1 146
订阅者
无数据24 小时
-37 天
-1830 天
帖子存档
1 146
የእንጦጦ ፖ/ቴ /ኮሌጅ
የሠራተኞች የእዉቅና መርሃ ግብር ተካሄደ።
ሐምሌ 13 ቀን 2016 ዓ.ም
የእንጦጦ ፖ/ቴ /ኮሌጅ በ2016 ዓ.ም የስራ ዘመን የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የሥራ ክፍሎችና ሠራተኞች የእዉቅና መርሃ ግብር በዛሬዉ እለት አከናወኗል።
በዚሁም መሰረት ዉጤታማ የአሰለጣጠን ሂደት ፣ ቴክኖሎጅና ምርምር፣ ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ፣ የፈጠራ ስራ ፣ የክህሎት ዉድድር ፣ፋሽን ሾዉ፣ ካይዘን አተገባበር ፣ የደንበኛ አገልግሎት እና የተቀላጠፈ አሰራር ፣ ስፖርታዊ ተሳትፎ ፣ ጥበቃና ደህንነት፣ ማህበራዊ አገልግሎት እንዲሁም በተለያዪ ዘርፎች የላቀ አስተዋፅኦ ያስመዘገቡ እና አርእያ ሊሆኑ የሚችሉ የስራ ክፍሎች እና ግለሰቦች የእዉቅና ሰርትፍኬት ተበርክቶላቸዋል ።
ሽልማቱ እና እዉቅናዉ የመስራት ሞራልን እና ምርታማነትን እንደሚጨምር
እና ለቀጣይ የስራ ዘመን በየክፍሉ አዉንታዊ የፉክክር መንፈስን እንደሚፈጥር የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ ተናግረዋል። ተሸላሚዎችም በመርሃ ግብሩ መደሰታቸዉንና እዉቅናዉ የሞራል ስንቅ እንደሆናቸዉ ለክፍላችን ተናግረዋል።
**በእያንዳንዱ ዘርፍ ላይ እዉቅና ያገኙ የስራ ክፍሎችና ግለሰቦችን ዝርዝር ከነፎቶ ማስረጃ በቀጣይ ይዘን እንመጣለን ።
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
የቢዝነስ ትምህርት ስልጠና ዘርፍ
የተቋም ዉሰጥ ምዘና አካሄደ።
ሀምሌ 10 ቀን 2016 ዓ.ም
የቢዝነስ ትምህርት ስልጠና ዘርፍ በ2016 ዓ.ም የተቀበላቸዉን የሰዉ ሃይል አስተዳደር ሰልጠኞች በደረጃ 2 የተቋም ዉስጥ ምዘና (Institutional Assessment) አካሂዷል። 21 ሰልጣኞች (ወንድ 2፣ ሴት 19 ) ወደሚቀጥለዉ ደረጃ ለመሸጋገር የተመዘኑ ሲሆን ምዘናዉን ያከናወኑት የቢዝነስ ት/ት ክፍል ባልደረቦች ወ/ት ሀብታም ዲበኩሉ እና አቶ አለማየሁ ፈንታ ናቸዉ።
የምዘናዉን ሂደት ለመመልከት የተገኙት የኮሌጁ የአካዳሚክ ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተሰፋዬ ለሰልጣኞች ስለምዘናዉ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን በማብራሪያቸዉም ሰልጣኞች እያንዳንዱን የተቋም ዉስጥ ምዘናንበማለፍ ለዋናዉ አገርአቀፍ ምዘና መዘጋጀት እንዳለባቸዉ የገለጹ ሲሆን ለተቋም ዉስጥ ምዘናዉም መልካም እድል እንዲገጥማቸዉ ተመኝተዉላቸዋል።
ምዘናዉን ከ84 ነጥብ በታች በማምጣት ማለፍ ያልቻሉ ሰልጣኞች
ከ10 ቀናት በኋላ የድጋሜ ምዘና እንደሚሰጠቸዉ የት/ክፍሉ ሃላፊ አቶ ጌታሁን ታደሰ ገልጸዋል።
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ለእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ የጥበቃ አባላት
የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም ተዘጋጀ።
ሀምሌ 10 ቀን 2016 ዓ.ም
ለእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ የእንጦጦ እና የሽሮሜዳ ካምፓስ የጥበቃ አባላት እና ካምፓስ ፖሊሶች ክረምቱን አስመልክቶ ከጥበቃ እና ደህንነት ጋር የተያያዘ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሂዷል።
መርሃ ግብሩ የተዘጋጀዉ የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ ከጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 02 መነን ፖሊስ ጣቢያ የማሀሰበረሰብ አቀፍ ፖሊስ ኮምኒዩቲ ጋር በመተባበር ሲሆን ግንዛቤዉን የሰጡት ዋና ሳጅን ተሾመ ባዬ እና ባልደረቦቻቸዉ በዋነኝነት ትኩረት አድርገዉ ያስገነዘቡት የክረምቱ ጊዜ የሚፈጥረዉ ዝናብ እንደዚሁም ቁጥቋጦ የጥበቃዉ ስራ ላይ ሊፈጥር የሚችለዉን አሉታዊ ተጽእኖ እንዴት መወጣት እንደሚቻል እንዲሁም በንቃት እና በጥንቃቄ ግቢዉን ከዘራፊዎች መከላከል እንዴት እንደሚቻል እና ጥበቃዎች ከፖሊስ ጋር ተቀናጅተዉ ስለሚሰሩበት ሁኔታ ነዉ።
ፕሮግራሙን የተካፈሉ የጥበቃ እና ካምፓስ ፖሊስ አባላት ከክረምቱ ጋር በተያያዘ ለክረምት የሚሆኑ የዝናብ አልባሳት እና ሌሎች ግብአቶች እንዲሟሉላቸው የጠየቁ ሲሆን በአጭር ጊዜ ዉስጥ ኮሌጁ ጥያቄያቸውን እንደሚመልስ በመድረኩ ተገልጿል ።
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ ኮሙኒኬሽን በድን
1 146
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ የ2016 ዓ.ም በጀት አመት
የአፈጻጸም ምዘና ተካሄደ ።
ሀምሌ 9 ቀን 2016 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ በየ 6 ወሩ የሚያከናዉነዉን የተቋማት ምዘና በእንጦጦ ኮሌጅ በመገኘት የ2016 ዓ.ም በጀት አመት የኮሌጁን የማጠቃለያ የስራ የአፈጻጸም ምዘና አካሂዷል።
የባለሙያ ቡድኑም በኮሌጁ ዉስጥ የሚገኙትን 5 ዲኖች ፣ 11 የስልጠና ዘርፎች ፣ 8 ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሮች እና 9 የስራ ክፍል አስተባባሪዎችን የስራ አፈጻጸም በመመዘኛ መስፈርቱ መስረት ተመልክቷል ።
የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ የምዘና ባለሙያዎች በሰጡት የቃል ግብረ መልስ የኮሌጁ የስራ አፈጻጸም አመርቂ መሆኑን ገልጸዉ አጠቃላይ የምዘና ዉጤቱን በጽሁፍ እንደሚያሳዉቁ ገልጸዋል ።
የኮሌጁ ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ለጉለሌ ክ/ከተማ ፓሊስ መምሪያ ተወርዋሪ ሃይል ክፍል የንብረት ድጋፍ ተደረገ።
ሀምሌ 9 ቀን 2016
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ ለአዲስ አበባ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ጉለሌ ክ/ከተማ ተወርዋሪ ሃይል ክፍል አባሎች ለመመገቢያ ክፍል የሚዉል በኮሌጁ ዉስጥ ያገለገሉ 13 ጠረንጼዛዎች እና 50 ወንበሮች በዛሬዉ እለት ድጋፍ አድርጓል።
ርክክቡን ያደረጉት የአንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ ንብረት አስተዳደር ዋ/ዳይሬክተር ወ/ሮ እየሩሳሌም መንግስቱ እና የጉለሌ ክ/ከተማ ፖሊስ ተወርዋሪ ሃይል ክፍል ማስተባበሪያ ሃላፊ ዋ /ኢንስፔክተር በቀለች ሽፈራዉ እና የጉለሌ ክ/ከተማ ፓሊስ መምሪያ ተወርዋሪ ሃይል ሻምበል መሪ ም/ኢንስፔክተር ሰለሞን ስሜ ናቸዉ።
የጉለሌ ክ/ከተማ ፓሊስ መምሪያ ተወርዋሪ ሃይል ክፍል ስለተደረገለት ድጋፍ አመስግኖ ከኮሌጁ ጋር በቀጣይም በቴክኒካዊ ስልጠና እና ሌሎች መስኮች አብሮ የመስራት ፍላጎት እንዳለዉ በርክክብ ስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት አመራሮች ገልጸዋል ።
የኮሌጁ ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
በአዲሱ የስልጠና ፖሊሲ ለሠለጠኑ እጩ ተመራቂ ሰልጣኞችበከተማ ደረጃ የተዘጋጀው ምዘና ለተከታታይ ሦስት ቀናት በቢዝነስ ስልጠና ዘርፍ ለማርኬቲንግ እና ሴክሬተሪ ሰልጣኞች የተሰጠ መሆኑ ይታወሳል።
በመሆኑም የምዘናውን አፈጻጸም መሠረት ያደረገ ግምገማ ከስልጠና ዘርፉ አሠልጣኞች፣ መዛኞችና ሱፐርቫይዘሮች ጋር በጋራ ውይይት ተካሂዷል።
በዚህ መልኩ ትኩረት ተሰጥቶት ምዘናው መካሄዱ ሠልጣኙንም ሆነ አሠልጣኙን ጠንክሮ እንዲሰራ የሚያደርግ በመሆኑ ጥሩ ጅምር መሆኑን ጠቁመው በማሰልጠን ሂደቱ ላይም ሆነ በምዘናው ፓኬጅ አሉ ያሏቸውን ክፍተቶች በማመላከት በቀጣይ መስተካከል አለባቸው ያሏቸውንም ጠቁመዋል።
በማጠቃለያ የኮሌጁ ሥ/አካ/ጉ/ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ የተነሱትን ሃሳቦች፣ማስተካከያዎች በየደረጃቸው ጥረት የሚደረግባቸው መሆኑን ጠቁመው በአጭር ግዜ ሠልጣኞቹን የማብቃት ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና ለአጠቃላይ ምዘናው ዝግጁ እንዲሆኑ የተቀመጠው አቅጣጫ በጋራ መግባባት ላይ ተደርሶበታል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
