1 148
订阅者
无数据24 小时
-37 天
-1830 天
帖子存档
1 148
+7
ክቡር አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ ከቀድሞ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ከነበሩት ከክቡር አቶ ጥራቱ በየነ ጋር የስራ ርክክብ አደረጉ።
🇪🇹ህዳር 1/2018 ዓ.ም🇪🇹
በቅርቡ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ሆነው የተሾሙት ክቡር አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ ከቀድሞ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ከነበሩት ከክቡር አቶ ጥራቱ በየነ ጋር የስራ ርክክብ አድርገዋል።
በዛሬዉ ዕለት በተደረገዉ የስራ ርክክብ ወደ ሌላ ተቋም የተሾሙት ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ ባደረጉት ንግግር በቢሮው በነበራቸው ቆይታ እና ለተመዘገቡ ስኬቶች የማኔጅመንት አባላቱን እና በየደረጃው የሚገኙ የክፍለ ከተማና የኮሌጅ ዲኖችን አመስግነዋል።
በቀጣይም ከአዲሱ አመራር ጋር በመቀናጀት የተጀመሩ ስራዎች ፍፃሜ እንዲያገኙ መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ በበኩላቸው የቀድሞው አመራር በሳል አመራር በመስጠት ቢሮው አሁን ለደረሰበት ደረጃ እንዲበቃ አስችሏል ብለዋል።
ክቡር አቶ ሚሊዮን አክለውም የጋራ ዓላማ በመያዝ እና እንደ አንድ ቡድን በመሆን የተያዙ ዕቅዶችን ለማሳካት እጅና ጓንት ሆነን እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል።
መረጃው የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ነው
1 148
01/03/2018 ዓ/ም
የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ፡፡
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ” ሙያዊ ስነ ምግባርን ማስረፅ” በሚል መሪ ቃል ለአስራ ሶስተኛ ቀን ተካሄደ ፡፡ በእለቱ የስራ ላይ ስነ ምግባር ለኮሌጁ ህብረተሰብ በአቶ ነገሰ ተፋረደኝ ግንዛቤ የተፈጠረ ሲሆን በዝርዝር የስራ ላይ ስነምግባር ምንድን ነው ? ፣ የሰራተኞች ስነ ምግባራዊ ኀላፊነት ፣የሙያ ላይ ስነ ምግባር ፣በስራ ላይ የሚታዩ የስነ ምግባር ጉለቶች ፣ ስነ ምግባር ችግር የሚፈታበት አሰራር ፣ የባለሙያ ሚና እና የኮሚኒኬሽን ባህሪያት በስፋት ቀርቧል ፡፡ የኮሌጁን ማህበረሰብ በየስራ ላይ ስነምግባር የተሻለ ግንዛቤ እንዳለው ቢታመንም ስራ ላይ በማዋል ስራን በተመደበለት ጊዜ በመስራት የተሰጣቸውን ኀላፊነት ለመወጣት ኀላፊነት መውሰድ እንዳልባቸው እና በመቀናጀትና በጋራ በመስራት አላማችንን እንደ ኮሌጅ ማሳካት እንደሚቻል ገልፀዋል ፡፡ የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ አብድልበር መሀመድ እንደተቋም እራሳችንን በደንብ ማየት እንዳለብንና ከእኔ ምንድን ነው የሚጠበቀው የሚለውን ያሳያል በማለት ትልቁ ሀብታችን ጊዜ ስለሆነ ጊዜያችንን ለስራ በማዋል በደንብ ኮሌጃችንን ለመገንባት እንጠቀምበት በማለት መልክት አስተላልፈዋል ፡፡
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 148
Repost from N/a
ሌሎቻችሁ ማለትም
🎨 Painting
Sculpture
Graphics Art
Theatrical Art
በተባለው ቀን መጥታችሁ እንድትፈተኑ !!!
1 148
https://vm.tiktok.com/ZMHc4j8ghvVfK-k5P6I/ This post is shared via TikTok Lite. Download TikTok Lite to enjoy more posts: https://www.tiktok.com/tiktoklite
1 148
26/02/2018 ዓ/ም
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለመለስተኛ የእደጥበብ የኢንዱስትሪ ባሌበቶች ስልጠና ተሰጠ ።
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ጋር በትብብር ለመለስተኛ የእደጥበብ የኢንዱስትሪ ባሌበቶች ስልጠና ተሰጥቷል !!!!
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 148
26/02/2018ዓ.ም
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለመጀመሪያ ዙር አዲስ ሰልጣኞች ኦሬንቴሽን ተሰጠ።
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ2018 ዓ.ም የመጀመሪያ ዙር አዲስ ሰልጣኞች ምዝገባ በአዲሱ አሰራር ላጠናቀቁ ኦሬንቴሽን በኮሌጁ ዋና ዲን አቶ አብዱልበር መሀመድ ፣ በኮሌጁ ስልጠና አካ/ጉ/ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ እና በሬጅስትራል ፅ/ቤት ሀላፊ በአቶ ስመኝ ሚደቅሳ እና በሰልጣኝ ካውንስል ፕሬዝዳንት በናሆሞ በመስጠት የስልጠና መርሀ ግብር ተጀመረ !!!!
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
