1 146
订阅者
无数据24 小时
-37 天
-1830 天
帖子存档
1 146
#ባህር_ዛፉ_ወይስ_እሸትና_አትክልቱ?
በእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ አስደናቂ #የግብርና_ስራ እየተከናወነ ነዉ።
ነሐሴ 22 ቀን 2016 ዓ.ም
""""""""""<<<<>>>>""""""""""
በእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ ከዚህ በፊት በባህር ዛፍ ተሸፍኖ የነበረ ከሶስት ሄክታር የበለጠ ቦታ በእንጦጦ እና አካባቢዉ ለሚኖሩ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው 7 ማህበራት ( 70 አባወራዎችና እማወራዎች ) እንዲሁም የኮሌጃችን ሰራተኞች ተሰጥቶ በሚያስደነቅ ሁኔታ በአዝርእትና በአትክልት እየለማ ይገኛል።
በ1886 ዓ.ም አካባቢ አፄ ምኒሊክ ከአውስትራሊያ አስመጥተው በእንጦጦ ጋራ አካባቢ በማስተከል ያስተዋወቁት ፤ ባህር ተሻግሮ የመጣ እፅ ነውና የባህርዛፍ ሲል የሰየሙት ተክል በፍጥነት የሚያድግ ፣ በወቅቱ የነበረዉን የማገዶ እና የግንባታ ፍጆታ የቀረፈ ባለዉለታ ተክል ነበር። ይሁን እንጅ ከስነ ምህዳር ጥበቃና እንክብካቤ አንጻር ከጥቅሙ ጉዳቱ እንደሚያመዝን ባለሙያዎች ይናገራሉ ።
ከ700 በላይ ዝርያ ያለው ባህርዛፍ በኢትዮጵያ 9
የሚደርሱ ዝርያዎች እንዳሉት ይነገራል። የከርሰ ምድርን ውሃን የመምጠጥ አቅሙ እስከ 40 ሜትር እንደሚደርስ እና በርሃማነትን በማስፋፈፋት ረገድ ከፍተኛ ተፅዕኖ እንዳለውም ይነገራል፡፡ ቅጠሉ በቶሎ የማይበሰብስ በመሆኑም የመሬት ለምነትን ይቀንሳል ፣ ውሀ ከመጠን በላይ ስለሚፈልግ የሌሎችን እፅዋት ምግብ ስለሚሻማ በአካባቢው ሌሎች እፅዋት እንዳይበቅሉና እንዳያድጉ ያደር ጋል፡፡
ይሁን እንጅ በእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ ግቢ ዉስጥ ከሶስት ሄክታር በላይ ሸፍኖ የነበረን የባህር ዛፍ ተክል በማስወገድ በምትኩ የተለያዪ አዝርእትና አትክልቶች እየለሙበት ይገኛል። ዘመናዊ የግብርና መርህን መሰረት ያደረገዉ የእርሻ ስርአት ከአዝርት መካከል በቦታው ገብስ፣ ባቄላ እና በቆሎ እሸት የተዘራበት ሲሆን ከአትክሎቶች ደግሞ ሽንኩርት ፣ ቆስጣ ፣ ሰላጣ ፣ ዱባ እና ቃሪያ በማብቀል የማሕበሩ አባላት ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን ከመጥቀም አልፈው ለኮሌጁ ማህበረሰብ በአነስተኛ ዋጋ በማቅረብ ላይ ይገኛሉ።
በወቅቱ የግቢዉ ባህርዛፍ በሚቆረጥበት ወቅት አንዳንድ ግለሰቦች በአሉታዊ መልኩ የተመለከቱት ቢሆንም ግቢዉን ከጫካነት መንፈስ ከማዉጣት በተጨማሪ ለወገን እና ሀገር የሚጠቅም ስራ እየተሰራበት እንደሚገኝ የማሕበራቱ እንቅስቃሴ ጉልህ ማሳያ ነዉ። በነገራችን ላይ ባህር ዛፍን ለሀገራችን ያስተዋወቀችው አውስትራሊያ እንኳ ጉዳቱን በማጤን በአሁኑ ሰአት ዛፉ እንዳይተከል በህግ ከልክላለች፡፡
ታዲያ ባህር ዛፉ ወይስ እሸትና አትክልቱ ነዉ ጠቃሚ?
ፍርዱን ለአንባቢያን በመተዉ ለሰሩ እጆች እና ለመልካም አሳቢያን ግን አድናቆታችንን እንቸራለን።
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
በእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ የአስተዳደር ሰራተኞች
#ግምገማዊ መድረክ እየተካሄደ ነዉ።
ነሐሴ 18 ቀን 2016
ትኩረቱን ሕብረ ብሄራዊ አንድነትን ማጎልበት ፣ የወል ታሪክን መፍጠር ፣ የሀገር አንድነትን ፣ ወንድማማችነትን ፣ ሀገር ወዳድነትን፣ ሠራተኝነትን፣ ቁርጠኝነትን ማጎልበት ፣ የመከባበር መንፈስን መፍጠር ፤ ለአንድ ኣላማ ለአንድ ግብ መትጋት፤ ለሀገር ዘላቂ ሰላም ፣ እድገትና አወንታዊ አመለካከት የነቃ ተሳትፎን ማድረግና ጠንካራ አገራዊ መንግስት መመስረት ያደረገ ግምገማዊ መድረክ በእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ እየተካሄደ ነዉ።
ስልጠናዉን እየተከታተሉ የሚገኙት የእንጦጦ እና አራዳ ክላስተር የአስተዳደር ሰራተኞች ሲሆኑ የአዲስ አበባ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች እያወያዪት ይገኛሉ ። በሂደቱም የጋራ የመወያያ ሰነድ ቀርቦ በትንንሽ ቡድኖች ዉይይት የተደረገ ሲሆን ሕብረ ብሄራዊ አንድነት ማጠናከር ፣ እንደ ሀገር እንቅፋት የሆነዉ ሌብነት እና ብልሹ አሰራር፣ እንደ ሀገር ሰላማችንን ያሳጡን ተግዳሮቶች ፣ ዲሞክራሲን የሚገዳደረዉ የአድር ባይነት አመለካከት ፣ የቴ /ሙ ስልጠና ሂደት ማነቆዎች አና አሁናዊ አገራዊ ሁኔታዎች ላይ በዋነኝነት ዉይይት እየተደረገ ነዉ። ዉይይቱ ዛሬና ነገ የሚከናወን ይሆናል።
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+5
ዕለተ ዓርብ ነሐሴ 17/2016ዓ.ም
በኤስቴቲክስ ስልና ዘርፍ የስፖርት ትምህርት ክፍል በአዲሱ የስልጠና ፖሊሲ የሠለጠኑ ሠልጣኞች በከተማ ደረጃ የተዘጋጀውን ምዘና ተመዘኑ ።
የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ልዩ በሆነበት በኤስቴቲክስ ስልጠና ዘርፍ ከሚሰጡ ስልጠናዎች መካከል የስፖርት ት/ት ክፍል አንዱ ሲሆን በአዲሱ የስልጠና ፖሊሲ የሰለጠኑ የደረጃ 4 የእግር ኳስ አሰልጣኝነት ሰልጣኞች በከተማ ደረጃ በተዘጋጀውን የንድፈ ሃሳብ እና የተግባር ምዘና ተመዝነዋል ።
16 ወንዶች እና 1ሴት ለምዘና የተቀመጡ ሲሆን 16ቱ በምዘናው ብቃታቸው ተረጋግጧል።
ይህ ምዘና በቀጣይ በሐገራቀፍ ደረጃ ለሚዘጋጀው የCOC ምዘና የዝግጅት ምዕራፍ እንደሚሆን የምዘናው አስተባባሪ አቶ ይስሃቅ አበራ ገልጸዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+6
የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተከናወነ ።
ነሐሴ 15/2016ዓ.ም
"የምትተክል ሀገር የሚያፀና ትውልድ"
በሚል መሪ ቃል የሚከናወነው የ6ኛው ዙር ሃገር አቀፍ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካል የሆነውና እንደሃገር 600,000,000 እንደ ከተማ/የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዛሬው ዕለት 6,000,000 ችግኞችን ለመትከል የወጣው መርሃ ግብር እውን እንዲሆን በዛሬው ዕለት ኮሌጃችን 1400 የተለያዩ ዝርያ ያላቸው ችግኞችን የመትከል መርሃ ግብር አከናውኗል።
ችግኞችን በመትከል ምህዳርን ለመጠበቅ ያለውን ወሳኝነት ከግምት በማስገባት በመጪው የበጋ ወራት የተከልናቸውን ችግኞች በመንከባከብ የበኩላችንን እንወጣ ። ለቀጣዩ ትውልድ አሻራችንን እናኑር!!!
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ሰላም እንዴት ናችሁ!!!
የኮሌጃችን ቁጠባና ብድር የተለያዩ የቤት ውስጥ መገልገያ እቃዎችን ለተቋሙ ሰራተኞች በብድር ውል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሲመዘግብና ከአቅራቢዎች ጋር በመሆን እቃዎችን በኮሌጁ ካፌ እያሳየ መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም የኮሌጁ አሰልጣኞች በቀጣይ ሳምንት ስልጠና ስለሚገቡ እቃዎችን ለመስጠት ስለምንቸገር ዛሬ በቀን 17/12/2016 ዓ.ም ከ8:30 ሰዓት ጀምሮ ፎርሙን እንድትሞሉ እያሳሰብን ሰኞ በቀን 20/12/2016 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ፎርም ማስሞላትና እቃ መስጠቱን የምናጠናቅቅ መሆኑን እናሳውቃለን።
ማኅበሩ
1 146
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴ/ሙ ትምህርትና ሥልጠና ሲከታተሉ የነበሩ #ሰልጣኞች_ተመረቁ።
ነሐሴ 16 ቀን 2016
የሀገሪቱን የገበያ ፍላጎት መሰረት አድርገዉ በተቀረጹ 22 የቴ/ሙ የስልጠና ዘርፎች የተግባር እና የንድፈ ሀሳብ (70/30) ስልጠናቸዉን በሚገባ አጠናቀዉ በሙያ ምዘና ብቃታቸዉን ያረጋገጡ 5120 ሰልጣኞች በዛሬዉ እለት በሚሊኒየም አዳራሽ በደማቅ ሥነ ስርአት ተመርቀዋል።
በምርቃት ሥነ ስርአቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክብርት አዳነች አቤቤ፣ ም/ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ፣ በም/ከንቲባ ደረጃ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ፣ የአ/አ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ፣ የቴ/ሙ ኮሌጆች አመራሮች፣ የተመራቂ ቤተሰቦች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በዛሬዉ እለት የተመረቁት ሰልጣኞች ከ14 የቴ /ሙ ኮሌጆች (6ፖሊ ቴ/ኮ እና 8 ኮሌጆች ) የተወጣጡ ሲሆን ስልጠናቸዉን ከደረጃ ሁለት እስከ አምስት የተከታተሉ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል ። ከአጠቃላይ ተመራቂዎች መካከልም 488 ሰልጣኞች በእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ ስልጠናቸውን የተከታተሉ ናቸዉ።
የዛሬ ተመራቂ ሰልጣኞች በተለይም ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክብርት አዳነች አቤቤ በተላለፈላቸዉ መልእክት የከተማዋን ብሎም የኢንዱስትሪዉን የሰለጠነ የሰዉ ሃይል ፍላጎት በሟሟላት በኩል ትልቅ አበርክቶ እንደሚጠበቅባቸው ፣ ከሃገር አልፎ በዉጭ አገር ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የተገለጸ ሲሆን በከተማዋ ልዪ ልዪ የልማት እንቅስቃሴ በሙያቸዉ እንዲሳተፉ ፣ ሥራን ሳይንቁ እንዲሰሩ ፣ ሀገርና ወገንን በቅንነት እና በታማኝነት ለማገልገል ቃል በመግባት በድምቀት ተምረቀዋል።
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+6
የቀድሞ የተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ተማሪዎች ህብረት በኮሌጁ ቅጥር ግቢ የችግኝ ተከላ አከናወኑ ።
ነሐሴ 15/2016ዓ.ም
"የምትተክል ሀገር የሚያፀና ትውልድ"
በሚል መሪ ቃል የሚከናወነው የ6ኛው ዙር ሃገር አቀፍ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካል የሆነውና የቀድሞ የተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ተማሪዎች ህብረት ከእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በጋራ በኮሌጁ ቅጥር ግቢ የተለያዩ ዝርያ ያላቸው ችግኞችን በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
በእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ የአሰልጣኞች
#ስልጠናዊ_ግምገማ እየተካሄደ ነዉ።
ነሐሴ 14 ቀን 2016
ትኩረቱን ሕብረ ብሄራዊ አንድነትን ማጎልበት ፣ የወል ታሪክን መፍጠር ፣ የሀገር አንድነትን ፣ ወንድማማችነትን ፣ የሀገር ወዳድነትን፣ ሠራተኝነትን፣ ቁርጠኝነትንና የመከባበር መንፈስን ማስተሳሰር ፤ ለአንድ ኣላማ ለአንድ ግብ መትጋት ለሀገር ዘላቂ ሰላም ፣ እድገትና አወንታዊ አመለካከት የነቃ ተሳትፎን በቴ/ሙያ አሰልጣኞች ላይ ማስረጽ ያደረገ ስልጠናዊ ግምገማ በእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ እየተካሄደ ነዉ።
ስልጠናዉን እየተከታተሉ የሚገኙት በእንጦጦ እና አራዳ ክላስተር ማእከል የሚገኙ ከ400 በላይ የቴ /ሙ አሰልጣኞች ሲሆኑ ዉይይቱን የአዲስ አበባ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች እያወያዪት ይገኛሉ ። በሂደቱም የዉይይት ሰነድ ቀርቦ በትንንሽ ቡድኖች ዉይይት የተደረገ ሲሆን ሕብረ ብሄራዊ አንድነት ማጠናከር ፣ እንደ ሀገር እንቅፋት የሆነዉ ሌብነት እና ብልሹ አሰራር፣ እንደ ሀገር ሰላማችንን ያሳጡን ተግዳሮቶች ፣ ዲሞክራሲን የሚገዳደረዉ የአድር ባይነት አመለካከት ፣ የቴ /ሙ ስልጠና ሂደት ማነቆዎች አና አሁናዊ አገራዊ ሁኔታዎች ላይ በዋነኝነት ዉይይት እየተደረገ ነዉ።
ሁሉም አሰልጣኞች እየተሳተፉበት በሚገኘዉ በዚህ ስልጠናዊ ግምገማ አዲስ እይታ ፣ አዲስ አስተሳሰብ ያለዉ ምርታማ ሰራተኛን መፍጠር ፣ ለሃገር ዘላቂ ሰላምና አድገት የሚተጋ ሀገር ወዳድ ዜጋን መስራት ፣ ከትርክት የዘለለ በምክንያት እና በእዉነት የሚያምን አሰልጣኝን መፍጠር የስልጠናዉ ግብ ነዉ ሲሉ መረጃዉን የሰጡን የኮሌጁ ዋ/ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ የገለጹ ሲሆን ስልጠናዉ ዛሬና ነገ ቀጥሎ በመጭዉ አርብ እና ቅዳሜ ደግሞ ተመሳሳይ ይዘት ያለዉ ስልጠና ለአስተዳደር ሰራተኞች እንደሚሰጥ ገልጸዋል ።
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ሠላም እንደምን አምሽታችኃል በነገው መድረክ ላይ መገኘት ያለባችሁ አሠልጣኞች በሙሉ ከላይ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ሰዓት አክብራችሁ እንድትገኙ።
የመግቢያ ባጅ ነገ ጠዋት የሚሰጥ ይሆናል። የሠልጣኞች ምርቃት ሀሙስ ጠዋት ተመራቂ ሠልጣኝ የምታሰለጥኑ አሠልጣኞች መረጃው ለሰልጣኞች ተደራሽ እንዲሆን መልህክት ይነገራቸው።
መልካም አዳር
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
