1 740
订阅者
+124 小时
+37 天
-530 天
帖子存档
የትኩረት አቅጣጫ በሆኑ የሙያ ዘርፎች ላይ የሴት ሰልጣኞችን ተሳፎ ማሳደግ እንደሚገባ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት ሴቶችን ተፈላጊ በሆኑ የሙያ ዘርፎች ለማሳተፍ በሚደረግ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ላይ ከዲፓርትመቶች ከተወጣጡ ሴት ሰልጣኝ ተማሪዎች ጋር የውይይት መድረክ ተካሄደ::
መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ የሴቶችና ህፃናት ክፍል ተጠሪ ወ/ሮ ራሄል እሸቱ ሲሆኑ በንግግራቸውም ሴት ሰልጣኞች በአብዛኛው Soft Skill የሚባሉ ሙያዎች ላይ ጥገኛ እንደሚሆኑ አስታውሰው በዛው መጠንም ተምረው ሲጨርሱ ስራ የማግኘት እድላቸው በጣም አናሳ እንደሆነ ይስተዋላል ያሉ ሲሆን ሴቶች ኢንዱስትሪው በሚፈልገውና ብዙ እድሎች ያሉባቸው ዘርፎች ላይ ትኩረታቸውን በማድረግ ተጠቃሚ ሊሆኑ ይገባልም ብለዋል::
በፍላጎት ዳሰሳ ጥናት መድረኩ ላይ ለሰልጣኞች ግንዛቤ የሰጡት የEASE ፕሮጀክት የሞኒተሪንግና ኢቫሉዌሽን አስተባባሪ ኢንጂነር ህይወት እሸቱ ሲሆኑ በመልእክታቸውም ሴቶች የኢንጂነሪንግ ዘርፎች ላይ ደፈር ብለው ተሳታፊ ቢሆኑ ተጠቃሚ የሚያደርጏቸው ብዙ እድሎች እንዳሉ አስታውሰው ይህ በኮሌጁ የሚዘጋጀው ጥናትም የችግሩን መንስኤ ከስር መሰረቱ በመለይትና ለሴቶች እስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ወቅቱ በሚጠይቀው የሙያ ዘርፍ ላይ በሚፈለገው ደረጃ እንዲሳተፉ ለማድረግ እንደሆነም ገልፀዋል::
በመድረኩ ሴት ሰልጣኞቹን በቡድን ተክፍለው የሚስተዋሉ ክፍተቶች ላይ እንዲወያዩ ማድረግ የተቻለ ሲሆን በዚህም ሴቶች Hard Skill የሚባሉ የሙያ ዘርፎችን ደፍረው እንዳይቀላቅሉ ምክንያት ናቸው ያሏቸውን መንስኤዎች በዝርዝር አንስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል::
በቀጣይም ከመድረኩ በተገኙ ግብዓቶች እንዲሁም ተጨማሪ በሚደረጉ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናቶች መሰረት የሚስተዋለውን ችግር ለመቅረፍ የሚያስችል አሰራር በመዘርጋት ወደ ትግበራ እንደሚገባም ተገልፇል::
በEASE ፕሮጀክት በአለም ባንክ በሚደርግ ድጋፍ ለቀጣይ 5አመት በሚቆየው ፕሮጀክት ውስጥ የትኩረት ዘርፍ ተብለው በተመረጡ 3 የሙያ መስኮች (Manufacturing, Electrical/Electronics, Automotive) ላይ በትኩረት የሚሰራ ሲሆን ሴቶች በነዚህ ዘርፎች ላይ ተሳትፎ ቢያደርጉ ተጠቃሚ እንደሚያደርጋቸውም ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
መጋቢት 10/2017 ዓ.ም
"ብሩህ አዕምሮዎች፣በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው 4ኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር መካሄድ ጀመረ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በዘንድሮ አመት የሚካሄደው 4ኛው የክህሎት ውድድር ጋር ተያይዞ በተቋም ደረጃ የሚደረገውን ውድድር በዛሬው እለት አስጀምሯል::
በተቋም ደረጃ በዛሬው እለት በተካሄደው ውድድር በተለያዩ የሙያ ዘርፎች አሰልጣኞች መምህራን እና ሰልጣኝ ተማሪዎችን ያሳተፈ ውድድር ሲሆን በመጀመርያው ቀን የውድድሩ ውሎም....
በAuto mechanics
በAutomotive body repair & painting wor
በBuilding Electrical Installation
በIndustrial Electrical/Electronic control technology
በFinishing Construction work
በPlumping installation
በStructural construction work
በWood work technology....
የሙያ ዘርፎች ውድድሮች ተካሂደዋል::
ይህ በተቋም ደረጃ የተጀመረው ውድድር በቀጣይ ቀናትም በቀሩት የሙያ መስኮች የክህሎት ውድድሩ የሚደረግም ይሆናል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
መጋቢት 10/2017 ዓ.ም
ከመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ኢንጅነሪንግ ኮሌጅ የተወጣጣ ልዑካን ቡድን በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሌጅ የተሞክሮ ልምድ ልውውጥ አካሄደ::
ልዑካን ቡድኑ በኮሌጁ በነበራቸው ቆይታም አጠቃላይ የኮሌጁን እንቅስቃሴ እና ያለበትን ደረጃ በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ሰፊ ገለፃ የተደረገላቸው ሲሆን እንዲሁም በቀጣይ ሁለቱ ተቋማት በትብብር ሊሰሩ በሚችሉበት አግባብ ላይ የሁለትዮሽ ውይይት ተካሂዷል::
በነበረው የተሞክሮ ልምድ ልውውጥ ልዑካን ቡድኑ ከተደረገላቸው ገለፃ በተጨማሪ በቀጣይ በምን ዘርፍ በትብብር ለመስራት ያስችላል ሚለውን ለመለየት ኮሌጁ ያለውን ፋሲሊቲ እና ማሰልጠኛ ወርክሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን ኮሌጁ በዚህ መልኩ ራሱን በማራጀራጀቱም አድናቆታቸውን ለግሰዋል::
በቀጣይም ልዑካን ቡድኑ በኮሌጁ ባገኙት የተሞክሮ ልምድ ልውውጥ መሰረት ሁለቱ ተቋማት በተለያዩ ዘርፎች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያችላቸውን የጋራ መግባቢያ ስምምነት በመፈራረም ወደ ተግባር እንደሚገቡም ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
መጋቢት 7/2017 ዓ.ም
ወጣቶችን በኢኮኖሚው እንቅስቃሴ የሚፈጠሩ በርካታ እድሎችን ተጠቃሚ በማድረግ ስራ አጥነትን ለመቅረፍ በሚደረገው ርብርብ የወላጆች እና የአካባቢው ማህበረሰብ ሚና የላቀ መሆኑ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት በ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለሚገኙ የወላጅ ኮሚቴዎች እንዲሁም በየወረዳው ለተመረጡ የመንደር ኮሚቴዎች በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ፖሊሲን አስመልክቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ::
የግንዛቤ መስጫ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የስራና ክህሎት ቢሮ ም/ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ስተላፉት በመልዕክታቸው በተለምዶ ያደጉ እያልን የምጠራቸው ሀገራት ዛሬ ለደረሱበት እድገት መነሻ የሆናቸው በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ላይ ያሳደሩት እምነትና ዘርፉ ላይ በሰሩት ጠንካራ ስራ መሆኑን ጠቅሰው ወጣቱን በዚህ ረገድ ግንዛቤው ተፈጥሮለት የክህሎት ስልጠናዎች ላይ እንዲሰማራ እንዲሁም እንዱስትሪውን እንዲያንቀሳቅስ የማድረጉ ተግባርና ሀላፊነት ከወላጆች ጀምሮ የሁላችንም ድርሻ ነውም ብለዋል::
ወጣቶች አጠቃላይ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ጉልህ ሚና እንዲኖራቸው ለማስቻል እና እየተፈጠሩ ያሉ እጅግ በርካታ እድሎችን ተጠቃሚ ለመሆን የመጀመርያ መግቢያ በሩ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ እንደሆነ የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ አክለውም ወጣቶች ወደ ዘርፉን በሚፈለገው መጠን እንዳይቀላቀሉ ቴክንክና ሙያ ላይ በተለምዶ ያልተገባ ስም ተልጥፏል ያሉ ሲሆን እንደ ኮሌጅ ይህንን አመለካከት ለመቅረፍ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ እንዳሉ ገልፀው ወላጆችን ጨምሮ ህብረተሰቡ ውስጥ ተሰሚነት ያላችሁ ሰዎች በተገኘው አጋጣሚ ለወጣቶች ግንዛቤ የመፍጠሩን ስራ ላይ መረባረብ ያስፈልጋልም ብለዋል::
በመድረኩ የተሻሻለውን የቴክኒክና ሙያ ፖሊሲ ሰነድ ለተሳታፊዎች ያቀረቡት የኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ም/ዲን አቶ ኤሊያስ አህመድ ሲሆኑ ባቀረቡት ሰነድም የቴክኒክና ሙያ እስፈላጊነት ጨምሮ ነባሩ ፖሊሲ ላይ የታዩ ክፍተቶች እንዲሁም የፖሊሲውን መሻሻል አስፈላጊነትን በዝርዝር ለመድረኩ ተሳቲፊዎች አቅርበዋል::
የEASE ፕሮጀክት ከአለም ባንክ ጋር የ5 አመት ፕሮጀክት እንዳለው የገለፁት ደግሞ የEASE ፕሮጀክት ዋና ኮርድኔተር ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ አያይዘውም ኮሌጁ መሰል ፕሮጀክቶችን በማፈላለግ አስፈላጊ የሚባለውን ሁሉ የሚያሟላው በከተማችን ያሉ ወጣቶችን አሰልጥኖ ከስራ ጋር ለማስተሳሰር እንደሆነም ጠቅሰው ወጣቶችን ወደዚህ እንዲመጡ ማበረታታት ያስፈልጋልም ብለዋል::
በመጨረሻም ከመድረኩ የተነሱ ጉዳዮችን መነሻ በማድረግ በተሳታፊዎች በርካታ ሀሳቦች ላይ ውይይት የተካሄደ ሲሆን በቀጣይ በቅንጅት በሚሰሩ ተግባራት ላይ ከመግባባት በመድረስ መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
መጋቢት 5/2017 ዓ.ም
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ4ኛ ጊዜ ለሚካሄደው የክህሎት ውድድር ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታወቀ፡፡
ኮሌጁ በ2017 ዓ.ም "ብሩህ አዕምሮዎች ፣በክህሎት የበቁ ዜጎች!" በሚል መሪ ሀሳብ ለሚካሄደው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች አጠናቆ ከመጋቢት 9 2017 ዓ.ም ጀምሮ ውድድሩ እንደሚካሄድ የገለፁት የኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ ውድድሩ ላይ የሚሳተፉ ተወዳዳሪዎችን ከመለየት አንስቶ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች በሟሟላት የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መከናወናቸውንም ገልፀዋል::
በዘንድሮ ውድድር ኮሌጁን እንዲሁም ከተማ አስተዳደሩን በሀገር አቀፍ ውድድር ላይ የሚወክሉ አሰልጣኞች፣ሰልጣኞች እንዲሁም ኢንተርፕራይዞችን አወዳድሮ ለመለየት በኮሌጅ ደረጃ ከመጋቢት 9 ጀምሮ የሚደረግ ሲሆን ውድድሩም በ7 የሙያ ዘርፎች ተወዳዳሪዎችን እንደሚያሳትፍ ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
መጋቢት 4/2017 ዓ.ም
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ የሚሰራውን ግንዛቤ የመፍጠር ስራ በማጠናከር በማርያም ሰፈር እና በመድሀንያለም አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ላይ ለሚገኙ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ዘርፉን አስመልክቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ::
በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይ ተማሪዎች ስለ ዘርፉ ተገቢውን ግንዛቤ እንዲኖራቸው ከማደረግ አኳያና እንደ ሀገር ከተያዘው የትኩረት አቅጣጫም አንፃር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ለወጣቱ በተለይም ከዚህ በኃላ ወደዘርፉ ለሚቀላቀሉ የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ብዙ መልካም እድሎችን የያዘ ዘርፍ መሆኑን በዝርዝር ማብራሪያ በመስጠት ሰፋ ያለ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ መስራት ተችሏል::
የግንዛቤ ማስጨበጫውን ለተማሪዎች የሰጡት የኮሌጁ ዲኖች እንዲሁም የዲፓርትመንት ተጠሪዎች ሲሆኑ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ወደ ቴክኒክና ሙያ ተቋም ከመቀላቀላቸው አስቀድሞ ከወዲሁ በአስተሳሰብም ሆነ ለዘርፉ ባላቸው አረዳድ ዝግጁ እንዲሆኑ የሚያደርጋቸውን ምክረ ሀሳብና በኮሌጁ ያለውን ተሞክሮ ለተማሪዎች አካፍለዋል::
በቀጣይም የፈጠራ አቅም ያላቸውን ተማሪዎች የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክህሎቶቻቸውን እንዲያዳብሩ የሚረዳቸውን የቴክኒክና ሙያ (STEM) ክበብ በየትምህርት ቤቶቹ በመቋቋም ላይ እንደሚገኙ የተገለፀ ሲሆን ይህም የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ቀደም ብለው ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ጋር ትስስር እንዲፈጥሩና በሲስተም ውስጥ እንዲያልፉ እድል እንደሚፈጥርላቸውም ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
መጋቢት 4/2017 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
