ch
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

关闭频道
1 149
订阅者
无数据24 小时
-37
-1830
帖子存档
photo content
+4

photo content
+9

ለውድ  የተከበራቹ  የአካዳሚክናስልጠና  ክፍል  ስር  ለምትገኙ  የፕሮሰስ ካውንስል  አባላት በሙሉ!!! እንደምን  አመሻቹ!!!! በሌላ አስቸኳይ ስብሰባ የነገው የ9 ወር እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ወደ ረቡዕ በ23/07/2018 ዓ.ም   ጠዋት  4ሰዓት  የተዘዋወረ መሆኑ ታውቆ በኮሪያ  ህንፃ  አዳራሽ  እንድትገኙ  ከወዲሁ  አሳውቃለሁ!!!! ማሳሰቢያ 1.የ2018  ዓ.ም  ተመራቂ  ሰልጣኞች  በቀን በማታ  በዊኬንድ  መለየቱ: ስልጠና  የሚያጠናቅቁበት  ቀን  የሚያሳይ መረጃ:ሞዴል ምዘና  የሚመዘኑበት ቀን መረጃ:የሀገር  አቀፍ ምዘና  የሚመዘኑበት ቀን መረጃ 2.የ2017ዓ.ም  ተመራቂ  ሰልጠኝ  የሀገር አቀፍ ምዘና  አፈፃፀም እና ስራ ትስስር  መረጃ 3.የስልጠና  ጊዜ  አጠቃቀም:የስራ ልብስ  መልበስ  ዲስፒሊን  ያለንበት  ሁኔታ በተካተተ መልኩ  ሪፖርቱ  የተጠመረ  እንዲሆን  በድጋሚ  አሳውቃለሁ!!! መልካም   አዳር!!!

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከሁሉም የስራ ክፍሎች እና ስልጠና ዘርፎች ለተውጣጡ አስተዳደር ሰራተኞች እና አሰልጣኞች ለካይዘን ትግበራ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ ። 🇪🇹22/07/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አስተዳደር ሰራተኞች እና አሰልጣኞች የስራ አፈፃፀም ለማሻሻልና የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን  ያለመ የካይዘን  ትግበራ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ። በኮሌጁ ቅጥር ግቢ እየተሰጠ በሚገኘው በዚህ ስልጠና ላይ አስተዳደር ሰራተኞች፣ አሰልጣኞች የካይዘን አስተባባሪዎች እና ወርክሾች ቴክኒሻል እየተሳተፉ ሲሆን ስልጠናው በዘርፉ ሰፊ ልምድ ባላቸዉ በካይዘን ልዕቀት ማዕከል ባለሙያዎች እየተሰጠ ይገኛል። የስልጠናው ዋና ዋና ዓላማዎች ብክነትን ማስወገድ ፣ በስራ ሂደት ውስጥ የሚታዩ አላስፈላጊ አሰራሮችንና የጊዜ ብክነትን በመቀነስ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የስራ አካባቢን ማደራጀት፦የ "5S" መርሆዎችን በመተግበር ምቹ የስራ ከባቢ መፍጠር ፣ የአገልግሎት ጥራት ለተገልጋይ ተማሪዎችና ለህዝብ የሚሰጠውን አገልግሎት ቀልጣፋና ጥራት ያለው ማድረግ ያተኮረ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል ። በስልጠናው መክፈቻ ላይ እንደተገለጸው፣ የካይዘን ፍልስፍና "ለተሻለ ለውጥ" የሚተጋና ቀጣይነት ያለው መሻሻልን መሰረት ያደረገ በመሆኑ፣ ኮሌጁ የጀመረውን የሪፎርም ስራ ከግብ ለማድረስ የላቀ ሚና ይኖረዋል። ሰራተኞችም በስልጠናው የሚያገኟቸውን እውቀቶች ወደ ተግባር በመለወጥ የኮሌጁን ተወዳዳሪነት እንዲያሳድጉ ጥሪ ቀርቧል።ይህ ስልጠና በቀጣይ ቀናትም በተግባር የተደገፈ ስልጠና በማካተት እንደሚቀጥል ታውቋል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+4

በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለአስተዳደር ሰራተኞች የካይዘን ስልጠና መሰጠት ተጀመረ ። 🇪🇹22/07/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለአስተዳደር ሰራተኞችን የስራ አፈፃፀ
+4
በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለአስተዳደር ሰራተኞች የካይዘን ስልጠና መሰጠት ተጀመረ ። 🇪🇹22/07/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለአስተዳደር ሰራተኞችን የስራ አፈፃፀም ለማሻሻልና የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን ያለመ የካይዘን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ። በኮሌጁ ቅጥር ግቢ እየተሰጠ በሚገኘው በዚህ ስልጠና ላይ የአስተዳደር የስራ ክፍሎች ሀላፊዎችና ሰራተኞች እየተሳተፉ ሲሆን፣ ስልጠናው በዘርፉ በበሰሉ የካይዘን ባለሙያ አቶ ከድር አሀመድ እየተሰጠ ይገኛል። የስልጠናው ዋና ዋና ዓላማዎች ብክነትን ማስወገድ ፣ በስራ ሂደት ውስጥ የሚታዩ አላስፈላጊ አሰራሮችንና የጊዜ ብክነትን በመቀነስ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የስራ አካባቢን ማደራጀት የ "5S" መርሆዎችን በመተግበር ምቹ የስራ ከባቢ መፍጠር ፣ የአገልግሎት ጥራት ለተገልጋይ ተማሪዎችና ለህዝብ የሚሰጠውን አገልግሎት ቀልጣፋና ጥራት ያለው ማድረግ ያተኮረ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል ። በስልጠናው መክፈቻ ላይ እንደተገለጸው፣ የካይዘን ፍልስፍና "ለተሻለ ለውጥ" የሚተጋና ቀጣይነት ያለው መሻሻልን መሰረት ያደረገ በመሆኑ፣ ኮሌጁ የጀመረውን የሪፎርም ስራ ከግብ ለማድረስ የላቀ ሚና ይኖረዋል። ሰራተኞችም በስልጠናው የሚያገኟቸውን እውቀቶች ወደ ተግባር በመለወጥ የኮሌጁን ተወዳዳሪነት እንዲያሳድጉ ጥሪ ቀርቧል።ይህ ስልጠና በቀጣይ ቀናትም በተግባር የተደገፉ ትምህርቶችን በማካተት እንደሚቀጥል ታውቋል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለአስተዳደር ሰራተኞች የካይዘን ስልጠና መሰጠት ተጀመረ ። 🇪🇹22/07/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለአስተዳደር ሰራተኞችን የስራ አፈፃፀ
+4
በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለአስተዳደር ሰራተኞች የካይዘን ስልጠና መሰጠት ተጀመረ ። 🇪🇹22/07/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለአስተዳደር ሰራተኞችን የስራ አፈፃፀም ለማሻሻልና የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን ያለመ የካይዘን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ። በኮሌጁ ቅጥር ግቢ እየተሰጠ በሚገኘው በዚህ ስልጠና ላይ የአስተዳደር የስራ ክፍሎች ሀላፊዎችና ሰራተኞች እየተሳተፉ ሲሆን፣ ስልጠናው በዘርፉ በበሰሉ የካይዘን ባለሙያ አቶ ከድር አሀመድ እየተሰጠ ይገኛል። የስልጠናው ዋና ዋና ዓላማዎች ብክነትን ማስወገድ ፣ በስራ ሂደት ውስጥ የሚታዩ አላስፈላጊ አሰራሮችንና የጊዜ ብክነትን በመቀነስ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የስራ አካባቢን ማደራጀት የ "5S" መርሆዎችን በመተግበር ምቹ የስራ ከባቢ መፍጠር ፣ የአገልግሎት ጥራት ለተገልጋይ ተማሪዎችና ለህዝብ የሚሰጠውን አገልግሎት ቀልጣፋና ጥራት ያለው ማድረግ ያተኮረ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል ። በስልጠናው መክፈቻ ላይ እንደተገለጸው፣ የካይዘን ፍልስፍና "ለተሻለ ለውጥ" የሚተጋና ቀጣይነት ያለው መሻሻልን መሰረት ያደረገ በመሆኑ፣ ኮሌጁ የጀመረውን የሪፎርም ስራ ከግብ ለማድረስ የላቀ ሚና ይኖረዋል።ይኖረዋል ሰራተኞችም በስልጠናው የሚያገኟቸውን እውቀቶች ወደ ተግባር በመለወጥ የኮሌጁን ተወዳዳሪነት እንዲያሳድጉ ጥሪ ቀርቧል።ይህ ስልጠና በቀጣይ ቀናትም በተግባር የተደገፉ ትምህርቶችን በማካተት እንደሚቀጥል ታውቋል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ "የወርቃማው ሰኞ " መድረክ በአዲሱ የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ ስልጠና በድምቀት ተካሄደ ። 🇪🇹21/07/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
+9
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ "የወርቃማው ሰኞ " መድረክ በአዲሱ የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ ስልጠና በድምቀት ተካሄደ ። 🇪🇹21/07/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ30 ተከታታይ ሳምንታት ሲካሄድ የቆየው "የወርቃማው ሰኞ" የልምድ ልውውጥ መድረክ፣ በዛሬው ዕለትም በልዩ ዝግጅቶች ተካሂዷል። መርሃ ግብሩ መግቢያ ላይ የአዲስ አበባን የብልጽግና ጉዞ እና የለውጥ ተቀባይነትን በሚዘክር ‘ዠረቱ’ በተሰኘ አስተማሪና አዝናኝ ተውኔት ቀርቧል። በዕለቱ በዋናነት ትኩረት የተሰጠው በአዲሱ የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ 87/2017 ዓ/ም ላይ ሲሆን፣ ከአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት የመጡት ባለሙያ አቶ መላኩ ገለፃ አድርገዋል። በገለፃቸውም ገለልተኛ የሲቪል ሰርቪስ ግንባታን ማፋጠን፣ የዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ ስርአት መዘርጋት፣ የሰራተኞች የብቃት ምዘና፣ የደመወዝ እስኬል እና የጥቅማ ጥቅም ማሻሻያዎችን በዝርዝር አብራርተዋል።ከመዱረኩም ለተጠየቁ ጥያቄዎች ማብራሪያ ሜብራሪያ ተሰቶባቸዋል ። የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ በበኩላቸው፣ የአንድ ተቋም ህልውና በሰራተኞች ጥንካሬና ሀላፊነት ላይ የተመሰረተ መሆኑን ገልጸው፤ እያንዳንዱ ሰራተኛ ስራውን በስታንዳርድ (በደረጃ) በማከናወን መብቱንና ግዴታውን በአዋጁ መሰረት እንዲወጣ አሳስበዋል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content

የካይዘን ስልጠና ነገ ማክሰኞ በ22/07/2018 ከጠዋት 2;30 የሚጀምር መሆኑን እናሳውቃለን። የስልጠና ቦታ ቴክኖሎጂ አዳራሽ መረጃውን ለሁሉም የስራ ክፍሎች እና ስልጠና ዘርፎች ስር ላሉት አድርሱ አደራ።

kaizen training.docx0.24 KB

የካይዘን ስልጠና ነገ ማክሰኞ በ22/07/2018 ከጠዋት 2;30 የሚጀምር መሆኑን እናሳውቃለን። የስልጠና ቦታ ቴክኖሎጂ አዳራሽ መረጃውን  ለሁሉም የስራ ክፍሎች እና ስልጠና ዘርፎች ስር ላሉት አድርሱ አደራ።

photo content

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከECDD ፕሮጀክት ጋር በመተባበር የተለያየ የአካል ጉዳት ላለባቸው ሰልጣኞች የሙያ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ ። 🇪🇹18/07/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን
+6
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከECDD ፕሮጀክት ጋር በመተባበር የተለያየ የአካል ጉዳት ላለባቸው ሰልጣኞች የሙያ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ ። 🇪🇹18/07/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ልማት ማህበር (ECDD) ጋር በመተባበር ለአካል ጉዳተኛ ሰልጣኞች የተዘጋጀ የሦስት ወር የክህሎት ስልጠና በይፋ ተጀመረ። ይህ የስልጠና መርሃ ግብር በዋናነት በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) እና በጋርመንት የስልጠና ዘርፎች ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ ከመሰረታዊ እውቀት ጀምሮ ተግባር ተኮር ስልጠናዎችን የሚያካትት ነው። የስልጠናው ዋና ዓላማ ሰልጣኞች የሦስት ወር ቆይታቸውን አጠናቀው በሚወጡበት ወቅት በራሳቸው ተነሳሽነት ወደ ስራ ዓለም እንዲገቡ ማስቻል፣ የተወዳዳሪነት አቅማቸውን ማሳደግ እና በኢኮኖሚ ራሳቸውን እንዲችሉ አስፈላጊውን ክህሎት ማስጨበጥ እንደሆነ ተገልጿል። ኮሌጁና የኢሲዲዲ (ECDD) ፕሮጀክት በጋራ በመሆን ያዘጋጁት ይህ ስልጠና አካል ጉዳተኞች በስራው ዘርፍ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግና የክህሎት ክፍተታቸውን ለመሙላት ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ታምኖበታል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content

photo content

photo content

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ "የወርቃማው ሰኞ" የልምድ ልውውጥ ተካሄደ። 🇪🇹14/07/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በየሳምንቱ የሚካሄደው "የወርቃማው ሰኞ" የጋራ
+8
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ "የወርቃማው ሰኞ" የልምድ ልውውጥ ተካሄደ። 🇪🇹14/07/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በየሳምንቱ የሚካሄደው "የወርቃማው ሰኞ" የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለ29ኛ ሳምንት በደመቀ ሁኔታ ተካሂዷል። በኮሌጁ በንብረት ክፍል በሹፌርነት ሙያ እያገለገሉ የሚገኙት አርቲስት ሻለቃ ስለሺ ፀጋዬ ለኮሌጁ ማህበረሰብ ሰፊ የሕይወትና የሥራ ተሞክሮአቸውን አቅርበዋል ። ሻለቃ ስለሺ በመርሃ-ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ በወታደራዊው ዓለም ውስጥ ከነበራቸው ተራ ወታደርነት ተነስተው እስከ ሻለቃነት ማዕረግ ድረስ የዘለቁበትን ፈታኝና ስኬታማ ጉዞ በዝርዝር አስረድተዋል። አክለውም የኮሌጁ ማህበረሰብ የሥራ ደረጃ ሳይገድበው ሁሉም እኩል መሆኑን ተገንዝቦ፣ ለሀገሩ ያለውን ፍቅር በሥራው ሊገልጽ እንደሚገባ አሳስበዋል። "የሀገር ፍቅር የሚገለጸው በሥራና እርስ በርስ በሚኖር ቀና የስራ መስተጋብር ነው" ያሉት ሻለቃ ስለሺ ሰራተኛው በሥራ ገበታው ላይ በቅንነትና በትጋት እንዲያገለግል አፅንዖት ሰጥተዋል። አርቲስት ሻለቃ ስለሺ ፀጋዬ ከወታደራዊና ከሹፌርነት ሙያቸው ባሻገር በኪነ-ጥበቡ ዘርፍ ያላቸውን ከፍተኛ ተሳትፎም ለታዳሚው አብራርተዋል። ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት በዲግሪ የተመረቁ ሲሆን እስካሁንም በርካታ ተወዳጅ ግጥሞችንና ዜማዎችን ለጥበብ አፍቃሪያን ማበርከታቸውን ገልጸዋል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

ከተማ፣ ከተሜነት፣ ክትመት እና የኮሪደር ልማት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቃና ቲቪ  ጋር ያደረጉት ቆይታ ማክሰኞ፣ መጋቢት 15 ምሽት 2:30 ይጠብቁን!

🙏ለኮሌጁ የእስልምና እምነት ተከታይ ሰራተኞች በሙሉ🙏 እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ። በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የደስታ ይሁንላችሁ! ኢድ ሙባረክ!
🙏ለኮሌጁ የእስልምና እምነት ተከታይ ሰራተኞች በሙሉ🙏 እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ። በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የደስታ ይሁንላችሁ! ኢድ ሙባረክ!