ch
Feedback
Ethiopian Public Service University

Ethiopian Public Service University

前往频道在 Telegram

ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

显示更多

📈 Telegram 频道 Ethiopian Public Service University 的分析概览

频道 Ethiopian Public Service University (@epsutelegram) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 12 737 名订阅者,在 教育 类别中位列第 15 736,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 645

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 12 737 名订阅者。

根据 13 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 112,过去 24 小时变化为 2,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 34.81%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.93% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 434 次浏览,首日通常累积 2 029 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 30

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

凭借高频更新(最新数据采集于 14 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。

12 737
订阅者
+224 小时
+217
+11230
帖子存档
19ኛዉ የኢትዮጵያ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በኢሲሰዩ ተከበረ ------------------------------------ 19ኛዉ የኢትዮጵያ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ “አገራዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት" መሪ ቃል ሕዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም በሕዳሴ አዳራሽ ተከበረ፡፡ በዝግጅቱ ላይም የዩኒቨርሲቲው የበላይ አመራሮች፣ መምህራንና ሰራተኞች እንዲሁም ተማሪዎች ተሳትፈዋል፡፡ በዝግጅቱ መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ ባደረጉት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በተለያዩ መሪ ቃላት ሲከበር መቆየቱን አስታውሰው ዘንድሮም በአገራችን ለአስራ ዘጠነኛ ጊዜ “አገራዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል በፌዴራሊዝም፣ በህገ መንግስት ስርጸትና ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ እየተከበረ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም በዓሉን በደመቀ ሁኔታ ለማክበር የኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የአገር ግንባታ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት በሚኖረው ሚና ላይ የውይይት ሠነድ አዘጋጅቶ ለትምህርት ተቋማት ማህበረሰብ ተደራሽ በማድረግና ስልጠና በመስጠት፣ ወደስራ የገባ ሲሆን የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲም በስልጠናው ላይ በመሳተፍ በዓሉን በዩኒቨርሲቲ ደረጃ ለማክበር ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡ በመቀጠልም ይህ በመከበር ላይ ያለው 19ኛዉ የኢትዮጵያ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል ኢትዮጵያውያን ህብረታቸውን አጉልተው የሚያሳዩበት፣ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታቸው ደምቆ የሚታይበት፣ የጋራ የሆነውን መገለጫቸውን በማድመቅ፣ በመቻቻል እኩልነትን በማስፈን እና አብሮነትን በማስቀጠል ረገድ ውጤት የሚመዘገብበት በዓል መሆኑን የገለጹት ፕ/ር ፍቅሬ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ኢትዮጵያውን በጋራ ለጋራ ጥቅም እጅ ለእጅ ተያይዘው ሀገራቸውን ወደፊት ለማራመድ ቃል የሚገቡበት እና ህብረ ብሔራዊ አንድነት የሚገለጽበት፣ በውጤቱም ሀገራዊ መግባባትን የሚረጋገጥበት እንደሚሆን አመላክተዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲያችንም የፐብሊክ ሰርቪሱን አቅም የመገንባት ተልዕኮ የተሰጠው እንደመሆኑ የመንግስት አገልግሎቶች ቀልጣፋና ጥራታቸውን የጠበቁ ይሆኑ ዘንድ በየደረጃው ያሉ የመንግስት ሰራተኞች የፌዴራል ሥርዓቱን ተረድተው ብዝሀነትን ባከበረ መልኩ እና ህዝብን እንዲያገለግሉ የበኩሉን አስተዋጽኦ በማበርከት ላይ ይገኛል፡፡ ይህን 19ኛዉ የኢትዮጵያ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል በዩኒቨርሲቲያችን ስናከብርም በዓሉ በሀገራችን ህዝቦች መካከል አንድነትን በማጉላት፣ ለሀገራዊ መግባባት የሚኖረውን አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት ነው፡፡ ምንም እንኳን በርካታ ስራዎች በመሰራት ላይ ያሉ ቢሆንም ካለፉት ጊዜያት ጀምሮ የነበሩ የሰላም መታጣትና ግጭቶች መኖራቸው ያላጠናቀቅናቸው ሥራዎች መኖራቸውን የሚያሳዩ ናቸው ያሉት ፕ/ር ፍቅሬ የተጀመረውን ሀገራዊ ምክክር ውጤታማ በማድረግ ለህዝባችን ሰላም፣ ልማትና አንድነት ሁሉም የባለድርሻ አካላት በአንድነት መስራት እንደሚጠበቅባቸው በአጽንኦት አሳስበዋል፡፡ በፕሮግራሙ ላይም የመወያያ ጽሑፍ በዶ/ር ግሩም ክንፈ ሚካኤል የፌደራሊዝም ትምህርት ክፍል ኃላፊ የቀረበ ሲሆን ዶ/ር ግሩም በጽሁፋቸው በማህበረሰቡ ዘንድ በፌዴራሊዝም እና በፌዴራል ሥርዓት ላይ ወጥ የሆነ ግንዛቤ አለመኖሩን ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም ህብረ ብሔራዊ የፌዴራል ሥርዓት ግንባታ ሂደት ላይ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶች በዝርዝር አቅርበዋል፡፡ ህብረ ብሔራዊ የፌዴራል ሥርዓት ግንባታ ሂደት ላይ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶች መካከልም የፌዴራል ሥርዓቱ በተገቢው ለመተግበር የሚያስችል ፌዴራላዊ እሳቤ በተገቢው ደረጃ አለመዳበር፣ የፌዴራል ሥርዓቱን ለመገንባት መሠረታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ በአገሪቱ ልሂቃን መካከል ደረጃውን የጠበቀ መግባባት አለመፈጠር፣ ህገመንግስታዊነት አለመዳበር፣የዲሞክራሲ አለመዳበር፣ የዳበረና ተቋማዊነትን የተላበሰ የመንግስታት ግንኙነት በተገቢው ሁኔታ አለመገንባት፣ሥርዓቱን ለመተግበር አስፈላጊ የሆኑ ተቋማት እና የአሰራር ሥልቶች አለመዳበር እና የመሳሰሉት ተግዳሮቶችን ለአብነት አሳይተዋል፡፡ ለእነዚህ ተግዳሮቾችም የመፍትሔ አማራጮችን ሲጠቅሱ በፌዴራሊዝምና በፌዴራል ሥርዓቱ ላይ ትክክለኛ እይታ መገንባት፣ የፌዴራል ሥርዓትን ለመገንባት ሀገራዊ መሰረት በሆኑ ጉዳዮች ላይ መግባባትን መፍጠር፣ ህገ-መንግስታዊነትን ማዳበር፣ በየወቅቱ ለሚነሱ ጉዳዮች ፌዴራላዊ በሆነ አግባብ ምላሽ መስጠት፣ አክራሪ ብሔርተኝነትን በማዳከም ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ማጎልበት፣ ብዝሀነትን ተቀብሎ በየደረጃው ማስተናገድና ሀገራዊ አንድነትን ማጎልበት እና የመሳሰሉት ጉዳዮችን በመፍትሔነት አቅርበዋል፡፡ በውይይቱ ላይም ከተሳታፊዎች የተለያዩ ሀሳብና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን የግለኝነት መስፋፋት፣ የሀገራዊ ስሜት መዳከም፣ የስልጣን ፍላጎት፣ የማያግባቡ ነገሮች መብዛት እና ሌሎችም ወቅታዊ ጉዮች የሀገር ፈተናዎች መሆናቸውን ተጠቅሰው ካለፈው ስህተት በመማርና ወደ እያንዳንዱ የማህበረሰብ ክፍል በጥልቀት ወደራሱ በመመልከት እና ለመጪው ትውልድ በማሰብ ሀገራዊ መግባባት ላይ መድረስ ተገቢ መሆኑ በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡

𝐄𝐂𝐒𝐔 𝐏𝐫𝐞𝐬𝐢𝐝𝐞𝐧𝐭 D𝐢𝐬𝐜𝐮𝐬𝐬𝐞𝐬 𝐰𝐢𝐭𝐡 𝐭𝐡𝐞 𝐂𝐮𝐥𝐭𝐮𝐫𝐚𝐥 𝐀𝐟𝐟𝐚𝐢𝐫𝐬 𝐎𝐟𝐟𝐢𝐜𝐞𝐫 𝐚𝐭 𝐭𝐡𝐞 𝐔𝐒 𝐄𝐦𝐛𝐚𝐬𝐬𝐲 --------------------- President of Ethiopian Civil Service University, Professor Fikre Dessalegne, Discussed with Ryan Bradeen, Cultural Affairs Officer at the US Embassy in Addis Ababa, on potential partnership opportunities between the parties on November 2, 2024 at ECSU Senate Hall. Professor Fikre welcomed the USA cultural affairs team lead by Ryan Bradeen and explained the overall Ethiopian Civil Service University establishment and its journey in the last three decades. Besides, he briefed what the university has done for the last two years in different phases to be an autonomous university and what will be done in the coming three consecutive years .He also briefed ECSU interest to create strong relations and make strategic partnership on different areas with international partners. Dr. Abrham Hagos, ECSU President’s Office Head, in is part explained the university’s overall profile and its strategic goal as research and autonomous university and its achievements to the team. Mr. Ryan Bradeen also explained USA and Ethiopian long relations in different areas and Education sector .He also expressed his interest to make collaborations and work together with Ethiopian Civil Service University in different academic areas. The discussion also focused on how to make different potential partnership and collaboration including workshop and seminar, joint research in different thematic areas, training and staff development, E-library, and scholarship for students and staff.

To those who have been accepted into the PhD programs to our University please refer to the following link for registration procedures and further instruction .

የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድና የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የመደበኛና የሪፎርም ስራዎች አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ፡፡ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድና የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የመደበኛና የሪፎርም ስራዎች አፈጻጸም ግምገማ ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም በሕዳሴ አዳራሽ አካሄደ፡፡ በግምገማ መድረኩም የ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት የዩኒቨርሲቲው አጠቃላይ ዕቅድ ላይ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖረት ላይ ካውንስሉ በዝርዝር ተወያይቷል፡፡ በግምገማ መድረኩም ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የቀረበው ዕቅድ የየዘርፍ አመራሮች የተሳተፉበትና በየደረጃው ሰፊ ውይይት ሲደረግበት የቆየ መሆኑን እንዲሁም የዩኒቨርሲቲውን የአስር ዓመት መሪ ዕቅድ እና በውስጡ የተቀመጡ ግቦችንና ቁልፍ ተግባራት መነሻ አድርጎ የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በመደበኛነት ከሚከናወኑት ተግባራት በተጨማሪም በቀጣይ ዩኒቨርሲቲውን ለመለወጥ የሚያስችሉ የሪፎርም ሥራዎችንም በዕቅዱ እንዲካተቱ መደረጉን፤ ዩኒቨርሲቲውም በቀጥታ ተጠሪነቱ ለኢፌዴሪ የትምህርት ሚኒስቴር እንደመሆኑ መጠንም የትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ያስተላለፈውን በዋናነት የትምህርትና የምርምር ሥራዎች ጥራትን ለማረጋገጥን የሚሰሩ ስራዎችን ለመለካት የተቀመጡ የውጤት አመላካቾችን መነሻ አድርጎ የታቀደ እቅድ መሆኑንም አመላክተዋል፡፡ ባለፉት ሶስት ወራም የክረምትና ተከታታይ ትምህርት ሲሰጥ የቆየ መሆኑን፣ የብሔራው ፈተና ተፈታኞች ድጋፍ ማድረግ፣ የመምህርን አቅምን የመገንባት ስራዎች፣ የተለያዩ ስልጠናዎችና የምዘና አገልግሎት ለሲቪል ሰርቪስ ተቋማት ሲሰጥ የቆየ መሆኑንና የ2017 ዓ.ም ተማሪዎችን የመመዝገብ እና የማስተማር ስራን ማስጀመር በአካዳሚክ ዘርፍ መከናወናቸውን የጠቀሱት ፕ/ር ፍቅሬ በምርምር ዘርፉም ከመንግስት በተፈቀደ በጀት የሚሰሩ ምርምሮችን የመምረጥ እና በበጀት የመደገፍ፣ የምርምር ውጤቶችን በጆርናሎችና ፕሮሲዲንግ በማሳተም ለተጠቃሚዎች ተደራሽ የሚሆኑበት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች፣ የምርምር ውጤቶችን በዲጂታል ቋት የማሰባሰብ ስራዎች፤ በአስተዳደርና ልማት ዘርፍም ለራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲነት እየተደረገ ባለው ጥረት ብቁና በቂ የሰው ኃይልን ከማጠናከር አኳያ የአካዳሚክ ሰራተኞችን ፕሮፋይል በማደራጀትና በመተንተን አዲስ ውል የሚገቡበት ሁኔታ የተዘጋጀ ሲሆን አስፈላጊው የትምህርት ግባትና መሰረተ-ልማት ማስፋፋት ስራዎች፣ አዳዲስ የገቢ ማመንጫ ስራዎችን የመለየት፣ የተለያዩ ትስስርና ጉድኝቶችንም ከተለያዩ ተቋማትና ድርጅቶ ጋር ለመመስረት ሰፋፊ ስራዎች ባለፉት ሶስት ወራት መከናወናቸውን ፕ/ር ፍቅሬ ለካውንስሉ ገልጸዋል፡፡ በማስከተልም የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድና የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት በአቶ ተፈሪ ጊሼ የስትራቴጂያዊ ጉዳዮች ሥራ አስፈጻሚ የቀረበ ሲሆን ዕቅዱም የትምህርትና ስልጠና አግባብነት፣ ተደራሽነትና ፍትሃዊነትን ማሳደግ፣ የጥናትና ምርምር፣ የማማከር አገልግሎት ማሳደግ፣ የማህበረሰብ ተሳትፎ፣ የሳይንስ ባህል ግንባታ እና የኢንዱስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግርን ማሳደግ፣ የትምህርትና የስልጠና አገልግሎት፣ አሠራርና ጥራትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ መመሪያዎችና ስታንዳርዶችን ማዘጋጀትና መተግበር፣ የሰው ኃይልና ተቋማዊ አቅምና ብቃት ማጎልበት፣ ቴክኖሎጂ፣ መሠረተ ልማትና ፋሲሊቲ ማሳደግ፣ አጋርነት፣ ትስስር እና አለማቀፋዊነትን ማሳደግ እንዲሁም የበጀት፣ የፋይናንስ፣ የንብረት አስተዳዳር አገልግሎትን ውጤታማነትን ማሻሻልና የውስጥ ገቢ ማሳደግ የሚሉትን ግቦች ያነገበ መሆኑን እና ግቦቹን ለማሳካት የሚከናወኑ ዓላማዎችና ዋና ዋና ተግባራቶችን በዝርዝር በሪፖርታቸው አመላክተዋል፡፡ በማስከተልም የመጀመሪያው ሩብ ዓመት በተቀመጡት ስትራቴጂያዊ ግቦችና ዓላማዎች መሰረት የተሰሩ ስራዎችን በሪፖርት ያቀረቡት ሲሆን በትምህርት አገልግሎት የላቀ ውጤት ማስመዝገብ፤ በጥናትና ምርምር ፤ በስልጠና አገልግሎት ፤ ማማከር አገልግሎት ፤ በማህበረሰብ አገልግሎቶች የላቀ ውጤት ማስመዝገብ እና የዩኒቨርሲቲው የውስጥ አቅም ግንባት የ2017 ዓ.ም ዋና ዋና የትኩረት መስኮች መሆናቸውን አቶ ተፈሪ በሪፖርታቸው ገልጸዋል፡፡ በግምገማ መድረኩ ላይም የሪፎርም ስራዎች አፈጻጸም ሪፖርት በዶ/ር አብርሃም ሐጎስ የፕሬዚደንት ጽ/ቤት ኃላፊ የቀረበ ሲሆን በሪፖርቱም መሰረት ዩኒቨርሲቲው በየደረጃው የተቀመጡትን መስፈርቶች በማሟላት ሙሉ በሙሉ ራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ ለመሆን በትምህርት ሚኒስቴር በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት በርካታ ስራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ በዚሁም መሰረት ዩኒቨርሲቲው በ2018 ዓ.ም ከፊል ራስ-ገዝነትን፣ በመቀጠልም በ2019 ዓ.ም ወደ ከፍ ያለ ራስ-ገዝነት ደረጃ በመሸጋገር በመጨረሻም በ2020 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ እራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ እንደሚሆን ፤ ይህ የጊዜ ሰሌዳም በዩኒቨርሲቲው የሥራ አመራር ቦርድም የጸደቀ መሆኑንና በዚህ የጊዜ ሰሌዳ መሰረትም የሚተገበሩ የሪፎርም ስራዎች ተለይተው በትኩረት እየተሰራባቸው መሆኑን ዶ/ር አብርሃም ገልጸዋል፡፡ በእስካሁኑ ሂደትም ተልዕኮና የትኩረት መስኮችን መለየትና ማጠናከር፣ የራስ-ገዝ የሽግግር ሰነዶችን ማዘጋጀት ፣ የምርምር ምርታማነትና ተጽዕኖ ማሳደግ፣ የውስጥ ገቢን ማሳደግ፣ በቂና ብቁ የሰው ኃይልን ማደራጀት፣ ትብብርና ትስስር ማጠናከር፣ መሰረተ-ልማቶችን ፋሲሊቲዎችን ማደራጀትና የመሳሰሉት ስራዎች በስፋት እየተሰራባቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የካውንስሉ አባላትም በቀረበው ዕቅድና የሩብ ዓመት የሥራ የአፈጻጸም ሪፖርት ላይ ያላቸውን ሀሳብና አስተያየት እንዲሁም ትኩረት ሊሰጣቸው ይገባሉ ያሏቸውን ጉዳዮች በማንሳት ሰፊ ውይይት አድርገዋል፡፡

Announcement to All Regular and Extension Students ............................... The Ethiopian Civil Service University acknowledges the requests from various students regarding an extension of the registration period. In response, we are pleased to announce that the late registration period, subject to a penalty, will be extended until Friday, October 11, 2024. We encourage all students who have not yet registered to take advantage of this opportunity. Ethiopian Civil Service University

𝗘𝗖𝗦𝗨 𝗣𝗿𝗲𝘀𝗶𝗱𝗲𝗻𝘁 𝗱𝗶𝘀𝗰𝘂𝘀𝘀𝗲𝘀 𝘄𝗶𝘁𝗵 𝘁𝗵𝗲 𝗣𝗮𝗸𝗶𝘀𝘁𝗮𝗻 𝗔𝗺𝗯𝗮𝘀𝘀𝗮𝗱𝗼𝗿 𝘁𝗼 𝗘𝘁𝗵𝗶𝗼𝗽𝗶𝗮 ....................................................... President of Ethiopian Civil Service University, Professor Fikre Dessalegn discussed with H.E. Mr. Atif Sharif Mian Ambassador of Pakistan to the Federal Democratic Republic of Ethiopia & the African Union in the area of collaboration and partnership in different areas on October 3, 2024. Professor Fikre warmly welcomed the Ambassador and briefed ECSU establishment and mission on building the capacities of the civil servants of the country. He also explained the University’s objective and strategic partnership in education, short term training, and research and consultancy services. Collaboration and networking is one of the strategic agenda of the university and currently ECSU is working with different institutions and organizations nationally and internationally he said. It is also working hard to create regional integration under the higher education capacity-building and be center of Excellence he emphasised H.E. Mr. Atif Sharif Mian also explained the overall public service systems and the National School of Public Policy of Pakistan. Besides, he also expressed his willingness to strengthen partnerships and enhance collaboration between ECSU and National School of Public Policy of Pakistan in different areas.

Urgent notice We have noticed two issues with our Google Form: 1. Some of you submitted your names even if you scored below 50 points. 2. Some listed master's or PhD programs that do not exist at our university. To address these problems, we have made the following changes: 1. You must now enter an NGAT score of 50 or higher to submit the form. If your score is below 50, you will not be able to submit. 2. For the program type, we have changed the question to a multiple-choice format, so you can select from a list of available programs. You cannot submit the form twice, but you can edit your response. Please use the same link to make these updates. It’s important to clarify your choice of master’s or PhD programs now. We will use your responses to make important decisions moving forward. Google form for master’s applicants (https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScvX3Q_BJLJpuqOtP9OhcaXXt3KhU5R0FhS8CQ2d-mZJAa-Xw/viewform?usp=sf_link) Google form for PhD applicants (https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSeXoN558giuuVZLlm_ZlgI_4VkDH-xma5tEsPxR1vrW-kEG6w/viewform?usp=sf_link)