ፍቅርን በመጽሐፍ ቅዱስ
前往频道在 Telegram
፦ እንዴት relationship ን ከእግዚአብሔር ቃል አንጻር እናስኪድ💏💏 💑ተከታታይ ጾታዊ ትምህርቶች 💑ማንን ላግባ? 💑 እንዴት r/ship በቅድስና እንያዝ 💑 pornography እና ሴጋ ጉዳቶቹ በሌሎችም ወሳኝ ርዕሶች ላይ እንማማራለን for any comment @edbornagain @relationship4christ
显示更多1 804
订阅者
无数据24 小时
-27 天
+2430 天
帖子存档
1 804
"ይህም በመሆኑ እግዚአብሔር ተስፋውንና ቃል ኪዳኑን ሰጥቶናል። እግዚአብሔር መዋሸት ስለማይችል በተስፋዉና በቃል ኪዳኑ የማይናወጥ እምነት ሊኖረን ይገባል።ስለዚህ የሰጠንን ተስፋ ለመጨበጥ ወደ እርሱ የቀረብን ሁሉ በዚህ ደስ ሊለንና ልንጽናና ይገባናል።ምክንያቱም እግዚአብሔር ስለ ደህንነት የሰጠዉ ተስፋ ምን ጊዜም አይታጠፍም" ዕብ6:17-18። ሕያዉ ቃል አዲስ ኪዳንና የዳዊት መዝሙር
1 804
ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፡፡
ኢየሱስ ሊመጣ በደጅ ነው፡፡
ይህ ጊዜ የመጨረሻው ዘመን መጨረሻ ነው፡፡ የተባረከው ተስፋችን የሆነው የጌታችን የኢየሱስ መምጣት እውን የሚሆንበት፥ በመምጣቱም ያመኑትንና የተከተሉትን ብሎም በተስፋ፣ በናፍቆትና በመዘጋጀት የሚጠብቁትን፥ የራሱ የሆኑትን ብቻ የሚውስድበት ጊዜ ይሆናል ፡፡ ተዘጋጅተሃል? ተዘጋጅተሻል?
“እናንተ ደግሞ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፥ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና።”
— ሉቃስ 12፥40
1 804
በፍፁም ጽድቅ በሚኖረው በቅዱስ አምላክ ፊት ያለ ነውር መቆም እንዴት ያለ መታደል ነው። ክሬዲቱ ወደ መስቀል ይሄዳል; ስለ ኃጢአታችን የተሰቀለው፣ የተቀበረው እና የተነሣው ክርስቶስ ነው።
መልካም እሁድ❤
1 804
ጊዜው ትዝ ይለናል የተጠራንበት
ትዳሩን ሊያሸንፍ ሁሉም በያለበት
ሲወጣና ሲወርድ አግኝተህ ስትጠራው
አልማረክ ብሎ እምቢ ያለ ማነው
አዝ፦ የናዝሬቱ ኢየሱስ ከእኛ ጋራ ያለኸው
የሚናወጠውን ወጀብ በሥልጣንህ ያዘዝከው
ሥምህ አይጠገብ ደግመን ብንወድሰው
ደንቆሮዎች የነበርን መልካም ዜና ሰማን
ከብርና ከወርቅ መብለጥህን ተረዳን
ሙታን ስታስነሳ እውር ስታበራ
ዓይናችን አይቶሃል ድንቅ ሥራ ስትሰራ
አዝ፦ የናዝሬቱ ኢየሱስ ከእኛ ጋራ ያለኸው
የሚናወጠውን ወጀብ በሥልጣንህ ያዘዝከው
ሥምህ አይጠገብ ደግመን ብንወድሰው
ከአንተ ጋር ስንጓዝ በዓለም ማዕበል ውስጥ
ነፋሱን ገሰጽከው እኛ እንዳንሰምጥ
ድምፅህ አይዘነጋም ያ የሚያጽናናው
ፍቅርህ እንደ ጠል ነው ለጠወለገ ሰው
አዝ፦ የናዝሬቱ ኢየሱስ ከእኛ ጋራ ያለኸው
የሚናወጠውን ወጀብ በሥልጣንህ ያዘዝከው
ሥምህ አይጠገብ ደግመን ብንወድሰው
ዘማሪ ፓስተር ተስፋዬ ጋቢሶ
1 804
የ12ኛ ክፍል ውጤቴ ትዝ አለኝ!
የዛሬ ስንት አመት እኔም የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ነበርኩኝ፡፡ አሁን ብዙዎቻችሁ እንደሆነባችሁ የያን ጊዜ ውጤቴ በፍጹም ያልጠበኩት ነበር፡፡ ያገኘሁት ውጤቴ ይቅርባችሁ፣ አይገለጽ
በዚያ ጊዜ መጥቶብኝ የነበረውን ስሜት እስካሁን አስታውሰዋለሁ፡፡
• ከትምህርት አንጻር አቅጄው የነበረኝ ህልሜ ሁሉ ጨልሞብኝ ነበር፡፡
• ለትምህርት ትኩረት የሰጠውም ሆነ ያልሰጠውም ሰው አንድ አይነት እንደሆነና የመማር ትጋት ትርጉም እንደሌለው እንዳስብ ሆኜ ነበር፡፡
• ከእኔ ብዙ ይጠብቁ የነበሩት የወላጆቼና የቤተሰቦቼ ነገር አስጨንቆኝ ነበር፡፡
• ሕይወቴን እንዴት እንደምቀጥልና ምን ማድረግ እንዳለብኝ ግራ ግብት ብሎኝ ነበር፡፡
• ስለውጤቴ የሚጠይቁኝ ሰዎች ሁኔታ አሸማቆኝ ነበር፡፡
• በአጭሩ ዞሮብኝ ነበር!!!
ሆኖም፣ የያን ጊዜው ውጤቴ የዛሬውን ሕይወቴን አልወሰነውም፡፡ የዛሬውን ሕይወቴን የወሰነው ለነበረኝ ውጤት የሰጠሁት ምላሽ ነው፡፡
የፈተና ውጤት ላልመጣላችሁ . . .
1. ሁኔታው ስሜታችሁን መንካቱ ጤናማ ሂደት እንደሆነ አስታውሱ
2. የእናንተን የወደፊት ሕይወት የሚወስነው ራእያችሁን ማወቃችሁና ያንን መከተላችሁ እንጂ በየጊዜ የምትወድቁትና የምትነሱት ልምምድ እንዳልሆነ እወቁ
3. ሰዎች ለሚሰነዝሩት ሃሳብ ብዙ ቦታ አትስጡ፡፡ ብዙዎቹ ሰዎች ለራሳቸው እንኳን ያላወቁበት ሰዎች ናቸው፡፡
4. ለሁኔታው የምትሰጡትን ምላሽና የሚቀጥለው እርጃችሁ ምን ሊሆን እንደሚገባው ተረጋግታችሁ አስቡ፡፡
ወደቃችሁ እንጂ ውዳቂ አይደላችሁም!
ውጤት ባይመጣም እናንተ ግን ወደ ወደፊት ራእያችሁና መልካም ፍጻሜያችሁ ትቀጥላላችሁ!
ምንጭ Dr eyob
1 804
በተልእኮው መስክ እንደ ጥንዶች እንዴት ማሸነፍ ይቻላል? ወይም ፍቅርን በመጽሐፍ ቅዱስ መሰረት እንዴት እናስኪድ?🌎
1. አንዳችሁ የሌላውን ድክመቶች ይሸፍኑ
2. አንዳችሁ የሌላውን ጥንካሬ ያክብሩ
3. ማውራት የማትችላቸው ርዕሰ ጉዳዮች የሉህም። ፍርድ የለውም። ግልጽነት አእምሮዎን ወደ መፍትሄዎች ይከፍታል።
4. አንዳችሁ የሌላውን አስተያየት እና አስተዋፅዖ ግምት ውስጥ ያስገቡ
5. 100% ሙሉ ቁርጠኝነት ይሁኑ
6. ተጨማሪ እድገት ያድርጉ. እድገትን እንጂ ፍጽምናን አትፈልግ
7. ግንኙነትዎን የመገምገም ባህልን ያዳብሩ; ደህና ነን ፣ እና የት ማሻሻል እንችላለን?
8. እርማትን ተቀበል ትሑት ሁን
9. ምርጥ ሚስት፣ ምርጥ ባል ለመሆን በራሳችሁ ላይ ሥሩ
10. የጋራ ግቦች ይኑርዎት
11. በግለሰብ ግቦችዎ ውስጥ እርስ በርስ መደጋገፍ
12. ጓደኞች እንዳላችሁ እንኳን አንዳችሁ ለሌላው ቅድሚያ ይኑራችሁ
13. እግዚአብሔርን አንድ ላይ አመስግኑ። የሚያመሰግኑ ጥንዶች ኃይለኛ ባልና ሚስት ናቸው
14. እርስ በርሳችሁ አትወዳደሩ, እርስ በርሳችሁ ተስማሙ
15. የተማራችሁትን ማንኛውንም ትምህርት ወይም እድሎች ወደ ትዳራችሁ አምጡ። አብራችሁ ተማሩ
16. ታጋሽ ሁን. አንዳንድ ድሎች ጊዜ ይወስዳሉ
17. እንደ ባልና ሚስት ወይም እንደ ግለሰብ ስትወድቁ እርስ በርሳችሁ ተነሱ
18. አብረው የገነቡትን ጠብቁ። በፍጥነት ማጣት በጣም ቀላል ነው
19. ቁጣህን ተቆጣጠር። በንዴት ጊዜ ብዙ መጥፎ ምርጫዎች ይደረጋሉ።
20. ሌሎች ጥንዶችን አትኮርጁ. ምስክርነቶችህን ፍጠር።
@relationship4christ
@edBornagain /owner
@Greatmission1
1 804
Repost from ክርሰቲያናዊ እጮኝነት(Christian Relationship )
በፍላጎት እንጂ በግፊት አታግቡ!
(“የፍቅር ሕይወት” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መጽሐፍ የተወሰደ)፡፡
አንዳንድ ሰዎች ፍቅረኛን ለመያዝና አልፎም ወደትዳር ለመሄድ የሚነሳሱባቸውን የተሳሳተ አመለካከቶች ጠቀስ እናድርግ፡-
1. ሰው ሁሉ ስላገባ?
አንዳንድ ሰዎች በዙሪቸው ያሉ አቻዎቻቸው፣ አብሮ አደጎቻቸውና፣ አንዳንዴም ታናናሽ እህትና ወንድሞቻቸው ተራቸውን እየጠበቁ ትዳር ሲይዙ ሲመለከቱ ይህ ነው የማይባል ስነ-ልቦናዊ ጫና ያድርባቸዋል፡፡ በዚህ ላይ የቤተሰብ ግፊትና የሕብረተሰቡ እረፍት-አሳጪ ሃሳብ ሰንዛሪነት ሰዎቹ ስለትዳር ትርጉም በሚገባ ሳይገነዘቡ በችኮላ በሚገባ ወዳላሰቡበት ግንኙነት ውስጥ በመግባት ትዳርን አደንዲመሰርቱ ግፊትን ያሳድርባቸዋል፡፡ የዚህ አይነቱን ውሳኔ መጨረሻ መገመት አያስቸግርም፡፡
2. የወሲብ ፍላጎትን ለማርካት?
በኋላ በሌላ ክፍላችን እንደምንመከተው ይህ የመነሻ ሃሳብ ትክክለኛ ገጽታ ቢኖረውም አንዳንድ ሰዎች ግን ሌላውን የትዳር ትርጉም ችላ በማለትና ሙሉ ስእሉን ባለመገንዘብ በወሲብና በወሲብብ ላይ ብቻ ያተኮረ መነሻ ሃሳብ ይዘው ለትዳር ይቸኩላሉ፡፡ ይህ ግማሽ ገጽታ ያለው ግንዛቤ ሊያስከትል የሚችለው ቀውስ ግልጽ ከመሆኑ የተነሳእዚህ ጋር መዘርዘር አስፈላጊ አይመስለኝም፡፡
3. ከጊዜያዊ ሁኔታ ለመገላገል?
ከላይ ከተጠቀሱት የተዛቡ የመነሻ ሃሳቦች በተጨማሪ አንዳንድ ሰዎች ጊዜያዊ ከሆነ ብቸኝነት ለማምለጥ ሲሉ ዘለቄታዊ ትርጉም ወዳለው ትዳር ፈጥነው ይገቡና የብቸኝነት ስሜታቸው ሲሰክን ስለወሰኑት ውሳኔ እንደገና ማሰብ ይጀምራሉ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ከጊዜያዊ የገንዘብ ችግር ለማምለጥና የመሳሰሉት ትንሽ ታግሰው ሊልፏቸው የሚችሉትን ሁኔታዎች ሽሽት ወደ ትዳር ዘልለው የሚገቡ ሰዎች አሉ፡፡
ከእነዚህ ሁኔታዎች አብዛኛዎቹ በትክክለኛና በተረጋጋ ምርጫ ውስጥ የምንጠቀምባቸው አስፈላጊ እውነታዎች ቢሆኑም ወደ አንድ ትዳር የመግቢያ ምክንያታችን እነሱ ላይ ብቻ ሲንጠለጠል መጨረሻውን አደገኛ ያደርገዋል፡፡
https://t.me/Christianrelationship
1 804
Keep your virginity and physical purity. Holiness is greater than virginity 💑👨❤️👨
@relationship4christ
@Bornagain
1 804
፦ እንዴት relationship ን ከእግዚአብሔር ቃል አንጻር እናስኪድ💏💏
💑ተከታታይ ጾታዊ ትምህርቶች
💑ማንን ላግባ?
💑 እንዴት r/ship በቅድስና እንያዝ
💑 pornography እና ሴጋ ጉዳቶቹ
በሌሎችም ወሳኝ ርዕሶች ላይ እንማማራለን
for any comment
@edbornagain
@relationship4christ
1 804
በሕይወት ውስጥ በሁለተኛነት ደረጃ የምናደርገው ከፍተኛ ውሳኔ ማንን እንደምናገባ የምንወስነው ነው። ክርስቲያን ስለ ፍቺ ለማሰብ አይችልም፤ ስለዚህ ለማግባት ከምንወስነው ተቃራኒ ፆታ ጋር የምናደርገው ቃል ኪዳን የዕድሜ ልክ ነው። በመሆኑም ስለ ትዳር ጓደኛችን ለመወሰን ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ አለብን። ሆኖም ግን የተቀረው ዓለምና እንዲሁም ብዙ ክርስቲያኖች የትዳር ጓደኛን ለመምረጥ ጥሩ መሠረት የሌላቸው መሆኑ የሚያሳዝን ነገር ነው። ለምርጫቸው ብዙ ጊዜ ሦስት መመዘኛዎችን ይጠቀማሉ፡፡
1. በሰዎች አመለካከት መልከ መልካም ነውን (ናትን)?
2. ሀብትና እውቀት አለውን (አላትን)?
3. እርሱ ወይም እርሷ ከትክክለኛ ቤተሰብ የተገኙ ናቸውን? ወላጆቻቸው ወንጌላውያን ወይም የታወቁ ናቸውን? ወይስ ባሪያዎች፥ ወይም ሸክላ ሠሪዎችና ብረት ቀጥቃጮች ናቸው?
መጽሐፈ ምሳሌ ስለ ትዳር ጓደኛ አመራረጥ ፍንጭ ይሰጠናል። ግልጽ የሆነውን ማብራሪያ የምናገኘው በምዕራፍ 31 ከተጠቀሰችው መልካም ሴት ነው። በእነዚህ ቍጥሮች በደም ግባትና በውበት ላይ ተመሥርተን እንዳንመርጥ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶናል (ምሳሌ 31:30)፡፡ በመሠረቱ አንዲትን ሴት መልካም ሚስት የሚያደርጓትን ነገሮች ብዙ ጊዜ ወንዶች የማይቀበሉኣቸው ናቸው። እነዚህ ቍጥሮች ለአንዲት ሴት ትልቅ ክብርና ሞገስ እንዲሁም በኅብረተሰቡ መካከል ከሁሉ የላቀ ስፍራ ስላሚያስገኝላት ባሕርያት ይናገራሉ። በምሳሌ 31 ስለ መልካም ሚስት የተጠቀሱ የሚከተሉትን ነገሮች ተመልከት፡-
1. መልካም ባሕርይና ከበሬታ ያላት ናት (ምሳሌ 31፡10፡ 25)።
2. በምታደርገው ነገር ሁሉ እምነት የሚጣልባት ስለሆነች የባልዋ ልብ ይታመንባታል (ምሳሌ 31፡11)።
3. ለባልዋና ለልጆችዋ የሚያስፈልጋቸውን ነገሮች ለማቅረብ ትጉ ናት።
4. ጐበዝና ጠንካራ ስለሆነች በራስ አነሣሽነት ወደ ገበያ በመሄድ ትገዛለች ትሸጣለች። በባሏ ሥር ብቻ የምትተዳደር ባሪያ አይደለችም። ይልቁንም ቤተሰቧን ትንከባከባለች (ምሳሌ 31፡27)።
5. ፈሪሀ-እግዚአብሔር የሞላባት፥ ጥበብ ያላትና ለሌሎች እውነተኛ ጥበብ የምታስተምር ናት።
6. እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ናት።
7. በባሏ የተመሰገነች ናት።
በዚህ ዘመን ብዙ ሴቶች አይከበሩም፤ በባሎቻቸው ቍጥጥር ሥር ናቸው። በሥራ ቦታ፣ በቤትና በትምህርት ቤት በራሳቸው አነሣሽነት እንዲንቀሳቀሱ አይፈቀድላቸውም። በመጽሐፈ ምሳሌ ከተጠቀሰችው መልካም ሴት ሥዕላዊ ሁኔታ በጣም ለየት ያለ ነው። በመጽሐፈ ምሳሌ የተጠቀሰችው ሴት ፈሪሀ- እግዚአብሔር የሞላበት ባሕርይና ከፍተኛ የአእምሮ እውቀት ያላት፥ በሥራዋ ንግድን ለማካሄድ የምትችል፥ የቤተሰቧንና የሌሎችን ፍላጎት ለማሟላት በትጋት የምትሰራ ናት፡፡ እንዲያውም ለሌሎች ጥበብን የምታስተምር ሴት ናት (ምሳሌ 31፡10፤ 8፡11)። በሕይወትህ ዘመን ሁሉ በእጅጉ የምታስደስትህ የትዳር ጓደኛ ትፈልጋለህን? እንግዲያውስ እንዲህ ዓይነቷን ሴት ፈልግ። ሴቷ ደግሞ እንዲህ ዓይነቱን ወንድ ትፈልግ። መልካም የትዳር ጓደኛ፡ ውበት፥ ሀብት፥ ወይም ከመልካም ቤተሰብ የመገኘትን መመዘኛ ማሟላት እንዳለበት በሚናገረው የዓለማዊ ጥበብ ወጥመድ ተሰናክላችሁ እንዳትወድቁ ተጠንቀቁ።
የውይይት ጥያቄ፥ በቤተ ክርስቲያንህ ለሚገኙ ወጣቶች ጥሩ የትዳር ጓደኛን ስለ መምረጥ እንዴት ታስተምራቸዋለህ?
@relationship4christ
@relationship4christ
1 804
ይህች ሴት ማናት?
@relationship4christ
@relationship4christ
ምሳሌ 31
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁰ ልባም ሴትን ማን ሊያገኛት ይችላል? ዋጋዋ ከቀይ ዕንቍ እጅግ ይበልጣል።
¹¹ የባልዋ ልብ ይታመንባታል፥ ምርኮም አይጐድልበትም።
¹² ዕድሜዋን ሙሉ መልካም ታደርግለታለች፥ ክፉም አታደርግም።
¹³ የበግ ጠጕርና የተልባ እግር ትፈልጋለች፥ በእጆችዋም ደስ ብሎአት ትሠራለች።
¹⁴ እርስዋ እንደ ነጋዴ መርከብ ናት፤ ከሩቅ አገር ምግብዋን ትሰበስባለች።
¹⁵ ገና ሌሊት ሳለ ትነሣለች ለቤትዋም ሰዎች ምግባቸውን፥ ለገረዶችዋም ተግባራቸውን ትሰጣለች።
¹⁶ እርሻንም ተመልክታ ትገዛለች፤ ከእጅዋም ፍሬ ወይን ትተክላለች።
¹⁷ ወገብዋን በኃይል ትታጠቃለች፥ ክንድዋንም ታበረታለች።
¹⁸ ንግድዋ መልካም እንደ ሆነ ትመለከታለች፤ መብራትዋ በሌሊት አይጠፋም።
¹⁹ እጅዋን ወደ አመልማሎ ትዘረጋለች፥ ጣቶችዋም እንዝርትን ይይዛሉ።
²⁰ እጅዋን ወደ ድሀ ትዘረጋለች፥ ወደ ችግረኛም እጅዋን ትሰድዳለች።
²¹ ለቤትዋ ሰዎች ከበረዶ ብርድ የተነሣ አትፈራም፥ የቤትዋ ሰዎች ሁሉ እጥፍ ድርብ የለበሱ ናቸውና።
²² ለራስዋም ግብረ መርፌ ስጋጃ ትሠራለች፤ ጥሩ በፍታና ቀይ ግምጃ ትለብሳለች።
²³ ባልዋ በአገር ሽማግሌዎች መካከል በሸንጎ በተቀመጠ ጊዜ በበር የታወቀ ይሆናል።
²⁴ የበፍታ ቀሚስ እየሠራች ትሸጣለች፥ ለነጋዴም ድግ ትሸጣለች።
²⁵ ብርታትና ከበሬታ ልብስዋ ነው፤ በኋላም ዘመን ላይ ትስቃለች።
²⁶ አፍዋን በጥበብ ትከፍታለች፤ የርኅራኄም ሕግ በምላስዋ አለ።
²⁷ የቤትዋንም ሰዎች አካሄድ በደኅና ትመለከታለች፥ የሀኬትንም እንጀራ አትበላም።
²⁸ ልጆችዋ ይነሣሉ፥ ምስጋናዋንም ይናገራሉ፤ ባልዋ ደግሞ እንዲህ ብሎ ያመሰግናታል፦
²⁹ መልካም ያደረጉ ብዙ ሴቶች አሉ፥ አንቺ ግን ከሁሉ ትበልጫለሽ።
³⁰ ውበት ሐሰት ነው፥ ደም ግባትም ከንቱ ነው፤ እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዋ ትመሰገናለች።
³¹ ከእጅዋ ፍሬ ስጡአት፥ ሥራዎችዋም በሸንጎ ያመስግኑአት።
@relationship4christ
@relationship4christ
1 804
Someday I'm going to
Marry a person who loves
Jesus more than me
👩❤️👨 @relationship4christ 👩❤️👨
👩❤️👨 @relationship4christ 👩❤️👨
👩❤️👨 @relationship4christ 👩❤️👨
1 804
👱♂ ወንዶች: #ትክክለኛዋ የፍቅር አጋርህ አንተን ወደ እግዚአብሔር የምታቀርብህ ናት።💟✝
👱♀ ሴቶች: #ትክክለኛው የፍቅር አጋርሽ አንቺን ወደ እግዚአብሔር የሚያቀርብሽ ነው።💟✝
❣
@relationship4christ
@relationship4christ
1 804
እንኳን ለ2016 ዓ.ም በሰላም አደረሳችሁ አመቱ የስኬት፣ የደስታ፣ ዳግም የመነሳት፣ ሃይላችሁ የሚታደስበት አመት ይሁንላችሁ።
እግዚአብሔርን በመተማመን ወጥጣችሁ የምትገቡበት ይሁን።
መልካም አዲስ አመት
🌻🌻🌻🌻🌻🌻
@relationship4christ
@relationship4christ
1 804
የአንዲት ሚስት ባል እና የሁለት ልጆች አባት ነኝ!!
ወጣቶች አግቡ!
ያላገባችሁ ሰዎች በተለይ እድሜያችሁ የደረሰ እንድታገቡ እመክራለሁ። በመምረጥና በተመራጭነት አባዜ ውስጥ ያላችሁ ወጣቶች በቅድሚያ ወደ ህይወታችሁ የሚመጣውን ሰው Overnight በChat ከመፈለግ(Search ከማድረግ) እግዚአብሔር እንዲሰጣችሁ በጌታ ፊት ሁኑ!!
አንዳንድ ወጣቶች ነገ የተሻለ ኑሮ መኖር አለብኝ በሚል የተሻለ የኑሮ Status ያላትን/ያለውን ሰው እስኪያገኙ ይኳትናሉ ይቅበዘበዛሉ ሰው ይቀያይራሉ። ወዳጄ! የተሻለ ኑሮ መለኪያው ውድ ቤትና መኪና ሳይሆን የእግዚአብሔር አብሮነት ነው።
እዚሁ ኢትዮጵያ ሆናችሁ ከሀገር ውጭ ያለን ሰው ካላገባሁ የምትሉ ወጣቶች ደግሞ እንደፍላጎታችሁ ይሳካላችሁ። ከሀገር ውጭ ያለን ሰው የፈለጋችሁት የተሻለ ኑሮ ለመኖር አይደል? ጥሩ ነው። ግን እምነት የጎደለው እሳቤ መሆኑን ልነግራችሁ እወዳለሁ። ሀገር ውስጥም ከሀገር ውጭም #የሚያኖር እግዚአብሔር መሆኑን ካላወቅን ኮሽ ባለ ቁጥር መስጋታችን አይቀርም።
የተሻለ ኑሮ መገለጫው የእግዚአብሔር በትዳር ውስጥ መገኘት ነው።
ያላገባችሁ ወጣቶች ሆይ!
አግቡ!!!!
ከአንድ ወንድማችን
@relationship4Christ
@relationship4christ
1 804
ወሲባዊ እርኩሰትን አትታገሱ
አንድ ሰው ህይወቱን እንዴት እንዳተረፈ ሲናገር አንድ እግሩ በወጥመድ ተይዞ ረዳት በማጣቱ ከኪሱ ቢለዋ አውጥቶ እግሩን በመቁረጥ እየዳኸ ወደህክምና የሚወስደውን ሰው በመፈለጉ ነበር ።
"ቀኝ ዓይንህም ብታሰናክልህ አውጥተህ ከአንተ ጣላት፤ ሙሉ ሰውነትህ በገሃነም ከሚጣል ይልቅ ከአካላትህ አንድ ቢጠፋ ይሻልሃልና። ቀኝ እጅህም ብታሰናክልህ ቆርጠህ ከአንተ ጣላት፤ ሙሉ ሰውነትህ በገሃነም ከሚጣል ይልቅ ከአካላትህ አንድ ቢጠፋ ይሻላልና። " ቀኝ እጅ ቢቆረጥም ግራ እጅ አያርፍም። ጌታእያስተማረን ያለው ለነፍስ ሲባል መውሰድ ስላለብን ቆራጥ እርምጃ ነው ።
1. ዘላለማችንን የሚወስን ጉዳይ ነው፥ ወሲባዊ እርኩሰትን ብንታገስ ቸልተኝነቻችን ዋጋ ያስከፍለናል።ሰሞኑን የምንሰማው ፀያፍ ወሬ ከጦርነት ወይም በሽታ በላይ ሊያሰጋንም ይገባል። ጌታ ሉቃስ 12:4-5 ላይ መፈራት ያለበት ስጋን የሚገድለው ሳይሆን እርሱ ብቻ እንደሆነ ተናግሯል። ይህ እርኩሰት ደግሞ ቁጣ ተቀጥሮለታል ። (ቆላስያስ 3:5-6)
2. ወሲባዊ ቅድስና የእምነታችን ማረጋገጫ ነው
በስም ክርስቲያን የሆኑ ሰዎች በእምነት ያገኙትን ደህንነትና ኑሯቸውን ይነጣጥሉታል። ስለዚህ በአጠቃላይ ስለቅድስና የተሰጡትን ማስጠንቀቂያዎች 'ባልሰማ' ያልፏቸዋል። በእርግጥም ፅድቅ በዕምነት ብቻ ነው። ከፀደቁትም መሀል ማንም አይጠፋም(ሮሜ8:30)። የስጋን ስራ የሚሰሩ ደግሞ ይጠፋሉ። (ገላ5:21) እነዚህ አይጣረሱም ምክኒያቱም የሚያፀድቅ ዕምነት የሚቀድስም ስለሆነ እርኩሰትን ይዋጋል። ከሲዖል የሚያድን እምነት ከእርኩሰት ያድናል። ማመን ለቅድስና ከመትጋት ጋር አይጣረስም። "ፅድቄ በዕምነት ቅድስናዬ በስራ" ብሎ ነገር የለም። ሁለቱም በዕምነት መንፈስቅዱስ የሚሰራው ስራ ነው። "አንዴ በእምነት ድኛለሁና ብረክስም ደህንነቴን አላጣም" ብሎ ሀጥያትን justify ማድረግ አለማመንን ያሳያል። ለመቀደስ መታገል ለዕምነት መታገል ነው።
3. የልብ አለመቀየርን ያሳያል
የክርስትና ስብከቱ "በደንብ ከለፋህ ሀጥያት ጨርሶ አትሰራም" አይደለም። ዋና ጥያቄው :በአንድ ወቅት ትወደው የነበረን እርኩሰት ከዳንክ በኀላ ጠላኸው ወይ ነው። ሙሉበሙሉ ነፃ ባትሆንም ዕለት ዕለት ትታገለዋለህ ወይ? ወይንስ ዕብራውያን 10:26 ላይ እንዳሉት ሰዎች ወደህ ሀጥያት እየሰራህ ስርየት ትጠብቃለህ?
ጌታዬ እኮ የሞተው በዚህ እርኩሰት ምክኒያት ነው። ታዲያ ምንስ ህጉ ቢፈቅድልኝ አለምና ዘመኑ ጎሽ ቢሉኝ ከውዴ ጠላት ጋር ጓደኝነት እንዴት ይሆንልኛል? ከአለም ጋር ወዳጅነት ከአብ ጋር ፀብ መሆኑን እያወኩ?(1 ዩሐ 2:16) ነፃ አውጥቶኛል ብዬ እንዴት በቀንበር እያዛለሁ? ለሀጥያት ሞቻለሁ ብዬ ለሀጥያት እንዴት እኖራለሁ? (ሮሜ 6:11) አዲስ ፍጥረት ሆኜ በአሮጌው ሰው እንዴት እመራለው?(ገላ 2:20, ኤፌሶን 4:22-24)
4. የላቀ ፍስሀ በክርስቶስ አለ
በተለይ አማኝ ግድ ሆኖበት አይደለም የሚወድቀው። ሀጥያት የሚሰጠውን ጊዜያዊ ደስታ ፈልጎ እንጂ። ጠላት ደግሞ እድልፈንታ ከሰጠነው ብንቀደስ ስለሚያመልጠን ነገር ይሰብከናል። የውሸት አባት መሆኑን ብንረዳ ግን በመቀደስ የምናመልጠው እንጂ የሚያመልጠን ነገር የለም። በህልውናው የዘላለም ፍስሀ በሙላት አለ (መዝሙር 16:11)
ልበ ንጹሖች ብፁዓን ናቸው፥ እግዚአብሔርን ያዩታልና።
(ማቴዎስ 5: 8) እርሱን ከማየት ጋር የሚወዳደር ምን ይሆን? ከዚህ በላይ ምን ተስፋ አለን? የውዳችንን ውበትና ክብር እናይ ዘንድ ከአይናችን ጋር ቃልኪዳን እንግባ (ኢዮብ 31:1)
ስለዚህ ያልዳንን ሰዎች ንስሀ እንግባና እምነታችንን ስለሰው ልጅ ሀጥያት በመስቀል የሞተው ላይ እናድርግ።
የዳንን ደግሞ ርኩሰትን በመታገስ የጠላትን ሀሳብ አንሳት። ላለፈው ቸልተኝነት ንስሀ እንግባና በመንፈስቅዱስ እርዳታ ትግል እንጀምር። የሚያስትህን ነገር ለማጥፋት አትራራ(ማቲ 18:9)። ነገ አድጎ የሚገድለንን አውሬ መንከባከብ ሞኝነት ነው። ጠላት አይተኛልንምና መዳናችንን ዕለት ዕለት እንፈፅም። ጌታችን ከሞት ሲነሳ ሀጥያት በኛ ላይ ያለውን ጌትነት አጥቷል። "ጐበዞች ሆይ፥ ብርቱዎች ስለ ሆናችሁ የእግዚአብሔርም ቃል በእናንተ ስለሚኖር ክፉውንም ስለ አሸነፋችሁ እጽፍላችኋለሁ።
(1ኛ የዮሐንስ 2: 14)
"፤ እንደ ሥጋ ፈቃድ ብትኖሩ ትሞቱ ዘንድ አላችሁና፤ በመንፈስ ግን የሰውነትን ሥራ ብትገድሉ በሕይወት ትኖራላችሁ። "
(ወደ ሮሜ ሰዎች 8: 13)
ፀጋው ለመዋጋት ብርታታችን ነው። የምንገድልበት ሰይፋችን ደግሞ ቃሉ ነው (ኤፌ 6:17)
(1ኛ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች 4:1-8)
------------
እንግዲህ በቀረውስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ልትመላለሱ እግዚአብሔርንም ደስ ልታሰኙ እንዴት እንደሚገባችሁ ከእኛ ዘንድ እንደ ተቀበላችሁ፥ እናንተ ደግሞ እንደምትመላለሱ፥ ከፊት ይልቅ ትበዙ ዘንድ በጌታ በኢየሱስ እንለምናችኋለን እንመክራችሁማለን። በጌታ በኢየሱስ የትኛውን ትእዛዝ እንደ ሰጠናችሁ ታውቃላችሁና። ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም መቀደሳችሁ ነውና፤ ከዝሙት እንድትርቁ፥ እግዚአብሔርን እንደማያውቁ አሕዛብ በፍትወት ምኞት አይደለም እንጂ፥ ከእናንተ እያንዳንዱ የራሱን ዕቃ በቅድስናና በክብር ያገኝ ዘንድ እንዲያውቅ፤
አስቀድመን ደግሞ እንዳልናችሁና እንደ መሰከርንላችሁ፥ ጌታ ስለዚህ ነገር ሁሉ የሚበቀል ነውና ማንም በዚህ ነገር አይተላለፍ ወንድሙንም አያታልል።
ለርኵሰት ሳይሆን እግዚአብሔር በቅድስና ጠርቶናልና። እንግዲህ የሚጥል ሰውን የጣለ አይደለም፥ መንፈስ ቅዱስን በእናንተ እንዲኖር የሰጠውን እግዚአብሔርን ነው እንጂ።
@relationship4christ
@relationship4christ
@relationship4christ
