ch
Feedback
የጋዜጠኛው ማጮለቂያ

የጋዜጠኛው ማጮለቂያ

前往频道在 Telegram

አያለሁ፣እሰማለሁ፣እናገራለሁ ሰለኢትዮጵያ

显示更多
465
订阅者
无数据24 小时
-27 天
-930 天
帖子存档
የቤት ሰራተኛዋን በመግደል ሁለት ህፃናትን አግተው፤ አስር ሚሊዮን ብር የጠየቁ አጋቾች በቁጥጥር ስር ዋሉ የቤት ሰራተኛዋን በመግደል ሁለት ህፃናትን አግተው አስር ሚሊዮን ብር የጠየቁ አጋቾችን በቁጥጥር ስር አውሎ ህፃናቱን፤ ለቤተሰቦቻቸው ማስረከቡን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ  አስታወቋል። ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ/ም በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ዓለም ባንክ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ-ክርስቲያን አካባቢ፤ ከቀኑ 11፡45 ላይ የቤት ሰራተኛ የሆነቸው ሀብታም ወርቁ በመኖሪያ ቤት ውስጥ በስለት ተወግታ መሞቷን እንዲሁም የ10 እና የ7 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ህፃን እምነት አሽናፊ እና ጄሊ አሽናፊ መጥፋታቸው ለአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ሪፖርት ይደርሰዋል። ጠቅላይ መምሪያው የፎረንሲክ፣ የምርመራ እና የክትትል ቡድን አባላትን አደራጅቶ ወንጀል ወደተፈፀመበት ስፍራ በመላክ ማስረጃዎችን በማሰባሰብ የምርመራ ሥራውን መጀመሩን የጠቅላይ መምሪያው የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ከማንደር ማርቆስ ታደሰ ገልፀዋል። የሟች ማንነት እንጂ የገዳይ ማንነት አለመታወቁ፣ ሀብታም ወርቁን ማን ገደላት? ህፃናቱስ የት ተሰውሩ? ለሚለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት እና ወንጀል ፈፃሚውን በቁጥጥር ስር ለማዋል እንዲሁም ህፃናት ለማግኘት ክትትሉ ቀጥሏል። ክትትሉ በቀጠለበት ሂደት መንግስቱ ደለሰ የተባለ ግለሰብ ለህፃናቱ ወላጅ እናት ለወ/ሮ ሃዊ ዮሴፍ ስልክ በመደወል ህጻናቱን ማገቱንና 10 ሚሊዮን ብር ካልተሰጠው ልጆቹን እንደሚገድላቸው ይዝታል። እንዲሁም ጉዳዩን ለፖሊስ ካሳወቀች በህፃናቱ ላይ የከፋ እርምጃ እንደሚወስድ የሚገልፅ መልዕክት ያስተላልፋል። ህፃናቱ ከዚህ ቀደም አጋቹን ስለሚያውቁትና የደገሰላቸውን የሞት ድግስ ባለማወቃቸው፤ ሲጫወቱ በመቅረጽ ልጆቹ እርሱ ጋር መሆናቸውን የሚያሳይ ቪዲዮ ለወ/ሮ ሃዊ ይልካል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ እና የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በመቀናጀት የፖሊስ የክትትል አባላት ቀንና ሌሊት ባደረጉት እልህ አስጨራሽ ሥራ፤ አጋቹን እና ሌሎች ተባባሪዎቹን ሐምሌ 5 ቀን 2017 ዓ/ም በቁጥጥር ስር ማዋል ችሏል። ሁለቱንም ህጻናት በአዳማ ከተማ ልዩ ቦታው ቦሌ ሰፈር እየተባለ ከሚጠራ አካባቢ ታግተው ከተቀመጡበት ቤት ጉዳት ሳይደርስባቸው ማስለቀቁንም ኮማንደር ማርቆስ ጨምረው ገልፀዋል። ከወንጀሉ ጋር በተያያዘ ተጠርጣዎችን ይዞ ምርመራው መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል። የህፃናቱ ወላጅ እናት ወ/ሮ ሃዊ ዮሴፍ እና አባታቸው አቶ አሸናፊ ጫኔ በወንጀል ድርጊት በእጅጉ ተጨንቀው እንደነበር ተናግረው፤ የአዲስ አበባ ፖሊስ እና ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ባደረጉት ጥረት ልጆቻቸውን በሰላም በማግኘታቸው በፀጥታ አካላት ተግባር ኩራት እንደተሰማቸው ገልፀዋል። ኮማንደር ማርቆስ ወንጀል ፈፃሚዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል በተደረገው እንቅስቃሴ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እንዲሁም የኦሮሚያ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ከፍተኛ ድርሻ ማበርከታቸውን ገልጸው፤ በአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። መሰል ችግር ሲያጋጥም ለፖሊስ ሪፖርት ማድረግ ተገቢ እንደሆነ ፖሊስ አስታውቆ፤ ልዩ ልዩ ማህበራዊ ሚዲያ በመጠቀም ስለ ወንጀሉ መረጃ ማሰራጨት ለወንጀል ፈፃሚዎቹ ምቹ ሆኔታን እንደሚፈጥር ህብረተሰቡ ተገንዝቦ ተገቢውን ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል።(AMN)

ለኬንያ የተሰጠ አልሚ ምግብ ኢትዮጵያ ውስጥ ሲሸጥ ተያዘ ከዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ለኬንያ ተረጂዎች ብቻ እንዲያገለግል የተሰጠ "ፕላምፒነት" የተሰኘ አልሚ ምግብ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ሲሸጥ በፖሊስ
ለኬንያ የተሰጠ አልሚ ምግብ ኢትዮጵያ ውስጥ ሲሸጥ ተያዘ ከዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ለኬንያ ተረጂዎች ብቻ እንዲያገለግል የተሰጠ "ፕላምፒነት" የተሰኘ አልሚ ምግብ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ሲሸጥ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር መዋሉን የአዲስ አበባ ከተማ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ለአሐዱ አስታውቋል። አልሚ ምግቡ ከኬንያ ተነስቶ ኢትዮጵያ የገባው በመድኃኒትነት ተመዝግቦ መሆኑ ታውቋል፡፡ ‎በባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ የምግብና ጤና ነክ ተቋማት ቁጥጥር ዳይሬክተር እስጢፋኖስ ጌታቸው ለአሐዱ እንደገለጹት፤ ለኬንያ ተብሎ የተሰጠን አልሚ ምግብ ወደ ኢትዮጵያ በማስገባት፣ በአዲስ አበባ ከተማ በመርካቶ አካባቢ በተደረገ ክትትል፣ ፕላምፒነቱ በቅርቡ ሙሉ በሙሉ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ሊውል ችሏል ተብሏል። ‎በዚህም ፕላምፒነት ወደ ሀገር ውስጥ ሲገባ ተመዝግቦ በመሆኑና ለአንዱ ሀገር የተሰጠው አልሚ ምግብ ወይም "ፕላምፒነት" ከሌላኛው ሀገር ጋር ተመሳሳይ ባለመሆኑ ከሀገር ሀገር ማንቀሳቀስ እንደማይቻል ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። ‎ "ፕላምፒነት" የተሰኘው አልሚ ምግብ በየትኛውም ቦታ ሊሸጥ የማይችልና ለእርዳታ አገልግሎት ብቻ የሚውል አልሚ ምግብ እንደሆነ ያብራሩት ዳይሬክተሩ፤ ማኅበረሰቡ በምግብ እጥረት ለተጎዱ ወገኖች የሚውለውን አልሚ ምግብ ሲሸጡ የተመለከታቸውን በ8864 በመደወል ጥቆማ እንዲሰጥም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ (አሃዱ)

አዲሱ የዩትዩብ ሞኒታይዤሽን መመሪያ‼ ከፊታችን ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ዩትዩብ፤ ዩትዩብን ተጠቅመው ገቢ በሚያስገቡ ላይ ጥብቅ መመሪያ አውጥቷል። መመሪያው ምን ይላል ? - ከአሁን በኋላ ዩትዩብ ክፍያ የሚፈጽመው አዲስና የራሳቸው ፈጠራ ብቻ ለሆኑ ፤ በብዛት ወይም በድጋሚ በዩትዩብ ላይ ላልዋሉ ስራዎች ነው። - ክፍያ የሚፈጸምላቸው ቪድዮዎች እውነት እና የራስ ስራ ላይ የተመሰረቱ ብቻ መሆን አለባቸው። - አርተፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ተጠቅመው የሚሰሩ ሰዎች ክፍያ አይከፈላቸውም። - በድምፅና ትንሽ የቪድዮ ስራ ብቻ ተጨማምሮባቸው የሚቀርቡ የሌላ ሰዎች ስራዎች ክፍያ አያገኙም። - በተለያዩ ተንቀሳቃሽ ቪድዮዎች ወይም የሰው ቪድዮዎች ላይ reaction መስጠት እና የሰው ቪድዮዎችን እየሰበሰቡ ማቅረብ ከዩትዩብ ክፍያ ውጭ ይደረጋሉ። - የራሳቸው ስራ ያልሆነ ቪድዮ ማለትም እዛው ዩትዩብ ላይ በሌሎች የተሰሩ ቪድዮ የሚያቀርቡ ሰዎች የራሳቸውን ሃሳብ እንዲጨምሩና እንዲሰሩ የሚጠየቁበት መንገድ ቢኖርም ያለማስጠንቀቂያም ሊታገዱ ይችላሉ። ዩትዩብ በአዲሱ መመሪያው ኦሪጅናል ለሆኑ እና ሰዎች በራሳቸው ጥረት ለሰሯቸው ስራዎች ክፍያ ይከፍላል። ክፍያ ለማግኘት የራስን የፈጠራ ስራ ዩትዩብ ላይ መጫን ግዴት ይሆናል። ዩትዩብ ይህን ወደማድረግ የገባው ሰዎች የራሳቸውን የፈጠራ ስራ እንዲሰሩ ለማበረታታ ነው። ዩትዩብ ክፍያ ለመክፈል ከዚህ ቀደም ያስቀመጠው አስገዳጁ 1 ሺህ ሰብስክራይበር እንዲሁም 4,000 የዕይታ ሰዓት በ12 ወራት ውስጥ ማግኘት አሁንም እንደ ግዴታ ይቀጥላል ተብሏል። via Tikvahethiopia

የትግራይ የሃይማኖት አባቶች የጠ/ሚኒስትሩ ንግግር እንዳሳሰባቸው ገለጹ • የሽማግሌዎች ልኡክ ወደ ጠ/ሚኒስትሩ ሊልኩ ነው የትግራይ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የሃይማኖት መሪዎች፣ ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ
የትግራይ የሃይማኖት አባቶች የጠ/ሚኒስትሩ ንግግር እንዳሳሰባቸው ገለጹ • የሽማግሌዎች ልኡክ ወደ ጠ/ሚኒስትሩ ሊልኩ ነው የትግራይ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የሃይማኖት መሪዎች፣ ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በቅርቡ በፓርላማ ተገኝተው ያደረጉት ንግግር እንዳሳሰባቸው ገለጹ። የጠ/ሚኒስትሩ ንግግር በጦርነት በተጎዳው ክልል ውስጥ ያለውን የሰላም ሂደት ሊያዳክም ይችላል ብለዋል፡፡ “የጠቅላይ ሚኒስትሩ የትግራይ ግምገማ ከሕዝቡ የኑሮ ሁኔታ ጋር የሚገናኝ አይደለም” ያሉት የሃይማኖት መሪዎቹ፤ እንዲህ ያለው አለመጣጣም ያለውን ሰብአዊ ቀውስ ሊያባብሰው እንደሚችል አስጠንቅቀዋል። የሃይማኖት መሪዎቹ ትላንት ረቡዕ ባወጡት መግለጫ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቦታው ያለውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እውነታዎች መረዳትን በተመለከተ በትግራይ ህዝብ ዘንድ ስጋት እየጨመረ መምጣቱንም ገልጸዋል። ቤተክርስቲያኗ የሽማግሌዎች ልዑክ በቀጥታ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር እንዲገናኝ እንደምትልክ ያስታወቁት የሃይማኖት መሪዎቹ፤ ዓላማውም የትግራይን ሕዝብ ስጋት ለማሳየትና ለሰላም ሂደቱ የበለጠ ምላሽ ሰጪና ውጤታማ አቀራረብን ለመደገፍ ነው ብለዋል። #አዲስ_አድማስን

የድሃ ድሃን የገቢ ግብር የሚያስከፍል ነው‼ አዲሱ የገቢ ግብር አዋጅ የድሃ ድሃን የገቢ ግብር የሚያስከፍል ነው በሚል ተተችቷል‼ ከሃምሌ ወር 2017 ዓ.ም ጀምሮ በስራ ላይ ይውላል ተብሎ የሚጠበቀው አዲሱ የገቢ ግብር አዋጅ ረቂቅ ከላይ ተያይዟል። የገቢ ግብር ማሻሽያ ረቂቅ አዋጁ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ያለባቸውን የግብር ጫና መቀነስ አንዱ አላማው ቢሆንም፤ በውስጡ የያዛቸው ድንጋጌዎች ግን እሱን አንደማያመለክቱ እንደራሴዎች ተናግረዋል፡፡ ረቂቅ አዋጁ በአለም ባንክ መስፈርት መሰረት የድሃ ድሃን የገቢ ግብር የሚያስከፍል ነው በሚል ተተችቷል፡፡ አንድ ሰው ከ30,000 ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ ማንኛውንም ነገር ከተገበያየ መቶ በመቶ እጥፍ ቅጣት እንዲከፍል የገቢ ግብር ማሻሽያ ረቂቅ አዋጅ ያስገድዳል፤ ይህም በፓርላማ ጥያቄ አስነስቷል፡፡ እንደራሴዎቹ በረቂቅ አዋጁ ላይ ትችት እና ቅሬታ ያቀረቡት ትናንት ከሰዓት በኋላ በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በገቢ ግብር ረቂቅ አዋጅ ላይ ውይይት ባካሄዱበት ወቅት ነው፡፡ በረቂቅ አዋጁ ላይ ሀሳባቸውን የሰጡት አንድ የምክር ቤት አባል በማሻሻያው ላይ የቀረበው፤ ሰራተኛ ከሚያገኘው ወርሃዊ ደመወዝ ላይ ተቆራጭ የሚደረግበት መነሻ የግብር ምጣኔ ምንን መሰረት ተደርጎ እንደተወሰነ ለእኔ ግልጽ አልሆነልኝም ብለዋል፡፡ ቢያንስ በደመወዝ ማሻሻያው በተደረሰበት ዝቅተኛ የደመወዝ መጠን 4570 ብር ያለውን ለምን ከታክስ ነጻ መደረግ እንዳልተቻለ የጠየቁት የምክር ቤት አባሉ ለምን ከ2000 በላይ የሚያገኙ ተቀጣሪ ሰራተኞች የገቢ ግብር እዲከፍሉ ተደረገ? ሲሉ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ ዝቅተኛ ገቢ ለሚያገኘው ሰራተኛ እኛ እና የገንዘብ ሚኒስቴር ነን እንጂ የምናስብለት ሌላ አካል ያለ አይመስለኝም ያሉት ተወካዩ ለምን የግብር መነሻ ከገንዝብ የመግዛት አቅም ጋር የሚመጣጠን አልሆነም? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ ገቢ እንዳይቀርብን እንፈልጋለን ያሉት እንደራሴው ግን ገቢውን ማሳደግ ያለብን በዚህ መንገድ መሆን የለበትም ብለዋል፡፡ አስተዳደራዊ ክፍሉን በአግባቡ ከያዝን ማካካስ አይቻልም ወይ ሲሉ የጠየቁት የምክር ቤት አባሉ ይሄ ነገር ቅሬታ ያስነሳብናል ይሄን እንዴት አይታችሁታል? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ መሆን የሚገባውን ነው ማድረግ ያልብን ያሉት የምክር ቤት አባሉ እኔ እያልኩ ያለሁት ዝቅተኛውም ሰው አይጎዳብን፣ የመንግስት ገቢም መቅረት የለበትም ነው ብለዋል፡፡  አቶ ወንደሰን አድማሴ የተባሉ ሌላ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው ግብር መክፈል ያለበት ማነው? የሚል ጥያቄ ከጠየቁ በኋላ የድሃ ድሃ ወይም ( #Absolute_Poverty ) ውስጥ ያለ ሰው ግብር መክፈል አለበት ወይ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ እ.ኤ.አ በ2022 በአለም ባንክ በተሰራ ጥናት አንድ ሰው በቀን ከ2.15 ዶላር በታች የሚያገኝ ከሆነ ድሃ እንደሆነ ያሳያል ያሉት አቶ ወንደሰን፤ የኢትዮጵያውን ግን አሁን ባለው የምንዛሪ ተመን ከዚያ ከፍ ያለ ስለ ሆነ absolute poverty ውስጥ ያለ ሰው ግብር መገበር አለበት ወይ ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ ሌላው የምክር ቤት አባሉ እና ቋሚ ኮሚቴው የጠየቀው ጥያቄ በጥሬ ገንዘብ ግብይት ላይ የተጣለውን ገደብ የተመለከተ ነው፡፡ በማሻሽያ ረቂቅ አዋጅ መሰረት ከ30,000 ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ የሚደረግ ግብይትን የሚከለክል ሲሆን ሲገበያይ የተገኘ ሰው ደግሞ የከፈለውን ገንዘብ በእጥፍ እንዲከፍል ያስገድዳል፡፡ Via :- Sheger fm https://www.facebook.com/share/1BEqA74FbX/

ተቋርጧል📍 የኢትዮጵያና ሶማሊያ የወደብ ቴክኒክ ኮሚቴ ስራ ማቆሙን አፍሪካን ኢንተለጀንስ ዘግቧል። በቱርክ አሸማጋይነት ኢትዮጵያና ሶማሊያ ሲያደርጉት የነበረው የወደብ የቴክኒክ ኮሚቴ ስራ ለጊዜው መ
+1
ተቋርጧል📍 የኢትዮጵያና ሶማሊያ የወደብ ቴክኒክ ኮሚቴ ስራ ማቆሙን አፍሪካን ኢንተለጀንስ ዘግቧል። በቱርክ አሸማጋይነት ኢትዮጵያና ሶማሊያ ሲያደርጉት የነበረው የወደብ የቴክኒክ ኮሚቴ ስራ ለጊዜው መቋረጡ ታውቋል። አንካራ ባለፈው አመት የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ መንግስታትን ወደ ጠረጴዛ ካቀረበች በኋላ ኢትዮጵያ በሶማሊያ ወደብ ለማገናኘት የሚያስችል የቴክኒክ ስምምነት ላይ ለመድረስ ጥረት ሲደረግ ቆይቷል ያለው አፍሪካንስ ኢንተሌጀንስ ውይይቶቹ ላልተወሰነ ጊዜ ተቋርጠዋል ብሏል።

ፎርብስ መፅሄት የ2025 የአፍሪካ ቢሊየነሮችን ደረጃ ይፋ አድርጓል።ከ1-10 ሆነ ከ1-22 አንድ ኢትዮጵያዊ ባለሃብት የለም።
+1
ፎርብስ መፅሄት የ2025 የአፍሪካ ቢሊየነሮችን ደረጃ ይፋ አድርጓል።ከ1-10 ሆነ ከ1-22 አንድ ኢትዮጵያዊ ባለሃብት የለም።

በመቀለ ከተማ ተዘርቶ የተገኘ ማሪዋና የተሰኘ አደንዛዥ እፅ ተወገደ በትግራይ ክልል መቀለ ከተማ ሰሜን ክፍለ ከተማ ላይ ተዘርቶ የተገኘ ማሪዋና የተሰኘ የአደንዛዥ እፅ ከህብረተሰብ በተገኘ ጥቆማ መወ
+2
በመቀለ ከተማ ተዘርቶ የተገኘ ማሪዋና የተሰኘ አደንዛዥ እፅ ተወገደ በትግራይ ክልል መቀለ ከተማ ሰሜን ክፍለ ከተማ ላይ ተዘርቶ የተገኘ ማሪዋና የተሰኘ የአደንዛዥ እፅ ከህብረተሰብ በተገኘ ጥቆማ መወገዱን የክፍለ ከተማው ፖሊስ አስታውቋል። በጉዳዩ ላይ ተጠርጣሪ የሆነችው እንስት የክፍለ ከተማው ነዋሪ ስትሆን ይጠቅምሻል ትከይው እኛ ራሳችን እንወስድልሻለን ካሏት ሰዎች ተቀብላ እንደዘራችው መናገሯን የሰሜን ክፍለ ከተማ ፖሊስ የወንጀል መከላከል ፅህፈት ቤት ሓላፊው ምክትል ኢንስፔክተር ፍስሃ ፀጋይ ገልፀዋል። ሓላፊው አክለው መረጃውን ለፖሊስ የሰጡ ሰዎችን ያመሰገኑ ሲሆን በቀጣይም በህብረተሰብ ላይ አደጋ የሚያስከትሉ እንቅስቃሴዎችን ሲመለከቱ ለፖሊስ በመጠቆም አጋርነታቸውን እንዲያሳዩ መጠየቃቸውን ብስራት ከ መቀለ ከተማ ፖሊስ ያገኘው መረጃ የሳያል።

ኤርትራ ከሰሞኑ የአብዛኞቹ የኤርትራ ሰራዊት አመራር አባላት የሞባይል ስልክ እንዲነጠቁ መደረጉን ሰምተናል። ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ በጋሽ ባርካ አንቴሬ አካባቢ የኤርትራ የጦር መሳሪያ ማከማቻ መቃጠሉን ተከትሎ ሲሆን ይህ ክስተት በኤርትራ ጦር አመራር ላይ ጥርጣሬ በማሳደሩ ምክንያት ነው። በዛላንበሳ በኩል ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎችም ታስረዋል። በተያያዘ ዜና የኤርትራ ጦር አባላት በኢትዮጵያ ድንበር ያሉ አካባቢዎችን አሁንም ተቆጣጥረው እንደሚገኙ እና የከፉ ጥሰቶች መፈጸም መቀጠላቸውን ሪፖርቶች እየወጡ እንደሆነ ኢትዮጵያ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ክስ አቅርባለች። ‎በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢትዮጵያ ተወካይ አምባሳደር ጸጋአብ ክበበው "የከፉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በድንበር አካባቢዎች እንደሚፈጸሙ ሪፖርቶች መውጣታቸውን" ቀጥለዋል ሲሉ ተናግረዋል። #አዩዘሀበሻ

ባጋጣሚ ተቀርጾ መነጋገሪያ የሆነው የኦሮሚኛ የባህል ሙዚቃ በአጋጣሚ በስልክ ተቀርጾ የተለቀቀው "በሸነና" የተሰኘው ኦሮሚኛ ሙዚቃ፣ ከሰሞኑ በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ከፍተኛ ተቀባይነት ያገኘ ሆኗል።
+1
ባጋጣሚ ተቀርጾ መነጋገሪያ የሆነው የኦሮሚኛ የባህል ሙዚቃ በአጋጣሚ በስልክ ተቀርጾ የተለቀቀው "በሸነና" የተሰኘው ኦሮሚኛ ሙዚቃ፣ ከሰሞኑ በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ከፍተኛ ተቀባይነት ያገኘ ሆኗል። በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ 'ቫይራል' በሆነው ተንቀሳቃሽ ምስል ላይ ይህን የሕዝብ ዜማ ሲጫወተው የሚታየው ወጣት ሊበን ጃርሶ፤ በሸነናን ሲጫወቱ የሚያሳየው ምስል ከተለቀቀ በኋላ በብዙዎች ተወዳጅነት ማግኘቱን ይገልጻል። ይህን ዜማ በሰርግና በተለያዩ የደስታ ጊዜዎች ማህበረሰቡ የሚጫወተው ሲሆን፤ ይህንኑ ዜማ በራሱ ግጥም እንደዘፈነው ነው ሊበን ጃርሶ ለኢቲቪ የተናገረው። መልዕክቱም ደስታና ሀሴት ለሁሉም ይገባል የሚል ነው ሲልም የሙዚቃውን ይዘት ገልጾታል። ዘፈኑ ስለ ደስታ የሚገልጽ ሲሆን፤ ከተለያየ ቦታዎች የሚመጡ እንግዶች ሰብሰብ ብለው የሚጫወቱት እንደሆነም ነው ያነሳው። በአጋጣሚ የተለቀቀው ተንቀሳቃሽ ምስል በብዙዎች ተወዳጅነት ማግኘቱም እንዳስደሰተው ይናገራል። ወጣት ሊበን ጃርሶ ሙዚቀኛ የመሆን ፍላጎት እንዳለውም የገለጸ ሲሆን፤ “የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲያበረታታኝና ድጋፉ እንዳይለየኝ እጠይቃለሁ” ብሏል። (EBCመዝናኛ)

አዲስ አበባ ከ68 ሺህ በላይ እግረኞች ተቀጡ‼ በአዲስ አበባ ከተማ ከ68 ሺህ በላይ ደንብ ተላላፊ እግረኞች መቀጣታቸውን የከተማዋ የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን እወቁልኝ ብሏል። 📌ከነዚህም መካከል 30 ሺህ 616 የሚሆኑት  በገንዘብ እንዲሁም 37 ሺህ 790 እግረኞች ደግሞ የአገልግሎት ስራ እንዲሰሩ መደረጋቸው ተጠቁሟል። 📌ቅጣቱ የተላለፈው ዜብራ ጠብቀው የማይሻገሩ፣ አደባባይ የሚያቋርጡ፣ እንዲሁም የትራፊክ መብራት በማያከብሩ እግረኞች ላይ መሆኑ ተገልጿል።

አዲስ የግብር አወሳሰን መመሪያ‼️ አዲስ የግብር አወሳሰን ለአከራዮች እና የሙያ አገልግሎት ሰጪዎች ይፋ ተደረገ‼️ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የ2017 የግብር ዘመን አዲስ የአወሳሰን ስርዓት ከሐምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆን ማድረጉን አስታወቀ። ይህ አዲስ መመሪያ የመኖሪያ ቤት አከራዮችን፣ የሙያ አገልግሎት ሰጪዎችን፣ እንዲሁም አንዳንድ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎችን ይመለከታል። የንግድ ስራ ያልሆነ ገቢ ያላቸው የመኖሪያ ቤት አከራዮች እና የንግድ ፍቃድ ሳይኖራቸው በሙያ ፍቃድ ብቻ አገልግሎት የሚሰጡ ግለሰቦች (እንደ ጠበቆችና ኢንሹራንስ ወኪሎች ያሉ) ከጠቅላላ ገቢያቸው 35 በመቶው እንደ ወጪ የሚቀነስ ሲሆን፣ ቀሪው 65 በመቶው ብቻ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ይሆናል። ይህ አሰራር የሂሳብ መዝገብ ማቅረብ ግዴታ ሳይኖርባቸው በግምት ገቢያቸው የሚሰላላቸውን ግብር ከፋዮች ጫና ለመቀነስ እና የግብር አሰባሰቡን ፍትሃዊ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ካፒታል ከመመሪያው ለመረዳት ችሏል። ከዚህ በተጨማሪ በህግ ደረሰኝ የመጠቀም ግዴታ የሌለባቸው የከተማ ውስጥ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች እንዲሁም በግል ኮድ 02 እና በንግድ ኮድ 03 የተመዘገቡ ተሽከርካሪ የኪራይ አገልግሎት ሰጪዎች ላይም አዲሱ መመሪያ ተፈፃሚ ይሆናል። ለእነዚህ ዘርፎች ግብሩ የሚሰላው በሰንጠረዥ "ሐ" መሰረት መሆኑን ተገልጿል። ከእነዚህ ዘርፎች ውጭ የሆኑ እና የሂሳብ መግለጫ የማቅረብ ግዴታቸውን ያልተወጡ ግብር ከፋዮች ግን ግብር ለመሸሽ በሚደረግ ተግባር እንደሚወገዱ ቢሮው አስጠንቅቋል። በዚህም መሰረት፣ የታክስ ጉዳቱ 40 በመቶ እና የታክሱ እጥፍ ቅጣት ሳይነሳ ገቢው እንደሚሰበሰብ ተገልጿል። #ካፒታል

ሀሰተኛ ባለ ሁለት መቶ ብር ወደባንክ ለማስገባት የሞከረ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዋለ 👉🏽“ወይፈን ሽጨ የተቀበልኩት ነው”ተጠርጣሪው በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን የገሳ ጫሬ ከ
ሀሰተኛ ባለ ሁለት መቶ ብር ወደባንክ ለማስገባት የሞከረ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዋለ 👉🏽“ወይፈን ሽጨ የተቀበልኩት ነው”ተጠርጣሪው በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን የገሳ ጫሬ ከተማ አስተዳደር 202 ፍሬ ወይንም 20‚400(ሃያ ሺህ አራት መቶ ብር) ስምንት ተመሳሳይ ቁጥሮች ያሏቸው ሀሰተኛ ባለሁለት መቶ ብር ወደ ባንክ ለማስገባት የሞከረ ተጠርጣሪን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያደረገ መሆኑን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገልፆአል። የኮሚሽኑ የወንጀል መረጃ እና ኢንተለጀንስ ዳይሬክቶሬት እንደገለፀው  ተጠርጣሪው በሰጠው ቃል ወይፈን በሬ ሸጦ በግብይት ላይ  ገዢዎች ገንዘቡን እንደሰጡት ቢገልፅም በህጉ መሠረት በእጁ የተገኘበት በአዘዋዋሪነት ይፈረጃል ሲል ፖሊስ መግለፁን ሸገር ታይምስ ሚዲያ የተመለከተው መረጃ ይጠቁማል። ፖሊስ ባስተላለፈው መልዕክት አርሶ አደሩ፣ሻጭና ሸማቾች የሚቀበሉትን ገንዘብ አጣርተው መቀበል እንዳለባቸውም ነው ያሳሰበው።

የስራ ማስታወቂያ ‼️
+4
የስራ ማስታወቂያ ‼️

በአዲስ አበባ ከተማ  በጥበቃ ስራ ከሚሰሩበት ተሸከርካሪ የሰረቁ ሦስት ግለሰቦች በወላይታ ሶዶ ከተማ በቁጥጥር ስር ዋሉ  በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ሶዶ ከተማ የክልሉ ፖሊስ ከብሔራዊ መረጃ ደህንነትና ከአዲስአበባ ፖሊስ ጋር በመሆን  በተሠራ ስራ ተጠርጣሪዎቹ ከተሽከርካሪው ሊያዙ ችለዋል። ድርጊቱን የፈፀሙት ተከሳሾች የስርቆት ወንጀሉን የፈጸሙት በአዲስ አበባ የካ ክፍለ ከተማ ውስጥ የጥበቃ ስራ ከሚሠሩበት ድርጅት እንደሆነ የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል። ግለሰቦቹ ተሽከርካሪዎችን ሠርቀው የተሰወሩ ቢሆንም ከተሰረቁት ተሽከርካሪዎች ውስጥ አንዱን  የክልሉ ፖሊስ ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በመሆን በትላንትናው እለት ማለትም ሰኔ29 ቀን2017ዓ/ም በሶዶ ከተማ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡ የተያዙት ተጠርጣሪዎችንና ተሽከርካሪውን የወንጀል ድርጊቱ ወደ ተፈጸመበት አዲስ አበባ ፖሊስ ተልኳል፡፡በአጠቃላይ አምስት ተሽርካሪዎች የተሰረቀ ሲሆን  አምስት ግለሰቦች ወንጀሉን እንደፈጸሙ ተገልጿል፡፡ በወላይታ ሦስት ተከሳሾች ከአንድ ተሸከርካሪ ጋር መያዙን የተነገረ ሲሆን በተለያዩ አካባቢዎች ላይ ይህን መሰል ድርጊቶች እየተበራከቱ በመምጣታቸውም በቀጣይ የቁጥጥር ስራው  ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል። #ዳጉ_ጆርናል

🌼🌼 ከ 800 በላይ ስራዎች ረፖርተር ጆብስ ( Reporter Jobs ) website ለይ ማግኘት ይችላሉ !! 🌼🌼  አሁኑኑ በፈለጉት አማራጭ ገብተው ያመልክቱ 🌟 አዲሱ ስራዎን በቀላሉ ያግኙ ! የረፖርተር  ስራዎችን በእነዚህ አማራጮች ማግኘት ይችላሉ፦ 💯 Website: www.ethiopianreporterjobs.com 💯 Facebook: http://bit.ly/2mPD7EG 💯 Telegram: https://bit.ly/3exwhdn 💯 Linkedin: https://bit.ly/2XJzm45 💯 Twitter: https://bit.ly/3cuJTnF 💯 Instagram: https://bit.ly/3fCE5j1 ይጎብኙን፤ ይከተሉን፤ ላይክ ሼር ያድርጉ። እናመሰግናለን። ⛔️⛔️በዚህ ሳምንት የወጡ ስራዎች ::•••••™ ✿::✿:: ✿::✿:: ✿™•••••:: ⛔️⛔️በዚህ ሳምንት የወጡ ስራዎች በ ስራ ቦታ ✅በ አዲስ አበባ የወጡ ስራዎች https://bit.ly/3rYVB41 ✅በ አማራ ክልል የወጡ ስራዎች https://bit.ly/3ErEGOI ✅በ ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የወጡ ስራዎች https://bit.ly/3NW1ucf ✅በ ሶማሌ ክልል የወጡ ስራዎች https://bit.ly/3NRuYrK ✅በ ኦሮሚያ ክልል የወጡ ስራዎች   https://bit.ly/3RG13mA ✅በ ደቡብ ክልል የወጡ ስራዎች https://bit.ly/3SLjZB6 ✅በ አፋር ክልል የወጡ ስራዎች https://bit.ly/3TjYGa4 ✅በ ትግራይ ክልል የወጡ ስራዎች https://bit.ly/3GUBlHM ✅በ ድሬደዋ የወጡ ስራዎች https://bit.ly/3hgQA4H ✅ Project based የሆኑ https://bit.ly/3fHiEx4 ::•••••™ ✿::✿:: ✿::✿:: ✿™•••••:: ::•••••™ ✿::✿:: ✿::✿:: ✿™•••••:: 💢 ከታች በተዘረዘሩት የሥራ ዘርፎች በተማሩበት መስክ ወይም የሙያ ስብጥር የሥራ ማስታወቂያዎችን ለማየት አንዲሁም ለማመልከት ሊንኮቹን ይጠቀሙ ✅Banking & Insurance  https://bit.ly/3xcxEKf ✅Finance & Accounting  https://bit.ly/3rfkkkp ✅NGO  https://bit.ly/3rdSNQq ✅Management  https://bit.ly/3v8JmTg ✅Economics  https://bit.ly/35XZJK6 ✅Public Relations https://bit.ly/37w1EWs ✅Nursing  https://bit.ly/3xvqVeH ✅Civil Engineering  https://bit.ly/3v4Jrrp ✅Electrical Engineering  https://bit.ly/3JomG6W ✅Mechanical Engineering  https://bit.ly/3JomG6W ✅Chemical Engineering  https://bit.ly/3JomG6W ✅Industrial Engineering  https://bit.ly/3JomG6W ✅Textile Engineering  https://bit.ly/3JomG6W ✅Hydraulics Engineering  https://bit.ly/3JomG6W ✅Food Engineering  https://bit.ly/3JomG6W ✅Const. & Architecture  https://bit.ly/3v4Jrrp ✅Insurance  https://bit.ly/3xcxEKf ✅IT & Telecom  https://bit.ly/35Ulpqj ✅Graphics Design  https://bit.ly/3rNxR30 ✅Hotel & Hospitality  https://bit.ly/3DVh6Yl ✅Healthcare  https://bit.ly/3xvqVeH ✅Agriculture  https://bit.ly/3KCZWBe ✅Driver  https://bit.ly/37z1rli ✅Legal  https://bit.ly/3LWVv4R ✅Language  https://bit.ly/3reDSoW ✅Business and Administration  https://bit.ly/3LNR3oM ✅Admin/Clerical & Secretarial  https://bit.ly/37tKgBN ✅Automotive, Machinery & Mechanic  https://bit.ly/3v7yqW2 ✅Logistics & Transportation  https://bit.ly/37z1rli ✅Advertising/Media & Journalism  https://bit.ly/3jjwvbJ ✅Education & Training  https://bit.ly/3NWVpfg ✅Human Resource  https://bit.ly/3re6jTX ✅Statistics  https://bit.ly/3Jp0xoQ ✅Pharmaceutical  https://bit.ly/35TZn74 ✅Travel & Tourism  https://bit.ly/3rd4nLB ✅Community & Social Science  https://bit.ly/37w1EWs ✅Customer Service & Support  https://bit.ly/3jmFngI ✅Program & Project Management  https://bit.ly/3DVikTr ✅Security  https://bit.ly/3DTkQtD ✅Cleaning  https://bit.ly/3uniwYu ✅Cook/Chef  https://bit.ly/3uniwYu ✅Supply Chain, Procurement & Purchasing  https://bit.ly/3NYu3W4 ✅Maintenance, Skilled Labor & Manufacturing  https://bit.ly/3uniwYu ✅Machine Operators https://bit.ly/3uniwYu ✅Environment & Natural Resource https://bit.ly/3EukR9n ✅Research & Science https://bit.ly/3Jp0xoQ ::•••••™ ✿::✿:: ✿::✿:: ✿™•••••:: 💯 Don't forget to share/ወዳጅ ዘመድዎ እንዲደርሰው ሼር ያድርጉ ::•••••™ ✿::✿:: ✿::✿:: ✿™•••••::🌼🌼 ከ 800 በላይ ስራዎች ረፖርተር ጆብስ ( Reporter Jobs ) website ለይ ማግኘት ይችላሉ !! 🌼🌼  አሁኑኑ በፈለጉት አማራጭ ገብተው ያመልክቱ 🌟 አዲሱ ስራዎን በቀላሉ ያግኙ !

ሐምሌ 1 2017 በኢትዮጵያ በስፋት አገልግሎት የሚሰጡ የግኙነት ሶፍትዌሮችን ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ በተሰሩት ለመተካት በሂደት ላይ መሆኑን ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ( #INSA ) ተናገረ፡፡ ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር እንደሰማነው ከሆነ ኢሜይል፣ ቴልግራምና ዋትሳፕን ጨምሮ ሌሎችም አለም አቀፍ ሶፍትዌሮች በሃገር ውስጥ በሚሰሩ ሶፍትዌሮች ተተክተው በመንግስት ተቋማት አገልግሎት መስጠት ችለዋል፡፡ ኢንሳ የሳይበር ደህንነትን ለማስጠበቅ ከምከውናቸው ስራዎች በተጨማሪ ለህዝብ አገልግሎት የሚውሉ ሶፍትዌሮችን እያበለፀግኩ አንዳንዶቹንም እየተካሁ ነው ብሏል፡፡ ይህንን ማድረግ ያስፈለገው የውጪዎቹን የመገናኛ ዘዴዎችን መጠቀም እንደ ሃገር ጥብቅ የሆኑ መረጃዎች ሳይቀሩ እንዲመዘበሩ ምክንያት ስለሚሆን ነው ያሉን የኢንሳ የሽያጭ ባለሙያው አቶ እሸቱ፤ በኢንሳ የተሰራው ’’ኤርጋሜይል’’ የተሰኘው ሶፍትዌር ኢ-ሜይልን ተክቶ ተቋማቸውን ጨምሮ በሌሎችም የመንግስት ተቋማት እየተሰራበት መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ሌላውና ቴልግራምንና ዋትስአፕን ተክቶ በተለይ በመንግስት ተቋማት እየተሰራበት ነው የተባለው  ’’ስርኩኒ’’ የተባለው ሶፍትዌር ነው፣ በዙም ለሚደረጉ ስብሰባዎች በሚል በኢንሳ የተሰራው ደግሞ ’’ደቦ’ የተባለው ሶፍትዌር መሆኑን አቶ እሸቱ ነግረውናል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የገቢዎች መስሪያ ቤት ግብር ለመሰብሰብ የሚጠቀምበትን የክፍያ ስርዓት እንዲሁም እያንዳንዱን የመሬት ይዞታ በዘመናዊ መንገድ ለመመዝገብ የተሰናዳው የካዳስተር ስርዓት ሰርቶ ያቀረበው ኢንሳ ነው ይላሉ ባለሙያው አቶ እሸቱ፡፡ እነዚህን ጨምሮ ሌሎችም በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር እየተሰናዱ ያሉና ሁሉንም አለም አቀፍ ሶፍትዌሮች ሊተኩ የሚችሉ ሶፍትዎሮች እንዳሉ ሰምተናል። ተቋሙ እስካሁን ሰርቶ የመንግስት ተቋማት የህዝብ አገልግሎት እንዲሰጡበት ያስረከባቸው ሶፍትዌሮች የወረቀት አሰራርን አስቀርተዋል፤ በተለይ የግብር አሰባሰብ ቀልጣፋ እንዲሆን አስችሏል፤ የካዳስተር ስርዓትም በአንድ የመሬት ይዞታ ሁለትና ሶስት ጊዜ ካርታ በማውጣት ይፈፀም የነበረውን ዘረፋ አስቀርቷል ተብሏል፡፡

ሳዑዲ አረብያ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ በሞት የምትቀጣቸው የውጭ ሀገር ዜጎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ነው - አምነስቲ - አብዘሃኛዎቹ ፈጸሙት የተባለው ወንጀል አደንዛዥ ዕፅ ጋር የተያያዘ ነው አለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል ያወጣው አዲስ ሪፖርት እንደሚያሳየው በሳዑዲ አረብያ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ የሞት ቅጣት የሚተላለፍባቸው የውጭ ሀገር ዜጎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል። አብዘሃኛዎቹ የሞት ቅጣት የተፈጸመባቸው እኒሁ ዜጎች ፈጸሙት ከተባሉት ወንጀሎች መካከል ከፍተኛ ቁጥሩን የሚይዘው የአደንዛዥ ዕጽ ዝውውር መሆኑን ሪፖርቱ አመላክቷል። የአደንዛዥ ዕጽ ዝውውር ወንጀል በአለም አቀፍ ሰብአዊ መብት ህግ እና መለኪያ የሞት ቅጣት የሚያስወስን አይደለም ያለው አምነስቲ ባሳለፍነው የሰኔ ወር ብቻ ሳዑዲ አረብያ 46 ሰዎች በሞት የቀጣች ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 37ቱ ከአደንዛዥ እጽ ጋር በተያያዘ መሆኑን ጠቁሟል፤ ከነዚህ ውስጥ 34ቱ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ የውጭ ሀገር ዜጎች ናቸው ብሏል። ለአምነስቲ ኢንተርናሽናል አናገርኩት ያለው አንድ የሞት ፍርድ የተላለፈበት ኢትዮጵያዊ ቤተሰብ “የፍርድ ቤት ዶክመንታቸውን መያዝ አለመያዛቸውን አናውቅም… ምንም አይነት ህጋዊ ሰነድ ማግኘት አልቻልንም፣ ምክንያቱም በሃገር ውስጥ ጉዳዩን የሚከታተልልን ሰው ስለሌለን፣ ህጋዊ ተወካይ ስለሌለን፣ የቋንቋ ችግርም አለ” ሲል መግለጹን ሪፖርቱ አካቷልል።(AS)

ሳዑዲ አረብያ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ በሞት የምትቀጣቸው የውጭ ሀገር ዜጎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ነው - አምነስቲ - አብዘሃኛዎቹ ፈጸሙት የተባለው ወንጀል አደንዛዥ ዕፅ ጋር የተያያዘ ነው አለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል ያወጣው አዲስ ሪፖርት እንደሚያሳየው በሳዑዲ አረብያ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ የሞት ቅጣት የሚተላለፍባቸው የውጭ ሀገር ዜጎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል። አብዘሃኛዎቹ የሞት ቅጣት የተፈጸመባቸው እኒሁ ዜጎች ፈጸሙት ከተባሉት ወንጀሎች መካከል ከፍተኛ ቁጥሩን የሚይዘው የአደንዛዥ ዕጽ ዝውውር መሆኑን ሪፖርቱ አመላክቷል። የአደንዛዥ ዕጽ ዝውውር ወንጀል በአለም አቀፍ ሰብአዊ መብት ህግ እና መለኪያ የሞት ቅጣት የሚያስወስን አይደለም ያለው አምነስቲ ባሳለፍነው የሰኔ ወር ብቻ ሳዑዲ አረብያ 46 ሰዎች በሞት የቀጣች ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 37ቱ ከአደንዛዥ እጽ ጋር በተያያዘ መሆኑን ጠቁሟል፤ ከነዚህ ውስጥ 34ቱ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ የውጭ ሀገር ዜጎች ናቸው ብሏል። ለአምነስቲ ኢንተርናሽናል አናገርኩት ያለው አንድ የሞት ፍርድ የተላለፈበት ኢትዮጵያዊ ቤተሰብ “የፍርድ ቤት ዶክመንታቸውን መያዝ አለመያዛቸውን አናውቅም… ምንም አይነት ህጋዊ ሰነድ ማግኘት አልቻልንም፣ ምክንያቱም በሃገር ውስጥ ጉዳዩን የሚከታተልልን ሰው ስለሌለን፣ ህጋዊ ተወካይ ስለሌለን፣ የቋንቋ ችግርም አለ” ሲል መግለጹን ሪፖርቱ አካቷልል።(AS)