ch
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

关闭频道
1 148
订阅者
无数据24 小时
-27
-1930
帖子存档
photo content

ሐምሌ 9/2017ዓ.ም የኮሌጁ የ2017በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም እና የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ ዕቅድ ለኮሌጁ ማኔጅመንት እና አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት ቀርቧል። የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
+5
ሐምሌ 9/2017ዓ.ም የኮሌጁ የ2017በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም እና የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ ዕቅድ ለኮሌጁ ማኔጅመንት እና አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት ቀርቧል። የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የዕቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት በጠራው የጋራ መድረክ የ2017በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም እና የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ ዕቅድን ያቀረቡት የዳይሬክቶሬቱ ተጠሪ ወ/ሪት ፀዳለ አድማሱ ናቸው። ሪፖርቱ ሁለት ቁልፍ እና አምስት ዓበይት ተግባራትን የዳሰሰ ነበር ። በተያያዘም በኮሌጁ የተሰየመው የአፈጻጸም ግምገማ ቡድን ባደረገው ምልከታ መስተካከል አለበት ብሎ ባቀረበው ትችት ውስጥ ሪፖርቱ  ከበጀት ዓመቱ ዕቅድ ጋር ያልተጣጣሙ አንዳንድ ተግባራት መኖራቸውን አመላክቶ ማስተካከያ እንዲደረግበትና ተናባቢ ዕቅድና ሪፖርት እንዲቀርብ አቅጣጫ ሰጥቷል ። በቀረበው ዕቅድና ሪፖርት ላይ ከቤቱ የተለያየ አስተያየት ተሰጥቷል ። በተመሳሳይ የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ በቀረበው ሪፖርት ግልፀኝነት የሚፈልጉትን ግልፅ በማድረግ እና ያለመጣጣም የሚታይባቸው ዕቅድና ሪፖርት  በአፋጣኝ እንዲጣጣሙ ለማድረግ የማስተካከያ ስራ እንዲሰራ በዋናነት የዕቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት  ሀላፊነቱን መውሰድ እንደሚገባው አቅጣጫ ሰጥቷል። በመጨረሻም በቀጣይ ለሚኖረው የግምገማ መድረክ ጠንከር ያለ ማስተካከያ መደረግ እንዳለበትም አሳስበዋል ።                 ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content

ሰኔ 2017ዓ.ም        የምድረ ግቢ የልማት እንቅስቃሴ በከፊል በዛሬው ምልከታችን በመጠናቀቅ ላይ ባለው ዋናው በር ወደ ግቢው ከመዝለቃችን በፊት የዋናው ግቢ በር ዲዛይን ከውስጥ የሚጠብቀንን ታሪካዊ ህንፃ ምን እንደሚመስል እንዲያመላክት ታስቦበት የተዘጋጀ መሆኑን ዲዛይኑን  ያዘጋጀው እና የግንባታ ክትትሉን የሚያከናወነው የኮሌጁ  አሠልጣኝ ሚኪያስ ይርጋለም መረጃውን አጋርቶናል ።  ሚኪያስ በመቀጠል በከርቭ መልክ የተሰራውና ቄንጠኛው የመግቢያ በር በሁለት ቋሚዎች መካከል የሚገኝ እና በሚያማምሩ ጥርብ ድንጋዮች የተገነባ ነው። ይህም ጥንካሬውን፥ ታሪካዊነቱን፥ ወቅታዊነቱን እና ቀጣይነቱን ያሳያል ይላል። እንደ ሚክያስ ገለጻ የከርቭ ቅርጽ  በጥበብ ቋንቋ የፈጠራስሜትን ለማበረታታት፣ እድገትን ለማመላከት ያገለግላል ይላል። በመግቢያ በሩ ስራ አድናቆታችንን ገልፀን ወደ ግቢው ስንዘለቅ  ደግሞ ሌላ እይታችንን የሚማርክ ስራ ተመለከትን።  ለወትሮ በየዛፍ ጥላ ስር ቆመው የምናያቸው መኪኖች በስርዓት ተደርድረውና ማቆሚያ ቦታውን ብአግባቡ ተጠቅመው ለጥበቃ በሚያመች መልኩ እና በተስተካከለ የመኪና ማቆሚያ ስፍራ መኪኖች ስንመለከት አድንቀን ብቻ በማለፍ ንፉግ ለመሆን አልዳዳንም።  በህንጻ አስተዳደር ጽ/ቤት የምድረ ግቢ ቡድን ተወካይዋን ወ/ሪት አዜብ በልዳን ስራውን አስመልክተን ምስጋናችንን በማስቀደም ጥያቄያችንን አቀረብን ። ወ/ሪት አዜብ  በልዳም አድናቆታችንን ተቀብለው አመሰገኑን ፤ ቀጥለውም ከአሁን ቀደም መኪኖች በተበታተነ መልኩ ቆመው ለዕይታ የማይሰቡና ለቁጥጥር አስቸጋሪ ሆነው እንደነበር ገልጸው አሁን ግን በአግባቡ በተዘጋጀ ቦታ ሲቆሙ የደህንነት ስጋቱ ከመቀረፉ በላይ ለንጽህናም ለእይታም አመቺ በሆነ መንገድ እየተስተናገዱ ይገኛል።  አዲሱ የመኪና ፓርኪንግ ስፍራ በአንድ ግዜ 20 የሚደርሱ መኪኖችን የማስተናገድ አቅም እንዳለው ወ/ሪት አዜብ ነግረውናል። እኛም በርቱ ተበራቱ ብለናል። የመኪና ማቆሚያውን አልፈን ወደ ህንፃ 19 ስናመራ ሌላ ልማት ሌላ አስደናቂ ነገር ተመለከትን  በኤሌክትሮኒክስ እና ሰርቬንግ የስልጠና ዘርፍ አባላት የተገነባ መናፈሻ ስፍራ ከስራ ወጥቶም ሆነ ወደ ስራ ለመግባት መንፈሰን የሚያድሱበት የአትክልት ስፍራ በመቀመጫዎች የታጀበ ፣ የደመቀ ውብ የአትክልት ስፍራ ለእግረኞች መንቀሳቀሻ በተዘጋጁት መንገዶች ተንቀሳቅሰን መቀመጫዎቹም ላይ ለአፍታ ተቀምጠን መንፈሳችንን በማደስ ደስታውን ተጋራን።  ተነሳሽነቱን ወስደው በዚህ መልክ እንዲለማ ለሰሩት አሰልጣኞች አለማየሁ ተስፋዬ ፥ታምራት ቦዳ እና ፍቅረ ማርያም ቦጃን ለመልካም ስራቸው አመስግነን ኃላፊነቱን እንዴት እንደወሰዱ ጠይቀናቸው የሚከተለው ምላሽ ሰጥተውናል ። ቦታው ከአሁን ቀደም ለቢዝነስ ፣ ኤሌክትሮኒክስ እንዲሁም ሰርቬንግና ድራፍቲንግ ስልጠና ዘርፎች የተሰጠ ነበር።  ለተወሰኑ ጊዜያት የስልጠና ዘርፎቹ ንጽህናውን በመጠበቅ በኩል ተባብረው ይሰሩ ነበር። በኋላ ላይ ግን ሶስታችን አሰልጣኞች ተመካክረን ወደ ተሻለ የመናፈሻ ቦታ እንድንቀየረው ወስነን የራሳችንን ዲዛይን አዘጋጅተን ከምድረ ግቢ አስተዳደር ጋር በመነጋገር የማቴሪያልና የጉልበት ሰራተኛ ድጋፍ በማግኘታችን ወደ ምትመለከቱት አይነት የመናፈሻ ስፍራ ቀየርነው ፤ በዚህም ደስተኞች ነን መንፈሳችንን እያደስንበትና ድካማችንን እያስወገድንበት እንገኛለን ብለውናል። እኛም ይህ ውብ መናፈሻ እንዲለማ ላደረጉት አካላት በድጋሚ ምስጋናችንን በማቅረብ ለሌሎች የስልጠናዘርፎች ተነሳሽነትን የሚፈጥር ጥሩ ምሳሌ ነው እንላለን።                  ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content
+9

ሰኔ 2017 ዓ.ም     ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከመሰንበቻው ከኮሌጁ የምዕተ ዓመት አከባበር እና ከስያሜ ለውጡ ጋር በተያያዘ  በርከት ያሉ እንቅስቃሴዎችን በማድረግ ላይ ይገኛል ። በመጠናቀቅ ላይ ያለው ዋናው በር የተመለሰውን ነባሩን ስያሜ ለመሸከም እና የመግቢያ አገልግሎት ለማስተናገድ ብቻ የተዘጋጀ ግንባታ አይደለም ፤ ወደ ግቢው ከመዝለቅዎ በፊት ከውስጥ የሚጠብቆትን ታሪካዊ ህንፃ ምን እንደሚመስል ለማመላከት ጭምር ታስቦበት የተዘጋጀ መሆኑን ዲዛይኑን  ያዘጋጀው እና የግንባታ ክትትሉን የሚያከናወነው የኮሌጁ  አሠልጣኝ ሚኪያስ ይርጋለም ይገልጻል ። ሚኪያስ በመቀጠል በከርቭ መልክ የተሰራውና ቄንጠኛው የመግቢያ በር በሁለት ቋሚዎች መካከል የሚገኝ እና በሚያማምሩ ጥርብ ድንጋዮች የተገነባ ነው። ይህም ጥንካሬውን፥ ታሪካዊነቱን፥ ወቅታዊነቱን እና ቀጣይነቱን ያሳያል ይላል። እንደ ሚክያስ ገለጻ የከርቭ ቅርጽ  በጥበብ ቋንቋ የፈጠራስሜትን ለማበረታታት፣ እድገትን ለማመላከት ያገለግላል ይላል። ው በዚህ መልክ የተሰራው ዋና በር ጠንከር ያለ ወጭ/4.5 ሚልየን ብር እንደሚገመት ተጠቁሟል። ይህ ወጪ ሙሉ በሙሉ በቀድሞ ተማሪዎች ማሀበር እንደተሸፈነም እንደዚሁ። ሚኪያስ በዚህ አጋጣሚ ማህበሩን በራሱና በኮሌጁ ስም ማመስገን ይፈልጋል ፤ ተገቢም ነው። ማህበሩ የሚያደርገዉ ድጋፍ በዚህ ብቻ የተወስነ አይደለም በፋይናንስም በማቴሪያልም ኮሌጁን ሲያግዝ ቆይቷል። አሁንም ባለ ሦስት ወለል ህንፃ ለማሰራት በጥረት ላይ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል ። በግንባታ ሂደት የኮሌጁ ሚና በዋናነት ዲዛይን እና ክትትልን አስመልክቶ ከሰርቬይንግ እና ድራፍቲንግ የስልጠና ዘርፍ ጋር የተያያዘ ነው ለማለት ይቻላል።  በዚህ አጋጣሚ የቀድሞ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ በሃሳብ አመንጭነትና ስራው እውን እንዲሆን ያበረከቱት አስተዋጽኦ  ያንበሳውን ድርሻ ይይዛል።  አሁን ያሉት አመራሮች ደግሞ የተጀመረውን ስራ እንዲጠናቀቅ እያበረከቱ ያሉት አስተዋጽኦ የሚደነቅ ነው ብለዋል።  የሰርቬንግና ድራፍቲንግ የስልጠና ዘርፍም በአሠልጣኝ ሚኪያስ በኩል በተነደፈው ዲዛይንና በግንባታ ክትትል ሙያዊ ስራ አሻራውን በትምሳሌትነት ያኖረ ነው። ከውጭም ሆነ ከውስጥ ግንባታውን የተመለከቱ የህብረተሰብ ክፍሎች ስራው ቀልብ የመግዛት አቅም እንዳለው በተለያዩ አጋጣሚዎች ሲናገሩ ይደመጣል።  ቀረብ ብለውም የትምህርት ቤቱ መስራች አልጋወራሽ ተፈሪ መኮንን ያስተላለፉትን መልዕክት በማንበብ ተጨማሪ መረጃ እያገኙ እንደሆነ በቆምንባቸው  አፍታዎች ለማድመጥ ችለናል። በመጨረሻም አሠልጣኝ ሚኪያስ ባስተላለፈው መልዕክት ስራውን ሲያይ በጣም እንደሚደሰትበት እና ኩራትም እንደሚሰማው በመግለጽ የቤተሰቡን በተለይም የባለቤቱን ጊዜ መስዋዕት በማድረግ እገዛቸውን ስላገኘ ሊያመሰግናቸው ወዷል ፤ ይገባቸዋልም። ይህ ስራ የሚያስተምረን ፤ የቁርጠኛነት ጉዳይ እንጂ  ኮሌጁን እና ተጠቃሚውን የሚረዱ ስራዎች ለመስራት የሚችል በቂ የሰለጠነ የሰው ኃይል ስላለ ማኔጅመንቱ በማስተባበር ወደ ተግባር እንዲቀየር ጥረት ማድረግ እንዳለበት ያመላከተ በመሆኑ የማበረታቻ ስርዓት ቢበጅለት ደግሞ የበለጠ ጥሩ እንደሚሆን ሚኪያስ መልእክቱን አስተላልፏል። የዝግጅት ክፍላችንም ሚኪያስና ቤተሰቦቹን ከማመስገን ባሻገር መልእክቱ በኢንተርፕራይዝ ምስረታና ትግበራ ላይ ትኩረት ቢሰጥበት እንላለን።              ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content
+3

ሰኔ 2017ዓ.ም የወጣቶች የክረምት ስልጠና መርሃ ግብር ተጀምሯል። በከተማዋ ካሉ 10 ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ አማተር ባለሙያዎች በዘመናዊና ባህላዊ ተወዛዋዥነት፣ የቲያትር ትወና ፣ ጽህፈተ ተውኔት
+4
ሰኔ 2017ዓ.ም        የወጣቶች የክረምት ስልጠና መርሃ ግብር                                       ተጀምሯል። በከተማዋ ካሉ 10 ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ አማተር ባለሙያዎች በዘመናዊና ባህላዊ ተወዛዋዥነት፣ የቲያትር ትወና ፣ ጽህፈተ ተውኔት እና በድምጽ /vocal የስልጠና መስኮች 321 ወጣቶች ተቀብሏል። በክረምት መርሃ ግብር ለ1 ወር የሚቆይ ስልጠና የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ላይ የተገኙት የሃገር ፍቅር ቲያትር ቤት ስራአስኪያጅ አቶ ሰለሞን ሓጎስ ሰልጣኞች በየዘርፋቸው ስልጠናቸውን በአግባቡ እንዲሰለጥኑ እና ስልጠናው በከተማ ደረጃ ትኩረት ተሰጥቶበት በጥብቅ ክትትል እንደሚመራ ገልፀዋል ። በተመሳሳይ የኮሌጁ ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች አቶ ደመላሽ ተስፋዬ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈው ሰልጣኞች ሊከተሏቸው የሚገቡ ህግና ደንቦችን እንዲሁም በስልጠና ወቅት ለሚያጋጥሟቸው ጉዳዮች ሁሉ ኮሌጁ ፈጣን ምላሽ እንደሚሰጥና ሰልጣኞች በዚህ አጭር ግዜ በአግባቡ መሠልጠን እንደሚገባቸው  አሳስበዋል። በመጨረሻም  የቲያትር ትምህርት ክፍል ተጠሪ አሠልጣኝ እያሱ ስለሺ ሰልጣኞችን በየዘርፋቸው በመለየት እና እንደየ ዘርፉ አስፈላጊ መረጃዎችን አጋርተዋል።                      ኮሙኒኬሽን ቡድን

ሰኔ/2017 ዓ.ም የበጀት ዓመቱ ዕቅድ ክንውን ግምገማ እየተካሄደ ነው። በ2017 በጅት ዓመት ስራዎችን ስኬታማ ለማድረግ የኮሌጁን ዕቅድ የጋራ በማድረግ ወደ ስራ መገባቱ ይታወቃል። ስራዎቹ ከዝግጅት
+8
ሰኔ/2017 ዓ.ም        የበጀት ዓመቱ ዕቅድ ክንውን ግምገማ                       እየተካሄደ ነው። በ2017 በጅት ዓመት ስራዎችን ስኬታማ ለማድረግ የኮሌጁን ዕቅድ የጋራ በማድረግ ወደ ስራ መገባቱ ይታወቃል።  ስራዎቹ ከዝግጅት ምእራፍ ጀምረው በየግዜው እየተገመገሙ  ከማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ደርሷል። የዕቅድ አፈጻጸማቸውን ያቀረቡት የስልጠና ዘርፎች ሲሆኑ የኮሌጁ ማኔጅመንት ፣አካዳሚክ ኮሚሽን ፣ የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን እና የኮሌጁ የበላይ አመራሮች በተገኙበት ለ2 ቀንት የተካሄደ ነው። አፈጻጸሙ በዕቅዱ ዓበይት እና ንኡሳን ተግባራት KPI  ታሳቢ  ያደረገ፣ የተመራቂ ሰልጣኞችን ሙሉ መረጃ ፣ የአሰልጣኞች መረጃና የምዘና አፈፃፀም ፣ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍና የቴክኖሎጂ አፈፃፀም ፣ ISO21001:2018 EOMS  ትግበራ ቀጣይነት እንዲሁም የጋጠሙ ችግሮችእና የተውስዱ መፍትሄዎች ተመላክተውበታል። በውይይቱ የኮሌጁ ዋና ዲንና ም/ዲኖች የተገኙ ሲሆን አቀራረቡ ከወትሮው ለየት ያለና እያንዳንዱ የስልጠና ዘርፍ የተዳሰሰበትና አስተያየት የተስጠበት መድረክ ነበር ። በቀጣይም ዳይሬክቶሬቶች በተመሳሳይ አፈጻጸማችውን የሚያቀርቡ መሆኑም ተጠቁሟል። በመጨረሻም ዲኖቹ በዕቅድ ክንውኑ ግምገማ ላይ የየበኩላቸውን አስተያየት ሰጥተዋል ። በመቀጠል የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ የISO 21001:2018 EOMS ትግበራና ምዘና ላይ የኮሌጁ ማህበረሰብ ላደረገው  ርብርብ እና ለተገኘው አወንታዊ ምላሽ ምስጋናቸውን አቅርበው ለማጠቃለያውና የእውቅና ሰርተፍኬት ቅበላ እንዲያገናኝን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል ።                ኮሙኒኬሽን ክፍል

ሰኔ 2017ዓ.ም የመጀመሪያ ዙር የፎቶ ግራፊና ቪዲዮ ግራፊ ሰልጣኞች ፕሮጀክት ተገመገመ። የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2017 ለመጀመሪያ ጊዜ የተቀበላቸውን የፎቶ ግራፊና ቪዲዮ ግራፊ የደረጃ
+5
ሰኔ 2017ዓ.ም     የመጀመሪያ ዙር የፎቶ ግራፊና ቪዲዮ ግራፊ ሰልጣኞች ፕሮጀክት ተገመገመ። የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2017  ለመጀመሪያ ጊዜ የተቀበላቸውን የፎቶ ግራፊና ቪዲዮ ግራፊ የደረጃ 4 ስልጣኞች ከደረጃ 2 ወደ ደረጃ 3 ለመሸጋገር የፕሮጀክት ስራቸውን አስገመገሙ። በአምስት ቡድን ተክፍለው በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ አጫጭር ፊልሞችን አቅርበዋል። በግምገማው የኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ስልጠና ዘርፍ ተጠሪ ፥የትምህርት ክፍሉ አሰልጣኞች፥ ስልጣኞች እና በ EBC የካሜራ ባለሙያው አቶ አብረሃም ተገኝተው ስራዎቹን በሙያዊ የመገምገሚያ መስፈርቶች አንጻር ተግምግሟል ። በቀረበው አስተያየት ትምህርት ክፍሉ አዲስ ከመሆኑ አንጻር ካለው የማሰልጠኛ ግብአት እና ልምድ ውስንነት ሰልጣኞች ያቀረቡት ስራ ለመጀመሪያ ስራ በቂ  ቢሆንም በእያንዳንዱ ቡድን መስተካከል ያለባችው ጉዳዮችን በጋራ እንዲያስተካክሉ አቅጣጫ ተሰጥቷል ።                ኮሙኒኬሽን ቡድን

ሰኔ 25/2017ዓ.ም በ2018 ዓ.ም ዓይነ ስውራን ሰልጣኞችን ለመቀል የዝግጅት ስራ ተጀመረ። የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አካል ጉዳተኛ ስልጣኞችን በአካቶ ስልጠና በማሰልጠን ፋና ወጊና ብቸኛ
+4
ሰኔ 25/2017ዓ.ም በ2018 ዓ.ም  ዓይነ ስውራን ሰልጣኞችን ለመቀል                      የዝግጅት ስራ ተጀመረ። የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አካል ጉዳተኛ ስልጣኞችን በአካቶ ስልጠና በማሰልጠን ፋና ወጊና ብቸኛ ከሌጅ ነው ። ከልጁ በ2018 በጀት ዓመት ዓይን ስውራን እና ከፊል ዓይነ ስውራንን ለማሰልጠን የሚያስችል የ JAWS ሶፍት ዌር ስልጠና ከህዳሴ አካል ጉዳተኞች ማህበር ጋር በመተባበር ለአሠልጣኞች፥ለስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች፥ለሬጅስትራርና የላይብረሪ ባለሙያዎች እንዲሁም አስተባባሪዎች የ3ቀናት ስልጠና ተሰጥቷል ። በስልጠናው መክፈቻ ላይ የተገኙት የኮሌጁ ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ምንም እንኳን የአካቶ ስልጠናን እየተገበርን ቢሆንም በሚፈለገው ልክ አለመሆኑን ጠቁመው ይህንን በዘላቂነት ለመፍታት እንዲያስችል ከEASE project ጋር  በማስተሳሰር በመደበኛ ስልጠናውም ሆነ በአጫጭር ስልጠና ለሚመጡ አካል ጉዳተኛ ሰልጣኞች ለስልጠናው አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶችን ለማሟላት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በተጨማሪም የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ወ/ሪት ቤተልሄም የፕሮጀክቱ ዓላማ   አካል ጉዳተኞችን እና ሴቶችን ወደ ፊት ማምጣት በመሆኑ የአካል ጉዳተኞችን ማእከል ለማጠናከር እና አስፈላጊ ቁሳቁሶችን ለማሟላት በትጋት እንሰራለን በማለት ቃል ገብተዋል። ስልጠናውን የሰጡት የህዳሴ አካል ጉዳተኞች ማህበር ም/ስራ አስኪያጅ አቶ መዓዛኃይማኖት እና አቶ አሚድ ኮሌጁ በዚህ ልክ ትኩረት ሰጥቶ ከሰራ እኛም ያለ ምንም ቅድመሁኔታ ስልጠናዎችን በመስጠት ባለሙያዎችን የማብቃት ስራ እንሰራለን በማለት  ተናግረዋል።             ኮሙኒኬሽን ቡድን

ሰኔ 19 /2017ዓ.ም የሆቴልና ቱሩዝም ስልጠና ዘርፍ የተቋም ምዘና አካሄደ። በሆቴልና ቱሩዝም ስልጠና ዘርፍ በCulinery Art ከደረጃ 1 ወደ ደረጃ 2 የሚሸጋገሩ 5 ወንዶች እና 22 ሴት ሰል
+6
ሰኔ 19 /2017ዓ.ም የሆቴልና ቱሩዝም ስልጠና ዘርፍ የተቋም ምዘና                                    አካሄደ። በሆቴልና ቱሩዝም ስልጠና ዘርፍ  በCulinery Art  ከደረጃ 1 ወደ ደረጃ 2 የሚሸጋገሩ 5 ወንዶች እና 22 ሴት ሰልጣኞች ለምዘና ተቀምጠዋል። ምዘናው የቲዎሪና የተግባርን ያጣመረ ነው።  ተመዛኞች በሁለቱም ምዘናዎች 100% ውጤታማ መሆናቸውን የትምህርት ክፍሉ ተጠሪ አቶ ገ/መድህን ብርሃኑ መረጃውን አጋርተውናል።                        ኮሙኒኬሽን ቡድን

ሰኔ 17/2017ዓ.ም አካል ጉዳተኝነትን አስመልክቶ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ተካሄደ። ቱጌዘር የበጎ አድራጎት ድርጅት በ5ዘርፎች ማለትም ቅድመ አይነስውርነትን መከላከል ፣ በቴክኖሎጂ ፣ በማቋቋም እና የስራ ትስስር ላይ የሚሰራ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ነው ያሉን በድርጅቱ የፕሮግራም አስተባባሪዋ ወ/ሪት ማርታ ንጉሴ ሴትነት እና ዓይነ-ስውርነት ያለውን ተደራራቢ ጫና አስመልክተውም በቡና ጠጡ ፕሮግራሙ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል ። የዚህ ፕሮግራም ዓላማ የዓይነ-ስውራን ሂወት ምን ይመስላል? ማንም ሰው ባለሙሉ አካል ሆኖ ለመኖሩ/ለመቀጠሉ/ ዋስትና የሌለው በመሆኑ በእያንዳንዱ ስራዎቻችን ላይ አካል ጉዳተኞችን ታሳቢ ያደረገ እና የነሱን ጉዳይ አካተን መስራት እንደሚገባ በአጽንኦት አሳስበዋል። በተያያዘም የአካል ጉዳተኞችን ጉዳይ እንዴት ልናካትት እንችላለን ? ከህግ አንጻርስ እንዴት ይታያል? በሚሉ ርዕሰ- ጉዳዮች ላይ  አቶ መአዛ ሃይማኖት ወርቁ የህዳሴ አካል ጉዳተኞች ማህበር ስራስኪያጅ እና የህግ ባለሙያ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ዓይነ- ስውርነትን አስመልክቶ ያለውን የተሳሳተ አመለካከት ለማስተካከልና በተለያዩ ጉዳዮች ወደ ኮሌጃችን የሚመጡትንም ሆነ በመንገዳችን ፣ በአካባቢያችን ማየት የተሳናቸውን ወገኖች እንዴት መርዳት እንዳለብን እና መደረግ ስላለበት ጥንቃቄና  ቅደም ተከተል ማብራሪያ ተሰጥቷል። በተጨማሪም የአይነ-ስውራንን ጫና ለመረዳት የሚያስችል ለ15 ደቂቃ አይንን በመጨፈን እና በመሸፈን ስሜታቸውን ለመዳት የሚያስችል ተግባራዊ ልምምድና የመማማሪያ መድረክ ተፈጥሯል። አቶ መአዛ አካል ጉዳተኞች ምን ይፈልጋሉ ? በተለይ  ዓይነ ስውራን ምን ይፈልጋሉ ? በሚለው ርዕሰ ጉዳይ ላይ ዘርዘር ያለ መረጃ አስተላልፈው ድጋፋችን በምርጫቸው ላይ የተመሠረተ እንዲሆን ፣ ሰብአዊ ክብራቸውን የማይነካ፣ ከአድልዎና መገለል የፀዳ፣ ውጤታማ ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚያስችልና ቀጣይነት ያለው እንዲሆን ምክራቸውን ለግሰዋል ።  አካል ጉዳተኞች በሚፈልጉት እና በሚመጥናቸው  ስልጠናዎችን ካገኙ እና ከተደገፉ ማንኛውንም ስራ መስራት የሚችሉ መሆኑንም ጠቁመዋል። ከዚህም ባሻገር የአካል ጉዳተኞችን ቤተሰብ በመደገፍ ጫናቸውን መቀነስ ያስፈልጋልም ብለዋል ።  በመጨረሻም ከቤቱ ሃሳብ አስተያየት ተነስቶ ውይይት ተካሂዶበታል። በቀጣይ በተጠናከረ መልኩ ስራዎችን እንደሚሰሩ ተጠቁሟል።               ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content
+8

ዓርብ ሰኔ 13/2017ዓ.ም 15ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ማጠቃለያ ፕሮግራም በከተማ ደረጃ ተከናውኗል። የኮሌጁ ማህበረሰብ እንኳን ደስ ያላችሁ ደስ ያለን!! "ብሩህ አዕምሮዎች ፣ በክህሎት የበቁ
+1
ዓርብ ሰኔ 13/2017ዓ.ም 15ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ማጠቃለያ ፕሮግራም በከተማ ደረጃ ተከናውኗል። የኮሌጁ ማህበረሰብ እንኳን ደስ ያላችሁ ደስ ያለን!! "ብሩህ አዕምሮዎች ፣ በክህሎት የበቁ ዜጐች '' በሚል መሪ ቃል በከተማ ደረጃ የተከበረው 15ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ላይ ከ150 በላይ የማምረቻ፣ የምርትና  የሀገር በቀል ቴክኖሎጂዎች ፣ የክህሎት ውድድር ፣ ስፖርታዊ ውድድር የተካሄደበት ነው። ኮሌጃችንን ወክሎ በክህሎት ውድድር  የተሳተፈው ሠልጣኝ ዳዊት ፋንታሁን በተሳተፈበት የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ዘርፍ በሃርድዌር እና ኔትወርኪንግ ሰርቪስ ( Hardware and Networking Service)   የክህሎት ዉድድር  1ኛ በመዉጣት 50,000 (ሃምሳ ሺህ )ብር  እና 106 ሺህ ብር ያወጣ ዴስክ ቶፕ ኮምፒውተር ተሸላሚ ሆኗል። ሰላጣኝ ዳዊት በሃገር አቀፍ ደረጃ 3ኛ በመውጣት የሦስት መቶ ሺህ ብር ተሸላሚ በመሆን የኮሌጃችንን ስም በሃገራቀፍ ደረጃ ያስጠራ መሆኑም ይታወቃል ። በተጨማሪም ከሆቴልና ቱሪዝም ስልጠና ዘርፍ በስነ-ውበት(በፀጉር ስራ ) የተወዳደረችው ሠልጣኝ ላምሮት አበበ 3ኛ በመውጣት የ30,000 (ሠላሳ ሺህ )ብር ተሸላሚ ሆናለች ። በጣም ከፍተኛ ውድድር የተደረገበትና አሠልጣኞቻችን እና ሠልጣኞቻችን በተጠበቡበት በፋሽን ሾው ውድድር 1ኛ በመሆን አጠናቀዋል። ዘወትር የኮሌጃችንን ስም የሚያስጠራው ስፖርታዊ ውድድር በወንዶች መረብ ኳስ 1ኛ በመውጣት የዋንጫ ተሸላሚ ፣ በወንዶች እግርኳስ 3ኛ በመሆን ሜዳልያ እና በጠረጴዛ ቴኒስ 2ኛ እና 3ኛ በመውጣት ተሸላሚ ሆነዋል ። በድጋሚ የኮሌጁ ማህበረሰብ እንኳን ደስ ያላችሁ ደስ ያለን!!      ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዓርብ ሰኔ 13/2017ዓ.ም ማኔጅመንቱ እና አካዳሚክ ኮሚሽን የጋራ የስራ አፈጻጸም የግም አካሄዱ ። የስልጠና ዘርፎች የ2017በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ ከወትሮው ለየት ባለ መልኩ በጥልቀት እያን
+5
ዓርብ ሰኔ 13/2017ዓ.ም ማኔጅመንቱ እና አካዳሚክ ኮሚሽን የጋራ የስራ                          አፈጻጸም የግም አካሄዱ ። የስልጠና ዘርፎች የ2017በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ ከወትሮው ለየት ባለ መልኩ በጥልቀት እያንዳንዱን መለየትና የጅምላ አካሄድን በማስቀረት ለቀጣይ ስራ ግብአት እሚሆን መደላድል ለመፍጠር የስልጠና ዘርፎችን በሦስት መድቦ በዛሬው ዕለት የአውቶ ሞቲቭ ፣ ኮንስትራክሽን እና ቢዝነስ ስልጠና ዘርፎች የተገመገሙ ሲሆን በእያንዳንዱ ስልጠና ዘርፍ መልካም የተባሉ ስራዎችና ጅማሮዎቻቸው ተገምግሟል ።  በተመሳሳይም እንደ ችግር ከየስልጠና ዘርፉ የተነሱ ሃሳቦችም ተቃኝተዋል። በቀረበው አፈጻጸም ላይ ሃሳብ አስተያየት ተነስቶ ውይይት ተካሄዶበታል ። በቀጣይ የስራ ቀናት በወጣው ፕሮግራም መሠረት ግምገማው የሚቀጥል መሆኑ ለማወቅ ተችሏል። በተጨማሪም ባሳለፍነው ሳምንት ከሰኔ 4-6 ኮሌጃችን ዓለምአቀፉን የትምህርት ጥራት (ISO 21001-2018)  ግምገማ  ማካሄዱ ይታወቃል ። በግምገማው አንዳንድ መስተካከል ያለባቸው  ጉዳዮችን በአጭር ግዜ ማስተካከል እሚያስችል የመሻሻል ዕድሎች( Potential impruvement ) የትግበራ ፕላን በአስተባባሪው አቶ ሚካኤል ጎኣ ቀርቧል። በመጨረሻም የትግበራ ዕቅዱ ውይይት ተካሂዶበት በጋራ ስብሰባው ፀድቋል ።             ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዓርብ ሰኔ 13/2017ዓ.ም በኤች አይ ቪ ሜይንስትሪሚንግ እና የኤድስ ፈንድ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ። የኤች አይ ቪ ሜይንስትሪሚንግ ክበብ በዛሬው ዕለት ባዘጋጀው ስልጠና አሁናዊ የኤች አይቪ ሁኔታ፣ የ
+5
ዓርብ ሰኔ 13/2017ዓ.ም በኤች አይ ቪ ሜይንስትሪሚንግ እና የኤድስ ፈንድ                              ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ። የኤች አይ ቪ ሜይንስትሪሚንግ ክበብ በዛሬው ዕለት ባዘጋጀው ስልጠና አሁናዊ  የኤች አይቪ ሁኔታ፣ የኤች አይቪ ሜኒስትሪሚንግ ምንድ ነው ? የኤድስ ፈንድ ምንድ ነው ?? አጠቃቀሙ ምን ይመስላል?? የግብረሃይሉ ተግባርና ሃላፊነት ምንድነው ? የእናት አምባሳደሮች ተግባርና ሃላፊነት ምንድነው ?? ለችግር የተጋለጡ ህጻናትን እንዴት እናሰባስባለን ?? በሚሉ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ስልጠናውን የሰጡት  ከአዲስ አበባ ጤና ቤሮ የመጡ ባለሙያ አቶ ስንታየሁ  ጎሹ ወቅታዊ መረጃዎችን በማጣቀስ ስልጠናውን ሰጥተዋል። በመድረኩ የተገኙት የኮሌጁ ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ የወገን ደራሽ ወገን ነውና ኮሌጁ ለሚያሳድጋቸው ህጻናት የሚዋጣው መዋጮ እንደ ኮሌጅ ያለን የሰው ሃይልና የሚዋጣው መዋጮ ኮሌጁን የማይመጥን በመሆኑ በቀጣይ በትኩረት እንደሚሰራበት ጠቁመዋል።  በመጨረሻም ከቤቱ ሃሳብ አስተያየትና ጥያቄ ቀርቦ ማብራሪያና ምላሽ በአሰልጣኙ ተሰጥቶበት የፕሮግራሙ ፍጻሜ ሆኗል።      ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content