Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗
前往频道在 Telegram
Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service
显示更多3 592
订阅者
+624 小时
+77 天
+4830 天
帖子存档
ጨረታ ቁጥር ECWCT-NCB-PG-30/2016
---------------------
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን በአገር አቀፍ ግልፅ ጨረታ አቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ ተጫራቾች በማወዳደር የተለያዩ የፅህፈት መሣሪያዎች ዕቃ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
1.በጨረታው ለመሳተፍ ፍላጎት ያላቸው ነገር ግን በአቅራቢዎች ዝርዝር ያልተመዘገቡ ተጫራቾች ለሚመለከተው የመንግስት መ/ቤት በማመልከት የምዝገባ ሰርተፊኬት ማግኘት ይችላሉ፡፡
2.በጨረታው ለመካፈል የሚፈልጉ ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የሚያስችላቸውን የዘመኑ ግብር የከፈሉበት ከሚፈለገው አገልግሎት ጋር የተዛመደ የ2015 የታደሰ ንግድ ሥራ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ መሆናቸውን ማረጋገጫ ሰርተፊኬት እና በጨረታው ለመሳተፍ ከሀገር ውስጥ ገቢዎች ቢሮ ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ በማቅረብ የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 400.00/አራት መቶ ብር/ በመክፈል ዘወትር በስራ ሰዓት የሀገር ውስጥ ጥቅል ግዥ ቡድን በመቅረብ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ መግዛት ይችላሉ፡፡
3.የጨረታው አሸናፊ የሚሆነው በጨረታ ሰነድ ውስጥ በተመለከቱት መስፈርቶች መሠረት ሲሆን ጨረታው ዜግነትን ሳይመለከት ለማንኛውም አቅራቢ ክፍት ነው፡፡ የጨረታው ሰነድ የተዘጋጀው በአማርኛ ቋንቋ ነው፡፡
4.አቅራቢዎች የጨረታ ሰነዳቸውን ለዚህ ተግባር በተዘጋጀ ሳጥን የሀገር ውስጥ ጥቅል ግዥ ቡድን ገቢ የሚያደርጉበት የመጨረሻ መስከረም 25 ቀን 2015 ዓ.ም እስከ ከሰአት 8፡30 ድረስ ብቻ ነው፡፡
5.ተጫራቾች ለሚጫረቱበት ጨረታ ብር 100,000.00/አንድ መቶ ሺህ/ የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ CPO ወይንም በባንክ ዋስትና ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ከዚህ ውጪ በኢንሹራንስ ወይም በሌላ መልክ የሚቀርብ የጨረታ ማስከበሪያ ተቀባይነት የለውም፡፡
6.ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻው በተገኙበት ታህሳስ 14 ቀን 2015 ዓ.ም ከሰአት 9፡00 የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ግዥ መምሪያ 1 የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
7.መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ ተጫራቾች የሚከተለውን አድራሻ መጠቀም ይችላሉ፡፡
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን
ግዥና ንብረት አስተዳደር ዋና መምሪያስልክ ቁጥር 0118-13 45 27/ 0118- 72 29 47
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
ጉርድ ሾላ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ህንጻ በስተጀርባ 200 ሜትር ገባ ብሎ አንድነት ኢንተርናሽናል ት/ቤት ፊት ለፊት
🚧 ስለ Quantity Surveying
ኳንቲቲ ስንሠራ ሁሌም የምንሠራው የኮንስትራክሽን እስቴፑን ተከትለን ነው፡፡ ለምሳሌ መጀመሪያ Substructure ነው
የምንሠራው እዛ ውስጥ site clearance, pit excavation,
trench excavation, bulk excavation, backfill, cartway, concrete
work ወዘተ ይኖራሉ፡፡ በመቀጠልም Superstructure ውስጥ ያሉትን ስራዎች ነው የምንሠራው፡፡
ብረትን በተመለከተ ደሞ ለምሳሌ የአንድን ኮለን concrete work ስንሠራ ለአሠራር እንዲቀለን ወዲያው Bar schedule ውስጥ ገብተን ለኮለኑ የሚያስፈልገውን ፌሮ እናስቀምጣለን፡፡
የተወሱኑት የምንጠቀምባቸውን Units Of Measurement
1)Site clearance = m2
2)Pit and Trench xcvn = m3
3)Bulk xcvn= ከ30 ሳንቲም በታች ከሆነ m2 በላይ ከሆነ m3
4)Backfill= m3
5)Cart away = m3
6)Lean concrete= m2
7)Reinforcement = kg
8)All Concrete Works (except Ribbed slab and
grouting) =m3
9)Ribbed slab = m2
10)Grouting & filling to holes = in number
11)Formwork= m2
12)Stone masonry= m3
13)Brick masonry= m2
14)Block masonry (HCB, SCB)= m2
15)Roof cover & side cladding = m2
16)Flashing & down pipes = m
17)Plastering & pointing = m2
18)Floor finish ( terrazzo, pvc, marble, etc.) = m2
19)Skirting= m
20)Glazing = m2
21)Painting = m2
22)Sanitary = in number
23)Electrical Installation = length/ number
.
.
ከላይ የተዘረዘሩት በጠቅላላ ዩኒታቸውን ብቻ ነው የጠቀስነው
ከዚህ ጎን ለጎን ግን የስራዎቹ ዝርዝር ሊገለፅ ይገባዋል፡፡ ለምሳሌ
HCB በሜትር እስኩዌር ቢገለፅም ቲክነሱም አብሮ መጠቀስ አለበት፡፡
ኢትዮጵያን ሄራልድ
መስከረም 18/2016 ዕትም
የግንባታ ስራ ተቆራጮች | ጨረታ
@unitysupplydb1 <<´ገፃችን
የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ
https://t.me/unityconsupply
----------- ጨረታ | bid -----------
ዩ ኒ ቲ´ ኮንስትራክሽን ኦፊሻሎች
በኮንስትራክሽን ውል ስለ ግንባታ ስራ ርክክብ/Acceptance/
======**=======
# በኮንስትራክሽን ውል ሁለት አይነት የግንባታ ስራ ርክክብ ያለ ሲሆን ይሄውም
ግዚያዊ ርክክብ(provisional acceptance) እና የመጨረሻ ርክክብ(final
acceptance) የሚያካትት ነው፡፡
# በዚህ ጽሁፍ በዋናነት በኮንስትራክሽን ውል ህግ እውቅና የተሰጣቸውን
የርክክብ አይነቶች ምንነትና ተያያዥ ውጤታቸውን አስመልክቶ የህግ
ድንጋጌዎችን እና አሁን ላይ በመንግስት ተቋማት እየተሰራበት ያለውን የፒፒኤ
2011 ጀኔራል ኮንዲሽን ድንጋጌዎችን ባካተተ ሁኔታ ለማብራራት ተሞክሯል፡፡
🚧 ግዚያዊ ርክክብ/Provisional Acceptance/
# ግዜአዊ ርክክብ በተለይ በኮንስትራክሽን ውል የተመለከቱ የግንባታ ስራዎች
ተከናውነው ካበቁ በኋላ ወዲያውኑ ሁለቱ ወገኖች ማለትም አሰሪውና ተቋራጩ
ባሉበት በስራው ላይ የሚደረግ የምርመራ ማረጋገጫ ስለመሆኑ የፍትሀብሄር
ህግ አንቀጽ 3274(1) ይደነግጋል፡፡ ይሄውም አሰሪው በትክክል የተገነባውን
ግንባታ በእጁ አግብቶ መያዙን ጭምር ያረጋግጣል፡፡ ስለዚህ ጊዜአዊ ርክክብ
በዋናነት የተሰራውን የግንባታ ስራ አሰሪው መብቱን ጠብቆ በመጀመሪያ
የሚረከብበት ሂደት ነው ማለት ነው፡፡በስራው ላይ ምርመራ መደረጉንም
የሚያረጋግጥ ነው፡፡
# ፒፒኤ 2011 ክሎስ 84.1 ላይ የስራ ምርመራ/verification and test/
በመሀንዲሱ ተቋራጭ ባለበት ሊደረግ እንደሚገባ በመርህ ደረጃ ተቀምጧል፡፡
ሆኖም ግን ተቋራጩ ምርመራው ከሚካሄድበት እለት ከ30 ቀን በፊት በተገቢ
ሁኔታ እንዲያውቀው ተደርጐ በምርመራው እለት ያልተገኘ እንደሆነ የስራ
ምርመራው ተቋራጩ በሌለበት ሊካሄድ እንደሚችል ይፈቅዳል፡፡
# እንግዲህ መሀንዲሱ ስራውን ከመረመረ በኋላ ያላመነበትን የስራ ክፍል ፈርሶ
እንደገና እንዲሰራ ወይም እንዲጠገን ተደርጐ የጥራት ደረጃውን ባሟላ ሁኔታ
እንዲከናወን ለማዘዝ እንደሚችል ፒፒኤ ክሎስ 85 ይፈቅድለታል፡፡
# በዚህም መሰረት ግንባታው የስራ ምርመራውን ካለፈ አሰሪው ግንባታውን
የሚረከበው ይሆናል ማለት ነው፡፡ስለዚሁም የጊዜአዊ ርክክብ ሰርተፍኬት
ለተቋራጩ የሚሰጠው ይሆናል፡፡በመሰረቱ ተቋራጩ የጊዜአዊ ርክክብ
ሰርተፍኬት እንዲሰጠው መጠየቅ ያለበት ስራው ሊጠናቀቅ ይችላል ብሎ
ከሚያስብበት ከ15 ቀን በፊት መሆን ይኖርበታል፡፡ከዚያም መሀንዲሱ ጥያቄው
በደረሰው በ30 ቀን ውስጥ የስራ ምርመራውን አጠናቆ ሰርተፍኬቱን መስጠት
ወይም ጥያቄውን ውድቅ ማድረግ ይኖርበታል፡፡መሀንዲሱ ሰርተፍኬቱን ሳይሰጥ
ወይም ጥያቄውን ውድቅ ሳያደርግ 30 ቀኑ ያለፈ እንደሆነ ለተቋራጩ የጊዜአዊ
ርክክብ ሰርተፍኬት እንደተሰጠው ግምት እንደሚወሰድ ፒፒኤ ክሎስ 87
ያስቀምጣል፡፡
# ሌላው ተቋራጩ በስራው ላይ ያደረገው መሻሻል/መለወጥ ቢኖር እንኳ
በዝምታ ግዜአዊ ርክክብ ከተደረገ መሻሻሉ ተቀባይነት እንዳገኘ የህግ ግምት
እንደሚያስወስድ የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3275(2) ይደነግጋል፡፡እዚህ ላይ
ተቋራጩ በተሰጠው ዲዛይን መሰረት የመስራት ግዴታ ያለበት መሆኑ ይታዎቅ፡፡
ስለዚህ የህግ ግምቱ እሳቤ ተቋራጩ ከዲዛይኑ በመውጣት አሻሽሎ የሰራው
ስራ ኖሮ በግዜአዊ ርክክብ ወቅት በዝምታ አሰሪው ካለፈው እንደተቀበለው
ይቆጠራል ነው፡፡
# እንዲሁም ግዜአዊ ርክክብ መደረጉ የመድህንነት ጊዜው(warranty period)
መጀመሩን እንደሚያመለክት የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3275(3) ይደነግጋል፡፡
# የመድህንነት ጊዜ(warranty period/Defects Liability period)
# የመድህንነት ጊዜ(warranty period) የሚባለው ከጊዜአዊ ርክክብ እስከ
መጨረሻ ርክክብ ያለው ጊዜ ሲሆን አሰሪው ግንባታው በተቋራጩ በደህና ሁኔታ
ስለመሰራቱ ለመመርመርና ለማረጋገጥ የሚያስችለው ጊዜ ነው፡፡የጊዜው
ርዝማኔም በውላቸው ላይ የሚወሰን ስለመሆኑ የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3277
ይደነግጋል፡፡ ሆኖም በውሉ ላይ የመድህንነት ጊዜው ርዝማኔ ያልተጠቀሰ
እንደሆነ ከጊዜአዊ ርክክብ ቀን ጀምሮ 365 ቀን ስለመሆኑ የፒፒኤ ክሎስ 88.7
ያስቀምጣል፡፡
# ተቋራጩ በዚሁ በመድህንነት ጊዜ በተለይ የተበላሹ ስራዎችን እንዲያድሳቸው
በአሰሪው በታዘዘ ጊዜ የማስተካከል ግዴታ እንዳለበት የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ
3278 ይደነግጋል፡፡ ለዚህም ለጥገና ወጭ ሲባል ከተቋራጩ ክፍያ ላይ ሪቴንሽን
ገንዘብ(retention money or bond) 5% እየተቀነሰ በአሰሪው ይያዛል፡፡
# በመድህንነት ጊዜ ውስጥ የተለዩ ብልሽት ያለባቸው ስራዎችን
እንዲያስተካክል ተቋራጩ ተጠይቆ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ያላስተካከለ
እንደሆነ አሰሪው የማስተካከያ ስራውን በተቋራጩ ወጭ በራሱ ወይም ሌላ
ቀጥሮ ሊያሰራው ወይም ውሉን ሊያቋርጥ ስለመቻሉ ፒፒኤ ክሎስ 88.3
ለአሰሪው መብት ይሰጠዋል፡፡
# ከፊል ርክክብ/Partial Acceptance/
-በፒፒኤ ክሎስ 86 ላይ የግንባታ ስራው በከፊል እርክክብ የሚደረግበትንም
አማራጭ ያስቀምጣል፡፡ይህ ማለት የተወሰነውን የስራ ክፍል(part of the
work) ከአጠቃላይ ውሉ ጊዜ በፊት ለማስረከብ በውል ላይ ከተቀመጠ
ተቋራጩ የተወሰነውን የስራ ክፍል ከአጠቃላይ የውሉ ጊዜ በፊት ለማስረከብ
ይገደዳል ማለት ነው፡፡በዚህም በአንድ ውል ውስጥ በተለያየ ጊዜ ጊዜአዊ
ርክክብ ሊደረግ የሚችልበትን ሁኔታ ይፈጥራል ማለት ነው፡፡
🚧የመጨረሻ ርክክብ/Final Acceptance/
# የመጨረሻ ርክክብ/Final Acceptance/ በተለይ የመድህንነት ጊዜ ካለቀ
በኋላ እና ተቋራጩ ጠቅላላ ግዴታዎቹን በደህና ሁኔታ የፈጸመ መሆኑን አሰሪው
ሲያረጋግጥ ግንባታውን ሙሉ በሙሉ በእጁ የሚያደርግበት(definitively
appropriate) ስለመሆኑ የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3279 ይደነግጋል፡፡
# የመጨረሻ ርክክብ አሰሪውና ተቋራጩ ባሉበት በጽሁፍ መደረግ እንዳለበት
በአስገዳጅ ሁኔታ በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3279(2) ላይ ተደንግጓል፡፡ሆኖም
ጊዜአዊ ርክክብ/ Provisional Acceptance/ በሚመለከት ግን በጽሁፍ
መደረግ እንዳለበት የሚያስገድድ ግልጽ ህግ የለም፡፡ስለዚህ ስራው ተጠናቆ
አሰሪው ግንባታውን በእጁ ካስገባ ጊዜአዊ ርክክብ መደረጉን የሚያስገነዝብ
ይሆናል ማለት ነው፡፡በእርግጥ በጽሁፍ መደረጉ ይመከራል፡፡
# በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3282 ላይ እንደተቀመጠው ከመጨረሻ ርክክብ
በኋላ ተቋራጩ እስከ 10 አመት ድረስ ስለስራው አሰራር ጉድለት ተቋራጩ
ሀላፊነት አለበት፣መድህን ሆኖ ይቀጥላል፡፡በመጨረሻ ርክክብ ወቅት የሚታዩ
ለነበሩ ጉድለቶች(apparent defect) ግን ተቋራጩ ሀላፊነት የለበትም፡፡
ሀላፊነቱ የሚመለከተው ግንባታው በውሉ የተመለከተውን የታለመለትን ጥቅም
እንዳይሰጥ የሚያደርጉ ወይም አጠቃቀሙን በጣም ውድ የሚያደርጉና አክሳሪ
የሚያደርጉ ጉድለቶችን ነው፡፡
# የመጨረሻ ርክክብ መደረጉ የተቋራጩን መሰረታዊ ግዴታ የሚያወርድለት
ሲሆን ቀሪ ክፍያ ካለው እንዲከፈለው እና ዋስትና እንዲወርድለትና የዋስትና
መያዣ ገንዘብ ካለም እንዲለቀቅለት ለተቋራጩ መብት የመስጠት ውጤት
እንደሚኖረው የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3281 ይደነግጋል፡፡
# ፒፒኤ ክሎስ 89 በተመሳሳይ ስለመጨረሻ ርክክብ የደነገገ ሲሆን የመጨረሻ
ርክክብ ሰርተፍኬትም በመሀንዲሱ ለአሰሪውና ለተቋራጩ እንደሚሰጥ
ያስቀምጣል፡፡
ስለ Take off sheet ኣዘገጃጀት
In taking off paper we have four column which have own their property.
ኮለመን 1..
ይህ ኮለመን ታይምሲንግ ይባላል ጥቅሙም ተመሳሳይ የሆኑ ስራዎች ላለመደጋገም ማባዣ ፋክተር ሁኖ ባንዴ ለመስራት ያገለግላል።
it used for the number of times an item occurs is called TIMISING COLUMN.
ኮለመን 2..
ይህ ደሞ ዳይሜንሽን ሲባል ማለትም ቁመት ጎን እና ርቀት የምናሰፍርበት ኮለመን ነው::
it used to inter the dimensions of the items of works and the dimension is entered in the order of :length,width,height or thickness and column 2 is called DIMENSION COLUMN.
ኮለመን 3..
ይህ ደሞ ኮለመን 2 ያሉ ዳሜንሽኖቹ በማባዛት ከነ ዩኒቱ የምናሰፍርበት ኮለመን ነው
it is stated dimension in column 2 are multiplied to determine the quantity of the works and it called SQUARING COLUMN.
ኮለመን 4..
ይህ የ ገለፃ ኮለመን ደሞ ጥቅሙ ጠለቅ ባለ እና ግልፅ በሆነ መልኩ የምንገልፅበት ኮለመን ነው
it used to briefly description of the work item and it is called DESCRIPTION COLUMN .
ለጓደኛዎ እና ለሚያቁት ያጋሩ
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
