤ ከግቢ ጉባኤ በማንኛውም ዓ.ም ተመርቀው ለወጡ ሁሉ በየሶስት ወሩ ይዘጋጃል።
598
16
没有文字...
991
17
"IMAANAATU NARA JIRA" አደራ አለብኝ! የግቢ ጉባኤ ምሩቃን መርሐግብር ቀን:- 8/2016 ዓ.ም ሰዓት :- 7:00 ጀምሮ ቦታ :- አዳማ ማዕከል
"IMAANAATU NARA JIRA" አደራ አለብኝ! የግቢ ጉባኤ ምሩቃን መርሐግብር ቀን:- 8/2016 ዓ.ም ሰዓት :- 7:00 ጀምሮ ቦታ :- አዳማ ማዕከል
779
18
ዘወረደ የዐቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት ነው። ስያሜውም የቅዱስ ያሬድ ነው። ትርጉሙም “ከሰማያት የወረደ” ማለት ነው። ቅድመ ዓለም ከአባቱ ከአብ የተወለደ ፣ድኅረ ዓለም ከድንግል ማርያም የተወለደ ነው። ስም አጠራሩ  ያለና የነበረ፣ እግዚአብሔር፣ በፈቃዱ ዓለምን ለማዳን የመምጣቱን ምሥጢር የምንረዳበት ሳምንት ነው። ይህ የመጀመሪያው ሳምንት ‹ጾመ ሕርቃል› እየተባለም ይጠራል፡፡ ሕርቃል (ኤራቅሊዮስ) በ፮፻፲፬ ዓ.ም የነበረ የቤዛንታይን ንጉሥ ነው፡፡ለክርስቲያኖች ባደረገው ርዳታ ምክንያት አንድ ሳምንት ጾመውለት ነበር፡፡ ዛሬም ድረስ ጾመ ሕርቃል እየተባለ ይጠራል፡፡ ሙሉ ታሪኩ በፍትሐ ነገሥት ትርጓሜ አንቀጽ ፲፭ ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ ሳምንት ቤተ ክርስቲያን ስለ ጾም ጥቅምና እንዴት መጾም እንዳለብን ታስተምረናለች፡፡ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው “አከለክሙ መዋዕል ዘኃለፈ ዘተቀነይክሙ ለግዕዘ ሥጋክሙ፤ ለሥጋቸሁ ፈቃድ የተገዛችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃችኋል፤ ከአሁን በኋላ ግን ጹሙ፣ ጸልዩ ለእግዚአብሔር ተገዙ” እያለ የጾም አዋጅ ያውጃል። ጾም ፈቃደ ሥጋን ለፈቃደ ነፍስ፣ ፈቃደ ነፍስን ለፈቃደ እግዚአብሔር የምናስገዛበት መንፈሳዊ መሣሪያ ነው፡፡ ጾሙ በሚጀመርበት ሰንበት በሚሰበከው ምስባክ እንዲህ ብሎ ያሳስበናል፤ “ለእግዚአብሔር በፍርሃት ተገዙ፣ በረዓድም ደስ ይበላችሁ” ጾም ከምግብና ከመጠጥ እንዲሁም ከሌሎች ምቾቶችና ደስታዎች ከመከልከል ያለፈ ጥልቅ ትርጉም ያለው ተግባር ነው። (መዝ.፪፥፲፩-፲፪) “ንጹም ጾመ ወናፍቅር ቢጸነ ከመ ያብርህ ብርሃነ ስብሐቲሁ በላዕሌነ፤ (የእግዚአብሔር) የክብሩ ብርሃን በላያችን ላይ ያበራ ዘንድ ጾምን እንጹም፤ወንድማችንንም እንውደድ” እንዲል። (ጾመ ድጓ) በዘወረደ እሑድ የሚነበቡት ምንባባትም ይህንን የጾምን ጸጋ የያዙ ናቸው። “ነገር ግን ፈጣሪያችን የምትበልጠውን ጸጋ ይሰጣል፤ ስለዚህም “እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፤ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል” ይላል፡፡ እንግዲህ እግዚአብሔርን እሺ በሉት፤ ሰይጣንን ግን እንቢ በሉት፤ ከእናንተም ይሸሻል፡፡ እግዚአብሔርን ቅረቡት፤ ይቀርባችሁማል፤ እናንተ ኃጥኣን እጆቻችሁን አንጹ፤ ሁለት አሳብም ያላችሁ እናንተ ልባችሁን አጥሩ፡፡ እዘኑና አልቅሱ፤ ሳቃችሁን ወደ ልቅሶ÷ ደስታችሁንም ወደ ኀዘን መልሱ፡፡ በእግዚአብሔር ፊት ራሳችሁን ዝቅ አድርጉ፤ እርሱም ከፍ ከፍ ያደርጋችኋል፡፡” (ያዕ.፬፥፮-፲) “በውኑ እንግዲህ በስሙ እናምን ዘንድ የከንፈሮቻችን ፍሬ የሚሆን የምስጋና መሥዋዕትን በየጊዜው ለእግዚአብሔር ልናቀርብ አይገባንምን? ነገር ግን ለድሆች መራራትን፥ ከእነርሱም ጋር መተባበርን አትርሱ፤ እንዲህ ያለው መሥዋዕት እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋልና፡፡” (ዕብ.፲፫፥፲፭-፲፮) በጾም የተጠቀሙ ቅዱሳንን እያሰብን ለጾም እንድንተጋም ወደ እነርሱ እንድንመለከት ቤተ ክርስቲያን ታስተምራለች፡፡“ ልባችሁ በመብል ያይደለ በጸጋ ቢጸና ይበልጣልና፤ በዚያ ይሄዱ የነበሩ እነዚያ አልተጠቀሙምና።” (ዕብ.፲፫፥፱) ሳምንቱ በሚጀምርበት ሳምንት የሚነበበው የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት እንዲህ ይላል፡፡ ጾመ ድጓው አባቶቻችን ያገኙትን በረከት እንደምናገኝበት ሲገልጽ “የእግዚአብሔር የክብሩ ብርሃን በላያችን ላይ ያበራ ዘንድ ጾምን እንጹም፤ ወንድሞቻችንም እንውደድ፤ ኤልያስ በጾም ወደ ሰማይ አርጓልና፤ዳንኤልም ከአናብስት አፍ ድኗልና፡፡” ጾም ፈቃደ ነፍስን በፈቃደ ሥጋ ለማሠልጠን የአጋንንት ኃይል ለመቋቋም የሚያስችል የክርስቲያኖች ጋሻ በመሆኑ በሃይማኖት ለሚመሩ ምእመናን እጅግ አስፈላጊና ከምንም በላይ የሕይወታቸው መርሕ መሆን እንደሚገባ ቅዱስ ጳውሎስ በመልእክቱ እንዲህ በማለት   ያስተምራል፡፡ ” አሁንም ወንድሞቻችን በዚህ በሥጋችን ሳለን ፈቃደ ሥጋችንን ልንሠራ አይገባም፤ ፈቃደ ሥጋቸውን የሚሠሩ ሰዎች በወዲያኛው ዓለም ምውታን ናቸውና፡፡ የሥጋችሁን ፈቃድ በነፍሳችሁ ፈቃድ ድል ከነሣችሁት ለዘለዓለም ሕያዋን ትሆናላችሁ፡፡ የነፍሳቸውን ፈቃድ የሚሠሩ ሰዎች ሁሉ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸውና፡፡" (ሮሜ ፰፥፲፪-፲፬) ጾም አበው ቅዱሳን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በጊዜ ቀምረው፣ በበታ ወስነው፣ በሁኔታ ገድበው... ባስቀመጡልን ወቅት ከእህልና ከውኃ በመከልከልና ሰውነትን በማድከም ብቻ ሳይሆን ለስሕተት ከሚዳርጉ ነገሮችና ቦታዎች ተቆጥቦ በጸሎት መትጋትም እጅጉን አስፈላጊ ነው፡፡ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊትም ይህንን እውነታ በተመለከተ እንዲህ ይላል፡፡ “እኔ ግን እዘንልን፤ ለምንልን ባሉኝ ጊዜ ማቅ ምንጣፍ ለብሼ አዘንኩላቸው፤ ሰውነቴን በጾም አደከምኩዋት፤ ልመናዬም እኔም ወደመጥቀም ተመለሰችልኝ፡፡” (መዝ. ፴፬/፴፭፥፲፫) ጾም ከሥነ ምግባራት ሕግ አንዱ በመሆኑ እንኳንስ ያልተፈቀደውን የተፈቀደውም ቢሆን የማይጠቅም ከሆነ ፈጽሞ በመተው ለእግዚአብሔር ያለንን ፍጹም ፍቅር የምናስመሰክርበት ምሥጢር ነው፡፡ ጾም ከመብልና ከመጠጥ ጋር የተያያዘም በመሆኑ መብል ጊዜያዊ ስለሆነ ማለትም በዚህ ዓለም እስካለን ብቻ የምንገለገልበት እንጂ ዘለዓለማዊ ስላይደለ ለጊዜያዊ መብልና መጠጥ ምክንያት ከሃይማኖት ሥነ ምግባር እንዳንወጣ ቅዱሳን አባቶቻችን ሐዋርያት ሲመክሩ “መብል በእግዚአብሔር ዘንድ ግዳጅ አይፈጽምልንም ወደ እግዚአብሔር አያቀርበንም፤ ብንበላም አይረባንም፤ አይጠቅመንም፤ ብንተወውም አይጎዳንም” በማለት ሲመክሩን ቅዱስ ጳውሎስም የመብልና የሆድ ጊዜያዊነት አስመልክቶ እንዲህ በማለት አስተምሯል፡፡ (፩ኛቆሮ.፰፥፰) “ሁሉ ነገር ተፈቅዶልኛል፤ ሁሉ ግን አይጠቅመኝም፡፡ ሁሉ ተፈቅዶልኛል በእኔ ላይ ግን አንድ ነገር እንኳን አይሠለጥንብኝም፡፡ መብል ለሆድ ነው ሆድም ለመብል ነው፡፡ እግዚአብሔር ግን ሁለቱንም ያሳልፋቸዋል”፤ (፩ኛቆሮ.፮፥፲፪-፲፫) “ለሚጠፋ ምግብ አትሥሩ፤ ይልቅስ የሰው ልጅ ለሚሰጣችሁ የዘለዓለም ሕይወት ስለሚሆን ምግብ ሥሩ” እንደ ተባለ (ዮሐ. ፮፥፳፯) ካለን ጊዜ ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ጊዜ በመስጠት ቢበሉት የማያስርበውን፣ ቢጠጡት የማያስጠማውን፣ የዘለዓለም ሕይወት የምናገኝበትን ሥጋ እና ደሙን ተቀብለን መንግሥቱን እንድንወርስ ቅዱስ ፈቃዱ ይሁንልን። ሥርዓት ቅዳሴ ከሠራኢ ካህን፣ ቅዳሴ፡ ዘእግዚእነ “ዘበእንቲኣነ ለሰብእ ወበእንተ መድኃኒትነ፡ ወረደ እምሰማያት። ተሰብአ፡ ወተሠገወ እመንፈስ ቅዱስ ወእማርያም እምቅድስት ድንግል፤ ስለ እኛ ስለ ሰዎች እኛን ለማዳን ከሰማይ ወረደ፤ በመንፈስ ቅዱስ ግብር  ከቅድስት ድንግል ማርያም ፍጹም ሰው ሆነ፡፡” ወንጌል፡ ዮሐ.፫፥፲-፳፬ የዕለቱ ምንባባት:- •  በሠራኢ ዲያቆን (ዕብ.፲፫፥፯-፲፯) •  በንፍቅ ዲያቆን (ያዕ.፬፥፮-ፍጻሜ) •  በንፍቅ ካህን (የሐዋ. ፳፭፥፲፫-ፍጻሜ) ምስባክ፡ “ተቀነዩ ለእግዚአብሔር በፍርሃት ወተሐሠዩ ሎቱ በረዓድ አጽንዕዋ ለጥበብ ከመ ኢይትመዐዕ እግዚአብሔር” (መዝ.፪፥፲፩) ወንጌል፡ ዮሐ.፫፥፲-፳፬ ስብሐት ለእግዚአብሔር ኪያነ ዘፈጠረ ከመ ናምልኮ፤ እንድናመልከው እኛን ለፈጠረ ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን!
922
19
የዐቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት ዘወረደ በዚህ ሳምንት የቃል ርደት፣ የወልድ ልደት፣ የአዳም ድኅነት ቢነገርም እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ከሰማይ የወረደ ሰማያዊ፣ በክብር ያረገ በኩረ ትንሣኤ መሆኑ
የዐቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት ዘወረደ በዚህ ሳምንት የቃል ርደት፣ የወልድ ልደት፣ የአዳም ድኅነት ቢነገርም እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ከሰማይ የወረደ ሰማያዊ፣ በክብር ያረገ በኩረ ትንሣኤ መሆኑ አይዘነጋም፡። ለዚህም ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ “እውነት እውነት እልሃለሁ፥ የምናውቀውን እንናገራለን፤ ያየነውንም እንመሰክራለን፥ ነገር ግን ምስክርነታችንንም አትቀበሉትም። በምድር ያለውን ስንነግራችሁ ካላመናችሁኝ፥ በሰማይ ያለውን ብነግራችሁ እንዴት ታምኑኛላችሁ? ከሰማይ ከወረደው የሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም፥ እርሱም በሰማይ የሚኖረው ነው። ሙሴ በምድረ በዳ እባቡን እንደ ሰቀለው የሰው ልጅ እንዲሁ ይሰቀል ዘንድ አለው፡፡ያመነበት ሁሉ ለዘለዓለም ሕያው ሆኖ እንዲኖር እንጂ እንዳይጠፋ፣ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘለዓለም ሕይወትን እንዲያገኝ እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን ቤዛ አድርጎ እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶታልና” እንዳለ እርሱ ምድራዊ ያይደለ ሰማያዊ ነው። (ዮሐ.፫፥፲፩-፲፮)  “ተጠምቀ ሰማያዊ በእደ መሬታዊ” ስለ ፍቅሩ በፈጠረው የተጠመቀ ሰማያዊ ነው። ጾመ ድጓው የሚጀምረውም እንዲህ በማለት ነው፤ “ዘወረደ እምላዕሉ፣ አይሁድ ሰቀሉ…. እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ በቃሉ፤ ….በቃሉ የሚያድነውን ከላይ የወረደውን የሁሉን ጌታ አይሁድ ሰቀሉት…”
552
20
没有文字...
932