ሰዋስው ☘☘☘☘
前往频道在 Telegram
በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።
显示更多1 161
订阅者
无数据24 小时
无数据7 天
无数据30 天
帖子存档
1 161
❤ ኤጲስቆጶስ አባ አላኒቆስ፦ ጣዖታቱን እንዲአቃልሉ ለሰዎች እንደሚያስተምራቸው ከሀዲው ንጉሥ በሰማ ጊዜ ይዘው ጽኑ ሥቃይን ያሠቀሠዩት ዘንድ መልክተኞችን ላከ። የንጉሥ መልክተኞች መላካቸውን የተመሰገነ አላኒቆስ ሰምቶ በአገረ ስብከቱ ያሉትን ሕዝቦች ሰበሰባቸውና የቊርባን ቅዳሴን ቀድሶ ሥጋውንና ደሙን አቀበላቸው። ከዚህም በኋላ "በቀናች ሃይማኖት ጽኑ ከእንግዲህ ፊቱን አታዩኝም" አላቸው። እነርሱም አለቀሱ ሊስተውትም አልተቻላቸውም ወጥቶም ራሱን ለንጉሥ መልክተኞች አሳልፎ ሰጠ እነርሱም ወስደው ለእዴናው አገር መኰንን ሰጡት። እነርሱም ወደ አገረ እንድኩ ወስዶ በዚያ ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃየው ማሠቃየቱም በሰለቸው ጊዜ ትከሻውን በሰይፍ ይሠነጥቁ ዘንድ ራሱንም ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ መሞቱን አውቆ አማንያን ከሆኑ መርከበኞች አንዱን እንዲህ ብሎ አዘዘው "ወደ ወደቡ ስትደርሱ ሥጋየን በኮረብታ ላይ አድርግ" እርሱም እንዳዘዘው አደረገ።
❤ ከዚህም በኋላ ምዕመናን ሰዎች መጥተው ሥጋውን ወስደው ገነዙት የስደቱም ወራት እስቲያልፍ በእነርሱ ዘንድ አኖሩት ቤተ ክርስቲያንም ሠርተው ሥጋውን በውስጧ አኖሩ ከእርሱም ታላላቅ የሆኑ ድንቆች ተአምራቶች ተደረጉ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ አላኒቆስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኚ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 2 ስንክሳር።
+ + +
❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "ወይንዕዋ ለነፍሰ ጻድቅ። ወይኴንን ደመ ንጹሐ። ወኮነኒ እግዚአብሔር ፀወንየ"። መዝ 93፥21። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 11፥1-8፣ 1ኛ ዮሐ 3፥6-13 እና የሐዋ ሥራ 12፥18-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 23፥13-23። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ አቤል የዕረፍት በዓልና የብርሃን ልደቱ በዓል ሰሞን ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ጥር ፪ (2) ቀን።
❤ እንኳን ለሙታን መዠመርያ በወንዱሙ ቃየን ተገድሎ ደሙ በግፍ ለፈሰሰ ለጻቁ ለቅዱስ አቤል ለዕረፍት በዓል መታሰቢያና ለሕርቃስም ልጅ ሕልምን ለምትተረጒም ለነቢዪት ለቅድስት ሳቤላ ለዕረፍት በዓል መታሰቢያ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከከበረ አባት ከኤጲስቆጶስ ከአባ አላኒቆስ በሰማዕትነት ከዐረፈ፣ ከእስክድርያ ዐሥራ ስድስተኛ ሊቀ ጳጳስ ከከበረ አባት ከአባ ቴዎናስ ዕረፍት፣ በአባ ሲኖዳ ገዳም ውስጥ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያኗ ከከበረችበት፣ ከቅዱስ ፊላታዎስ ጋር ሰማዕትነት ከተቀበሩ ከዘጠኝ ሽህ ሰባት መቶ ሰዎች ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
❤ "ሰላም ለሳቤላ ዘአእመረት ፍካሬ፱ ፀሓይ ዘይከውን ሀሎ ፍካሬሁ ለኲሉ በበዘመኑ"። ትርጉም፦ በየዘመኑ ኸሉ ይከናወን ዘንድ ስላለው የዘጠኙ ፀሓይን ፍቺ ያወቀች ለኾነች ሳቤላ ሰላምታ ይገባል። አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ።
+ + +
❤ የሙታን በኵር ጻድቁ አቤል፦ ምክንያቱም አዳም የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ ተላልፎ እንዳይበላው የታዘዘውን ዕፅ በላ ያን ጊዜ በእርሱና በልጆቹ ላይ ሞት ሠለጠነ ለኃጢአትም ተገዥ ሆነ። ሰይጣንም ሰውን ለማሳት ሠለጠነ ከዚህም በኋላ አዳም ከገነት ወጥቶ ወደታችኛዋ ምድር ወረደ ስለ በደለና የፈጣሪውንም ትዕዛዝ በመተላለፉ ፈጽሞ እያዘነና እያለቀሰ መቶ ዓመት ኖረ።
❤ ከዚህም በኋላ አዳም ሔዋንን በግብር አወቃት ፀንሳ ቃየልንና እኅቱን ኤልዩድን ወደለች ሁለተኛም ዐወቃት አቤልንና እኅቱን አቅሌማን ወለደቻቸው አዳምም ሔዋንን "እነሆ ልጆችሽ አካለ መጠን አደረሱ ጐለመሱ ቃየል የአቤልን እኅት አቅሌማን ያግባት አቤልም የቃየልን እኅት ኤልዩድን ያግባት" አለ። ቃየልም እናቱን ሔዋንን እንዲህ አላት "ለእኔ ከእኔ ጋር የተወለደች እኅቴን ማግባት ይገባኛል አቤልም ከእርሱ ጋር የተወለደች እኅቱን ያግባ" ቃየል ከእርሱ ጋር የተወለደ ኤልዮድም እናቷ ሔዋንን የምትመስል እጅግ የምታምር መልከ መልካም ናትና።
❤ አዳምም ይህን ነገር በሰማ ጊዜ እጅግ ጭንቅ ሆነበት ቃየልንም "አብራህ የተወለደች እኅትህን ታገባት ዘንድ አይገባህም አለዚያም ለእግዚአብሔር መሥዋዕትን አቅርቡና መሥዋዕቱን ለተቀበለው ይሁን" አለው። መሥዋዕትንም በአቀረቡ ጊዜ የአቤልን መሥዋዕት እግዚአብሔር ተተቀበለ የቃየልን ግን አልተቀበለም ስለዚህም ቃየል ፈጽሞ አዘነ ሰይጣንም ተገናኘውና "ምን ያሳዝንሃል?" አለው ቃየልም "ለወንድሜ ለአቤል እኅቴን እተውለት ዘንድ አባቴ አዘዘኝ" አለው። ሰይጣንም "ምክርን ከኔ ስማ ወንድምህን ወደ ውኃ ምንጭ ይዘኸው ሒድ ውኃንም ሲጠጣ ራሱን በደንጊያ ምታው በሞተ ጊዜ ሁለቱንም ታገባቸዋለህ የሚከለክልህ ማነው" አለው ለቃየልም የሰይጣን ምክር ደስ አሰኘው ልቡም በዝሙት እሳትነት ነደደ ሰይጣን እንዳስተማረውም ወንድሙን አቤልን ገደለው ለሴት ስለ መቅናትም ጻድቁ አቤል በወንድሙ እጅ ሞተ እንዲህም ሞት ወደ ዓለም ገባ።
❤ እግዚአብሔርም ቃየልን "ወንድምህ አቤል ወዴት ነው" አለው። ቃየንም "አላውቅም በውኑ እኔ የአቤል ጠባቂው ነኝን" አለው። እግዚአብሔርም እንዲህ አለው "ቃየል ምን አድርገሃል የወንድምህ የአቤል ደም ጩኸት ከምድር ወደኔ ደርሷል። አሁንም በእጅህ የፈሰሰውን የወንድምህን ደም ትጠጣ ዘንድ አፍዋን የከፈተች ምድር የተረገመች ትሁን አንተ ታርሳታለህና በረከቷን ትሰጠሰህ ዘንድ አትጨምርም በምድር ላይ ፈሪ ተቅበዝባዥ ሁን"። ይህም መርገም ዘሩ በጥፋት ውኃ ከምድር ገጽ እስከ ሚደመሰስ በቃየል ላይ የበዛ ሆነ።
❤ የክብር ባለቤት ጌታችንም ጸሐፍት ፈርሳውያንን ሲዘልፋቸው እንዲህ አላቸው "ስለዚህ ነቢያትን፣ ሊቃውንትን፣ ጥበበኞችን ወደናንተ እልካለሁ ከነርሱ የምትገድሉት አለ የምትሰቅሉትም አለ በምኵራባችሁ የምትገርፋት አለ ካንድ አገር ወዳንድ አገር ታሳድዷቸዋላችሁ። ከጻድቁ ከአቤል ጀምሮ በቤተ መቅደስና በመሠዊያው መካከል እስከገደላችሁት እሰሰከ በራክዩ ልጅ እስከ ዘካርያስ ደም ድረስ በዓለም የፈሰሰው የጻድቃን ደም ሁሉ በእናንተ ላይ ይደርስ ዘንድ"።
❤ ቅዱስ ጳውሎስም አለ "ቃየን ካቀረበው መሥዋት ይልቅ አቤል በሃይማኖት ለእግዚአብሔር ያቀረበው መሥዋዕት ተሻለ" ስለ እርሱም ደግ እንደሆነ መሰከረለት መሥዋዕቱንም በመቀበሉ ምስክሩ እግዚአብሔር ነው ደግ እንደሆነም ከሞተ በኋላ ተናገረ።
❤ ከዚህም በኋላ አዳም ልጁን በአጣው ጊዜ "ወንድምህ አቤል ወዴት አለ" ብሎ ቃየልን ጠየቀው ቃየልም በቁጣ "አላውቅም" ብሎ መለሰ አዳምም ልጁን ይፈልግ ዘንድ ወደ ዱር ሮጠ በወንዝ ዳርም በድንኑን አገኘና አንገቱን አቅፎ "ማን ገደለህ?" አለው ከበድኑም "ወንድሜ ቃየን ገደለኝ" የሚል ቃል ወጣ። አዳምና ሔዋንም በልጃቸው በአቤል ሞት ሃያ ስምንት ዓመት ያህል ሲያለቅሱ ኖሩ።
❤ ከዚህም በኋላ መላእክት ወደ አዳም መጥተው "የዓለሙ ሁሉ አባቶች አባት አዳም የምሥራች እነሆ ልጅህ አቤል የገነትን ዛፎች ተሳለመ ነፍሱም እንደ ተወደደ መሥዋዕቶ ወደ እግዚአብሔር ዐረገች" አሉት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን የአባቶቻችንም በረከት ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ አባ ቴዎናስ፦ እርሱም ለእስክንድር ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ዐሥራ ስድስተኛ ነው። ይህም ቅዱስ አዋቂ ብልህ በቀናች ሃይማኖት የጸና በሥራው ሁሉ ያማረ ስለ ዕውቀቱም ሰዎች ሁሉ የሚወዱትና የሚሹት ነው። በዚያም ወራት ከሀድያንን በመፍራት በሥውር ከዋሻ ውስጥ በቀር በግልጥ ሊጸልዩና ሊቀድሱ ለክርስቲያኖች አልተቻላቸውም ነበር ይህም አባት አብያተ ክርስቲያናትን እስከሠሩ ድረስ አግባባቸው በእመቤታችንም በቅድስት ድንግል ማርያም ስም ያማረች ቤተ ክርስቲያን ሠሩ ከከሀድያንም ብዙዎችን መልሶ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው።
❤ በተሾመባት በመጀመሪያ ዓመት ተፍጻሜተ ሰማዕት የሆነ ሊቀ ጳጳሳት ጴጥሮስን ያጠመቀው እርሱ ነው። በተሾመ በአምስተኛ ዓመቱም አናጒንስጢስነት ሾመው በዐሥራ ሁለተኛም የሹመቱ ዓመት ቅስና ሾመው።
❤ በዚህም አባት ዘመን አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ ገጽ የሚል ከሀዲ ሰባልዮስ በእስክንድርያ አገር ተነሣ ይህም አባት አውግዞ ለየው የከፋች ሃይማኖትንም አጠፋት። ዳግመኛም በዘመኑ ቆዝሞስና ድምያኖስ ወንድሞቻቸው እናታቸው ቴዎዳዳም በሰማዕትነት ሞቱ ይህም አባት ያመረ ጒዞውን በመጓዝ እግዚአብሔርን አገልግሎ በዚች ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ቴዎናስ ጸሎት ይማረን በረከቱ ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
1 161
ገባ። እርሷም "አምላካቸው ጽኑዕና ኃያል ነውና ክርስቲያኖች አትጣላቸው አላልኩህምን" አለችው። ይህንንም ከእርስዋ ሰምቶ በእርሷ ላይ እጅ ተቆጣ ወደ ክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስ እምነት ቅዱስ ጊዮርጊስ እንደአስገባት አወቀ። ከዚህም በኋላ ከከተማ ውጭ እንዲጐትቷትና በመጋዝም እንዲሰነጥቋት አዘዘ የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለች።
❤ በዚያም ጊዜ ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሥራ ነገሥታቱ ሁሉም ደነገጡ ኀፍረት ደግሞ እንዳይጨምርባቸው ከእርሱም እንዲአርፍ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ እንዲጽፍ ንጉሥ ዱድያኖስን መከሩት። ያን ጊዜም የክብር ቅዱስ ጊዮርጊስን ራስ በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ድል አድራጊ ቅዱስ ጊዮርጊስም እጅግ ደስ አለው እሳት ከሰማይ አውርዶ ሰባውን ነገሥታትን ያቃጥላቸው ዘንድ መከራውም ከክርስቲያን ወገን ጸጥ ይል ዘንድ ጌታችንን ለመነው። ወዲያው እሳት ወርዶ ከሠራዊታቸው ጋራ ሰባውን ነገሥታት አቃጠላቸው።
❤ ከዚህም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተገልጾ ብዙ ቃል ኪዳን ሰጠው። በምድር መታሰቢያህን ለሚያደርግ ሁሉ እኔ ኃጢአቱን ሁሉ እደመስሳለሁ በመከራም ውስጥ ሁኖ በባሕርም ሆነ፣ በየብስ ወይም በደዌ በስምህ የሚለምነኝን እኔ ፈጥኜ ከመከራው አድነዋለሁ ይህንንም ጌታችን ተናግሮ በክብር ወደ ሰማይ ወጣ።
❤ ከዚህም በኋላ ወታደሮቹ የቅዱሳን የከበረች ራሱን ቈረጡት ደም፣ ውኃና ወተት ፈሰሰው፤ ጌታም ቅዱስ ሚካኤልን በብርሃን ልብስ ደሙን እንዲቀበለው አዘዘ። ጌታችንም የኃያሉ የቅዱስ ጊዮርጊስን ነፍስ በእጁ ተቀብሎ ሳማት፤ በሰማያዊ ልብስም አጐናጥፎ ከእርሱ ጋራ ወደ ሰማይ አሳረጋት። አየር በሙሉ ቅዱሳን መላእክትን ተሞላ። ለቸር አባቱና ለመንፈስ ቅዱስ ቊርባን አድርጎ እስኪያቀርበው ድረስ ቅዱሳን ሁሉ በየወገናቸው ያመሰግኑ ነበር። የብርሃን ልብስ አለበሰው። በዕንቈ ባሕርይ ያጌጠ ከጽሩ ወርቅ የተሠሩ መከራ በተቀበለባቸው ሰባት ዓመታት ልክ ከዕፀ ሕይወት አበቦች የተሠሩ አክሊሎች ያሉበትን ዘውድ አቀዳጀው ለዘላለም ከማኅበረ በኵር ጋራ ስሙን ጻፈው። ሰማያውያን መላእክትና ቅዱሳንንም ሁሉ በየወገናቸው በመንበሩ ላይ እንዲአስቀምጡት፤ በኢየሩሳሌም ሰማያዊት በዓል እንዲ ያደርጉለት አዘዛቸው።
❤ ከዚህም በኋላ ከመብረቁ፣ ከነጐድጓድ፣ ከንውጽውጽታው ጽናት፣ ከዝናሙ ብዛት የተነሳ በምድር ላይ ትልቅ ድንጋፄ ሆነ። ምድርም ሦስት ጊዜ ተናወጸች ከዚያ ቆመው የነበሩ ሰዎች ሁሉ ሸሹ ወደ ከተማም ሔዱ ጭፍሮችም ይህንን በአዩ ጊዜ በቅዱስ ጊዮርጊስ አምላክ አመኑ። ነፍሱም ወደ ሰማይ በዐረገች ጊዜ በእግዚአብሔር ፊት ሰገደች። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የምታምን ነፍስ ከሥጋዋ በተለየች ጊዜ አስቀድሞ ለሥሉስ ቅዱስ ትስገድ ከዚህ በኋላ ወደ ወዳጄ ወደ ጊዮርጊስ ይወሰዷት እና ለርሱ እጅ ትንሣ ብሎ አዘዘ፤ በዚህ ሁኔታ የቅዱስ ጊዮርጊስ ምስክርነቱ ሚያዝያ በባተ በሃያ ሦስት ቀን በዕተ ዓርብ ዘጠኝ ሰዓት ተፈጸመ። አገልጋዮቹም ሥጋውን ወስደው በልብስ ጠቀለሉት ወደ ሀገሩ ልዳም ወስደው ቤተክርስቲያን ሰርተው በውስጡ አኖሩት፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን የቅዱስ ጊዮርጊስም በረከትቱ ረድኤቱ ሁላችን የክርስቲያን ወገኖችን ከሥጋና ከነፍስ መከራ ይጠብቀን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ ገድለ ጊዮርጊስ እና የሚያዚያ23 ስንክሳር።
+ + +
❤ አቡነ ገብረ ክርስቶስ ዘዳግና፦ የጻድቁ ንጉሥ የዐፄ ይኩኖ አምላክና የልዕልተ ወይን ልጅ ሲሆኑ ንግሥናን ትተው በመልአክ መሪነት አክሱም ሄደው ነው የመነኑት፡፡ በዚያም አስደናቂውን ባለ12 ቤተመቅደስ ገዳም ገድመዋል፡፡ ቀደምት የተባሉትን ብዙ መነኰሳትንም አመንኩሰዋል፡፡ አቡነ ገብረ ክርስቶስ ጻድቁ በአንድ ወቅት ርሃብ ሆኖ ከብቶች አልቀው የሚታረስ ቢጠፋ እጃቸውን አጨብጭበው አንበሳና አጋዘንን ጠርተው በአንድ አድርገው ጠምደዋቸው አርሰውና ዘርተው ዕለቱን አድርሰው ሕዝቡን የመገቡ የበረከት አባት ናቸው፡፡
❤ ጻድቁ በተከዜ ወንዝ ላይ ሕዝቡን በተአምራት በገመድ ያሻገሩ አባት ናቸው፡፡ እንግዶች መነኰሳት ሊጠይቋቸው ሲመጡ ለእንግዶቹ ብለው ቆቅ ይዘው አርደው በድስት አድርገው ሰርተው አቀረቡላቸው፡፡ እንግዶቹ ግን"እኛ መነኵሴዎች ነን እንዴት ሥጋ ያበላናል?" እያሉ ሲያሙ ጻድቁ የውስጣቸውን ዐውቀውባቸው ታርደው ወጥ የተሠሩትን ቆቆቹ እፍ ቢሉባቸው ቆቆቹ ነፍስ ዘርተው ከድስቱ ላይ በረው ሄደዋል፡፡ ይህን ተአምር ያዩ እንግዶቹም እጅግ ደንግጠው ይቅር በሉን ብለው ንስሓ ገብተዋል፡፡ ጻድቁ ከጌታችን ታላቅ ብዙ ቃል ኪዳን ከተቀበሉ በኋላ በዚች ቀን በሰላም ዐርፈዋል፡፡ ምንጭ መዝገበ ቅዱሳንና ቅዱሳን በዓላት።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ጥር ፪ (2) ቀን።
❤ እንኳን ለኢትዮጽያዊ ጻድቅ በዓለም ላይ በንግሥና መኖርን ንቀው ለመነኑትና ብዙ ተአምራትን በማድረግ ለሚታወቁት ለንጉሥ ዐፄ ይኩኖ አምላክ ልጅ ለሆኑት ለአቡነ ገብረ ክርስቶስ ዘዳግና ለዕረፍታቸው በዓል፣ ለሊቀ ሰማዕታት ለቅዱስ ጊዮርጊስ ለልደት በዓል በሰላም አደረሰን።
+ + +
❤ "ሰላም ለጊዮርጊስ ሰማዕት ዘፀሓየ ጽድቅ ዘተአምሪሁ ከመ ኆጻ ባሕር ዘኢይትኀኌለቊ ኮከበ ክብር ዘማእከለ ምድር ዘአርአየ ኀይለ በዲበ ሰሌዳ መንበር ብእሲ አዛል ወመስተጋድል ኀያል ዝሕዙሐ ገድል"። ትርጉም፦ ገድሉ የበዛ የተትረፈረፈ ኃያል፤ ተጋዳይ ጎልማሳ (ብርቱ) ሰው፤ በተዘረጋ ዙፍን ላይ ኃይልን ያሳየ በሰማይና በምድር መኻከል ያለ የማይቆጠር የክብር ኮከብ፤ ተአምሩ እንደ ባሕር አሸዋ የበዛ የኾነ፤ የፀሓየ ጽድቅ የኢየሱስ ክርስቶስ ሰማዕት ለኾነ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ።
+ + +
❤ ፀሐይና የአጥቢያ ኮከብ የተባለ ታላቁና ክቡር የሆነ ሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ፦ የዚህም ቅዱስ አባቱ መስፍን ነው ስሙም አንስጣስዮስ ይባላል ከቀጰዶቅያ አገር ነው የእናቱም ስም ቴዎብስታ ይባላል ከፍስጥዓዔም አገር ናት ታናሽ ሆኖ ሳለ አባቱ ዐረፈ። ሃያ ዓመትም በሆነው ጊዜ የአባቱን ሹመት ሊቀበል ወደ ንጉሥ ዱድያኖስ ዘንድ ሔደ። ንጉሡም ጣዖት አቁሞ ጣዖትን እንዲአመልኩ ሰዎችን ሁሉ ሲያስገድዳቸው አገኘው። ይህንንም አይቶ ቅዱስ ጊዮርጊስ እጅግ አዘነ በእርሱ ዘንድ ያለውን ገንዘቡን ሁሉ ለድኆች ለምስኪኖች ሰጠ ባሮቹንም ነፃ አወጣቸው።
❤ ከዚህ በኋላ በንጉሥ ፊት ቁሞ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ። ንጉሡም አባበለው ብዙ ቃል ኪዳንም ገባለት እርሱ ግን አልተቀበለውም። ለመስማት እንኳ የሚያስጨንቅ ሥቃይን አሠቃየው ጌታችን ግን ያጸናዋል ቊስሉንም ያድነዋል ሦስት ጊዜም እንደ ሚሞት እርሱም እንደሚአስነሣው በአራተኛውም የምስክርነት አክሊል እንደሚቀበል ነገረው። ቃል ኪዳንም ሰጠው ስሙ በዓለሙ ሁሉ የተገለጠ ይሆን ዘንድ በተጋድሎና መከራ በመቀበልም ጽኑዕ በሆነ ሥቃይም ሰባት ዓመት እንደሚኖር መላእክትም እንደሚአገለግሉት ነገረው።
❤ ንጉሡም ቅዱስ ጊዮርጊስ ባለመታዘዙና ባለመመለሱ እጅግ አዘነ ስለዚህም አትናስዮስ የሚባል ታላቅ ሥራየኛ አመጣ እርሱም መርዝን ቀምሞ በጽዋ መልቶ አስማት ደግሞ እንዲጠጣ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሰጠው። ወዲያውኑ የሚሞት መስሎት ነበር። ቅዱሱም ያንን ጽዋ በመስቀል መልክት አማትቦ ጠጣው ምንም ጉዳት አልደረሰበትም። ያ መሠርይም በክብር ባለቤት በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ በሰማዕትነት ሞተ። ከእርሱ ጋራ ሌሎች ብዙዎች ሰዎች በሰማዕትነት ሙተው የሕይወት አክሊል ተቀበሉ ቊጥራቸውም ሠላሳ ሺህ ሰባት መቶ ነፍስ ነው።
❤ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዱድያኖስና በሰባ ነገሥታት ፊት በቆመ ጊዜ በዚያም የተቀመጡባቸው የዕንጨት ወንበሮች ነበሩ። ቅዱሱንም "እሊህን የተቀመጥንባቸውን ወንበሮች እንዲበቅሉ እንዲአብቡና እንዲአፈሩ ታደርጋቸው ዘንድ ከአንተ እንሻለን" አሉት። በዚያን ጊዜ ጸለየ እንዳሉትም አደረጋቸው ይህንንም ድንቅ ሥራ አይተው ቊጥር የሌላቸው ብዙ አሕዛብ በጌታችን አመኑ።
❤ ከዚህም በኋላ ቅዱሱን ወስደው በጐድጓዳ ብረት ምጣድ ውስጥ አበሰሉት። አቃጥለው አሳርረው ሥጋውንና ዐጥንቱን ፈጭተው አመድ አድርገው ከረጅም ይድራስ ከተባለ ተራራላይ በተኑት። ጌታችንም ነፍሱን ወደ ሥጋው መልሷት ደግሞ አስነሣው። ወደ ነገሥታቱም ተመልሶ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ስም ሰበከ። ቊጥር የሌላቸው አሕዛብ አይተው አደነቁ በጌታችንም አምነው በሰማዕትነት ሞቱ።
❤ ነገሥታቱም ደግመው ሙታኖችን ብታስነሳ አምላክህ ዕውነተኛ አምላክ እንደሆነ እናውቃለን በእርሱም እናምናለን" አሉት። ቅዱሱም ጸለየ ከመቃብር ጒድጓድም ውስጥ ወንዶችና ሴቶችን ጐልማሶችንም አስነሣላቸው እነዚያም በክብር ባለቤት በጌታችን ስም አስተማሩ የገሀነምንም ወሬ ተናገሩ ጥምቀትንም ተቀብለው ተመልሰው ዐረፉ። ከሀድያን ነገሥታት ግን ሙታንን ያስነሣህ አይደለም የረቀቁ ሰይጣናትን አሳየህ እንጂ ብለው ተከራከሩ።
❤ ከዚያም ከጭንቀታቸው ብዛት የተነሣ ከአንዲት ድኃ ሴት ዘንድ አስጠበቁት እርሷም እንጀራ ልትለምንለት ወጣች የእግዚአብሔርም መልአክ በላዩ ከበጎ ነገር ሁሉ የተመላ ማዕድን አቀረበለት። የዚያች መበለትም ቤቷ ምሰሶ ቅርጫፍን አበቀለ ታላቅ ዛፍም ሆነ። ያቺም መበለት በተመሰለች ጊዜ የቤቷ ምሰሶ ቅርንጫፍ አብቅሎ ታላቅ ዛፍ እንደሆነ ስለ ማዕዱም ይህን ታላቅ ምልክት አይታ "የክርስቲያኖች አምላክ ሰው ተመስሎ ወደእኔ መጣ" አለች። ቅዱሱም "እኔ አምላክ አይደለሁም የአምላክ ባሪያ ነኝ እንጂ" አላት። እርሷም እንዲህ ብላ ለመነችው "የአምላክ አገልጋይ ከሆንክ ቸርነትህ እንድትደርሰኝ እለምንሃለሁ። ዕውር፣ ደንቆሮ፣ ዲዳ፣ ጐባጣ የሆነ ልጅ አለኝና ታድንልኝ ዘንድ እለምህሃለሁ"። ስለ ጌታችን እምነትም አስተማራትና በመስቀል ምልክት አማተበው ያንጊዜም አየ። ቅዱስም "በሌላ ጊዜ እንዲሰማ እንዲናገርና እንዲሔድ እንዲአገለግለኝም እኔ እሻለሁ" አላት። በዚያን ጊዜ ንጉሡ በአገሩ ሜዳ ውስጥ ሲዘዋወር ያቺን ዛፍ አይቶ አደነቀ ስለ እርሷም ጠየቀ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከእርሷ ዘንድ የተቀመጠባት የዚያች መበለት የቤቷ ምሰሶ እንደሆነ ነገሩት። ንጉሡም ተቆጣ ቅዱሱንም ከዚያ ወስዶ አስገረፈው በመንኰራኵር አበራዩት ሙቶም በከተማ ውጭ ጣሉት ጌታም ከሞት አስነሣው ወደ ነገሥታቱም ተመለሰ ንጉሡም አይቶ ደነገጠ ስለ ሕይወቱም አደነቀ።
❤ ከዚህም በኋላ ይሸነግለው ዘንድ ጀመረ በመንግሥቱ ላይም ሁለተኛ ያደርገው ዘንድ ቃል ገባለት ቅዱስ ጊዮርጊስም እየዘበተበት "ነገ በጥዋት ለአማልክቶችህ መሥዋዕትን አቀርባለሁ አንተም ሕዝቡ እንዲሰበሰቡ እዘዝ እኔ ስሠዋ እንዲአዩ" አለው። ንጉሡም ዕውነት የሚሠዋ መስሎት ደስ አለው ወደ ቤተ መንግሥቱም እልፍኝ አስገብቶ አሳደረው። ለጸሎትም ተነሣ የዳዊትንም መዝሙር አነበበ የዱድያኖስ ሚስቱ እለእስክንድርያ ንግሥት ሰምታ ቃሉ ደስ አሰኛት የሚያነበውንም ይተረጒምላት ዘንድ ለመነችው እርሱም እግዚአብሔር ዓለምን ከፈጠረበት ሰው እንደሆነበት ጊዜ የሆነውን ሁሉ ሊያስረዳትና ሊያስገነዝባት ጀምረ ትምህርቱም በልቡዋ ተቀርጾ በክብር ባለቤት በጌታችን አመነች።
❤ በማግሥቱም ቅዱስ ጊዮርጊስ ለአማልክት ሲሠዋ ለማየት ሰው ሁሉ እንዲሰበሰብ ዐዋጅ ነጋሪ ዞረ የቤቷን ምሰሶ ያበቀለላት ያቺ መበለት ሰምታ ዕውነት መስሏት እጅግ እያዘነች ልጅዋን ተሸክማ እያለቀሰችም ወጣች። ቅዱስ ጊዮርጊስ በአያት ጊዜ ፈገግ አለ "ልጅሽን በምድር ላይ አኑሪው" አላት ከዚያም ልጅዋን ጠርቶ "ወደ አጵሎን ሒድ ወደእኔም ይመጣ ዘንድ በክብር ባለቤት በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም እዘዘው" አለው። ያን ጊዜ ያ ልጅ ድኖ ቅዱስ ጊዮርጊስ እንዳዘዘው ወደ ጣዖቱ ቦታ ሒዶ አዘዘው። በጣዖቱ ያደረ ያ ርኵስ መንፈስም ከማደሪያው ወጥቶ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ አለበት መጥቶ "እኔ ሰውን ሁሉ የማስት እንጂ አምላክ አይደለሁም" ብሎ በሕዝቡ ሁሉ ፊት አመነ። ቅዱሱም ትውጠው ዘንድ ምድርን አዘዛትና ወዲያውኑ ዋጠችው ጣዖታቱም ከአገልጋዮቻቸው ጋራ አጠፋቸው ከወገኖቹ ጋራ ዐፈረ። ብስጭትና ቁጣንም እንደተመላ ወደ ንግሥት ሚስቱ ዘንድ
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
+ + +
❤ "ሰላም ለጸአተ ነፍስከ ሠርቀ ወርኀ ጥር ወርኀ ሱላሜ። እንተ ይእቲ ትትበሀል ዐውደ ዓመቶሙ ለሰብአ ሮሜ። ሶበ ጸለይከ እስጢፋኖስ? ለስምዐ ነድልከ ጊዜ ፍጻሜ። ከመ ተመጠወ መድኃኒነ ነፍስ ዚአከ አበሜ። ተመጠው ነፍስየ ዘአልቦ ቅያሜ"። ትርጉም፦ ቅዱስ እስጢፋኖስ ሆይ የሮሜ ሰዎች የዓመት መጀመርያቸው የምትባል የሰላም ወር በሆነች በጥር ወር መባቻ ላረፈች ነፍስህ ሰላምታ ይገባል። በገድልህ ሰማዕትነት በመጨረሻ ሰዓት በጸለይኽ ጊዜም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሽቱ መዓዛ የአንተን ነፍስ እነደተቀበለ አንተም ቂም በሌለበት ልቡና ነፍሴን ተቀበል። መልከአ እስጢፋኖስ።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
+ + +
❤ "ሰላም ለእስጢፋኖስ በኵረ ሰማዕታት ሊቀ ዲያቆናት ዐምደ ሃይማኖት ቅድስተ ሥላሴ ዘርእየ በዐይኑ ወልዱ ለአብ እንዘ ይነብር በየማኑ ተቃውሞቶ መዋግድ ዘስእኑ ነባቤ ጥበብ በልሳኑ ጽጉያተ ወጽዱላተ አቅማኀ ቃሉ ማዕከለ አይሁድ በውስተ ዐውድ ዘኮነ ሰማዕተ ወልድ"። ትርጉም፦ የሰማዕታት መዠመሪያ የዲያቆናት አለቃ፣ የሃይማኖት ምሰሶ፤ የተለየች ሦስትነትን በዐይኑ ያየ፤ የአብ የባሕርይ ልጁ በቀኙ ተቀምጦ ያየ፤ መከራከሩን ጨፋጮች አይሁድ ያልቻሉ በአንደበቱ ጥበብን የሚናገር የቃሉ ፍሬዎችም ብርሃናውያትና ያበቡለት፤ በአይሁድ መኻከል በዐደባባይ ውስጥ የወልድ ምስክርን ኾኖ ለተገኘ ለእስጢፋኖስ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ።
https://t.me/Eotcw
1 161
+ + +
❤ የከበሩ የአክሚም ሰማዕታት ቅዱሳን ዲዮስቆሮስና ሰከላብዮስ፦ እክሚም በሚባል አገር ሹም የሆነ አንድ ሰው ነበር በወርቅ በብር ባለጸጋ ነው ስሙም አልሰመማልዮስ ይባላል ስማቸው ዲዮስቆሮስና ሰከላብዮስ የሚባል ሁለት ልጆቹን ወለደ እነርሱም ከመጾምና ከመጸለይ ጋር እግዚአብሔርን በመፈራት አደጉ። አባታቸው በሞተ ጊዜ ምንኵስናን ተመኙ የእግዚአብሔርም መልአክ ተገልጦላቸው ወደ ገዳማዊ አባ ሙሴ ገዳም እንደመሔዱ አዘዛቸው ሒደውም በዚያ መነኰሱ ድንቆች ተአምራቶችንም እያደረጉ በብዙ ተጋድሎ ኖሩ። ከጥቂት ወራትም በኋላም ዲዮስቆሮስ ቅስና ሰከላብዮስም ዲቁና ተሾሙ። ዲዮቅልጥያኖስም የክብር ባለቤት ክርስቶስን በካደው ጊዜ ለጣዖታት የማይሰግዱ ክርስቲያኖችን ሁሉ ይገድል ዘንድ የእንዴናው ገዥ አርያኖስን አዘዘው።
❤ አርያኖስም አክሚም ከተማ በደረሰ ጊዜ ኤጲስቆጶስን አባ ብኑድያኖስን ያዘውና አሥሮ ወደ አገር ውስጥ ገባ። የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤልም ለዲዮሰሰቆሮስና ለሰከላብዮስ ተገለጸላቸው ወደ መኰንኑም ሒደው የምስክርነት አክሊልን እንዲቀበሉ ነገራቸው እነርሱም ታኅሣሥ ሃያ ስምንት ቀን ሃያ አራት መነኰሳት ሁነው ሔዱ። ወደ አክሚም ከተማም ሲደርሱ በመድኃኒታችን ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የከበረ የልደትን በዓል ለማክበርና ስለ ከበረ ስሙም ይሞቱ ዘንድ የክርስቲያን ወገኖችን ከሴቶቻቸውና ከልጆቻቸው ጋር ተሰብስበው አገኙአቸው ኤጲስቆጶሱ አባ ብኑድያኖስም ከእርሳቸው ጋር ገባ። በማግሥቱም አባ ብኑድያኖስ ቀደሰ አግዮስ ወደሚባለው በደረሰ ጊዜ መላእክት እንዲህ ብለው በታላቅ ድምጽ አመሰገኑ "ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር አሸናፊ ፍጹም የጌትነትህ ምስጋና በሰማይና በምድር የመላ ነው"። ያን ጊዜ መድኃኒታችንን በመሠዊያው ታቦት ላይ ተቀምጦ መላእክትም በዙሪያው ቁመው ቊርባኑን እያነሣ በካህኑ እጅ ላይ በማድረግ የተሰበሰቡትን ሲያቆርባቸው ቅዱሳኑ አዩት።
❤ በዚያንም ጊዜ መኰንኑ አርያኖስ ደረሰ ተቆጥቶም ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ስማቸው ብሕዋፋና ውኒን የሚባሉ ሁለት የአገር አለቆችን ይዞ ራሳቸውን በሰይፍ ቆረጠ ከእነርሱም በኋላ ዲያቆናትን ንፍቀ ዲያቆናትን መዘምራንን የቤተ ክርስቲያን ሹሞች ደማቸው ከቤተ ክርስቲያን ደጃፍ ወጥቶ ሃያ ክንድ ያህል እስቲጎርፍ ሴቶችና ልጆችንም ሳያስቀር አረዳቸው።
❤ ከዚህም በኋላ ኤጲስቆጶሱን አባ ብኑድያስን ዲዮስቆሮስን ሰከላብዮስን ከእርሳቸውም ጋር ያሉ መነኰሳትን ከእርሱ ጋር ወሰዳቸው ለጣዖትም ይሰግዱ ዘንድ ሸነገላቸው እምቢ በአሉትም ጊዜ ዐጥንቶቻቸው እስከሚለያዩ ድረስ ይደበድቧቸው ዘንድ አዘዘ የእግዚአብሔርም መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ተገልጾላቸው አዳናቸው የአርያኖስም የጭፍሮቹ ታላላቆች ኮርዮንና ፊልሞና ከጭፍሮችም አርባ ሰዎች ይህን ድንቅ ተአምር አይተው በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ወደ እሳት ማንደጃም እንዲጥሏቸው አዘዘ። ተጋድሏቸውንም ታኅሣሥ ሠላሳ ቀን ፈጸሙ ከተሰበሰቡትም ውስጥ ብዙዎች የሚያስገድዳቸው ሳይኖር በእውነተኛ አምላክ በክርስቶስ እናምናለን እያሉ ወደ እሳቱ ማንደጃ ራሳቸውን ወረወሩ ምስክርነታቸውንም እንደዚህ ፈጸሙ።
❤ ከዚህም በኋላ ጥር አንድ ቀን ቅዱሳን ዲዮስቆሮስና ሰከላብዮስ ታሥረው ሳሉ የመላእክት አለቃ ቅዱሰሰ ሚካኤል ተገለጠላቸውና ምስክርነታቸውን እንደመፈጽሙ አበረታቸው በነጋም ጊዜ ለአማልክት ስለ መስገድ አርያኖስ ተናገራቸው አይሆንም በአሉትም ጊዜ የዲዮስቆሮስን ዐይኖቹን ያወልቁ ዘንድ አዘዘ ቅዱሱም የወለቁ ዐይኖቹን አንሥቶ ወደ ቦታቸው መለሳቸው መኰንኑ ሉክዮስ አይቶ ከሠራዊቱ ጋር በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ ወደ እሳትም ወርውረዋቸው ምስክርነታቸውንም ፈጸሙ።
❤ ከዚህም በኋላ የከበሩ ሰማዕታትን ይገደሏቸው ዘንድ አርያኖስ አዘዘ ሲጸልዩም የክብር ባሌበት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጠላቸው ስማቸውን ለሚጠረሠ መታሰቢያቸውንም ለሚያደርግ ገድላቸውንም ለሚጽፍ ከቅዱሳን አንድነት ይቈጥረው ዘንድ ቃል ኪዳን ሰጣቸው። ከዚህም በኋላ ወታደሩ ቀርቦ የቅዱስ ዲዮስቆሮስን ራሱ ቆረጠ ሰከላብዮስንም ከወገቡ ላይ ቆረጡት ሃያ አራቱን መንኰሳትም ከቁመታቸው ሠነጠቋቸው በዚች በጥር አንድ ቀን ተቆረጡ ከዘመዶቻቸው የሆነ ሳሙኤልም በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም በከበረች ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቀበራቸው በአገረ አክሚም የተገደሉ ሰማዕታትም ቊጥራቸው ስምንት ሺህ አንድ መቶ አርባ ሆነ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሁሉ ቅዱሳን ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር1 ስንክሳር።
+ + +
❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "ወይርአዩ አሕዛብ በቅድመ አዕይንቲነ። በቀለ ደሞሙ ለአግብርቲከ ዘተክዕወ። ይባዕ ቅድሜከ ገዐሮሙ ለሙቁሓን"። መዝ78፥10-11። የሚነበበው ወንጌል ማር13፥9-23።
+ + +
❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "እስመ በጻሕኮ በበረከት ሠናይ። ወአንበረከ አክሊለ ዲበ ርእሱ ዘእምዕንቊ ክቡር። ሐይወ ሰአለከ ወወሀብኮ"። መዝ 20፥3-4። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 11፥32-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 4፥12-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 7፥51-58። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 21፥33-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ቅዳሴ ነው። መልካም የብርሃነ ልደቱ ሰሞን፣ የቅዱስ እስጢፋኖስ የልደትና የዕረፍት በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ የተባረከ የጥር ወር የመዓልቱ ሰዓት ዐሥር ነው ከእንግዲህ ይጨመርለታል።
❤ ጥር ፩ (1) ቀን።
❤ እንኳን ለሊቀ ዲያቆናት ለቀዳሜ ሰማዕት ለቅዱስ እስጢፋኖስ ለልደቱና ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና ከሶርያ አገር ለሆነ በከሀዲው መክስምኖስ ዘመነ መንግስት ሰማዕትነት ለተበቀበለ ለቅዱስ ለውንድዮስ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከእስክድርያ ስልሳ ዘጠነኛ ሊቀ ጳጳስ ከአባ መቃርስ ዕረፍት፣ ከከበሩ ከአክሚም ሰማዕታት የምስክርነታቸውን ተጋድሎ ከፈጸሙ ስማቸው ዲዮስቆሮስና ሰከላብዮስ ዕረፍት፣ በዲዮቅልጥያኖስ እጅ ሰማዕትነት ከተቀበሉ ቊጥራቸው ከካህናት ስምትት መቶ፣ ከዲያቆናት መቶ ሠላሳ፣ ከመምህራን ኃምሳ፣ ከሦስት ከቤተ ክርስቲያን ሹማምንት ከሰማንያ መሳፍንት፣ ከሠላሳ ሁለት ንፍቅ ዲያቆናትና ከመቶ፥ ኃምሳ ሕዝባውያን ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
❤ የዕለቱ አንገርጋሪ ግእዝ ዜማ፦ ሃሌ ሉያ "እንዘ ይነብር ለአብ በየማኑ ወይረፍቅ ውስተ ሕፅኑ ርእየ ወልደ እስጢፋኖስ በዓይኑ ኲሉ ትውልድ ያስተበጽዕዎ በበዘመኑ አማን ምዑዝ ጽጌ ልሳኑ"። ትርጉም፦ በአብ ቀኝ በዕቅፋም ሲቀመጥ ወልድን ቅዱስ እስጢፋኖስ በዓይኑ አየው ትውልድ ሁሉ በየዘመኑ ያመሰግኑታል በእውነት አንደበቱ ጣፋጭ (ያማረ) አበባ ነው።
+ + +
❤ የዕለቱ እግ.ነግ ዓራራይ ዜሜ፦ "ዘበመትልወ በዓለ እግዚእከ ኮነ በዓልከ ብፁዕ እስጢፋኖስ እስመ ለኲሉ ነባሪ ወቀናዪ ዕረፍተ ኮነ በዓልከ"። ትርጉም፦ የጌታ በዓል በመከተልህ ንዑድ ክቡር እስጢፋኖስ ለሁሉ ኗሪና ቀጥተኛ በዓልህ ዕረፍት ሆነ። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ።
+ + +
❤ ቀዳሜ ሰማዕታት ቅዱስ እስጢፋኖስ፦ ለዚህም ለከበረ እስጢፋኖስ እግዚአብሔር ኃይልን ጸጋ የተመላ ሰው እንደነበረና በሕዝቡም መካከል ታላላቅ ተአምራትንና ድንቅ ሥራን ይሠራ እንደነበረ የሐዋርያት ሥራ የተባለ መጽሐፍ ስለርሱ ምስክር ሆነ። ከዚህም በኋላ አይሁድ ቀኑበት የሐሰት ምስክሮች የሚሆኑ ሰዎችንም አስነሡበት "ይህን ሰው በሙሴና በእግዚአብሔር ላይ የስድብ ቃልን ሲናገር ሰምተነዋል እንዲሉ ሐሰትን አስተማሩአቸው። ሕዝቡንና ሽማግሌዎችን ጸሐፊዎችንም አነሣሡአቸው አዳርሱን ብለው ከበው እየጐተቱ ወደ ሸንጎ ወሰዱት።
❤ የሐሰት ምስክሮችንም አቆሙበት እነርሱ ይህ ሰው በቤተ መቅደስ ላይ በኦሪትም ላይ ስድብን ሲናገር ተው ብንለው እምቢ አለ። "የናዝሬቱ ኢየሱስ ቤተ መቅደሳችሁን ያፈርሰዋል ሙሴ የሰጣችሁን ኦሪታችሁንም ይሽራል" ሲል ሰምተነዋል አሉ። በአደባባይ ተቀምጠው የነበሩት ሁሉ ተመለከቱት ፊቱም የእግዚአብሔርን መልአክ ፊት ሁኖ አዩት። ሊቀ ካህናቱም "እውነት ነውና እንዲህ አልክ" አለው። እርሱም እንዲህ አለ "ወንድሞቻችንና አባቶቻችን ስሙ ወደ ካራን ከመምጣቱ አስቀድሞ በሶርያ ወንዞች መካከል ሳለ ለአባታችን ለአብርሃም የክብር ባለቤት እግዚአብሔር ተገለጠለት። ካአገርህ ውጣ ከዘመዶችህም ተለይ እኔ ወደማሳይህ አገርም ና" አለው።
❤ "ከዚህም በኋላ ከከላውዴዎን ወጥቶ በካራን ተቀመጠ አባቱም ከሞተ በኋላ ዛሬ እናንተ ወደ አላችሁባት ወደዚች አገር አመጣው። ከዚህም በኋላ የግዝረትን ሥርዓት ሰጠው ይስሐቅም በወለደው ጊዜ በስምንተኛው ቀን ገዘረው እንዲሁ ይስሐቅም ያዕቆብን ገዘረው ያዕቆብም ዐሥራ ሁለቱን ነገድ አባቶች ገዘረ። የቀድሙ አባቶቻችንም በዮሴፍ ላይ ቀንተው ወደ ግብጽ አገር ሸጡት እግዚአብሔር ግን አክብሮት ነበር። ከመከራው ሁሉ አዳነው በግብጽ ንጉሥ በፈርዖን ፊትም ዕውቀትን መወደድን ሰጠው በግብጽ አገር ሁሉና በቤቱ ሁሉ ላይ ሾመው"። ነገርም በማስረዘም በሰሎሞን እጅ እስከተሠራችው ቤተ መቅደስ ያለውን ተረከላቸው።
❤ ከዚህም በኋላ ድምፁን ከፍ ከፍ አድርጎ "እናንተም እንደአባቶቻችሁ ዘወትር መንፈስ ቅዱስን የምታሳዝኑት ዐይነ ልቡናችሁ የታወረ ዕዝነ ልቡናችሁ የደነቈረ አንገተ ደንዳኖች" አላቸው። "አባቶቻችሁ ከነቢያት ያላሳደዱት ያልገደሉት ማን አለ እናንተ ክዳችሁ የገደላችሁትን ገደላችኋቸው። በመላእክት ሥርዓት ኦሪት ተቀብላችሁ አልጠበቃችሁም"።
❤ ይህንንም ሰምተው ተበሳጩ ልባቸውም ተናደደ ተነሠሣ ጥርሳቸውንም አፋጩበት። በቅዱስ እስጢፋኖስም መንፈስ ቅዱስ አደረበት ሰማይም ተከፍቶ ኢየሱስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ የእግዚአብሔርን ክብር አየ። "እነሆ ሰማይ ተከፍቶ የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ አያለሁ" አለ።
❤ ዶሮአቸውን ይዘው በታላቅ ድምፅ ጮኹ በአንድነትም ከበው ጐተቱት። እየጐተቱም ከከተማ ወደ ውጭ አውጥተው በደንጊያ ወግረው ገደሉት የገድሉትም ሰዎች ልብሳቸውን ሳውል ለሚባል ጐልማሳ ልጅ ያስጠብቁ ነበር። "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ነፍሴን ተቀበል" እያለ ሲጸልይ እስጢፋኖስን በደንጊያ ወገሩት።
❤ ዘለፍለፍ ባለ ጊዜም ድምፁን ከፍ አድርጎ "አቤቱ ይህን ኃጢአታቸውን ይቅር በላቸው በደልም አታድርግባቸው" ይህንንም ብሎ ዐረፈ። ደጋግ ሰዎችም መጥተው የቅዱስ እስጢፋኖስን ሥጋ ወስደው ቀበሩት ታላቅ ልቅሶም አለቀሱለት። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ሐዋርያና ሰማዕት በሆነ በቅዱስ እስጢፋኖስ አማላጅነት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ ሰማዕቱ ቅዱስ ለውንድዮስ፦ የዚህም ቅዱስ ዜና እግዚአብሔርን የሚያመልክ ተጋዳይ እንደሆነ ንጉሥ መክስምያኖስ በሰማ ጊዜ ልኮ ወደርሱ አስመጣው ሃይማኖቱንም ትቶ አማልክቶቹን ያመልክለት ዘንድ ብዙ ገንዘብ አቀረበለትና ይሸነግለው ጀመረ የከበረ ቅዱስ ለውንድዮስ ግን ዘበተበት ስጦታውንም በማቃለል ክብሩን አጐሳቈለ የረከሱ አማልክቶቹንም ረገመ።
❤ ያን ጊዜ እጅግ ተቆጥቶ በመንኰራኵር ውስጥ ሰቅለው ጽኑዕ የሆነ ሥቃይን እንዲ አሠቃዩት አዘዘ። ንጉሥ እንዳዘዘ አደረጉበት የክብር ባለቤት ጌታችን ግን ያለ ጥፋት በጤና አወጣው። ዳግመኛም በብረት ዘንጎች ይደበድቡት ዘንድ ቅባትና ስብንም በታላቅ ድስት አፍልተው ቅዱስ ለውንድዮስን ከውስጡ ይጨምሩት ዘንድ አዘዘ ይህን ሁሉ ሥቃይንም አሠቃዩት የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያጸናውና ያስታግሠው ያለ ጉዳትም በጤና ያስነሣው ነበር።
❤ ማሠቃየቱንም በደከመው ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ። ከሥጋውም ድንቆች የሆኑ ብዙዎች ተአምራቶች ተገለጹ ዜናውም በሶርያ አገር ሁሉ ተሰማ አብያተ ክርስቲያናትና ገዳማት ተሠሩለት ከገዳማቱም በአንዲቱ የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት የሆነው የከበረ ሳዊሮስ በሕፃንነቱ ተጠመቀባት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ለውንድዮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
