ch
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

关闭频道
1 148
订阅者
-124 小时
-27
-1830
帖子存档
የ2018 ዓ.ም የስልጠና ዘመን የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና የመደበኛ ስልጠና መርሃግብር መግቢያ ነጥብ ይፋ ሆነ

photo content

6/02/2018 ዓ/ም የ2018 ዓ.ም የ1ኛ ሩብ አመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ። በግምገማው የኮሌጁ ማኔጅመት አባላት የተሳተፉ ሲሆን በመርሀግብሩ ዶ/ር ከበደ በሬቻ ፣ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ እና አቶ ወንድም ሲያምረኝ (የሶስቱም ምክትል ዲኖች) እቅድ አፈጻጸም ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ስር የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የዛሬው መርሀግብር በ2018 ዓ.ም አንደኛ ሩብ አመት አጠቃላይ በዘርፉ የተለያዩ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቁመው በኮሌጁ የ2018 ዓ.ም የመደበኛ ነባር ሰልጣኞች ተመዝግበውና የምዝገባ መረጃ ተደራጅቶ ስልጠና መጀመራቸውንና የኢንተርፕራይዞች ልየታና የድጋፍ ማዕቀፍና የቴክኖሎጂ መቅዳትና ማሸጋገር ስራው ለማሳለጥ በዳሰሳ ጥናት እየተሰሩ መሆናቸው፣ ስልጠናው በዕቅድ በተያዘው መሰረት ለመስራት የተቋማት አቅም ግንባታ ግብዓቶች ለማሟላት እና የማሰልጠኛ ወርክ ሾቦችን ዝግጁ በማድረግ የተሰሩ በርካታ ተግባራት መኖራቸው ሶስቱም ምክትል ዲኖች አብራርተዋል። በተጨማሪም መረጃው ለሚመለከተው አካል ተደራሽ መደረጉን የዕቅድ ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ዳሬክተር የሆኑት ወ/ሮ ንግስቲ  በመግለጽ አጫጭር ሰልጣኞች እና የልዩ ፍላጎት ሰልጣኞች የሚያስፈልጉ ግብዓት በአግባቡ ተደራጅቶ እየተሰራ መሆኑን ሪፖርቱ ለሚመለከተው አካል እንዲደርስ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል ማድረግ የሚጠበቅባቸው መሆኑን አስገንዝበዋል።የተቋሙ ኃላፊ አቶ አብዱልበር መሀመድ አያይዘውም በዘርፍ (ስራ ክፍሉ) የተቋማቱ ሁለንተናዊ እድገት እና መሻሻል የታቀደው መሪ ዕቅድ ከባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ ባደረገው መሰረት አሰፈላጊውን መረጃ በመሰብሰብ፤ በመተንተን የትኩረት አቅጣጫ በኬፒአይ ላይ ባስቀመጠው ቁልፍና አበይት ተግባራት እየገመገመ መረጃ እያደራጀና እያዘጋጀ በመስራት እንዳለበት ገልጸው በቀጣይ ከአጠቃላይ የኮሌጁ የመረጃ ባለሙያዎች፣ አሰልጣኞች እና አስተዳደር ሰራተኞች ጋር በሪፖርቱ ዙሪያ በመግባባት የተቋማቱም ዕቅድ ማስፈፀም ስራ እንደሚሰራ አመላክተዋል።                   https://t.me/EntotoPtc1917 ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+6

photo content
+9

06/02/2018 ዓ/ም በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በተለያዩ የስልጠና መስኮች አጫጭር ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በተፈሪ መኮንን ፖ/ቴ/ኮሌጅ በልዪ ልዪ የስልጠና መስኮች አጫጭር ስልጠና እየተሰጠ ሲሆን ከጉለሌ ክፍለ ከተማ ስራና ክህሎት ጽ/ቤት በኩል ተመልምለው ለመጡ የቴክኒካል ክህሎት ሰልጣኞች በኮሌጁ አሰልጣኞች ስልጠና እየተሰጣቸው ይገኛል ። በዚህም መሰረት ከ500 በላይ ለሚሆኑ  ሰልጣኞች የንግድ ክህሎት ፤ የንብ እርባታ እና የልብስ ስፌት ስልጠና  የበሰልጠና ዘርፎች አየተሰጠ ሲሆን ከስልጠናው መጠናቀቅ በኋላም ለሰልጣኞች  ምዘና (COC) እንዲወስዱ በማድረግ ብቃታቸውን በምዘና የማረጋገጥ ሥራ የሚሠራ መሆኑን ከአጫጭር ስልጠና አስተባባሪ አቶ ታደሰ አበራ የተገኘዉ መረጃ ያመላክታል ።በቀጣይም ኮሌጁ በልዩ ልዪ የስልጠና መስኮች የአጫጭር ስልጠናዎችን አዘጋጅቶ ለመስጠት በሙሉ አቅም ላይ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል። ከኮሚኒኬሽን ቡድን

5/02/2018 ዓ/ም የ2018 የመጀመሪያው ሩብ አመት እቅድአረፃፀም ሪፖርትበተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማኔጅመንት አባላት ቀረበ ። በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማኔጅመንት አባላት የ2018 ዓ/ም የሶስት ወር እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በተቋማት አቅም ግንባታ ፣በሰልጣኝ ልማት እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እንዲሁም በእቅድና በጀት ዲያሬክቶሬት ቀርቧል።የቀረበው እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ በሜኔጅመንቱ አባላት አስተያየት የተሰጠበት ሲሆን የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ አብድልበር መሀመድ በቀረበው የ2018 ዓ/ም የሶስት ወር እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ማጠቃለያ ሰጥተዋል። ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+6

05/02/2018 ዓ/ም የ2018 ግልጽ ጨረታ በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ። በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የግልጽ ጨረታ በተያዘለት ጊዜ ትግበራው እንዲሆን ለተጫራቾች ጥራት እና ግልጽነት ለመፍጠር ኮሌጅ ደንቡን ተከትሎ መስራቱ አስፈላጊ ከመሆኑም በላይ ለኮሌጁ የስልጠና ግብአት የሚያሟላበት የመጀመሪያው ዙር የግልጽ ጨረታ ስርአት ተካሄደ ። ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+5

03/02/18 ዓ/ም በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የችግኝ ተከላ እና እንክብካቤ ተካሄደ ። በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከኮሌጅ ማህበረሰብ  እና ሰልጣኞች ጋር በመሆን የችግኝ ተከላና እንክብካቤ መርሀ ግብር ተካሄደ በእለቱም 1000 ችግኞችን ለመትከል ተችሏል። ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+9

ጥቅምት 03/02/2018 ዓ/ም የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ። በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለዘጠነኛ ቀን ተካሄደ።በእለቱ ተሞክሮአቸውን ያካፈሉት አቶ ተስፋፅዮን Team work በሚል መሪ ቃል ለኮሌጁ ህብረተሰብ ግንዛቤ የፈጠሩ ሲሆን የኮሌጁን ህብረተሰብ በመቀናጀትና በጋራ በመስራት አላማችንን እንደ ኮሌጅ ማሳካት እንደሚቻል ገልፀው የኮሌጁ ህብረተሰብ እንደ ግለሰብ ያለውን እውቀትና ልምድ ከኮሌጅ ማህበረሰብ ጋር ማቀናጀትና አብሮ መስራት እንዳለበት መልክት አስተላልፈዋል። ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+9

Repost from TMPC 1917
photo content

03/02/18 ዓ/ም በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሰንደቃላማ ቀን ተከበረ። ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ! በሚል መሪ ቃል የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከኮሌጅ ማህበረሰብ ጋር በመሆን የሰንደቃላማ ቀን በደመቀ ሁኔታ አከበረ። ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+5

03/02/18 ዓ/ም በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የችግኝ እንክብካቤ ተካሄደ ። በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከኮሌጅ ማህበረሰብ  እና ሰልጣኞች ጋር በመሆን የችግኝ ተከላና እንክብካቤ መርሀ ግብር ተካሄደ በእለቱም 1000 ችግኞችን ለመትከል ተችሏል። ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content

photo content