ch
Feedback
ሰዋስው ☘☘☘☘

ሰዋስው ☘☘☘☘

前往频道在 Telegram

በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።

显示更多
1 161
订阅者
无数据24 小时
无数据7 天
无数据30 天
帖子存档
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ማቴ. 18:12- 23 "ምን ይመስላችኋል? ለአንድ ሰው መቶ በጎች ቢኖሩት ከእነርሱም አንዱ ቢባዝን፥ ዘጠና ዘጠኙን በተራራ ትቶ ሄዶም የባዘነውን አይፈልግምን? ቢያገኘውም፥ እውነት እላችኋለሁ፥ ካልባዘኑቱ ከዘጠና ዘጠኙ ይልቅ በእርሱ ደስ ይለዋል። እንደዚሁ ከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዱ እንዲጠፋ በሰማያት ያለው አባታችሁ ፈቃድ አይደለም። ወንድምህም ቢበድልህ፥ ሄደህ አንተና እርሱ ብቻችሁን ሆናችሁ ውቀሰው። ቢሰማህ፥ ወንድምህን ገንዘብ አደረግኸው፤ ባይሰማህ ግን፥ በሁለት ወይም በሦስት ምስክር አፍ ነገር ሁሉ እንዲጸና፥ ዳግመኛ አንድ ወይም ሁለት ከአንተ ጋር ውሰድ፤ እነርሱንም ባይሰማ፥ ለቤተ ክርስቲያን ንገራት፤ ደግሞም ቤተ ክርስቲያንን ባይሰማት፥ እንደ አረመኔና እንደ ቀራጭ ይሁንልህ። እውነት እላችኋለሁ፥ በምድር የምታስሩት ሁሉ በሰማይ የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈቱት ሁሉ በሰማይ የተፈታ ይሆናል። ደግሞ እላችኋለሁ፥ ከእናንተ ሁለቱ በምድር በማናቸውም በሚለምኑት ነገር ሁሉ ቢስማሙ በሰማያት ካለው ከአባቴ ዘንድ ይደረግላቸዋል። ሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸው እሆናለሁና። በዚያን ጊዜ ጴጥሮስ ወደ እርሱ ቀርቦ። ጌታ ሆይ፥ ወንድሜ ቢበድለኝ ስንት ጊዜ ልተውለት? እስከ ሰባት ጊዜን? አለው። ኢየሱስ እንዲህ አለው። እስከ ሰባ ጊዜ ሰባት እንጂ እስከ ሰባት ጊዜ አልልህም።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

1.70 KB

12/4/2015 ዓ.ም (፲፪/፬/፳፻፲፭ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚሰበክ ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 ይትዐየን መልአከ እግዚአብሔር ዐውዶሙ። ለእለ ይፈርህዎ ወያድኅኖሙ። ጠዐሙ ወታእምሩ ከመ ኄር እግዚአብሔር፡፡ መዝ. 33÷7 🕯 ትርጉም የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፤ ያድናቸውማል። እግዚአብሔር ቸር እንደሆነ እወቁ። 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በዕለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ማቴ. 6፥19 - ፍ ም " ብልና ዝገት በሚያጠፉት ሌቦችም ቆፍረው በሚሠርቁት ዘንድ ለእናንተ በምድር ላይ መዝገብ አትሰብስቡ፤ ነገር ግን ብልም ዝገትም በማያጠፉት ሌቦችም ቆፍረው በማይሠርቁት ዘንድ ለእናንተ በሰማይ መዝገብ ሰብስቡ፤ መዝገብህ ባለበት ልብህ ደግሞ በዚያ ይሆናልና። የሰውነት መብራት ዓይን ናት። ዓይንህ እንግዲህ ጤናማ ብትሆን፥ ሰውነትህ ሁሉ ብሩህ ይሆናል፤ዓይንህ ግን ታማሚ ብትሆን፥ ሰውነትህ ሁሉ የጨለመ ይሆናል። እንግዲህ በአንተ ያለው ብርሃን ጨለማ ከሆነ፥ ጨለማውስ እንዴት ይበረታ! ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ማንም የለም፤ ወይም አንዱን ይጠላል ሁለተኛውንም ይወዳል፤ ወይም ወደ አንዱ ይጠጋል ሁለተኛውንም ይንቃል፤ ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ መገዛት አትችሉም። ስለዚህ እላችኋለሁ፥ ስለ ነፍሳችሁ በምትበሉትና በምትጠጡት፥ ወይም ስለ ሰውነታችሁ በምትለብሱት አትጨነቁ፤ ነፍስ ከመብል ሰውነትም ከልብስ አይበልጥምን? ወደ ሰማይ ወፎች ተመልከቱ፤ አይዘሩም አያጭዱምም በጎተራም አይከቱም፥ የሰማዩ አባታችሁም ይመግባቸዋል፤ እናንተ ከእነርሱ እጅግ አትበልጡምን? ከእናንተ ተጨንቆ በቁመቱ ላይ አንድ ክንድ መጨመር የሚችል ማን ነው? ስለ ልብስስ ስለ ምን ትጨነቃላችሁ? የሜዳ አበቦች እንዴት እንዲያድጉ ልብ አድርጋችሁ ተመልከቱ፤ አይደክሙም አይፈትሉምም፤ ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ሰሎሞንስ እንኳ በክብሩ ሁሉ ከነዚህ እንደ አንዱ አልለበሰም። እግዚአብሔር ግን ዛሬ ያለውን ነገም ወደ እቶን የሚጣለውን የሜዳን ሣር እንዲህ የሚያለብሰው ከሆነ፥ እናንተ እምነት የጎደላችሁ፥ እናንተንማ ይልቁን እንዴት? እንግዲህ ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤ ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል። ነገ ለራሱ ይጨነቃልና ለነገ አትጨነቁ፤ ለቀኑ ክፋቱ ይበቃዋል።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

1.42 KB

12/4/2015 ዓ.ም (፲፪/፬/፳፻፲፭ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በእለቱ በነግህ የሚሰበክ ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 ጻድቅሰ ከመ በቀልት ይፈሪ። ወይበዝኃ ከመ ዘግባ ዘሊባኖስ። ትኩላን እሙንቱ ውስተ ቤተ እግዚአብሔር። መዝ 91÷12 🕯 ትርጉም ጻድቅ እንደ ዘንባባ ያፈራል። እንደ ሊባኖስ ዝግባም ያድጋል። በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ ተተክለዋል። 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ + + + ❤ "ሰላም ለአንቂጦስ ሰማዕት ዘተዐገሠ ሥቃያተ ወእስከ ይፌጽም ገድሎ ዘአንኀ ትዕግሥተ"። ትርጉም፦ ሥቃያትን የታገሠና፤ ገድሉን እስኪፈጽም ድረስ ትዕግሥትን ያረዘመ ለኾነ ለሰማዕቱ ለአንቂጦስ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ላይ። + + + ❤ "ሰላም እብል እንዘ አሐሊ ሐዋዘ። ለአንቂጦስ ሰማዕት ምስለ ፍጢኖስ እኁዘ። ይውግርዎ ሎቱ ሶበ ንጉሥ አዘዘ። ፁገተ አንበሳ መንገለ የዋኃት ግዕዘ። እስከ መልታሕቶ ኃሠሠ ወጽሕሞ መዝመዘ። ትርጉም፦ ከፎጢኖስ ጋር የተያዘ (የታሰረ) ለኾነ ለሰማዕቱ አንኪጦስ መልካም ምስጋናን እያመሰገንኊ ሰላምታ አቀርባለኊ፤ ርሱን እንዲወግሩት ንጉሥ ባዘዘ ጊዜ ጒንጩን እስኪያድፍ (እስኪወልውል) እና ጢሙን እስኪያሽ ድረስ የአንበሳ ጭካኔ ወደ የዋህነት ተጓዘ (ተመለሰ)። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የታኅሣሥ 12። https://t.me/Eotcw

photo content
+1

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ + + + ❤ የዕለቱ አንገርጋሪ ግእዝ ዜማ፦ ሃሌ ሉያ "ኮከብ ጽዱል ዘገዳም ወዘሐቅል፤ ሰአል አባ ወተንብል፤ ካህን ዐቢይ ወመልአክ ዘውገ ሚካኤል፤ አማን ሳሙኤል ትሩፈ ገድል"። ትርጉም፦ የገዳምና የበረሃ ወጋገን የምትሆን ኮከብ አባታችን ሆይ ለምንልን የሚካኤል ወገን ታላቅ ካህንና ምድራዊ መልአክ የኾንክ ትሩፈ ገድል የተባልክ ሳሙኤል ሆይ ለምንልን። ከሊቁ ቅዱስ ያሬድ ድጓ። https://t.me/Eotcw

photo content
+3

❤ እርሱ ግን ከክፋ ሐሳቡ ተመልሶ ትምርታቸን አልተቀበለም። አውግዘውም ከምእመናን ለዩት በትምህርቱ የሚያምኑትንም ሁሉ ለዩአቸው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ12 ስንክሳር። + + + ❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "ጻድቅሰ ከመ በቀልት ይፈሪ። ወይበዝኅ ከመ ዘግባ ዘሊባኖስ። ትኩላ እሙንቱ ውስተ ቤተ እግዚአብሔር"። መዝ91፥12-13። የሚነበበው ወንጌል ማቴ6፥6፥19-ፍ.ም። + + + ❤የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "ይትዐየን መልአከ እግዚአብሔር ዐውዶሙ። ለእለ ይፈርህዎ ወያድኅኖሙ። ጠዐሙ ወታእምሩ ከመ ኄር እግዚአብሔር"። መዝ 33፥7-8 ወይም መዝ 98፥6-7። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 6፥1-13፣ ይሁ 1፥9-14 ወይም ያዕ 5፥14-ፍ.ም፣ የሐዋ ሥራ 10፥2-9 ወይም 5፥29-39። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 18፥12-23። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ የያዕቆብ ዘሥሩግ ቅዳሴ ነው። መልካም የአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ የዕረፍት በዓልና የነቢያት (የገና) ጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ታኅሣሥ ፲፪ (12) ቀን። ❤ እንኳን ለመላእክት አለቃ ለቅዱስ ሚካኤል ለወራዊው በዓል መታሰቢያና ከሃዲው ዲዮቅልጥያኖስ ዘመን ሰማዕትነት ለተቀበሉ ለቅዱሳን ለአንቂጦስና ለፎጢኖስ ለዕረፍት በዓል ሰላም አደረሰን። በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከአባ ነድራ፣ ከደብረ እስዋን ከታማኙም ከቅዱስ ዮሐንስ ከመታሰቢያቸው፣ ስለ ቀሲስ ብናጥስ በሮሜ አገር ከተሰበሰብ ከኤጲስ ቆጶሳት፣ ከቀሳውስትና ከዲያቆናት፣ ከዕረፍታቸው፣ ከቅዱሳን ሰማዕት ከአውሲስና ከእንጦንዮስ፣ ከሮሜው ከአባ መሐር ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ በዚች ቀን የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው። በዚች ቀን በዚህ ወር እግዚአብሔር ወደባቢሎን አገር ላከው የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ሦስቱን ልጆች አናንያን አዛርያንና ሚሳኤልን ከእሳት ማንደጃ ውስጥ በጣላቸው ጊዜ አራተኛ ገጽ ሁኖ ታየ። የእሳቱም ነበልባል አርባ ዘጠኝ ክንድ ያህል ወላይ ከፍ ከፍ አለ የጨመሩአቸውን ሰዎችና እሳት የሚያንዱትን አቃጠላቸው ይህም የከበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል የእሳቱን ነበልባል በበትሩ መትቶ ከሠለስቱ ደቂቅ ላይ አጥፍቶ አዳናቸው ምንም አልነካቸውም እንደ ቀዘቀዘ እንደ ጧት ጤዛ አድርጎታልና። ❤ በዚያንም ጊዜ የአባቶቻችን ፈጣሪ እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን እያሉ ስድስት ቃላትን ተናገሩ በዚህም ከስድስት መቶ ዓመት በኋላ ክርስቶስ እንደሚወለድ ትንቢት ተናገሩ። ከዚህም በኋላ የጌታ እግዚአብሔር ሥራዎቹ ሁሉ ያመሰግኑታል እርሱ ለዘላለሙ ምስጉን ልዑልም ነው እያሉ ሠላሳ ሦስት ጊዜ አመሰገኑት በዚህም በምድር ላይ ሠላሳ ሦስት ዓመት ክርስቶስ እንደሚኖር አመለከቱ። ❤ ስለዚህም አባቶቻችን የቤተ ክርስቲያን መምህራን የመላእክት አለቃ የሆነ የቅዱስ ሚካኤልን የበዓሉን መታሰቢያ እንድናደርግ ሥዓትን ሠሩ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ ቅዱሳን ሰማዕታት አንቂጦስና ፎጢኖስ፦ ይህም ሰማዕት አንቂጦስ ንጉሡ ምእመናንን ያሥራቸው ዘንድ አሠርቶ በፊቱ ያኖራቸውን የሥቃይ መሣሪያዎች በአየ ጊዜ በቆራጥነት ከሕዝብ መካከል ተነሥቶ ንጉሡን ተከራከረው ንጉሡም አሥረው ወደ ጨዋታ ማያ ቦታ አውጥተው ክፉውን አንበሳ እንዲለቁበት አዘዘ። አንበሳውም ወደርሱ በደረሰ ጊዜ እጁን ዘርግቶ ፊቱንና ጒንጩን አሻሽቶ ተወው ንጉሡም ከይቶ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ። ወታደሩም ሰይፉን በመዘዘ ጊዜ ተንቀጠቀጠ መንቀሳቀስም ተሳነው ሁለተኛም ሰውነቱ ፈጥና እንደትቆራረጥ ከበታቹ የእሳት ፍም ወደተነሠነሠበትና ቆራርጦ የሚለያይ መሣሪያ ወዳለው መንኰራኵር ውስጥ እንዲጨምሩት አዘዘ እግዚአብሔርም ከዚህ አድኖት ያለ ጉዳት በጤና አስነሣው። ❤ ዳግመኛም በውስጧ እርሳስ ወደአፈሉባት ጋን ውስጥ እንዲጨምሩት አዘዘ ሕዝቡም እያዩ የእግዚአብሔር መልአክ መጥቶ ከጋኑ ውስጥ ነጥቆ በዲዮቅልጥያኖስ ፊት አቆመው ፎጢኖስም ይህን ድንቅ ተአምር በአየ ጊዜ ልብሱን ጥሎ ተነሥቶ ወንድሙን አንቂጦስን ሳመው። "ከዳተኛውንም ንጉሥ አንተ ጐስቋላ ወንድሜን እንዴት ታሸንፈዋለህ" ብሎ ረገመው ዲዮቅልጥያኖስም ሰምቶ በአንገታቸው ዛንጅር በእግሮቻቸው እግር ብረት አግብተው ወደ ወህኒ ቤት እንዲጨምሩአቸው አዘዘ። ❤ ከዚህም በኋላ ሥጋቸው ሁሉ ይበታተን ዘነድ ጥፍር በአለው ብረት እንዲሰነጣጥቋቸው አዘዘ ዳግመኛም ወደ ጨዋታ መስክ ወስደው በድንጋይ ይወግሩአቸው ዘንድ አዘዘ። ምንም ምን የነካቸው የለም ዳግመኛም በብዛት ገርፈው በቊስላቸው ውስጥ ጨው ጨመሩ ሦስት ቀንም ወደ አንደዱበት የውሽባ ቤት ማንደጃ ውስጥ ጨመሩአቸው እርሱም እንደ ቀዘቀዘ ጠል ሆነላቸው የውሽባ ቤቱንም በከፈቱት ጊዜ የእግዚአብሔርን ገናናነት ሲነጋገሩ አገኙአቸው። ❤ ከዳተኛው ንጉሥም በአየ ጊዜ እጅግ ተቆጣ ነበልባሉም ከፍ ከፍ እስከሚል በማንደጃው ውስጥ እሳትን አንድደው ቅዱሳኑን ወደዚያ ይጥሏቸው ዘንድ አዘዘ በውስጡም ቁመው ረጅም ጸሎትን አደረጉ አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ፊታቸውን አማተቡ ነፍሳቸውንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጡ። ሥጋቸውም ከቀኑ ሁለት ሰዓት ጀምሮ እስከ ሌሊቱ ስድስት ሰዓት ድረስ በእሳቱ ፍም ላይ ነበር የነካው ነገር የለም የራሳቸው ጠጒር እንኳን አልተቃጠለም ምእመናንም ሥጋቸውን በሌሊት ወሰዱ ለክብራቸውም እንደሚገባ ገንዘው በመልካም ቦታ ቀበሩአቸው። ከእሳቸውም አስደናቂዎች ተአምራት ተገለጡ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ሰማዕታት አንቂጦስና ፎጢኖስ በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ የቅዱሳን ኤጲስቆጶሳት የቀሳውስትና የዲያቆናት የአንድነት ስብሰባ በሮሜ ከተማ፦ ይህም የሆነው ከሀዲው ዳኬዎስ በነገሠ በመጀመሪያው ዓመት በሮሜው ሊቀ ጳጳሳት በቆርኔሌዎስ የሹመት ዘመን በእስክድርያ ሊቀ ጳጳሳት በዲዮናስዮስ ዘመን በላንድዮስም በአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት ሁኖ ሳለ ግርማኖስም በኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ ሁኖ ሳለ ነው። ይህም የሆነበት ምክንያት በስደት ጊዜ የካደ ቢኖር ወይም በዝሙት የወደቀ ወይም በየአይነቱ በሆነ ኃጢአት ቢሰናከል በንስሐ ሊቀበሉት አይገባም በማለቱ ስለ ቀሲስ ብናጥስ ነው። ❤ አባት ቆርኔሌዎስ ስለዚህ አንድ ጊዜ ዳግመኛም ሦስተኛም ጊዜ ገሠጸው መከረውም ግን አልሰማውም ስለዚህም ስልሳ ኤጲስቆጶሳትን መጻሕፍትን የተማሩ ዐሥራ ስምት ቀሳውስትና አርባ ዲያቆናትን በርሱ ላይ ሰበሰበ። እርሱም ስለዚህ ነገር ብናጥስ ቀሲስን ተከራከሩት ቀስሲ ብናጥስም ምክንያት አድርጎ የተነሣው ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ ለዕብራውያን ሰዎች በስድስተኛው ምዕራፍ "ጥምቀትን ከተቀበሉ በኋላ ከሰማይ የሚሰጥ ጸጋውን ከቀመሱ በኋላ በመንፈስ ቅዱስ አንድ ከሆኑ በኋላ አይቻልም። መልካሙንም የእግዚአብሔርን ቃልና በኋላ የሚመጣውን የዓለምን ኃይል ከዐወቁ በኋላ ንስሓቸውን ሊአድሷት የእግዚአብሔርን ልጅ ሊሰቅሉላቸው ሊዋርዱላቸው ዳግመኛ ሊወድቁ አይገባም" ያለውን ኃይለ ቃል ምክንያት አድርጎ ነው። ❤ እሊህ አባቶችም እንዲህ ብለው መለሱለት "ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ ንስሓ ስለማገባ ሰው ይህን አላለም በኃጢአት በወደቀ ጊዜ በየጊዜው የክርስትና ጥምቀትን ስለሚጠመቅ ነው እንጂ ስለዚህም ሐዋርያው እንዲህ የሚለውን ቃል አስከተለ ዳግመኛ የእግዚአብሔርን ልጅ ሊሰቀሉላቸው ሊያዋርዱላቸው ይገባልን? መከራ መስቀሉ አንድ ጊዜ ብቻ ናትና ንስሓ ግን በሁሉ ጊዜ ትገኛለች። አንተ እንደምትለው ከሆነ በኃጢአት የወደቀ ዳዊትን ጌታችንን ክዶት የነበረ ጴጥሮስን ንስሓ አልተቀበለምን? አጽናኝ የሆነ የመንፈስ ቅዱስን ሀብት አልሰጠውምን? በምእመናንስ ላይ በከንቱ ሾመውን? በእጁ የሠራው ሁሉ የተጠመቀውም የጠፋ ነውን? አንተ እንደምትለው ይህ ስንፍናና ድንቁርና ነው። ክብር ይግባውና ጌታችን ግን ሃይማኖቱን ለካደ ወይም በኃጢአት ለወደቀ ለሁሉም ንስሓን ሠርቷል "ብናጥስ ሆይ ከዚህ ከረከሰና ከከፋ ምክርህ ተመልሰህ ንስሓ ግባ ለእግዚአብሔርም ለራስህና ለሰውም ሁሉ ጠላት አትሁን"።

photo content
+3

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ታኅሣሥ ፲፪ (12) ቀን። ❤ እንኳን ለኢትዮጵያኑ ጻድቃን ታላቁ ዋልድባ ገዳምን ላቀኑ ምድራን እንደ መሶበ ወርቅ ከፍ አድርገው ላስባረከ አራዊተ እንስሳ ለሚታዘዝላቸው አንበሳን እንደ ፈረስ ሲያገለግላቸው ለነበረ ለታላቁ አባት ለአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ለዕረፍት በዓል፣ ለዳግማዊ ቂርቆስ ለቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ልጅ ብሔረ ብፁዓን ለገባበት መታሰቢያ ቀንና ከአጽማቸው ጠበል ላፈለቁት ለታላቁ አባት ለአቡነ ቶማስ ለዕረፍት በሰላም አደረሰን። + + + ❤ አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ፦ ለዚህም ቅዱስ የአባ ስም እስጢፋኖስ የእናቱ ስም አመተ ማርያም ነው። እነርሱም በዘመድ የከበሩ ደጎች ናቸው በአክሱም ምድርም ወለዱት በአደገ ጊዜም የቤተ ክርስቲያንን መጸሐፍት አስተማሩት አባቱና እናቱም በሞቱ ጊዜ ወደ ደብረ በንኰል ገዳም ወደ አባ መድኃኒነ እግዚእ ሒዶ የምንኵስና ልብስን ለብሶ በጾምና በጸሎት እየተጋደለ ኖረ። ፈጽሞ ከሻገተ ጎመን በቀር አይበላም የሚጠጣውም ውኃ ነው እህል በመፍጨትና ውኃ በቅዳት ሥራ መነኰሳትን ይረዳቸው ነበር። ❤ ዘመዶቹም ወደርሱ እየመጡ በአስቸገሩት ጊዜ ወደሌላ ቦታ ሔደ እግሮቹም እስቲያብጡ ድረስ በጾም በስግደት በመቆም ተጋደለ ከዚያም ወደሌላ በረሀ ሒዶ አርባ መዓልት አርባ ሌሊት ምንም ምን ሳይቀምስ ኖረ አንበሶችና ነብሮች የሚያስፈሩም አራዊት ሁሉ ወደርሱ በመምጣት ይሰግዱለታል የእግሮቹን ትቢያ ይልሱ ነበር። በአንዲት ዕለትም በጐዳና ሲጓዝ ታላቅ ወንዝን ውኃው መልቶ አገኘ መጽሐፍና እሳትም ከእርሱ ጋር ነበር ጸሎትንም አድርጎ ወደ ውኃው ገባ ውኃውም ዋጠውና ወደታች አወረደው በእግዚአብሔርም ኃይል ወደማዶ በጣለው ጊዜ መጽሐፉ ሳይደመሰስ እሳቱም ሳይጠፋ አገኘው። ❤ ሰይጣንም በሚያስፈራ አራዊት እየተመሰለ ይፈታተነው ነበር እርሱ ግን ፈጣሪውን በመታመን ልቡ የታሠረና የጸና ስለሆነ አይፈራም። እርሱም ሲጸልይ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደርሱ መጣ በምራቁም መላ ሕዋሳቱን ቀብቶ ኃይልን አሳደረበት ከዚያችም ዕለት ጀምሮ እግሮቹን የሚያሥር ሆነ። ማቅንም ለብሶ በየሌሊቱ ሁሉ ከውኃ ውስጥ በመግባት የዳዊትን መዝሙር አምስት ጊዜ ያደርሳል ቊጥር በሌለውም ግርፋት ጀርባውን ይገርፍ ነበር። ❤ አንበሶችም በበዓቱ አጠገቡ ይሰማራሉ እርሱም አካላቸውን ይሰፍራል ይለካል ቊስላቸውንም በጥቶ እሾህና አሜከላ ያወጣላቸዋል። ከዚህም በኋላ ብዙ ደቀ መዛሙርት ወደርሱ ተሰበሰቡ በተጋድሎም ተጠመዱ ከእርሳቸውም የመጀመሪያው አባ ዘሩፋኤል ነው። በአንዲትም ዕለት በገዳመ ለጋስ የሚኖር ከአባ ገብረ መስቀል ጋር ተገናኘ ከዚህም በፊት አልተያዩም ነበር የእግዚአብሔርንም ገናናነት ሲጨዋወቱ ዋሉ በራት ጊዜም ጸሎትን ሲያደርጉ የተዘጋጀ ማዕድ ወርዶላቸው ተመግበው እግዚአብሔርን አመሰገኑ። ❤ ከዚህም በኋላ በአንዲት ዕለት ከአንድ ገዳማዊ ጋር ተገናኘ እግዚአብሔርም ያደረገላቸውን ምሥጢር በሚነጋገሩ ጊዜ አባታችን አባ ሳሙኤል እንዲህ አለ "እንሆ እኔ በአርያም ቁሜ ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር የአምላክን መንበር ሳጥን ዐሥራ ሁለት ዓመት ሆነኝ"። ለመቀደስም በሚገባ ጊዜ ኅብስትና ወይንን የተመላ ጽዋ ይወርድለታል። የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ውዳሴዋን ሲያነብ ክንድ ያህል ከምድር ወደ ላይ ከፍ ከፍ ይላል እመቤታችን ማርያምም ወደ ርሱ መጥታ የሚያበራ ዕንቊንና ንጹሕ ዕጣንን ሰጠችው። ❤ ፍልሰቱም ሲቀርብ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በክንፎቹ ተሸክሞ አወጣው ሰማያዊት ኢየሩሳሌምን ተድላዋን ሁሉ አሳየው ወደ ልዑል እግዚአብሔርም ዙፋን ፊት አቅርቦት ስሙን ለሚጠራ መታሰቢያውንም ለሚያደርግ ቃል ኪዳን ተቀበለ ወደ በዓቱም ሲመለስ ለደቀ መዛሙርቱ ነገራቸው ከዚህም በኋላ ታኅሣሥ12 ቀን በሰላም አረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ሳሙኤል ጸሎት ይማረን በረከቱ ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ12 ስንክሳር። + + + ❤ ዳግማዊ ቂርቆስ ዘብሔረ ቡልጋ፡- የታላቋ እናት የቅድስት ክርስቶ ሠምራ የመጨረሻ ልጇ ነው። አባቱ ሠምረ ጊዮርስ የተባለ ጻድቅ ጻድቅ ሲሆን እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ዐሥራ አንድ ልጆችን ወልዳ በትዳሯ እጅግ የተመሰገነች ሆና ትኖር ነበር። ❤ ከዕለታት አንድ ቀን እንዲህ ሆነ ብፅዕት ቅድስት እናታችን ክርስቶስ ሠምራ ከአገልጋዮቿ መካከል አንዷ ምግባሯ የከፋ ነበርና በጣም ስላበሳጨቻት በዚያች አገልጋይ አፍ ውስጥ የእሳት ትንታግ ጨመረችባት፡፡ ያም የእሳት ትንታግ እስከ ጉሮሮዋ ዘለቀና አገልጋይዋን ገደላት፡፡ በዚህ ጊዜ ብጽዕት ክርስቶስ ሠምራ ደንግጣ ወደ ሌላ ክፍል ገባችና ኃጢአቷን ለእግዚአብሔር እየተናዘዘች እጅግ በጣም አዝና ጥፋቷ እንደ ጸጸታትና እግዚአብሔር አምላክም በእጇ የሞተችውን አገልጋይዋን ከሥጋዋ አዋሕዶ ቢያሥነሳላት ያላትን ገንዘብና ሀብት ትታ ባላት ዘመኗ ሁሉ አገልጋዩ እንደምትሆን ብጽዓት (ስዕለት) አደረገች፡፡ እግዚአብሔርም ጸሎቷን ሰምቶ አገልጋይዋን ከሞት አሥነሳለት፡፡ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ "ልመናዬን ቸል ያላለ ቸርነቱንም ከእኔ ከባሪያው ያላራቀ አምላክ ይክበር ይመስገን" ብላ በታላቅ ምስጋና እግዚአብሔርን ካመሰገነች በኋላ አስቀድማ የገባችውን ቃል አስባ ልብሰ ምንኩስናዋን አዘጋጀች፡፡ ሕፃን ልጅዋንም ይዛ ወደ ደብረ ሊባኖስ ሄደች፡፡ ስትሄድም በልስላሴና በእንክብካቤ የኖረ እግሯ ከመንገዱ ብዛት ከእንቅፋቱም የተነሳ ፈለግ ሲያወጣ ሥጋውን እየቆረጠች ስትጥለው ደሟ መሬት ለመሬት እየፈሰሰ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ደረሰችና አስቀድማ ያዘጋጀችውን ልብሰ ምንኩስናዋን ለብሳ ከሴቶች ገዳም ገባች፡፡ ❤ ቅድስት እናታችን ይዛው የተሰደደችውን የ3 ዓመቱ ሕፃን ግን ወንድ ስለሆነ ከደጅ ላይ አስቀምጣው ስለገባች ሕፃኑ አምርሮ አለቀሰ፡፡ በዚህም ጊዜ ከመነኮሳይያቱ አንዲቷ "ሕፃኑ ሲያለቅስ ከሚያድር" ብላ ወደ በአዓቷ ልታስገባው ስትል የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ሕፃኑን ነጥቆ ወስዶ በገነት አስቀመጠው፡፡ እርሱም ታኅሣሥ 29 ቀን ተወልዶ በ3 ዓመቱ ታኅሣሥ 12 ቀን ብሔረ ብፁዓን ገብቷል፡፡ እጅግ አሳዛኝ ገድሉ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ይገኛል፡፡ ምንጭ፦ ገድለ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራና መዝገበ ቅዱሳን። + + + ❤"ሰላም ለከ ዘፈረይከ ሕገ። ሳሙኤል ዘኮንከ ለአስካለ ወይን ሐረገ። በረድኤትከ ክፍለኒ ወእደ ሀሎከ ዐሪገ። ረድኤትከሰ ወለተ ከለባት መዘገ። ምስለ ክቡራን ከመ ተሀሉ ደርገ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የታኅሣሥ 12። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት https://t.me/Eotcw

07-ይሔውጽዋ መላዕክት.amr0.83 KB

06-ይሰግዱ በብረኪሆሙ.amr1.02 KB

+1
06-ይሰግዱ በብረኪሆሙ.amr1.02 KB

04-አንተ እስየነ.amr0.61 KB

03-እስመ ለዓለም ምሕረቱ.amr0.63 KB