1 146
订阅者
-224 小时
-47 天
-1930 天
帖子存档
1 146
በጀርመን : ሀገር : የሚኖረው : : ሠዓሊ : ተገኔ : ኩምቢ : ዛሬ : ከተማሪዎች : ጋር : የልምድ : ልውውጥ : አደረገ ።
መጋቢት : ፬ , ፳፻፲፯ ዓ.ም.
ሠዓሊ : ተገኔ : ከዚህ : ቀደም : በጀርመን : በርሊን : በተገናኘን : ጊዜ : ለተማሪዎች : አንድ : ሻንጣ : ሙሉ : የሥዕል : ቁሳቁስ : ገዝቶ : ሰጥቶን : ያመጣን : ሲሆን ፤ ዛሬም : በተለይ : ሀገር : ውስጥ : የማይገኙ : ቀለሞችን : አምጥቷል ።
በዚህ : ልምድ : ልውውጥ : የኮሌጃችን : አንጋፋ : ሠዓሊ : ሉልሰገድ : ረታ : የተገኘ : ሲሆን ፤ ሠዓሊ : ተገኔም : ወደፊት : በሚችለው : ሁሉ : ድጋፍ : ከማድረግ : ባሻገር ፣ ከተማረበት : በርሊን : የሥነ - ጥበብ : ዩኒቨርስቲ : ጋር : ትስስር : በመፍጠር : የትምህርት : እድል : እንዲያገኙ : እንደሚሰራ : ቃል : ገብቶልናል ።
ተማሪዎችም : ላደረገው : በጎ : ተግባር : እራሱ : ባመጣው : ቀለም : ምስሉን : በመስራት : ስጦታ አበርክተውለታል ።
እኛም : ላደረገው : ቀና : ተግባር : በተማሪዎችና : መምህራን : ስም : ከልብ : አመስግነናል ።
1 146
+2
ዕለተ ማክሰኞ መጋቢት 2/2017ዓ.ም
ከጉለሌ ክፍለ ከተማ ለተውጣጡ
ጎልማሶች ኦረንቴሽን ተሰጠ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ከስራና ክህሎት ቢሮ ጋር ባደረገው ስምምነት መሠረት የጎልማሶች ትምህርት በአምስት የሙያ ዘርፎች ላይ የሚሰጥ ሲሆን እነሱም በልብስ ስፌት፣ የምግብ ዝግጅት ፣ጸጉር ስራ፣ እንጨትና ብረታብረት ዘርፍ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።
በኦረንቴሽኑ መክፈቻ የተገኙት የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ በዚህ የመጀመሪያ ዙር የጎልማሶች ትምህርት ለ181 ሠልጣኞችን የምንቀበል ቢሆንም አሁን ላይ የመጡት ቁጥራቸው አነሶተኛ መሆኑን ጠቁመዋል ። በተደረገው ልየታ የመጡት ሰልጣኞች የትምህርት ዝግጅታቸው ዝቅተኛ በመሆኑ በልብስ ስፌት ሙያ ለማሰልጠን የተዘጋጀው አዲሱ ሞጁል የማይመጥናቸው ስለሆነ ወደ ሌላ ዘርፍ ቢቀይሩ የሚሻላቸው መሆኑንም አሳስወዋል ። አያይዘውም ያልተሟሉ መረጃዎችን ከላካቸው አካል አሟልተው እንዲመጡም አሳስበዋል ።
በመቀጠልም አቶ ታደሰ አበራ ከቤቱ ለተነሱ ጥያቄ ፣ ሃሳብና አሰተያየት ምላሽ ሰጥተው ሠልጣኞች የሚሰለጥኑበትን ሾፕ ጉብኝት አካሂደዋል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+4
ዕለተ ማክሰኞ መጋቢት 2/2017ዓ.ም
የተከለሰ የህይወት ክህሎት ስልጠና ለአሠልጣኞች ተሰጠ ።
በየካቲት ወር በተሠጠው ስልጠና ላይ በተለያዩ ምክንያቶች ላልተገኙ አሠልጣኞች የተዘጋጀ የስልጠና መድረክ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። "ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ " ፕሮግራም በተተገበረባቸው ሁለት ዓመመታት ውስጥ የታዩ ክፍተቶችን በማስተካከል የተዘጋጀ ሲሆን ዋና ዓላማውም በከተማ ደረጃ የወጣቶች ስራ አጥነትን ለመቀነስና ለስራ ቅጥር ማዘጋጀት መሆኑንም አሰልጣኙ ገልጸዋል ።
"ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ" ስልጠናው በሁለት ዋና ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሲሆን ቀድሞ ለየብቻ ይሰጥ የነበረው የህይወት ክህሎትና ስራ ማፈላለግ ስልጠና በጣምራ የሚሰጥ ሲሆን
1. የስራ ላይ ደህንነት
2. ፆታን መሠረት ያደረገ ጥቃትን እንዴት መከላከል እንደሚቻል እና ከተከሰተም ምን ማድረግ እንዳለባቸው አቅጣጫ ማመላከት ላይ ያተኩራል።
ስልጠናው በቀደሙ ግዚያት ክፍተት አለበት እየተባለ የተገመገመ ሲሆን አሁን ላይ በተከለሰው የስልጠና ስርዓት ምላሽ ያገኛል ተብሎ ይታሰባል ይላሉ አስተባባሪው አቶ አለማየሁ ፈንታ ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ዕለተ ማክሰኞ መጋቢት 2/2017ዓ.ም
በልዩ ፍላጎት ዙሪያ የተዘጋጀ የግንዛቤ መፍጠሪያ
መርሃ ግብር ተጀመረ ።
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ስልጠና ነው ።
በመክፈቻ ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የኮሌጁ ስልጠናና አካዳሚክ ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ኮሌጃችን በከተማ ደረጃ ካሉ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች በልዩነት መስማት የተሳናቸውን ሰልጣኞች ተቀብሎ የሚያሰለጥን ሲሆን እነኝህን ሰልጣኞች ከግቢ መግቢያ በር ጀምሮ በተለያዩ ቦታዎች ላይ ለመርዳትና /ለማገዝ ያስችል ዘንድ ከሁሉም ክፍል ለተውጣጡ የኮሌጁ ማህበረሰብ ስልጠናውን መስጠት አሌ የማይባል ተግባር መሆኑን ጠቁመዋል።
በመቀጠልም ልዩ ፍላጎት ምንድ ነው? አስፈላጊነቱስ ? ልዩ ፍላጎትን ተግባራዊ ለማድረግ ምን እንቅፋቶች አሉት ? ወ.ዘ.ተበሚሉ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ የሰጡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የልዩ ፍላጎት ትምህርት ክፍል መምህር አቶ ሲሳይ አለሙ(MA)
አካቶ ትምህርት ምንድ ነው ? ለምን አስፈለገ ? እንዴትስ ይሰጣል ? አካቶ ትምህርት ዘር ፣ቀለም፣ የአካል ሁኔታ ሳይለይ ሁሉንም በአንድ ጥላ ስር ማካተት እና ማስተማር ነው በማለት በአካቶ ትምህርት ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገቡ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል በተጨማሪም የአካቶ ትምህርት ጠቀሜታዎችን ምስል ከሳች በሆኑ ምሳሌዎች በየኔነት ስሜት መረዳት በሚያስችል መልኩ መረጃውን አጋርተዋል። ከቤቱ ሃሳብ አስተያየት ተነስቶ ውይይት ተካሂዶበታል።
በመጨረሻም አስተባባሪው ስልጠናው ለሰጡት መምህር ምስጋናቸውን አቅርበው ስልጠናው ቀጣይነት ያለው በመሆኑ ሁሉም በሰዓቱ በመገኘት ሃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል ። ይህ ተግባር ከመንግስት ስራ በተጨማሪ ለሞራል ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የውስጥ ፍላጎትን የሚጠይቅም ነው ብለዋል ። በመሆኑም ሁላችንም ይህን ሃላፊነት በመወጣት ነገ የሚገጥመንን አናውቅምና በእኔነት ከልብ ልንሰለጥን እና ልንከታተል ይገባል በማለት ከአደራ ጭምር አሳስበዋል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ዕለተ ማክሰኞ መጋቢት 2/2017 ዓ.ም
የስዕል ኤግዚቢሽን ጉብኝት ተደረገ።
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመጀመሪያና ሁለተኛ ዓመት የሥዕል ሠልጣኞች በአላያንስ ፍራንስ የተዘጋጀውን የሥዕል ኤግዚቢሽን በትላንትናው ዕለት ጉብኝት አካሄዱ።
የዚህ ሥዕል ኤግዚቢሽን ጉብኝት ዋና ዓላማ በክፍል ውስጥ / በኮሌጁ ከሚሰጠው ስልጠና በተጨማሪ ሠልጣኞች ልምድ የሚቀስሙበትና ክህሎታቸውን ለማዳበር የሚያስችል እንደሆነ የስልጠና ዘርፉ አስተባባሪ ወ/ሮ ዊንታና ንጉሴ ገልጸዋል።
በኤግዚቢሽኑ የቀረቡት ሥዕሎች በእውቁ አፍሪካዊ ሰዓሊ ጆ ሚሼል ቦስክያት የተፈጠሩ ሲሆን በኢትዮጵያውያን ሰዓሊያን መልሰው የተሠሩና የተለያዩ ፈጠራ ታክለውበት ተመልካቹን እንዲስቡና መልእክታቸውን በቀላሉ እንዲገነዘብ ለማድረግ ጥረት የተደረገባቸው እንደሆነ ለመረዳት አያዳግትም ።
ሰዓሊው ከሚከተለው ፍልስፍና አንጻር ስዕሎቹ በእውኑ ዓለም የሚታዩ የአፍሪካዊ ማህበረሰብ ወግና ልማድ፣ እምነትና ትውፊት እንደዚሁም ባህል እና አስተሳሰብ የሚያንፀባርቁ ከመሆናቸው በተጨማሪ የእሳት፣ውኃ፣አፈርና ንፋስ ተፈጥሯዊ ክስተቶች ውህድ መሆናቸውን አስጎብኝዋ ወ/ሮ ሳሌም ጉልላት ገልፀዋል ።
አስጎብኝዋ እንደሚሉት የጆ ሥዕሎች አፍሪካዊውን/የጥቁር ማህበረሰብ ማንነት ከማንፀባረቅ በዘለለ የኢትዮጵያ ታሪክ መለያ የሆኑትን አቢሲኒያ የሚለውን ቃል እና በተለያዩ ቦታዎች የሚታዩት የዘውድ ምስሎች የተለየ ቁርኝት አለው ። ኤግዚቢሽኑ ለሁለተኛ ግዜ በኢትዮጵያ መታየቱም እንደዚሁ ።
የሥዕል ሥራ ውጤቶቹ ከተለያዩ ማቴሪያሎች ማለትም እንጨት፣ሸራና ቀለም ቁርጥራጭ ቁሳቁሶች ወ.ዘ.ተ የተጠቀመ በመሆኑ የፈጠራ አቅሙ የላቀ እንደነበር ለመገመት አያዳግትም ።
ሰዓሊው በ1980ዎቹ የበለጠ ተቀባይነት እና እውቅና ያገኘበት እንደነበር 1986 የመጀመሪያ ኤግዚቢሽኑ በናይጄሪያ አቡጃ እንዳቀረበ እና በ1987 ደግሞ ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለየ ከአስጎብኝዋ ከቀረበ መረጃ ለማወቅ የተቻለ ሲሆን ከህልፈቱ በኋላ የስራው ውጤቶች ህያው ሆነው እንደቀጠሉ ናቸው።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ዕለተ ዓርብ የካቲት 28/2017ዓ.ም.
የ8ኛ ወር የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ተገመገመ ፡፡
በመድረኩ የኮሌጁ ኮር አመራሮች ፣ ማኔጅመንት እና አካዳሚክ ኮሚሽን የተሳተፉበት ሲሆን በዕቅድ ዝግጅት እና ክትትል ዳይሬክቶሬት የአፈፃፀም ሪፖርቱን ቀርቧል ። የISO ትግበራ ሂደትም ተዳሶበታል።
የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖረቱ በስምን ት ወራት አፈጻጸም ላይ መሰረት ያደረገ ሲሆን በዕቅድ ዝግጅትና ክትትል ዳይሬክቶሬት ባለሙያ ቀርቧል ።
በአጠቃላይ አቀራረቡም ሆነ ዝግጅቱ ከቀደሙት ግዚያት አንጻር የተሻለ መሆኑ ተጠቁሟል። በሪፖርቱ ያልተካተቱና አፈጻጸማቸው በውል ያልተለካ ተግባራት መኖራቸው ከቤቱ በቀረበ አስተያየት ተንጸባርቋል ። በተጨማሪም በቂ ማብራሪያ ያልቀረቡባቸው ርእሰ ጉዳዮች መኖራቸው ተመላክቷል ።
የISO ትግበራ ስራዎች ተጠናክሮ እየተሰራ ቢሆንም የኮሌጁ ማህበረሰብ በሚፈለገው ልክ ግንዛቤውን በውል የጨበጠው ስለማይመስል በየዘርፉ የተጠናከረ ስራ መሰራት አለበት በማለት አቅጣጫ ተቀምጧል ።
በአጠቃላይ ከቤቱ የተነሱ ሃሳቦችን መሠት በማድረግ መስተካከል ያለባቸው ጉዳዮች ተስተካክለውና ክትትል የሚያስፈልጋቸው ስራዎችን በየዘርፉ በመከታተል እንዲፈፀሙ አቅጣጫ ተሰጥቷል ።
ኮሙኒኔሽን ቡድን
1 146
+7
ዕለተ ዓርብ የካቲት 28/2017ዓ.ም
የክህሎት ክፍተት ስልጠና በመሠጠት ላይ ነው ።
ከሃገረ ቻይና በመጡ ከፍተኛ ባለሙያ (Liu Shaohua, Ph.D.) በትላንትናው ዕለት የተጀመረው የክህሎት ክፍተትን የሚሞላና ተጨማሪ አቅምን የሚፈፈጥር ስልጠና ለ25 የአውቶሞቲቭ አሠልጣኞች በመሠጠት ላይ ነው ።
ስልጠናው የሚያተኩረው በኤሌክትሪክ ሃይል በሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ላይ ሲሆን በመስኩ ከዘመኑ ቴክኖሎጂ (Mecatronic Technology) ጋር አብሮ ለመራመድ እና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በር ይከፍታል ተብሎለታል ።
በዋና አሠልጣኝ ተባባሪ ፕሮፌሰርና ዋና ቴክኒሻን ዶ/ር ሊዮ ሻዎሃ ለአምስት ተከታታይ ቀናት የሚሰጠው ስልጠና በቪዲዮ የተደገፈ ሲሆን በተቋማችን የሚታየውን ዘመኑ የሚጠይቀውን ሾፕ እና የማሰልጠኛ መሳሪያዎች ያለመኖር ችግር ይቀርፋል ተብሏል።
የስልጠና አመቻቿ ሚስ ሊ (Ms .Lii) ይህ ስልጠና እውን እንዲሆን የተጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተጠቁሟል።
ይህ የአቅም ግንባታ ስልጠና የቻይና አፍሪካ አጋርነት በሚል የትብብር ስምምነት ማዕቀፍ ስር እየተካሄደ መሆኑን የአውቶ ሞቲቭ ስልጠና ዘርፍ ተጠሪ አቶ ደሳለኝ አዱኛ ገልፀዋል ። አስተባባሪው እንደሚሉት ስልጠናውን ለማግኘት የመስኩ አሠልጣኞች ለረጅም ግዚያት ሲጠይቁት የቆየ እና በአሁኑ ሰዓት ምላሽ እያገኘ ነውም ብለዋል ።
በስልጠናው መክፈቻ ላይ የተገኙት የተቋማት አቅም ግንባታ ም/ዲን ዶ/ር ከበደ በዬቻ የእንኳን ደህን መጣችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈው አሠልጣኞቹ ከዚህ ስልጠና ጨማሪ ክህሎት አግኝተው እና የክህሎት ክፍተታቸውን ሞልተው በስልጠና ሂደቱ ላይ አወንታዊ ለውጥ እንደሚኖረው እምነታቸው የፀና መሆኑን ገልፀዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
