ch
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

关闭频道
1 146
订阅者
-224 小时
-47
-1930
帖子存档
የካቲት 12/2017 ዓ.ም ለ6ኛ ዙር ስራ ፈላጊ ወገኖች የህይወት ክህሎት ስልጠና መስጠት ተጀመረ ። ከጉለሌ ክ/ከተማ 9 ወረዳዎች ለተወጣጡ ለስራ ፈላጊ ወገኖች መደበኛውን የሙያ ስልጠና ከመጀመራቸው
+6
የካቲት 12/2017 ዓ.ም ለ6ኛ ዙር ስራ ፈላጊ ወገኖች  የህይወት ክህሎት ስልጠና መስጠት ተጀመረ ። ከጉለሌ ክ/ከተማ  9 ወረዳዎች  ለተወጣጡ ለስራ ፈላጊ ወገኖች መደበኛውን የሙያ ስልጠና  ከመጀመራቸው በፊት የህይወት ክህሎት ስልጠና የሚሰጣቸው ሲሆን ሰልጣኞች እንደየ ዝንባሌያቸው ስራ ፈጥረው ለመስራት የሚያስችላቸውን የተግባቦት አቅምን በማሳደግ ስራቸውን በአግባቡ ለመከወን የሚያግዛቸው እና  በህይወታቸው ስኬታማ ለመሆን መከተል ያለባቸውን ነገሮች በውል ለመገንዘብ የሚያስችላቸው መሆኑ ተገልጿል። በዚህ ስልጠና የተሳተፉት ከ 5,000 በላይ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።  በያዝነው ሳምንት የህይወት ክህሎት ስልጠናውን አጠናቀው በቀጣይ  የሙያ ስልጠናውን የሚጀምሩ ሲሆን ከስልጠና በኋላ በምዘና ብቃታቸውን አረጋግጠው የሚወጡ ይሆናል በማለት የስልጠና አስተባባሪው አቶ ታደሰ አበራ መረጃውን አጋርተውናል።                        ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ረቡዕ የካቲት 12/2017ዓ.ም የኮሌጃችን የlSO 21001:2018EOMS ትግበራ በውስጥ ኦዲት ተገመገመ ። ኰሌጃችን የISO 21001:2018 EOMS እውቅና የማግኘት መርሀግብር በሰፊው እየ
+6
ዕለተ ረቡዕ የካቲት 12/2017ዓ.ም የኮሌጃችን የlSO 21001:2018EOMS ትግበራ በውስጥ ኦዲት ተገመገመ  ። ኰሌጃችን የISO 21001:2018 EOMS እውቅና የማግኘት መርሀግብር በሰፊው እየተሠራበት ያለና ወደ መጨረሻው የማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ የደረሰ ሲሆን በትላንትናው ዕለት የተጀመረው የውስጥ ኦዲት ሦስት ዓላማዎች አሉት እነሱም 1. የመሻሻል ዕድሎች እና በውስጥ ኦዲት የተገኙት ክፍተቶች ያሉበትን ደረጃ መፈተሽ ። 2. በድጋሚ የሚታዩ ክፍተቶችን መለየት እና  ማስተካከል። 3. ለውጭ ኦዲት ምዘና ብቁ ሆኖ ለመገኘት ሲሆን  ኦዲቱ በኮሌጁና በሽሮ ሜዳ ካምፓስ የሚካሄድ መሆኑ ታውቋል ። የ ISO 21001:2018EOMS ትግበራ ንቅናቄ ሁሉን አቀፍ በሆነ መልኩ ከእያንዳንዱ ባለድርሻ አካላት ጋር ግንዛቤ በመፍጠር የአሰራር ሂደቱን ከማሻሻል አንጻር ስራዎች እንደሚሰሩ የገለጹት አስተባባሪው አቶ ሚካኤል ጎኣ ሱፐፐር ቪዥኑ በሦስት ቡድን የተዋቀረ  የግምገማ ቡድን እንደሚካሄድም ጠቁመዋል ።                         ኮሙኒኬሽን ቡድን

ሰላም የኮሌጃችን የህይወት ክህሎት አሰልጣኞች በሙሉ ከMOLS በተላለፈ መልዕክት መሰረት በቀጣይ አርብ እና ቅዳሜ በ14 እኛ 15  በተከለሰው ብቃት የወጣቶች የህይወት ክህሎት ስልጠና የአሰልጣኞች ስልጠና TOT ስለሚስጥ ሁሉም አሰልጣኝ ከጠዋቱ 3: 00 በሰዓቱ NCR  እንድትገኙ። ማሳበቢያ 👉 በዚህ የTOT ስልጠና ያልስለጠነ በቀጣይ ምደባ የማይሰጥ መሆኑን እናሳውቃላት። 👉 ስርተፊኬት ኮፒ  ያላስገባችሁ  እንድታሰገቡ እናሳስባለን።

ዕለተ ማክሰኞ የካቲት 11/2017ዓ.ም የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ለሠልጣኞች ተዘጋጀ። በመጀመሪያ ኰሌጃችን እያከናወነ ላለዉ የISO 21001:2018EOMS እውቅና የማግኘት መርሀግብር በሰፊው እየተ
+7
ዕለተ ማክሰኞ የካቲት 11/2017ዓ.ም የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ለሠልጣኞች ተዘጋጀ። በመጀመሪያ ኰሌጃችን እያከናወነ ላለዉ የISO 21001:2018EOMS እውቅና የማግኘት መርሀግብር በሰፊው እየተሠራበት ያለና ወደ መጨረሻው የማጠናቂያ ምዕራፍ ላይ መሆኑ ይታወቃል። እውቅና የማግኘት ዓላማው ለሠልጣኙ፣ ለአሠልጣኙ፣ ለኰሌጁም ሆነ ለሀገር ያለውን ፋይዳ በመገንዘብ ሠልጣኞች በዚህ የተቀደሰ ተግባር ግንዛቤ ኖሮአቸው ተሣታፊ እንዲሆኑ ታልሞ የተዘጋጀ መርሀግብር ሲሆን በዛሬው ዕለት ከቢዝነስ የሥልጠና ዘርፍ ከ350 በላይ ሠልጣኞች መሳተፋቸዉን ለማወቅ ተችሏል። የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናው በቀጣይ ቀናት በኰሌጁ ውስጥ ላሉት ሁሉም ሠልጣኞች የሚሰጥ መሆኑም ታውቋል። በመቀጠልም በግንዛቤ መፍጠሪያ መድረኩ የቀጠለው የEthio- coders የሙያ ስልጠና ሃሳቦች ሲሆኑ የሚከተሉትን የIT የክህሎት ስልጠናወችን እንደሚያካትት ከመረጃ ምንጮቹ ለማወቅ ተችሏል። "Artifical  intellgence , Android, Data science and Web Development"  የግንዛቤ ማስጨበጫ መረጃውን ያጋሩት አቶ አለማየሁ ፈንታ ሠልጣኞች በነዚህ የስልጠና መስኮች በኦንላይን ተምረው እንዲያጠናቅቁ  መክረዋል። ለዚህ ፕሮግራም ሥልጠና የሚረዳ መረጃም አጋርተዋል።  አቶ አለማየሁ ፈንታ ፕሮግራሙ ያለዉን ጠቀሜታ ሲያብራሩ ሠልጣኞች ባሉበት ቦታ ሆነዉ የሥራ ዕድል ለማፈላለግ ወይም ደግሞ ቀጣሪ እና ተቀጣሪ በቀላሉ ለመገናኘት ያስችላል ብለዋል።                        ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content

ENTOTO POLY TECHNIC COLLEGE 70 Days left ⤵️ For 100 years Anniversary

ዕለተ ዓርብ የካቲት 7/2017ዓ.ም ለlSO 21001:2018EOMS ትግበራ በውስጥ ኦዲት ግኝት ላይ በሽሮ ሜዳ ካምፓስ ውይይት ተካሄደ ። በመክፈቻው ፕሮግራም ላይ የተገኙት የሽሮ ሜዳ ካምፓስ ም/ዲ
+4
ዕለተ ዓርብ የካቲት 7/2017ዓ.ም ለlSO 21001:2018EOMS ትግበራ በውስጥ ኦዲት ግኝት ላይ በሽሮ ሜዳ ካምፓስ ውይይት ተካሄደ ። በመክፈቻው ፕሮግራም ላይ የተገኙት የሽሮ ሜዳ ካምፓስ ም/ዲን አቶ ተስፋጽዮን ኮሌጃችን ዕውቅና ለማግኘት የሚያስችለው ስራ ከብዙድካም በኋላ ወደ መጠናቀቂያው ምዕራፍ  መድረሱን አውስተው  በዚህ ምዕራፍ ላይ የlSO 21001:2018EOMS  ምንድ ነው ? የኮሌጁ የስልጠና ጥራት ፓሊሲ ምንድ ነው ? ምን ምን ተግባራትስ ይከናወናሉ ? እሚለውን ላይ ሰራተኞች ግንዛቤ እንዲኖራቸው ለማስቻል እና በቀጣይ ከኛ ምን ይጠበቃል? እሚለውን በትኩረት ልናጤነው ይገባልም በማለት አቅራቢውን አቶ እንግዳ ወንደሰንን ጋብዘዋል ። አቅራቢው አቶ እንግዳ ወንደሰን የlSO 21001:2018EOMS ትግበራችንን ለውጫዊ ምዘና/ External audit ለመጋበዝ የቀሩት ቀናት የተወሰኑ በመሆናቸው በቀሩት ቀናት የተገኙ Non-Conformity  መለየት ፣ማረምና ማስተካከል ይጠበቅብናል ብለዋል። አያይዘውም እያንዳንዱ ምን ምን መስተካከል አለበት የሚለውን እና ትኩረት ሊደረግበት ይገባል ያሏቸውን ጉዳዮች በዝርዝር አቅርበዋል ። በመቀጠልም ከቤቱ ሐሳብ አስተያየት ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል። በመጨረሻም በኮሌጁ ዲን አቶ ተስፋጽዮን ትኩረት ሊሰጥባቸው ይገባል የተባሉት ላይ በአጽንኦት የስራ አቅጣጫ ሰጥተዋል ።                      ኮሙኒኬሽን ቡድን

ሐሙስ የካቲት 6/2017ዓ.ም ከጉለሌ ክ/ከተማ ለተውጣጡ ስራ ፈላጊ ወጣቶች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ። ከጉለሌ ክ/ከተማ ለተውጣጡ ከ1100 በላይ ለሆኑ ስራ ፈላጊ ዜጎች ሲሰጥ የሰነበተው የን
+4
ሐሙስ የካቲት 6/2017ዓ.ም ከጉለሌ ክ/ከተማ ለተውጣጡ ስራ ፈላጊ ወጣቶች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ። ከጉለሌ ክ/ከተማ ለተውጣጡ ከ1100 በላይ ለሆኑ ስራ ፈላጊ ዜጎች ሲሰጥ የሰነበተው የንግድ ስራ ስልጠና በዛሬው ዕለት  መጠናቀቁን አስተባባሪው አቶ ታደሰ አበራ  መረጃውን አጋርተውናል ።                          ኮሙኒኬሽን ቡድን

የአልጋወራሽ ኃ/ሥላሴ የሉክሰንበርግ ጉብኝት 100ኛ ዓመት ሲታወስ! ከሰዓሊ ኃይሉ ክፍለ ጋር የተደረገ ቆይታ በለዛ... https://youtu.be/083zpEH5Fkw
የአልጋወራሽ ኃ/ሥላሴ የሉክሰንበርግ ጉብኝት 100ኛ ዓመት ሲታወስ! ከሰዓሊ ኃይሉ ክፍለ ጋር የተደረገ ቆይታ በለዛ... https://youtu.be/083zpEH5Fkw

ዕለተ ሐሙስ የካቲት 6/2017ዓ.ም ለlSO 21001:2018EOMS ትግበራ በውስጥ ኦዲት ግኝት ላይ በስልጠና ዘርፎች ውይይት ተካሄደ ። የlSO 21001:2018EOMS ትግበራን አስመልክቶ በሦስት
+9
ዕለተ ሐሙስ የካቲት 6/2017ዓ.ም ለlSO 21001:2018EOMS ትግበራ በውስጥ ኦዲት ግኝት ላይ በስልጠና ዘርፎች ውይይት ተካሄደ ። የlSO 21001:2018EOMS ትግበራን አስመልክቶ በሦስት ዙር የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ መሠጠቱ ይታወሳል ። ስልጠናው  የውስጥ ኦዲት  ስራውን አጠናክሮ በመቀጠል የተገኙት Non-Conformity  በመለየት ፣በማረምና በማስተካከል ኮሌጁ የሚያደርገው የዕውቅና ጉዞ ውጤታማ እንዲሆን በሁሉም ስልጠና ዘርፎች አሠልጣኙ በቂ ግንዛቤ እንዲኖረው በየስልጠና ዘርፉ እና በየክፍሉ እንዲወያይበት በተሰጠው አቅጣጫ መሠረት በዛሬው ዕለት በቴክስታል ጋርመንት እና በአውቶሞቲቭ ስልጠና ዘርፍ ውይይቱ ተካሂዷል።                      ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ረቡዕ የካቲት 5/2017ዓ.ም ለlSO 21001:2018EOMS ትግበራ በውስጥ ኦዲት ለክትትል ስራ የጋራ መድረክ ተከናወነ ። የlSO 21001:2018EOMS በውስጥ ኦዲት አጠናክሮ መቀጠል ስራ
+6
ዕለተ ረቡዕ የካቲት 5/2017ዓ.ም ለlSO 21001:2018EOMS ትግበራ በውስጥ ኦዲት ለክትትል ስራ የጋራ መድረክ ተከናወነ  ። የlSO 21001:2018EOMS በውስጥ ኦዲት አጠናክሮ መቀጠል ስራው የሚፈልገውን እና በየዘርፉ የተከናወኑ እንዲሁም የተገኙት Non-Conformity  በመለየት ፣በማረምና በማስተካከል ኮሌጁን አንድ እርምጃ ከፍ ለማድረግ ፖሊሲውን መረዳት ወሳኝ ነው ። በሦስተኛ ዙር የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ማኔጅመንቱ ፣ አካዳሚክ ኮሚሽን እና አስተባባሪዎች የተሳተፉበት ሲሆን Root cause analysis and corrective action ላይ በአስተባባሪው አቶ ሚካኤል ጎኣ ሰፊ ማብራሪያ ቀርቧል።  ከዚህም በመቀጠልም ኮሌጁን ለውጫዊ ምዘና/ External audit ዝግጁ የማድረግ ስራ እንደሚሰራ የጠቆሙት አስተባባሪው እያንዳንዱ ስራ የሚከናወንበትን ፕሮግራምም አሳውቀዋል ። በመቀጠልም የኮሌጁ ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ ስልጠናው ያልተጠናቀቁ ስራዎቻችንን የምናስተካክልበት እና በቀጣይ ላለው ውጫዊ ምዘና  የምንዘጋጅበት ነው ያሉት ዲኑ እስካሁን ያለው ሂደት በውስን ስራዎች ላይ ብቻ ያጠነጠነ መሆኑ በአጠቃላይ ISO ን አስመልክቶ የግንዛቤ ክፍተት መኖሩን አመላካች በመሆኑ አሁን በተሰጠን አቅቃጣጫ መሠረት ባሉን ቀሪ ግዚያት አድምተን መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል። በአጠቃላይ ከውይይቱ/ከስልጠናው ተሳታፊዎች  አስተያየት፣ ጥያቄና ሊፈቱ የሚገባቸው ያሏቸውን ጉዳዮች በማንሳት ውይይት ተካሂዶባቸዋል ።               ኮሙኒኬሽን ቡድን

የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መረጃዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን እስካን አድረገው ይቀላቀሉ፡፡ ኮሙኒኬሽን ቡድን
የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መረጃዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን እስካን አድረገው ይቀላቀሉ፡፡ ኮሙኒኬሽን ቡድን

የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መረጃዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን እስካን አድረገው ይቀላቀሉ፡፡ ኮሙኒኬሽን ቡድን
የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መረጃዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን እስካን አድረገው ይቀላቀሉ፡፡ ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content

የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መረጃዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን እስካን አድረገው ይቀላቀሉ፡፡ ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ማክሰኞ የካቲት 4/2017ዓ.ም ወቅታዊ የክትትል ስራ በISO የትግበራ ሂደት ተከናወነ ። በመክፈቻ ፕሮግራሙ ንግግራቸዉ ዶ/ር ከበደ የISO ትግበራው እና ፍጻሜው የሁሉም የዚህ ፕሮግራም ተዋና
+9
ዕለተ ማክሰኞ የካቲት 4/2017ዓ.ም ወቅታዊ የክትትል ስራ በISO የትግበራ ሂደት ተከናወነ  ። በመክፈቻ ፕሮግራሙ ንግግራቸዉ ዶ/ር ከበደ የISO ትግበራው እና ፍጻሜው የሁሉም የዚህ ፕሮግራም ተዋናዮች የጋራ ህልማችን በመሆኑ እስከ የካቲት 30 ድረስ ሰርተን ማጠናቀቅና ዕውቅና ለማግኘት የሚደረገውን ጉዞ ማሳለጥ ዋነኛ ተግባራችን ሊሆን ይገባል ብለዋል ። ሁላችንም እይታችን ክፍተቶችን በማጥበብ ወደ አንድ አቅጣጫ ኮሌጃችንን እውቅና እንዲያገኝ ማስቻል የሚለው የጋራ ሃሳባችን መሆን አለበት በማለት መልካም የቆይታ ግዜን ተመኝተው ውይይቱ ተጀምሯል ።  በውስጥ ኦዲት የተገኙት Non-Conformity በማረምና በማስተካከል ኮሌጂ አንድ እርምጃ ከፍ ለማድረግ ፖሊሲውን መረዳትና የጋራ ውይይት በማድረግ ወደ ስራ መግባትን ለመፍጠር የተመቻቸ መድረክ ነው ። በዛሬው ዕለት የቀረበው ለ lSO አስተባባሪዎች ፣ ለ lSO የውስጥ ኦዲት ቡድን ስለ lSO 21001:2018EOMS በውስጥ ኦዲት ግኝት መሠረት እና ተቋሙን ለውጫዊ ምዘና ዝግጁ ለማድረግ የጋራ ግንዛቤ ሊፈጠርባቸው የሚገቡ 6 ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ያቀረቡት አቶ እንግዳ ወንደሰን ውይይቱ የበለጠ የተጠናከረ እንዲሆን በቡድን ውይይት በማጎልበት ለቀጣይ የስራ አቅጣጫ ተሰጥቷል  ። በተመሳሳይ ለፀሐፊዎች ፣ለባለሙያዎች እና የጥበቃ ሰራተኞች የከሰዓቱን መድረክ የያዙት አቶ ታደሰ ወርቅነህ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል ። ከቤቱ የተነሱ ሐሳብ አስተያየቶች ውይይት ተደርጎባቸዋል ።               ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content

photo content
+1

ዕለተ ቅዳሜ የካቲት 1/2017ዓ.ም የ6 ወር ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ተከናወነ። የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ በመጡ የሱፐርቪዥን ቡድን የ6 ወር ዕቅድ ክንውኑ ተገመገ
+9
ዕለተ ቅዳሜ የካቲት 1/2017ዓ.ም    የ6 ወር ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ተከናወነ። የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ  ከአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ በመጡ የሱፐርቪዥን ቡድን  የ6 ወር ዕቅድ ክንውኑ ተገመገመ። የግምገማ ቡድኑ የመገምገሚያ መስፈርቶችን መሠረት በማድረግ የሰነድ መረጃዎችን ከማረጋገጥ በተጨማሪ ከሚመለከተው አካል ማብራሪያዎችን በመጠየቅ ግምገማውን አካሂደዋል። የግምገማ ቡድኑን የመሩት አቶ ቸርነት የግምገማውን ዓላማ ሲገልጹ ኮሌጁ ለአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ  የላከው የ6 ወር የስራ አፈጻጸም  ሪፖርት በቢሮው የተገመገመ ሲሆን የቀረበውን ሪፖርት በመረጃ የተደገፈ እና መሬት ላይ ያለውን አፈጻጸም  ለማመሳከር መሆኑን ለኮሌጁ አመራርና ለሚመለከታቸው ባለሙያዎች አስረድተዋል ። ግምገማው  ሁለት ዓበይት ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሲሆን   ቁልፍ ተግባራት እና የዕለት ተዕለት ተግባራትን አካቷል። እነኝህም የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን፣ ስልጠና ነክ ጉዳዮች እና የአቅም ግንባታ ስራዎች መሆናቸው ታውቋል ።  በአጠቃላይ የግምገማ ሂደቱ በግልጽ መረጃዎችን  የተለዋወጡበት ፣ መስተካከል ያለባቸው ጉዳዮች የተጠቆሙበት ፣ ኮሌጁ ያለውን እምቅ አቅም በመጠቀም በቀጣይ መስተካከል ያለባቸውን እና የተሰጡ አቅጣጫዎች ወደተግባር በመቀየር በቀጣይ 6 ወራት አሁን የታዩ ክፍተቶችን ለማስተካከል እንሰራለን በማለት አሳስበዋል የኮሌጁ ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ።                    ኮሙኒኬሽን ቡድን

Entoto Ptc (Tms) 1917: በኮሙኒኬሽን ቡድን ስራዎች ላይ ያለዎትን ሃሳብ አስተያየት የሚያሳውቁበት ስለሆነ ፎርሙን መሙላትዎን አይዘንጉት፡፡ https://forms.gle/H19SMjJi6VJqyQ5n6