ch
Feedback
Mentesnot Kebede

Mentesnot Kebede

前往频道在 Telegram

~To reach people with Gospel 📖 ~To edify the believes ~I serve in Mercy in Christ Church ⛪ ~mob.0911693190📞

显示更多
685
订阅者
+124 小时
+37 天
+1430 天

数据加载中...

标签云
无数据
有任何问题?请刷新页面或联系我们的客服
进出提及
---
---
---
---
---
---
吸引订阅者
九月 '26
九月 '26
+5
在0个频道中
八月 '26
+27
在0个频道中
Get PRO
七月 '26
+16
在0个频道中
Get PRO
六月 '26
+23
在0个频道中
Get PRO
五月 '26
+9
在0个频道中
Get PRO
四月 '26
+14
在0个频道中
Get PRO
三月 '26
+11
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+11
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+16
在0个频道中
Get PRO
十二月 '25
+16
在0个频道中
Get PRO
十一月 '25
+11
在0个频道中
Get PRO
十月 '25
+19
在0个频道中
Get PRO
九月 '25
+13
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+11
在0个频道中
Get PRO
七月 '25
+13
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+26
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+36
在1个频道中
Get PRO
四月 '25
+23
在0个频道中
Get PRO
三月 '25
+28
在0个频道中
Get PRO
二月 '25
+22
在0个频道中
Get PRO
一月 '25
+41
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+23
在0个频道中
Get PRO
十一月 '24
+21
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+39
在1个频道中
Get PRO
九月 '24
+44
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+26
在0个频道中
Get PRO
七月 '24
+24
在0个频道中
Get PRO
六月 '24
+15
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+15
在0个频道中
Get PRO
四月 '24
+20
在0个频道中
Get PRO
三月 '24
+9
在1个频道中
Get PRO
二月 '24
+31
在0个频道中
Get PRO
一月 '24
+36
在1个频道中
Get PRO
十二月 '23
+31
在0个频道中
Get PRO
十一月 '23
+15
在0个频道中
Get PRO
十月 '23
+20
在0个频道中
Get PRO
九月 '23
+37
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+24
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+23
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+20
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+12
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+17
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+23
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+13
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+22
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+12
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+20
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+211
在0个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
08 九月0
07 九月+1
06 九月+1
05 九月+1
04 九月+1
03 九月+1
02 九月0
01 九月0
频道帖子
ማክሰኞ 03/13/18 የማቴዎስ ወንጌል መልዕክት (ክፍል 59) እናንተው የሚበሉትን ስጡአቸው ማቴ14:13-21 የመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ወደ ጌታ መጥተው የዮሐንስን መሠዋት ሲነግሩት ከነበረበት ስፍራ ወደ ምድረ በዳ ፈቀቅ አለ፡፡ ምክንያቱም ሄሮድስ በኢየሱስ እየተፈጸመ ያለውን ተዓምራት ሰምቶ ይህ መጥምቁ ዮሐንስ ነው፤ እርሱ ከሙታን ተነሥቶአል፥ ስለዚህም ኃይል በእርሱ ይደረጋል በማለት ስጋት ላይ በመሆኑ ለጥንቃቄ ራሱን መሰወሩ ነው፡፡ ሰይጣን በምድራዊ ነገሥታት በኩል ስለሚሰራ አስፈላጊው ነገር ጥንቃቄ ነው፡፡ ብዙ ሰዎች ያለ እግዚአብሔር ፈቃድ አንዳች አይሆንም ይላሉ ነገር ግን በምድር ላይ ብዙ አመጾች እየሆኑ ያሉት እኮ ያለ እግዚአብሔር ፈቃድ መሆኑን አያስተውሉም፡፡ ደግሞም የሰይጣን ዋንኛ ዓላማ የእግዚአብሔርን ፈቃድ በምድር ላይ ማስተጓጎል ነው፡፡ ስለዚህ ነው ጥንቃቄ ያስፈለገው ጠቢቡ ሲናገር “ጥንቃቄ ይጠብቅሃል፥ ማስተዋልም ይጋርድሃል” ምሳ2፡11 አለ፡፡ ህዝቡ ጌታ ፈቀቅ ማለቱን ሲያውቁ በእግር ተከተሉት፣ ከእርሱ ጋር ብዙ ሰዓታት ቆይተዋልና ኢየሱስ ያደረገላቸውን ተአምራትና ለደቀ መዛሙርቱ በቀጣይ አገልግሎታቸው ትልቅ ትምህርት የሚሆን እውቀት የሰጠበትን ይህን ክፍል እንመለከታለን፡- 1. ርህራሄው "ወጥቶም ብዙ ሕዝብ አየና አዘነላቸው ድውዮቻቸውንም ፈወሰ" ማቴ14:14 አገልግሎት የሚጀምረው ለምናገለግለው ግለሰብ ይሁን ህዝብ ሸክምና የልብ ርህራሄ ሲኖረን ነው፡፡ ጸጋም በሙላት መለቀቅ የሚጀምረው በዚህ ዓይነት መንፈስ መንቀሳቀስ ስንችል ነው፡፡ እናት ልጅ ስትወልድ ልጁን በህይወት የሚያስቀጥል ወተት ታግታለች፣ ይህ ተፈጥሮአዊ ክስተት ነው፡፡ ጳውሎስ ሲናገር “ስለዚህም አሕዛብ ስለ ሆናችሁ ስለ እናንተ የክርስቶስ ኢየሱስ እስር የሆንሁ እኔ ጳውሎስ ለእግዚአብሔር እንበረከካለሁ። ለእናንተ ስለ ተሰጠኝ ስለ እግዚአብሔር ጸጋ መጋቢነት በእርግጥ ሰምታችኋል” ኤፌ3፡1,2 ጳውሎስ ለአህዛብ ጥሪና በእግዚአብሔር ፊት የሚያበረክከው ሸክም ብቻ ሳይሆን የነበረው፣ ህዝቡን የሚያገለግልበት የመጋቢነት ጸጋም ተሰጥቶታል፡፡ ኢየሱስም ህዝቡን አይቶ አዘነላቸውና ድውያቸውን ፈወሰ፡፡ ስለ ፈውስ መወዛገብና መንታ ልብ ሊኖረን አይገባም፣ እንደህ ዓይነት አቋም እምነትን ሽባ ያደርገዋል ያዕ1፡7,8፡፡ ጌታ ራሱ ፈውስ የልጆች እንጀራ ነው ብሎአል ማቴ15፡26 ጌታ በሚያደርገው ነገር ሁሉ አንድም እንዲ አንድም እንዲያ የሚባል ነገር የለውም “ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ለዘላለምም ያው ነው” ዕብ13፡8 በሰንበት ሰዎች ያርፉ ዘንድ ሰንበትን የሰጠ ጌታ በሰንበት ሰዎችን ይፈውስ የነበረው ሰዎች እረፍታቸው ሙሉ ይሆን ዘንድ ፈቃዱ በመሆኑ ነው፡፡ ፈወሳቸው የሚል ቃል እያነበብን በሽታ የለም የሚል አቋም ሊኖረን አይችልም፡፡ ፈውስ ግን ፈቃዱ ነው፡፡ ዛሬም ህዝብን በዚህ አገልግሎት መጥቀም፣ ጸጋን ማካፈል የምንችለው እንዲህ ዓይነት አቋም ሲኖረን ብቻ ነው፡፡ 2. የሰው ምክንያት "በመሸም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ወደ እርሱ ቀርበው፡— “ቦታው ምድረ በዳ ነው አሁንም ሰዓቱ አልፎአል፤ ወደ መንደሮች ሄደው ለራሳቸው ምግብ እንዲገዙ ሕዝቡን አሰናብት፡” አሉት" ማቴ14:15 ስጋዊና መንፈሳዊ አስተሳሰብ ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል እንዲሁ የተራራቁ ናቸው ኢሳ55፡9፡፡ ስጋዊ አስተሳሰብ በውጫዊ አምስቱ የስሜት ህዋሳት መረጃዎች ላይ ጥገኛ በመሆኑ ከዚህ ሌላ መንገድ አይታየውም፡፡ ደቀ መዛሙርትም ጊዜው መምሸቱን፣ ስፍራው ምንም የማይገኝበት ምድረ በዳ መሆኑን፣ ህዝቡም መራቡን አስተውለዋል፣ ከዚህም ግንዛቤ በመነሳት በቀጣይ ጌታ ህዝቡን እንዲያሰናብት ምክራቸውን ለገሱ፡፡ ደቀ መዛሙርት በመንፈስ ዓለም ሌላ ዳይሜንሽን መኖሩን ገና አልተረዱም፡፡ ስለዚህ ነው ጠቢቡ “በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ” ምሳ3፡5 ያለው፡፡ በስጋ ብቻ ስንመላለስ እግዚአብሔርን ደስ አናሰኝም ሮሜ8፡7-8 ነገር ግን ደቀ መዛሙርት በፍጻሜው አገልግሎታቸው በዚህ መረዳት አልቀሩም ጴጥሮስን እንኳን ለሽባው ሰው ፈውስ “ያለኝን እሰጥሃለሁ” በማለት ተነስቶ እንዲራመድ አዘዘው፡፡ መንፈሳዊውን እውነታና ከእርሱም የተሰጠንን ስንረዳ ለሌሎች የምንሰጠው በውጫዊ አስተሳሰብ ያልተገደብን እንሆናለን፡፡ 3. መለኮታዊ አቅርቦት "ኢየሱስም፡— “እናንተ የሚበሉትን ስጡአቸው እንጂ ሊሄዱ አያስፈልግም” አላቸው" ማቴ14:16 ጌታ ያመጡትን መረጃ ሰምቶ መልካም ነው አላለም ነገር ግን፣ እናንተው ራሳችሁ ስጡአቸው እንጂ መሄድ አያስፈልጋቸውም በማለት ሴቶችና ህጻናት ሳይቆጠሩ ለአምስት ሺህ ወንዶች ይህን ማለቱ የሚያስገርማቸው ጉዳይ ነው፡፡ ይሁን እንጂ እኔ እመግባቸዋለሁ ብሎአቸው ቢሆን በደስታ በፈነደቁ ነበር ነገር ግን እናተው ስጠአቸው ማለቱ ግራ ገብቶአቸው ከአንድ ህጻን ልጅ የተቀበሉትን ጥቂት ነገር ይዘው መጡ “ከአምስት እንጀራና ከሁለት ዓሣ በቀር በዚህ የለንም አሉት” “የለንም” የሚለው ቃል በኋላ “ያለኝን እሰጥሃለሁ” በሚለው ቢተካም አሁን ግን ከስጋዊ መረጃ ውጪ ሌላ እይታ የላቸውም፡፡ ስጋዊ እይታ ውስን ሲሆን መለኮታዊ እይታ ግን እጅግ ሰፊ ነው፡፡ በዚህም ጌታ የመለኮታዊ አቅርቦት ምስጥርን ገለጠላቸው፡፡ በመጀመሪያ እነዚያን አምጡልኝ አለ፣ በእርግጥ ይህ በቂ ሆኖ ሳይሆን ዘር ስለሆነ ነው፡፡ ሁለተኛ የሚመጣውን አቅርቦት በሚገባ ለማስተዳደር እንዲቻል ህዝቡን በስርዓት በማስቀመጥ የማኔጅመንት ስራ እንዲሰሩ አደረገ በሶስተኛ ደረጃ ያመጡትን ይዞ በረከትን በሚሰጥ አምላክ ፊት አመሰገነ፣ በመጨረሻም ከጌታ የተቀበሉትን ለህዝቡ በታማኝነት ሰጡ፡፡ ሁሉም በልተው ጠገቡ አተረፉም፡፡ ጸጋ ይብዛላችሁ Telegram:- @mentesnotkebede2020 👍 Join በማድረግ እየተቀላቀሉን ሌሎችም እንዲሳተፉ ሼር በማድረግ ይሳተፉ Email:- mentesnot_kebede@yahoo.com ስልክ:- 0911693190

2
没有文字...
239
3
ዓርብ 29/12/18 የማቴዎስ ወንጌል መልዕክት (ክፍል 58) ስውሩ የጠላት እጅ ማቴ14፡1-12 ይህ ስለ ክርስቶስ ዝና የሰማው ሄሮድስ አንቲጳስ ሲሆን የአራተኛው ክፍል ገዢ ተብሎ ይጠራ ነበር ምክንያቱም ታላቁ ሄሮድስ ሥልጣኑን ለአራት ልጆቹ አከፋፍሎት ስለ ነበረ ነው፡፡ ይህ ቤተሰብ እጅግ ክፉና በነፍሰ ገዳይነት መንፈስ የተያዙ፣ ሥልጣናቸውን አላግባብ የሚጠቀሙ ሰዎች ነበሩ፡፡ ማርቆስና ሉቃስ እንደተረኩት ማር6፡14-29፣ ሉቃ9፡7-9 ጌታ ኢየሱስ አስራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርቱን በገሊላ ከተሞች እንዲያገለግሉ በላካቸው ጊዜ ያደርጉአቸው በነበሩ ተአምራቶች የጌታን ዝና ከፍ አድርጎት ነበር፡፡ ስለዚህ የሰሙት ነገር ያስደነገጣቸው እነዚህ ሰዎች ስራቸው ክፉ ነበርና መጥምቁ ዮሐንስ ከሙታን ተነስቶአል፣ በእርሱ መንፈስ ነው ተአምራት እየተደረገ ያለው በማለት እረፍት በሌለው ህሊናቸው ይቃዡ ነበር፡፡ ማቴዎስ ይህንን ተከትሎ ስልጣንን ተገን አድርጎ በስውር ቅዱሳንን ስለሚሰዋው የጠላት እጅ በመተረክ ሄሮድስ እንዴት መጥምቁ ዮሐንስን እንዳስገደለው ይናገራል፡፡ በዚህ ክፍል ይህ መንፈስ እንዴት እንደሚሰራ እንመለከታለን፡- 1. ኩነኔ “ሄሮድስ በወንድሙ በፊልጶስ ሚስት በሄሮድያዳ ምክንያት ዮሐንስን አስይዞ አሳስሮት በወህኒ አኑሮት ነበርና፤ ዮሐንስ፦ እርስዋ ለአንተ ትሆን ዘንድ አልተፈቀደም ይለው ነበርና” ማቴ14፡3,4 ዮሐንስ ጠንካራ በሆኑ መልዕክቶቹ ይታወቃል ማቴ3፡7፣ የተገለጠውም በኤልያስ መንፈስ ነው ሉቃ1፡17፡፡ እርሱ የመጨረሻው የብሉይ ኪዳን ነብይ በመሆኑ የፍርድ መልዕክቶችን ይናገር ነበር፡፡ ሄሮድስን የወንድሙን ሚስት አግቦቶ ስለ ነበር ያ በህጉ የተከለከለ በመሆኑ ዘሌ20፡21 በመልዕክቱ ክፉኛ ኮንኖታል፡፡ ሄሮድስም ሆነ ሚስቱ ሄሮድያዳ በመልዕክቱ ከመመለስ፣ ንስሐ ከመግባት ይልቅ ለቁጣ፣ ለጥፋት ልባቸውን አነሳሳው፡፡ ኩነኔ ከእግዚአብሔር የሚመልስ፣ የሚያርቅ እንጂ ወደ እርሱ የሚያስጠጋ አይደለም፡፡ ኩነኔ ሰዎችን ለአመጽ ያነሳሳል፡፡ ይህም አገልግሎት መጥምቁ ዮሐንስን በእስር ቤት እንዲማቅቅ አድርጎታል፡፡ አዲስ ኪዳን ከብሉይ ኪዳን አገልግሎት የሚለየውም በዚህ ነው ሮሜ8፡1፡፡ በአዲስ ኪዳን ብናስተምር፣ ብንሰብክ፣ ትንቢትን ብንናገር፣ ብንዘምር ወይም በየትኛውም አቅጣጫ ብንናገር ቃላችን ለሰዎች ጸጋን የሚሰጥ እንዲሆን ታዘናል ኤፌ4፡29 ይህ ማለት ትክክል ያልሆነውን ትክክል አይደለም አንበል፣ እውነትን እንሸፋፍን ማለት አይደለም ነገር ግን መልዕክታችን በፍርድ መንፈስ ሳይሆን እውነትን በፍቅር ሊሆን ይገባል ነው ኤፌ4፡15 ሰዎች ከክፉ ስራቸው በእግዚአብሔር ጸጋ እንዲመለሱ እንረዳለን፡፡ የቀደመው ኪዳን ግን አግልግሎቱ የኩነኔ ነው 2ቆሮ3፡9 ጸጋ የመጣው ሰውን ከኩነኔ አውጥቶ በኃጢአት ላይ እንዲሰለጥኑና ከኃጢአት እንዲርቁ ጉልበት ለመስጠት ነው ቲቶ2፡11፣ ሮሜ6፡14፡፡ 2. በቀል “ነገር ግን ሄሮድስ የተወለደበት ቀን በሆነ ጊዜ፥ የሄሮድያዳ ልጅ በመካከላቸው ዘፈነች ሄሮድስንም ደስ አሰኘችው፤ ስለዚህም የምትለምነውን ሁሉ እንዲሰጣት በመሐላ ተስፋ አደረገላት። እርስዋም በእናትዋ ተመክራ፦ የመጥምቁን የዮሐንስን ራስ በዚህ በወጭት ስጠኝ አለችው” ማቴ14፡6-8 ሄሮድስ ስለ መጥምቁ ዮሐንስ ህዝቡን ስለ ፈራ በወህኒ አስሮ አስቀምጦታል፡፡ ነገር ግን ሚስቱ ሄሮዳያዳ ውስጥዋ በበቀል መንፈስ ተሞልቶ ስለ ነበር በሄሮድስ የልደት ቀን ልጅዋ በፊቱ እንድትደንስ አደረገች ምክንያቱም በውስጥዋ ያደረው የበቀል መንፈስ ስውር አጀንዳውን ሊፈጽም፣ የዮሐንስን አንገት ሊቀላ አድብቶአልና ነው፡፡ ኩነኔ ወደ በቀል ይመራልና እውነትን ተናግረን የሚቃወመን ሰው ካለ ጊዜ ጠብቆ ሊበቀለን ያደባል ነገር ግን እውነት ሁልጊዜ ዋጋ ማስከፈልዋ ግድ መሆኑ እያወቅን፣ ልባችንን በፍቅር እየጠበቅን መንገዳችንን ለጌታ አደራ መስጠት ያስፈልጋል፡፡ ሙዚቃው እየተደለቀ፣ ዘፈኑ እየቀለጠ፣ የደስታ በዓሉ እየደመቀ፣ ሳቁ እየደራ፣ ምግቡ እየተበላ፣ መጠጡ እየተጠጣ ከጀርባው ግን የአንድን ጻድቅ ሰው ህይወት ሊቀጥፍ ራሱን ሸፍኖአል፡፡ ዓለም ይህ ነው፡፡ ሄሮድስ ደስ ስላሰኘችው የምትለምነውን ሁሉ ሊሰጣት መሐላ ገባ፡፡ ያ መንፈስ ግን ከቅዱሳን ደም በቀር ሌላ ስጦታ አይፈልግምና የዮሐንስን አንገት እንዲሰጣት በእናትዋ ተመክራ ያንን ጠየቀች፡፡ ምንግዜም ክርስቲያን ዋጋ ሊከፍል የሚገባው ስለ እውነት እንጂ በሌላ ጉዳይ ሊሆን አይገባም፡፡ ጴጥሮስ ሲናገር “ከእናንተ ማንም ነፍሰ ገዳይ ወይም ሌባ ወይም ክፉ አድራጊ እንደሚሆን ወይም በሌሎች ጒዳይ እንደሚገባ ሆኖ መከራን አይቀበል፤ ክርስቲያን እንደሚሆን ግን መከራን ቢቀበል ስለዚህ ስም እግዚአብሔርን ያመስግን እንጂ አይፈር” 1ጴጥ4፡15,16 3. ኩራት “ንጉሡም አዘነ፥ ነገር ግን ስለ መሐላው ከእርሱም ጋር ተቀምጠው ስላሉት ሰዎች እንዲሰጡአት አዘዘ፤ ልኮም የዮሐንስን ራስ በወህኒ አስቆረጠው። ራሱንም በወጭት አምጥተው ለብላቴናይቱ ሰጡአት፥ ወደ እናትዋም ወሰደችው” ማቴ14፡9-11 “መጨረሻቸው ጥፋት ነው፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው፥ ክብራቸው በነውራቸው ነው፥ አሳባቸው ምድራዊ ነው” ፊል3፡19 እንደሚል አመጽን ማስቆም ሲቻል ሰው ግብዝ ሲሆንና ስለ ክብሩ በኩራት ከተያዘ የሰይጣን አጀንዳ መፈጸሚያ መሆኑ ግድ ነው፡፡ ይህ ሰው የጻድቁን ሰው አንገት ስትጠይቀው አይሆንም ማለት አልቻለም ነገር ግን ስለ ማሐላው ተገበዘ፣ በዙሪያው ስለተቀመጡት ሰዎች ፈቀደላት፡፡ በዙሪያው ያሉ ሁሉ ይህ ሲጠየቅና አንገት ተቆርጦ በወጪት ሲቀርብ እያዩ ምናልባት ደስታቸውን በፉጨት፣ በሳቅ፣ ጽዋውን በማንሳት እየገለጡ ናቸው፡፡ ዓለም ሰውን እስረኛ የምታደርገው በጥቅም ነው፡፡ ለጥቅምዋ ነፍሱን ያነሳ፣ በአመጻዋ አለማጨብጨብ ፈጽሞ አይችልም፡፡ ስለዚህ ክፉ ምክር ባለበት የምናገኘውን ደስታ፣ ጥቅም፣ በዚያ ያለውን ህብረት ካልተጸየፍን እኛም ነፍሰ ገዳዮች መሆናችንን ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ ጸጋ ይብዛላችሁ Telegram:- @mentesnotkebede2020 👍 Join በማድረግ እየተቀላቀሉን ሌሎችም እንዲሳተፉ ሼር በማድረግ ይሳተፉ Email:- mentesnot_kebede@yahoo.com ስልክ:- 0911693190
151
4
"ወደ ቀኝም ሆነ ወደ ግራ ዘወር ብትል ጆሮህ ከኋላህ፣ “መንገዱ ይህ ነው፤ በእርሱ ሂድ” የሚል ድምፅ ይሰማል" ኢሳ30:21
117
5
ረብዕ 27/12/18 የማቴዎስ ወንጌል መልዕክት (ክፍል 57) ይህንን ጥበብ ከወዴት አገኘው ማቴ13:53-58 ጌታ ኢየሱስ መንግሥተ ሰማይ በምድር ምን እንደምትመስል በብዙ ምሳሌዎች ሲያስተምር ቆይቶ አሁን ደግሞ ወደ ገዛ አገሩ ወደ ናዝሬት ሄደ፡፡ ጸሐፊው ስለ ጉዞው የሚነግረን ጌታ ትምህርቶቹ ብቻ ሳይሆኑ እያንዳንዱ እንቅስቃሴው በሙሉ በመለኮታዊ ፈቃድና እቅድ መሆኑን ነው፡፡ ነገር ግን ለምን በዚህ ጊዜ ወደ ገዛ አገሩ ወደ ናዝሬት ለመሄድ አሰበ ብለን ብንጠይቅ ምንዓልባት በማቴ13፡12፡46,47 ላይ እናቱ ወንድሞቹ ሊፈልጉት መጥተው ስለ ነበር በእናቱ እንዲመጣ ተነግሮት ሊሆን እንደሚችል ማሰብ እንችላለን ምክንያቱም የአሁን ጉዞው እነርሱ ከፈለጉት በኋላ የተከናወነ በመሆኑ ነው፡፡ ወደ ቤት ገብቶ ቤተሰቡን ካገኘ በኋላ ወዲያው ወደ ዋንኛው ተልዕኮው ወደ ማስተማሩ ተመለሰ፡፡ እነዚህ ሰዎች ትልቅ እድል አግኝተዋል ነገር ግን ኢየሱስን የተመለከቱበት መንገድ የተሳሳተ በመሆኑ “ነቢይ ከገዛ አገሩና ከገዛ ቤቱ በቀር ሳይከበር አይቀርም” የተባለው የነቢያት ቃል ተፈጸመባቸው ስለዚህም የእድሉ ተጠቃሚ ሊሆኑ አልቻሉም፡፡ በዚህ ክፍል የምንመለከተው ይህን እውነት ነው፡- 1. ቃሉን አለመቀበል "ወደ ገዛ አገሩም መጥቶ እስኪገረሙ ድረስ በምኩራባቸው ያስተምራቸው ነበር፤ እንዲህም አሉ፡— “ይህን ጥበብና ተአምራት ይህ ከወዴት አገኘው?" ማቴ13:54 ጌታ ወደ ሙክራባቸው ገብቶ ያስተምር ነበር የሚሰሙትም ሁሉ በትምህርቶቹ ይገረሙ ነበር ምክንያቱም ከመምህሮቻቸው አንዳቸውም እንደዚህ የሚያስተምር ስለሌለ ነው፡፡ ማቴዎስ አስቀድሞ “ኢየሱስም ይህን ነገር በጨረሰ ጊዜ ሕዝቡ በትምህርቱ ተገረሙ፤ እንደ ጻፎቻቸው ሳይሆን እንደ ባለ ሥልጣን ያስተምራቸው ነበርና” ማቴ7፡28,29 እነዚህ ሰዎች አንዱን ከሌላው እያወዳደሩ በመሆናቸው ቃሉን ልባቸውን ከፍተው አልተቀበሉትም፡፡ ሰው ቃሉን እየሰማ ከቃሉ ጋር ላይዛመድ፣ እየተደነቀም ገንዘቡ ሊያደርገው ላይችል ሁሉ ይችላል፡፡ በምንም ምክንያት ይሁን ሰው ቃሉን የሚቀበል ልብ ካጣ በዘሪው ምሳሌ ላይ እንዳየነው ፍሬአማ ሊሆን አይችልም፡፡ ቃሉን ከልብ አለመስማትና አለመቀበል የሚያመጣውን አደጋ የዕብራውያን ጸሐፊ ሲናገረው “ለእነዚያ ደግሞ እንደ ተነገረ ለእኛ የምስራች ተሰብኮልናልና፤ ዳሩ ግን የሰሙት ቃል ከሰሚዎቹ ጋር በእምነት ስላልተዋሐደ አልጠቀማቸውም” ዕብ4፡2 ጌታን በስጋ ማንነቱ ብቻ መመልከታቸውና ሰባኪን ከሰባኪ ጋር እያወደዳደሩ ልባቸውን ማደንደናቸው የከበረውንና ህይወት ሰጪውን ቃል ሳይጠቀሙበት ቀረ፡፡ 2. አሳንሶ መመልከት "ይህ የጸራቢ ልጅ አይደለምን? እናቱስ ማርያም ትባል የለምን? ወንድሞቹስ ያዕቆብና ዮሳ ስምዖንም ይሁዳም አይደሉምን? እኅቶቹስ ሁሉ በእኛ ዘንድ ያሉ አይደሉምን? እንኪያስ ይህን ሁሉ ከወዴት አገኘው?” ተሰናከሉበትም" ማቴ13:55,56 ይህ የተከናወነው በገዛ አገሩ በመሆኑ በስጋ ከሚያውቁት ነገር ውጪ ነገሮችን ሊያስተውሉ አልቻሉም፡፡ በስጋ ከፍ ብሎ መገኘትን ትልቅ ዋጋ በሚሰጥ ማህበረሰብ መካከል ተራ ከሆኑ ሰዎች ህይወት የላቀ መንፈሳዊ ነገር መጠበቅ አይቻለውም፡፡ የሰው መንፈሳዊ አቋምና ልክነቱ በስጋዊ ሁኔታው ፈጽሞ ሊለካ አይቻልም፡፡ መቼም በገዛ ቤቱ ጀግና ሆኖ የሚያውቅ ሰው ማግኘት ይቸግራልና ጌታም በዚያ ስጋዊ እድገቱ በሚታወቅበት፣ እንደ ማንኛውም ሰው ሲወጣና ሲገባ በኖረበት ከተማ በእውነተኛ ማንነቱ ልክ ሊያዩት የቻሉ ሰዎችን ማግኘነት የቸገረ ሆኖ ተገኘ፡፡ ይህ ተራው ሰው ብቻ የሚሳሳትበት ሳይሆን ታላቁን ነብይ ሳሙኤልንም የፈተነ አረዳድ ነበር ኤልያብን በቁመቱ ዘለግታና በትከሻው ስፋት እግዚአብሔር የሚቀባው ይህ ነው ሲል “እግዚአብሔር ግን ሳሙኤልን፦ ፊቱን የቁመቱንም ዘለግታ አትይ፤ ሰው እንዲያይ እግዚአብሔር አያይምና ናቅሁት፤ ሰው ፊትን ያያል፥ እግዚአብሔር ግን ልብን ያያል አለው” 1ሳሚ16፡7 በዚያ የተከናወነው፣ ዛሬም በዘመናችን በቤተክርስቲያንም ውስጥ ይኸው እውነት እየሰራ የምናየው ሃቅ ነው፡- ጌታ ስጋዊ ማንነቱና ቤተሰቡ በብዙ ትህትና ማንነቱን አዋርዶ የተገኘበት ማንነቱ ሲሆን እርሱ ግን አምላክ ነው ነገር ግን ከገዛ ወንድሞቹና ወገኖቹ ግን ይህንን ሊረዳ የቻለ የለም ፊል2፡፡6-8፡፡ 3. በአለማመን መጠቃት "ኢየሱስ ግን፡— “ነቢይ ከገዛ አገሩና ከገዛ ቤቱ በቀር ሳይከበር አይቀርም፡” አላቸው። በአለማመናቸውም ምክንያት በዚያ ብዙ ተአምራት አላደረገም" ማቴ13:57,58 አገልጋይ ምንም ያህል ጸጋ ይኑረው እርሱን የምንመለከተው እንደ አንድ ተራ ሰው አድርገን ከሆነ ለብዙዎች መፍትሄ የሆነው ቃሉ ለእነርሱ ግን አንዳች የሚረባ ነገር አይፈይድም፡፡ ማርቆስ ሲናገር “በዚያም በጥቂቶች ድውዮች ላይ እጁን ጭኖ ከመፈወስ በቀር፥ ተአምር ሊያደርግ ምንም አልቻለም። ስለ አለማመናቸውም ተደነቀ …” ማር6፡5,6 በመንፈሳዊው ዓለም አለማመን እጅግ አደገኛ ነገር ነው ምክንያቱም ያለ እምነት ከመንፈሳዊው ዓለም ጋር መገናኘት አይቻልም፡፡ ጌታን እንደ አንድ ተራ ሰው መቁጠራቸው ልባቸውን አደነደነ፣ የልባቸው መደንደን ደግሞ አለማመንን አመጣ፣ አለማመን ደግሞ እጁን ጭኖ ቢጸልይላቸው እንኳ ስንቶችን ሽባዎች፣ አንካሶች፣ እውራን ሲፈውስ ሙታንን ሲቀሰቅስ የነበረ ጌታ በእነርሱ ዘንድ ግን ይህ ሊከውን አልቻለም፡፡ አለማመን የልብ ችግር ሲሆን ከመንፈሳዊ ነገር ይልቅ ለዚህ ዓለምና ለስጋዊ ነገሮች ትልቅ ዋጋ በመስጠት የሚከሰት ነው፡፡ የዚህ ችግር ሰለባ የሚሆኑ ሰዎች የማያምኑ ብቻ ሳይሆን አማኝ ነን በሚሉ ሁሉ የሚከሰት ችግር ነው፡፡ ጸጋ ይብዛላችሁ Telegram:- @mentesnotkebede2020 👍 Join በማድረግ እየተቀላቀሉን ሌሎችም እንዲሳተፉ ሼር በማድረግ ይሳተፉ Email:- mentesnot_kebede@yahoo.com ስልክ:- 0911693190
465
6
ማክሰኞ 26/12/18 የማቴዎስ ወንጌል መልዕክት (ክፍል 56) የመንግሥተ ሰማይ የምድር መልክ/02/ ማቴ13:45-52 4. እንቁ የሚሻ ነጋዴ "ደግሞ መንግሥተ ሰማያት መልካምን ዕንቁ የሚሻ ነጋዴን ትመስላለች፤ ዋጋዋም እጅግ የበዛ አንዲት ዕንቁ በአገኘ ጊዜ ሄዶ ያለውን ሁሉ ሸጠና ገዛት" ማቴ13:45,46 ይህ ምሳሌ ከላይ በእርሻ ውስጥ የተሰወረ መዝገብ አይቶ ከደስታው የተነሳ ያለውን ሽጦ እርሻውን ከገዛው ሰው ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ በዚህም እግዚአብሔር ከሁሉ አስቀድሞ ምንም እንኳን የሰው ልጅ በኃጢአት ቢወድቅም በሰው ልጆች መካከል ለእርሱ እንደ እንቁ የሆኑ ሰዎችን ስላየ አለኝ የሚለውን፣ እንደ እንቁ የሆነውን አንድያ ልጁን /ራሱን/ በመስጠት ያንን የተሰወረ እንቁ ገዛው፡፡ እኛ ምንም እንኳ የማይገባን ብንሆንም በፊቱ የታየነው እንደ ከበረ እንቁ ነው፡፡ ስለዚህ ነው ጳውሎስ “… ክርስቶስ ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ወደዳት… በውኃ መታጠብና ከቃሉ ጋር አንጽቶ እንዲቀድሳት ስለ እርስዋ ራሱን አሳልፎ ሰጠ፤ እድፈት ወይም የፊት መጨማደድ ወይም እንዲህ ያለ ነገር ሳይሆንባት ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ” ኤፌ5፡25-7 በዘመናት ሁሉ ቤተክርስቲያንን ስናይ ብዙ የምንቆጥረው ድካምና ነቀፋ ቢኖርባትም ምን ያህል በእግዚአብሔር ፊት የከበረች እንቁ እንደሆነች ነው፡፡ ውጫዊ ገጽታዋን ብቻ እያየን አንፍረድ እንቁ እስካልጠራ ድረስ ከሌሎች ማዕድናት መካከል ተለይቶ አይታወቅም ስለዚህ ምርቱ ከግርዱ እስኪለይ ድረስ ዋጋዋን አናቃል፡፡ 5. መረብ "ደግሞ መንግሥተ ሰማያት ወደ ባሕር የተጣለች ከሁሉም ዓይነት የሰበሰበች መረብን ትመስላለች፤ በሞላችም ጊዜ ወደ ወደቡ አወጡአት፥ ተቀምጠውም መልካሙን ለቅመው በዕቃዎች ውስጥ አከማቹ ክፉውን ግን ወደ ውጭ ጣሉት" ማቴ13:47,48 በምድር ካለችው ከቤተክርስቲያን ፍጽምናን አንጠብቅ እርስዋ የምትመስለው ከሁሉ ዓይነት የሰበሰበች መረብን ነው፡፡ ለኛ መፍረድ አልተሰጠንም ነገር ግን በውስጥዋ ያሉ የከበሩና መልካም የሆኑ ነጥረው ይወጡ ዘንድ በተሰጠነን ጸጋ ቤተክርስቲያንን በብዙ መሰጠት ማገልገል ነው፡፡ በምድር ያለችው ቤተክርስቲያን በውስጥዋ ሁሉን አቅፋ ትቀጥል ዘንድ የአባት ፈቃድ ነው እርሱ ራሱ ለመፍረድ፣ እውነተኛውን ከሐሰተኛው፣ ስንዴውን ከእንክርዳዱ፣ እውነተኛውን አሳ ካልሆነው የሚለይበት የራሱን ጊዜ ቀጥሮአል ስለዚህ ነው ጳውሎስ “ስለዚህም በጨለማ የተሰወረውን ደግሞ ወደ ብርሃን የሚያወጣ የልብንም ምክር የሚገልጥ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ጊዜው ሳይደርስ አንዳች አትፍረዱ፤ በዚያን ጊዜም ለእያንዳንዱ ምስጋናው ከእግዚአብሔር ዘንድ ይሆናል” 1ቆሮ4፡5 ይህ ማለት ፊት ለፊት የሚታዩ የስህተት ትምህርቶችን፣ የአመጽ አካሄዶችን ወዘተ… አንነቅፍም ማለት አይደለም ነገር ግን በጅምላ ቤተክርስቲያንን መንቀፍ የምድር መልክዋን አለመረዳት ነው፡፡ 6. አዲሱንና አሮጌውን የሚለይ "እርሱም፡— “ስለዚህ የመንግሥተ ሰማያት ደቀ መዝሙር የሆነ ጻፊ ሁሉ ከመዝገቡ አዲሱንና አሮጌውን የሚያወጣ ባለቤትን ይመስላል፡” አላቸው" ማቴ13:52 ማንኛውም ሰው ኢየሱስ እያወጀ ወዳለው መንግሥት የሚገባው በልባቸው ላይ የተዘራውን የእግዚአብሔርን ቃል በማመንና ዳግመኛ በመወለድ ብቻ ነው 1ጴጥ1፡23 ይህም በዘሪው ምሳሌ ላይ ተገልጦአል፡፡ የዚህ አዲስ ኪዳን ህይወት ከቀድሞው የኦሪት ሕግ ፈጽሞ የተለየ ነው ገላ3:7-14 ስለዚህም ነው ኢየሱስ ቁ.51 ላይ ደቀ መዛሙርቱን “ይህንን ሁሉ አስተውላችኋልን?” ብሎ የሚጠይቃቸው። ከዚያም ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለመጥቀስ “ጻፊ” የሚለውን ቃል በመጠቀም እነዚህ ሰዎች ምንም እንኳ መደበኛ ትምህርት ባይኖራቸውም፣ ከሁሉ በሚበልጠው መምህር እግር ስር ተቀምጠው እነዚህን የአዲን ኪዳን እውነታዎች ተምረዋል። ስለዚህ እነዚህ ደቀ መዛሙርት የቃሉን ትክክለኛ ትርጉም በመረዳት አዲሱን ከአሮጌው የሚለዩ ጻፊዎች/አስተማሪዎች/ ነበሩ። ጻፊዎች እውቀታቸውን ለሌሎች የማስተማርና የማካፈል ኃላፊነት ነበራቸው፡፡ ስለዚህ ነው ኢየሱስ እነዚህን እውነቶች ከአሮጌው እየለዩ ማስተማር እንደሚገባቸው የሚናገረው፡፡ ምንም እንኳ ለህግ የነበረው ቅንአቱ ከፍተኛ የነበረው ጳውሎስ ከተለወጠና የቤተክርስቲያን አገልጋይ ከሆነ በኋላ የአዲሱን የህይወት ስርዓት ከህጉ እየለየ ያስተማረ ዋንኛ ጻፊ በመሆን ጥሩ ምሳሌ ነው 2ቆሮ217፡፡ ዛሬ የቤተክርስቲያንን ምስል ከሚያበላሹ መምህራን መካከል በአዲሱ ኪዳን ለሚኖሩ ቅዱሳን የአሮጌውን ኪዳን እውነታ ከአዲሱ ሳይለዩ ወይም እየደባለቁ በማስተማር ችግር የሚፈጥሩት፡፡ የአዲስ ኪዳን አስተማሪ ግን አዲሱንና አሮጌውን ለይቶ የሚያስተምር ነው። ጸጋ ይብዛላችሁ Telegram:- @mentesnotkebede2020 👍 Join በማድረግ እየተቀላቀሉን ሌሎችም እንዲሳተፉ ሼር በማድረግ ይሳተፉ Email:- mentesnot_kebede@yahoo.com ስልክ:- 0911693190
457
7
ሰኞ 25/12/18 የማቴዎስ ወንጌል መልዕክት (ክፍል 55) የመንግሥተ ሰማይ የምድር መልክ/01/ ማቴ13:31-33; 44-46 መንግሥተ ሰማይ ማለት የሰማይ መንግሥት ወይም እግዚአብሔር የሚያስተዳድርበት መንግሥት ማለት ነው፡፡ ይህች የእግዚአብሔር መንግሥት እግዚአብሔር በምድር ላይ ከኃጢአት ውድቀት በኋላ ከሰዎች ጋር ባደረገው ኪዳን መሰረት ሲሰራ ቆይቶአል እነርሱም የአዳም፣ የኖህ፣ የአብርሃም፣ የዳዊትና የክርስቶስ ኪዳን ሲባሉ የመጨረሻው የዘላለም ኪዳን ነው፡፡ እስራኤል በተሰጣት ኪዳን መሰረት ለመኖር ባለመቻልዋ የእግዚአብሔር መንግሥት ከእነሱ ተወስደች ጌታ ሲናገር “ስለዚህ እላችኋለሁ፥ የእግዚአብሔር መንግሥት ከእናንተ ትወሰዳለች ፍሬዋንም ለሚያደርግ ሕዝብ ትሰጣለች” ማቴ21፡43 አለ፡፡ አሁን ግን በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር መንግሥት በህጋዊ መንገድ፣ ክርስቶስን የህይወታቸው ጌታ ወዳደረጉ ሁሉ መጥታለች ስለዚህ ነው “የእግዚአብሔር መንግሥት ቀርባለችና ንስሃ ግቡ” ሲል ጌታ ኢየሱስ ግብዣውን ያቀረበው፡፡ ዛሬ ይህ መንግሥት የሚሰራው ከቤተክርስቲያን ጋር ነው፡፡ ምንም እንኳ ቤተክርስቲያንንን የሚያስተዳድራት ፍጹም የሆነው ራሱ እግዚአብሔር ቢሆንም እርስዋ ግን ፍጹም ባለመሆንዋ የዘላለሙ መንግሥት እስከሚጀምር ድረስ በብዙ ጉድለቶች፣ ነቀፋዎችና ተግዳሮቶች በምድር ትመላለሳለች ለዚህም ነው በምድር ያለችው ይህች መንግሥት ምን እንደምትመስል ጌታ በምሳሌዎቹ የሚነግረን፡- 1. የሰናፍጭ ቅንጣት "... መንግሥተ ሰማያት ሰው ወስዶ በእርሻው የዘራትን የሰናፍጭ ቅንጣት ትመስላለች፤ እርስዋም ከዘር ሁሉ ታንሳለች፥ በአደገች ጊዜ ግን፥ ከአታክልቶች ትበልጣለች የሰማይም ወፎች መጥተው በቅርንጫፎችዋ እስኪሰፍሩ ድረስ ዛፍ ትሆናለች" ማቴ13:31,32 የቤተክርስቲያን አጀማመርዋ እጅግ አናሳ በሆኑ በአስራ ሁለት ተራ ሰዎች አማካኝነት ነው፡፡ ጌታ በምሳሌው እርስዋ የሰናፍጭ ቅንጣት ማለትም ከዘር ሁሉ በምታንስ ሆና በምድር ላይ ብትዘራም አድጋ ከዛፎች ሁሉ በመብለጥ የሰማይ ወፎች እስኪሰፍሩባት ድረስ ገዝፋለች፡፡ ቤተክርስቲያን ዛሬ በመላው ዓለም እጅግ ታላቅ ተቋም ናት ነገር ግን የወፎች መጠለያ መሆንዋ በብዙ መንገድ የሚያስነቅፋት ሆንዋል፡፡ እነዚህ ወፎች ምንድናቸው? እነዚህ ወፎች የሚወክሉት ክፉ መናፍስትን ሲሆን ሰይጣን በስምዋ ሐሰተኛ ትምህርቶችንና ሐሰተኛ ኃይማኖቶችን በማስፋፋት በስምዋ ይነግዳል ማር4፡4 ፡፡ ዛሬ በዚሁ አንጋፋ ዛፍ ላይ የተጠለሉ፣ የቤተክርስቲያንን ስም ያነገቡ እጅግ ብዙ ተቋማትና የሐይማኖት ቤቶች አሉ፡፡ ይህንን ምሳሌ በሌላ መንገድ ስናየው ደግሞ ቤተክርስቲያን በአንድ ቦታ ስትተከል ምንም እንኳ አናሳ መስላ ብትታይም የመብዛት አቅምዋ ምን ያህል ተጽዕኖ አምጪ እንደሆነ ያሳያል፡፡ 2. እርሾ "ሌላ ምሳሌ ነገራቸው እንዲህም አለ፡- “መንግሥተ ሰማያት ሁሉ እስኪቦካ ድረስ ሴት ወስዳ በሦስት መስፈሪያ ዱቄት የሸሸገችውን እርሾ ትመስላለች" ማቴ13:33 የሰማይ መንግሥት የሚያስተዳድራት ቤተክርስቲያን ምን እንደምትመስል ጌታ በዚህ ሌላ ምሳሌ ደግሞ ሲናገር አንድ ሴት ሊጥዋ እስኪቦካ ወስዳ የጨመረችበትን ዱቄት ትመስላለች፡፡ በእግዚአብሔር ቃል እርሾ የኃጢአት 1ቆሮ5፡8፣ የሐሰት ትምህርትና ማቴ16፡6-12 የግብዝነት ሉቃ12፡1 ምሳሌ ተደርጎ ተጠቅሶአል፡፡ እርሾው ወዲያውኑ ሊጡን በሙሉ እንደሚያዳርሰው እንዲሁ ቤተክርስቲያን በምድር ይህን ትመስላለች፡፡ ቤተክርስቲያን በኃጢአት፣ በግብዝነትና በሐሰት ትምህርቶች እየተናጠች ትገኛለች፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ችግሮች ገና ከጅማሬዋ የነበረ ነገር ግን በዓለም ፍጻሜ በጎቹ ከፍየሎቹ፣ ስንዴው ከእንክርዳዱ ሲለይ በዘላለም መንግሥት ውስጥ ፍጹምነትዋን ይዛ ትቀጥላለች፡፡ ይህንን ምሳሌ በበጎ አቅጣጫ ስንመለከተው እርሾ በአንድ ሊጥ ውስጥ ከገባ በፍጥነት ሊጡን ሁሉ እንደሚያቦካ በአንድ ማህበረሰብ መካከል ጥቂት ቅዱሳን በሚሰጡት አገልግሎት ክርስትና በፍጥነት እንዴት እንደሚባዛና እንደሚሰፋ ሁሉ ተጽዕኖ ፈጣሪነትዋ ከፍተኛ መሆኑን ያሳያል፡፡ 3. የተሰወረ መዝገብ "ደግሞ መንግሥተ ሰማያት በእርሻ ውስጥ የተሰወረውን መዝገብ ትመስላለች፤ ሰውም አግኝቶ ሰወረው፥ ከደስታውም የተነሣ ሄዶ ያለውን ሁሉ ሸጠና ያን እርሻ ገዛ" ማቴ13:44 በዚህ ምሳሌ እግዚአብሔር ዓለምን እንዲሁ በመውደዱ ዓለም ሳይፈጠር በክርስቶስ ያያቸውንና የወሰናቸውን የእርሱን ሰዎች /የተሰወሩ መዝገቦች/፣ የራሱ ሊያደርግ በኃጢአት ወደ ወደቀው ወደዚህ ዓለም ወይም /እርሻ/ መጣ እግዚአብሔርም አንድያ ልጁን ለኃጢአት መስዋዕት ይሆን ዘንድ በመስጠት እርሻውን ገዛ፡፡ ስለዚህ ቤተክርስቲያን ምንም እንኳ ነቀፋና ዘርፈ ብዙ ችግሮች ቢኖርዋትም በታላቅ ዋጋ የተገዛች የእግዚአብሔር የራሱ ናት 1ቆሮ6፡20፡፡ ስለዚህ በዘመናት ሁሉ ይህንን ዋጋ የተረዱ፣ የጌታቸውን ፈለግ በመከተል ቤተክርስቲያንን ለማስቀጠል እንደ ጌታቸው ዋጋ እየከፈሉ እዚህ አድርሰዋታል ቆላ1፡24፡፡ ጸጋ ይብዛላችሁ Telegram:- @mentesnotkebede2020 👍 Join በማድረግ እየተቀላቀሉን ሌሎችም እንዲሳተፉ ሼር በማድረግ ይሳተፉ Email:- mentesnot_kebede@yahoo.com ስልክ:- 0911693190
403
8
ዓርብ 22/12/18 የማቴዎስ ወንጌል መልዕክት (ክፍል 54) የመንግሥተ ሰማይ ተግዳሮት ማቴ13፡24-30፣ 36-43 ከአረም ጋር የተያያዘ ሌላ ምሳሌ ደግሞ ነገራቸው፡፡ ትምህርቱ እየረዘመ በሄደ ጊዜ ያስተምር የነበረበት ስፍራ የወደብ አካባቢ ነበርና ተመልሶ ወደ ቤት ገባ ቁ.36፡፡ በዚህ ጊዜ ልክ እንደ ዘሪው ምሳሌ ሁሉ ደቀ መዛሙርቱ ስለ ምሳሌው ትርጓሜ ጠየቁት “እርሱም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ መልካምን ዘር የዘራው የሰው ልጅ ነው፤ እርሻውም ዓለም ነው፤ መልካሙም ዘር የመንግሥት ልጆች ናቸው፤ እንክርዳዱም የክፉው ልጆች ናቸው፥ የዘራውም ጠላት ዲያብሎስ ነው፤ መከሩም የዓለም መጨረሻ ነው፥ አጫጆችም መላእክት ናቸው” ማቴ13፡37-39 ይህ ትንቢታዊ የሆነ በቤተክርስቲያን ዘመን ሁሉ በአለም ዙሪያ ስለሚነሱ የሐሰት ትምህርቶችና፣ የሐሰት የኃይማኖት ቡድኖችን የሚመለከት ነው፡፡ ይህም በሰው ልጅ ወይም በጌታ በኢየሱስ በመልካም ዘር በምድር ላይ በቆመችው እንደ ማቴዎስ አጠራር መንግሥተ ሰማይ ወይም ቤተክርስቲያን ላይ የሚመጣውን አስመሳይና በሰይጣን አነሳሽነት የሚዘራውን ክፉ ዘር ወይም የሐሰት ትምህርቶች የሚያሳድሩትን ተጽዕኖ እየገለጠ ነው፡፡ በዚሁ ምዕራፍ ብቻ ሰባት ጊዜ መንግሥተ ሰማይ ምን እንደምትመስል በምሳሌ ይናገራል ቁ. 24,31,33,42,45,47,52፡፡ ምሳሌውንና ትርጓሜውን እንመልከት፡- 1. አደገኛው እንቅልፍ “ሰዎቹ ሲተኙ ግን ጠላቱ መጣና በስንዴው መካከል እንክርዳድን ዘርቶ ሄደ። ስንዴውም በበቀለና በአፈራ ጊዜ እንክርዳዱ ደግሞ ያን ጊዜ ታየ” ማቴ13፡25,26 ይህንን ትምህርት ስንማር ብዙዎች ከተሰናከሉበት፣ ትክክል ካልሆነ አንድ አስተሳሰብ ያድነናል፡፡ እርሱም ቤተክርስቲያንን ፍጹም አድርጎ ከማየት የተነሳ የተለያዩ ችግሮች፣ ሐሰተኛ ትምህርቶች፣ የተበላሸ የሰዎች ባህርይ፣ አድሎአዊነት፣ ፖለቲከኝነት ወዘተ… በውስጥዋ መገኘቱን ማየታችን ነው፡፡ ጌታ ግን መንግሥተ ሰማይ ወይም ቤተክርስቲያን በምድር ምን እንደምትመስል እያሳየ ነው፡፡ በእርግጥ በመልካም ዘር የተተከለችው ቤተክርስቲያን ለክፉው ዘር መዘራት ያላት አስተዋጽዖ በተዘናጋችበትና እንቅልፍ ውስጥ እየገባች በሄደች ቁጥር ጠላት ክፉ ዘሩን ለመርጨት እድሉን አግኝቶአል፡፡ ክፉው ዘሩን መዝራት የጀመረው ገና በሐዋርያት አገልግሎት ዘመን ነው፣ እነርሱም በንቃት ታግለውታል ለምሳሌ ጳውሎስ “የወንጌልም እውነት በእናንተ ዘንድ ጸንቶ እንዲኖር ለአንድ ሰዓት እንኳ ለቅቀን አልተገዛንላቸውም” ገላ2፡5 ይህ የተደረገው በብዙ መንገድ ነው፡፡ ነገር ግን ቤተክርስቲያን እየሰፋችና እያደገች ተጽዕኖዋም በዓለም ዙሪያ ሁሉ እየበረታ በሄደ ቁጥር በውስጥዋም በውጪም ብዙ ችግሮችን እየስተናገደች ሄደች፡፡ በትምህርት መለያየት፣ ከአለማዊ አስተሳሰብ ጋር መጋባት፣ የፖለቲከኞች መጠቀሚያ መሆን፣ በዘር በጎሳ መከፋፈል፣ ተልዕኮን በመሳት በውጫዊ ህንጻ ላይ ትኩረት ማድረግ፣ የገንዘብ ማግኛ መድረክ ማድረግ ወዘተ… ይህ ሁሉ እንቅልፍ ነው፡፡ በዚህም ሁኔታዋ ለብዙ ኃይማኖቶች፣ ለሐሰት አስተምህሮቶች ማንሰራራትና መፈልፈል ምክንያት ሆነ፡፡ ዛሬም አደጋችንን ለመቀነስ የሚያስፈልገን ከእንቅልፍ መነሳት እንጂ የትም የማትገኘዋን ንጹህ ቤተክርስቲያን ፍለጋ መንከራተት የለብንም፡፡ 2. ጨካኙና መሃሪው ልብ “የባለቤቱም ባሮች ቀርበው፦ ጌታ ሆይ፥ መልካምን ዘር በእርሻህ ዘርተህ አልነበርህምን? እንክርዳዱንስ ከወዴት አገኘ? አሉት። እርሱም፦ ጠላት ይህን አደረገ አላቸው። ባሮቹም፦ እንግዲህ ሄደን ብንለቅመው ትወዳለህን? አሉት። እርሱ ግን፦ እንክርዳዱን ስትለቅሙ ስንዴውን ከእርሱ ጋር እንዳትነቅሉት አይሆንም” ማቴ13፡27-29 ጌታ በምሳሌው ከእንቅልፍ የባነኑና መንፈሳዊ ቅንዓት የያዛቸው የባለቤቱ ባሪያዎች ይህ እንክርዳድ ከየት መጣ? የተዘራው መልካም ዘር አልነበረም? ስለዚህ እንንቀለው አሉ፡፡ ጌታም ይህንን ያደረገው ሰይጣን እንደሆነ ተረጎመ ቁ. 39፡፡ እዚህ ጋር ቤተክርስቲያን ውስጥ ያለን ፖለቲከኞች፣ ጎሰኞች፣ ጥቅም ፈላጊዎች፣ ከፋፋዮች፣ አስመሳዮች ወዘተ… የማን ዘር ተጽዕኖ እያሳደረብንና ማንን እያገለገልን መሆናችንን ማወቅ ያስፈልገናል፡፡ ጌታ ግን እንክርዳዱን ልትነቅሉ ስትነሱ ስንዴውን ትነቅሉታላችሁ ምክንያቱም የመከር ጊዜ ካልደረሰ በቀር እንክርዳድና ስንዴው አይለዩም ብዙ መመሳሰል አለባቸው፡፡ ስለዚህ ጌታ በምህረቱ ብዛት እድል እየሰጠ ከክፉ ስራቸው ንስሃ እንዲገቡ ጊዜ እየገዛላቸው ነው፡፡ ቅንዓት ከምህረት ልብ ጋር ካልሆነ ንጹሃንን ልንጎዳ፣ ስንዴውን ልንነቅል እንችላለን፡፡ የራስን ድካም በማወቅ ለሚስቱ የሚራራና ይቅር የሚል ልብ ሊኖረን ይገባል፡፡ ባለቤቱ ከራራለት እኛ የምን ቤት ልንሆን ነው፡፡ 3. የፍጻሜው ፍርድ “ተዉአቸው፤ እስከ መከር ጊዜ አብረው ይደጉ፤ በመከር ጊዜም አጫጆችን፦ እንክርዳዱን አስቀድማችሁ ልቀሙ በእሳትም ለማቃጠል በየነዶው እሰሩ፥ ስንዴውን ግን በጎተራዬ ክተቱ እላለሁ አለ” ማቴ13፡30 ነገር ሁሉ ወደ ፍጻሜው እየቸኮለና እየሄደ ነው ስለዚህ ፍርዱን ለፈራጁ ሰጥተን እኛ ግን ስራችን ላይ ልንጠመድ ይገባል፡፡ የዘመኑ ፍጻሜ እየደረሰ ስለመሆኑ እየሆኑ ያሉ ሁኔታዎች እየነገሩን ነው፡፡ በነዚህ ቀናት እንኳ በቻይናና በህንድ ቦርደር ላይ በምትገኘው በኔፓል የደረሰው የጎርፍ እልቂት አንቂ ክስተት ነው፡፡ መፈራረዱን ትተን መከሩ ከእጃችን ሳይወጣ መከሩን ለመሰብሰብ ልንጋደል ይገባል፡፡ ለሁሉ እንደየ ስራው ፍርድ የሚሰጠው ጌታ በፍጻሜው ምርቱን ከእንክርዳዱ ለይተው ስንዴውን ወደ ጎተራ፣ እንክርዳዱንም ወደ እሳት ለይተው ይጥሉ ዘንድ መላዕክቱን ይልካል፡፡ የሚያመልጥም የለም ጌታም አላውቃችሁም ይላቸዋል፡፡ ይህንን ስንነጋገር ቸርችን ብቻ እያሰብን አይደለም ነገር ግን ራሱን የአምላክ ተጠሪ አድርጎ የሾመ ኃይማኖተኛን ሁሉ እያሰብን ነው፡፡ ጸጋ ይብዛላችሁ Telegram:- @mentesnotkebede2020 👍 Join በማድረግ እየተቀላቀሉን ሌሎችም እንዲሳተፉ ሼር በማድረግ ይሳተፉ Email:- mentesnot_kebede@yahoo.com ስልክ:- 0911693190
627
9
ሐሙስ 21/12/18 የማቴዎስ ወንጌል መልዕክት (ክፍል 53) ፍሬአማነትን የሚከለክሉ ሶስቱ እንቅፋቶች ማቴ13:4-9; 18-23 ጌታ ኢየሱስ የዘሪውን ምሳሌ ካስተማረ በኋላ ደቀመዛሙርቱ ለምን በምሳሌ ትናገራለህ ብለው ጠይቀውት ነበር እርሱም “ለእናንተ የመንግሥተ ሰማያትን ምሥጢር ማወቅ ተሰጥቶአችኋል፥ ለእነርሱ ግን አልተሰጣቸውም” በማለት መለሰላቸው፡፡ በዚህም ተስፋ መሰረት የተናገረውን ምሳሌ ይተረጉምላቸው ዘንድ ጀመረ፡፡ በክርስቶስ የዳነ ሰው ቃሉን ይረዳና ይገልጥለት፣ ዘንድ መንፈስ ቅዱስን ሰጥቶታል፡፡ ስለዚህ እያንዳንዱ አማኝ ቃሉን ከጌታ እግር ስር ቁጭ ብሎ መማር ያስፈልገዋል፡፡ የኤማዎስ መንገደኞች በክርስቶስ ሞት ተስፋ ቆርጠውና ጠውልገው ወደ ቀዬአቸው ሲመለሱ ጌታ ቀርቦ “ከሙሴና ከነቢያት ሁሉ ጀምሮ ስለ እርሱ በመጻሕፍት ሁሉ የተጻፈውን ተረጐመላቸው” ሉቃ24፡27 በዚህ ጊዜ ዓይናቸው ተከፍቶ ቀድሞ ወደ ተሰጣቸው ተስፋ ተመለሱ፡፡ እነዚህ ሰዎች የሚያውቁት ከጊዜው ሁኔታ ጋር አመሳክሮ ለመረዳት ከደራሲው ከራሱ፣ ትርጓሜ አስፈልጓቸው ነበር፡፡ ስለዚህ ነው ለእናንተስ የመንግሥተ ሰማያትን ምሥጢር ማወቅ ተሰጥቶአችኋል የተባለው፡፡ ስለዚህ ጌታ የዘሪውን ምሳሌ ስሙ በማለት ትርጓሜውን ይነግራቸው ጀመር፡- 1. አለማስተዋል "የመንግሥትን ቃል ሰምቶ በማያስተውል ሁሉ፥ ክፉው ይመጣል፥ በልቡ የተዘራውንም ይነጥቃል፤ በመንገድ ዳር የተዘራው ይህ ነው" ማቴ13:19 ዘሪው የምስራቹን ቃል የሚያበስር፣ ቃሉን የሚያስተምርን ሰውን የሚወክል ሲሆን ዘሩ ደግሞ የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡ ይህ ቃል በሰው ጆሮ ከደረሰ በኋላ ከሰዎች የሚገኘው ምላሽና በዚያ ሰው ህይወት የሚገኘው ፍሬ እንደየ ሰው ልብ ምንነት ይለያያል፡፡ በዚህ ምሳሌ ጌታ ያቀረበው የመጀመሪያው ቃሉ ፍሬ እንዳያፈራ እንቅፋት የሚሆነበት ዋንኛ ጉዳይ አለማስተዋል ነው፡፡ ቃሉን በደስታ ይሰማል ግን አያስተውለውም የዚህ ሰው ልብ ልክ ብዙ ሰው እየረገጠው እንደሚሄድና በሰዎች እግር እንደ ተደመደመ መንገድ በመሆኑ የተዘራው ዘር ወደ ውስጥ የመግባት እድል አያገኝም፡፡ ይህ ማለት ይህ ሰው ብዙ አሳቦች ልቡን ስለሚያደነደኑት ቃሉ ወደ ልቡ አይገባም ስለዚህ ወደ መሬት ያልገባ ዘር በወፎች እንደ ሚለቀም ሁሉ እንዲሁ ወደ ልብ ያልገባ ወይም ቃሉ ሲነገር በሚገባ ያልተረዳ ሰው የሰማውን ቃል በሰይጣን ይነጠቃል፡፡ ይህ ሰው ቃሉን ስለተነጠቀ ፍሬ ሊያፈራ አይችልም፡፡ ሰው ቃሉን ሲሰማ ልቡን ከተለያዩ አሳቦች ሰብስቦ በጥሞና መስማት ያስፈልገዋል፡፡ በተለያየ አሳብ የሚዋከብ ሰው ቃሉን በሚገባ ሊሰማና ሊረዳው አይችልም፡፡ ስለዚህ ነው ሰይጣን ሰዎች ቃሉን በሚሰሙበት ሰዓት ማስተዋል እንዳያገኙ በተለያዩ አሳቦች ልባቸውን የሚሞላው፡፡ ይህንን የተረዳ ሰው ይህንን ችግር ድል መንሳት ይችላል፡፡ 2. በፈተና መፈታት "በጭንጫ ላይ የተዘራውም ይህ ቃሉን ሰምቶ ወዲያው በደስታ የሚቀበለው ነው፤ “ነገር ግን ለጊዜው ነው እንጂ በእርሱ ሥር የለውም፥ በቃሉ ምክንያትም መከራ ወይም ስደት በሆነ ጊዜ ወዲያው ይሰናከላል" ማቴ13:20,21 ሁለተኛው ቃሉ ወደ ሰው ህይወት መጥቶ ፍሬ እንዳያፈራ የሚያደርገው ልክ በጭንጫ ወይንም ትንሽ አፈር ብቻ ያለበት ድንጋያማ ቦታ እንደ ተዘራና ተክሉ ሥር ባለመስደዱ ምክንያት ጸሐይ በወጣ ሰዓት እንደሚጠወልግ ተክል እንዲሁ ቃሉን የሰማ ሰው ቃሉን በቀጣይነት የሚማር ካልሆነ በቃሉ ምክንያት ስደት፣ መከራ ሲመጣበት ወዲያውኑ መሰናከል ይጀምራል፡፡ ጌታ ላመኑ አይሁድ ይህንን ችግር ስለሚያውቅ ካመኑ በኋላ እንዲህ አላቸው "በትምህርቴ ብትጸኑ እናንተ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ፤ እውነትንም ታውቃላችሁ፤ እውነትም ነጻ ያወጣችኋል" ዮሐ8:31-32 በቃሉ አማካኝነት አርነት ማግኘት በቃሉ የምናገኘው አንድ ፍሬ ነው፡፡ ለዚህም አማኝ በቃሉ መጽናት፣ በቃሉ ትምህርት መቀጠል ይኖርበታል፡፡ በዚህ ጊዜ የትኛውም ፈተናና መከራ በህይወቱ ሲመጣ ሊነቀንቀው አይችልም፡፡ ይህ ማለት የእግዚአብሔርን ቃሉ ከብዙ የህይወት አቅጣጫ አኳያ ሊማረው ያስፈልገዋል ምክንያቱም ቃሉ ለየትኛውም የህይወት ትግል መልስና መፍትሄ አለው፡፡ ቃሉን መማር ያቆመ ሰው ለህይወት ፈተናዎች ይረታል፣ ስለዚህ ፍሬ ሊያፈራ አይችልም፡፡ 3. የዚህ ዓለም አሳብ "“በእሾህ መካከል የተዘራውም ይህ ቃሉን የሚሰማ ነው፥ የዚህም ዓለም አሳብና የባለጠግነት መታለል ቃሉን ያንቃል፥ የማያፈራም ይሆናል" ማቴ13:22 አማኝ ፍሬ የማያፈራበት፣ በህይወት ጸንቶ የማይቆምበት ሌላው ሶስተኛው ችግር ልክ ዘሩ በእሾህ መካከል እንደተተከለ ዘርና ባደገ ጊዜ አረሙ አንቆት ፍሬአማ እንዳይሆን እንደሚያደርገው ሁሉ እንዲሁም የሰው ልብ በዚህ ዓለም አሳብ፣ በባለጠግነት ጉዳይ ሲጠመድ ቃሉ ፍሬ እንዳያፈራ አረም ይሆንበታል፡፡ መቼም ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚችል ስለሌለ ሁለቱንም አብሮ ማስኬድ አይቻለውም፡፡ አንዱ በዚህ ዓለም የኑሮ አሳብ ሌትና ቀን ተጠምዶ ቃሉን የሚፈልግበት ክፍተት ያለው ልብ የለውም ልቡ ቢዚ በመሆኑ ቃሉን ሲሰማ እንቅልፍ እንቅልፍ ይለዋል፡፡ የሚውልበት አሳብ ለመንፈሳዊው ነገር ረሃብ እንዳይኖረው ያደርገዋል፡፡ ሌላው በእጁ ገንዘብ የያዘ ሰው መተማመኑን በገንዘቡና በንብረቱ ላይ ስለሚያደርግ ቃሉን ተጠምቶ አይፈልገውም ወይም ቃሉን የህይወቱ መሪና መተማመኛ ሊያደርገው አይችልም፡፡ 4. ድል ነሺው ልብ "በመልካም መሬት የተዘራውም ይህ ቃሉን ሰምቶ የሚያስተውል ነው፤ እርሱም ፍሬ ያፈራል አንዱም መቶ አንዱም ስድሳ አንዱም ሠላሳ ያደርጋል" ማቴ13:23 በመጨረሻም ከላይ የተዘረዘሩትን ችግሮች በሙሉ ድል የነሳ የትኛውም ሰው እርሱ የፍሬ ባለቤት ነው፡፡ የመልካም መሬት ባለቤት ለመሆን አለማስተዋልን፣ ቃሉን በቀጣይነት አለመማርንና የዚህን ዓለም አሳብና በባለጠግነት መታለልን መስወገድ ግድ ይላል፡፡ ፍሬ የሚያፈሩ ራሳቸው በፍሬአቸው ብዛት ይለያያሉ ይህ የሚያሳየው ብዙ መሰጠትን ነው፡፡ ትጋት፣ መሰጠት መቶ ወይም ፍጹም ፍሬአማ ለመሆን ምክንያት ይሆናል፡፡ ጸጋ ይብዛላችሁ Telegram:- @mentesnotkebede2020 👍 Join በማድረግ እየተቀላቀሉን ሌሎችም እንዲሳተፉ ሼር በማድረግ ይሳተፉ Email:- mentesnot_kebede@yahoo.com ስልክ:- 0911693190
533
10
没有文字...
163
11
ሰኞ 19/12/18 የማቴዎስ ወንጌል መልዕክት (ክፍል 52) ለደነደነ ልብ ነገር በምሳሌ ማቴ13፡1-3፣ 10-17 ጌታ ኢየሱስ ፈሪሳውያን በመንፈስ ቅዱስ ላይ የሰነዘሩትን አስከፊ ኃጢአት በተመለከተ ምዕራፍ 12 ላይ በብዙ አቅጣጫ ነገሮችን ሲናገር፣ ሲያስጠነቅቅና ሊያስከትል የሚችለውን ፍርድ እያሳየ ቆይቶ ወደ ገዛ አገሩ ለመሄድ በታንኳ ላይ ወጣ ማቴ13፡53፡፡ ነገር ግን አሁንም እጅግ ብዙ ህዝብ በወደቡ አካባቢ ተሰብስበው እንዳሉ ሲያይ ማስተማሩን ቀጠለ፡፡ ጌታ በዚህ ትምህርቱ ቃሉን መስማት መልካም እንደሆነ ነገር ግን ቃሉ ውጤት እንዲያመጣ ወይም ፍሬአማ እንዳይሆን ስለሚያደርገው ስለ ሰው የልብ ዓይነት አስተማረ፡፡ ጌታ በመቀጠልም እነዚህን የከበሩ እውነታዎች መስማት ብዙ የቀድሞ አባቶች ሲናፍቁት የነበረ እድል ቢሆንም ትክክል ባልሆነ አቋም ላይ ባለ ልብ መዘራቱ ግን ችግሩ ፍሬ አለማፍራት ብቻ ሳይሆን ይበልጥ ልብን ለከፋ ድንዳኔ እንደሚዳርግ አስጠነቀቀ፡፡ ሰው የጌታን ቃል መስማቱ ትልቅ እድል ሲሆን ለሰማው ቃል ምላሽ ካልሰጠ ግን ያው የተሰጠው እድል ይወሰድበታል፡፡ በዚህ ክፍል ልብ ለምን እንደሚደነድን የተናገረውን ካየን በኋላ በቀጣዩ ጥናታችን ስለ አራቱ የልብ ሁኔታዎች እንመለከታለን፡- 1. ዘሪው ሊዘራ ወጣ “እርሱም በታንኳ ገብቶ እስኪቀመጥ ድረስ ብዙ ሰዎች ወደ እርሱ ተሰበሰቡ፥ ሕዝቡም ሁሉ በወደቡ ቆመው ነበር። በምሳሌም ብዙ ነገራቸው እንዲህም አላቸው፦ እነሆ፥ ዘሪ ሊዘራ ወጣ” ማቴ13፡2,3 ሰዎች ሳያስተውሉ ምን እየሆነ እንዳለ ሳያውቁ እንዲሁ በጭፍን ጌታን እያጋፉ ይከተሉታል ጌታም ዓይናቸውን ሊያበራ የሚችለውን ቃሉን ያለ መሰልቸት በትጋት ያስተምራቸዋል፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ጌታ ሲያስተምር ነገሮችን በምሳሌ ያስረዳል ምክንያቱም ስለ መሲሁ “አፌን በምሳሌ እከፍታለሁ፤ ከቀድሞ ጀምሮ፥ ያለውንም ተምሳሊት እናገራለሁ” መዝ78፡2 ተብሎ በመዝሙራት ስለተጻፈ በምሳሌ ይናገራል፡፡ ምሳሌ በሁለት አቅጣጫ ይሰራል አንዱ ለሚሰሙና ቀና ልብ ላላቸው ነገሮችን በቀላሉ፣ በማይረሳ መንገድ፣ በልብ ውስጥ ምስል በመፍጠር ሲሰራ በሌላ አቅጣጫ ጆሮአቸው እየሰማ ልባቸውን ግን ወደው ለዘጉ ነገሩን ቁልፍልፍ የሚያደርግ የፍርድ ተግባር ይሆናል፡፡ ቃሉን ማስተማር ልክ ዘር፣ ሊዘራ እንደወጣ ገበሬ ነው፡፡ በቀድሞ ዘመን ዘር የሚዘራው በባህላዊ መንገድ ዝም ብሎ በእጅ መበተን በመሆኑና ዘሩ በተመረጠ ስፍራ ላይ ብቻ ስለማይበተን በየትኛውም ዓይነት መሬት ላይ ያርፋል ነገር ግን ዘሩን ከተቀበሉት አራት ዓይነት መሬቶች አንዱ ብቻ ፍሬአማ ይሆናል፡፡ 2. ሚስጥርን ማወቅ ተሰጥቶአል “ደቀ መዛሙርቱም ቀርበው፦ ስለ ምን በምሳሌ ትነግራቸዋለህ? አሉት። እርሱም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ ለእናንተ የመንግሥተ ሰማያትን ምሥጢር ማወቅ ተሰጥቶአችኋል፥ ለእነርሱ ግን አልተሰጣቸውም” ማቴ13፡10,11 ልባቸው ቃሉን ለመቀበል የቀናና ለመታዘዝም ፈቃደኛ የሆኑ ሰዎች የእግዚአብሔርን መንግስት ሚስጥር ማወቅ ተሰጥቶአቸዋል፡፡ ዳግም የተወለደ ሰው ሁሉ ሚስጥራትን የመረዳት አቅም አለው፡፡ መንፈሳዊ ነገሮች በመንፈስ ብቻ እንጂ በአእምሮ ስለማይመረመሩ ማንም ሊረዳቸው አይችልም 1ቆሮ2፡14 ስለዚህ ነው ጳውሎስ “መንፈስም የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር ስንኳ ሳይቀር ሁሉን ይመረምራልና ለእኛ እግዚአብሔር በመንፈሱ በኩል ገለጠው” 1ቆሮ2፡10 መንፈስ ቅዱስ የተሰጠን አንዱ አላማ የእግዚአብሄርን ጥልቅ ነገሮች ሊገልጥልን ነው፡፡ ይሁን እንጂ ዳግም በተወለዱት መካከልም እውነትን የመረዳት አቅማቸው የሚወሰነው ቃሉን ከመስማት አልፈው ለመታዘዝ በሚያሳዩት ትጋት ልክ ይወሰናል “ትእዛዜ በእርሱ ዘንድ ያለችው የሚጠብቃትም የሚወደኝ እርሱ ነው፤ የሚወደኝንም አባቴ ይወደዋል እኔም እወደዋለሁ ራሴንም እገልጥለታለሁ” ዮሐ14፡21 ለሌሎች ግን አልተሰጣቸውም፡፡ ያልተሰጣቸው ዋንኛው ምክንያት ልባቸውን በፈቃደኝነት ዝግ ስላደረጉ ነው፡፡ 3. እያዩ አለማየት እየሰሙ አለመስማት “ስለዚህ እያዩ ስለማያዩ እየሰሙም ስለማይሰሙ ስለማያስተውሉም በምሳሌ እነግራቸዋለሁ። መስማት ትሰማላችሁና አታስተውሉም፥ ማየትም ታያላችሁና አትመለከቱም” ማቴ13፡13,14 እያዩ አለማየት እየሰሙ አለመስማት ምን ያህል አደገኛ ነገር ነው፡፡ ዘሩ ልዩነት ሳያደርግ ሁሉ ዘንድ ደርሶአል፣ የእግዚአብሔር ዘላለማዊ አጀንዳ ለሰው ሁሉ ተገልጦአል ጳውሎስ ለቲቶ ሲነግረው “ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና” ቲቶ2፡11 እውነቱ ለሰው ሁሉ እንጂ ለተወሰኑና ለተመረጡ ብቻ አይደለም፡፡ ሰዎች ፈቃደኛ አይደሉም እንጂ የእግዚአብሔር ዓላማ ሁሉን በክርስቶስ መጠቅለል ነው “በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው አሳቡም በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው” ኤፌ1፡10 ሰው ግን የመምረጥ መብት ስላለው ነገርን ገላጭ የሆነው ምሳሌ ዓይንን የሚከድን ጭንብል ሆነባቸው ስለ እንደዚህ ዓይነት ሰዎች ኢሳይያስ ሲናገር ምሳሌ የሚረዳቸው ሳይሆን ይበልጥ ወደ አስከፊ ጨለማ የሚወስዳቸው እንደሆነ ተናግሮአል “በዓይናቸው እንዳያዩ፥ በጆሮአቸውም እንዳይሰሙ፥ በልባቸውም እንዳያስተውሉ፥ ተመልሰውም እንዳልፈውሳቸው፥ የዚህ ሕዝብ ልብ ደንድኖአልና ጆሮአቸውም ደንቁሮአል ዓይናቸውንም ጨፍነዋል የሚል የኢሳይያስ ትንቢት በእነርሱ ይፈጸማል” ማቴ13፡15 ጸጋ ይብዛላችሁ Telegram:- @mentesnotkebede2020 👍 Join በማድረግ እየተቀላቀሉን ሌሎችም እንዲሳተፉ ሼር በማድረግ ይሳተፉ Email:- mentesnot_kebede@yahoo.com ስልክ:- 0911693190
609
12
ሰኞ 18/12/18 የማቴዎስ ወንጌል መልዕክት (ክፍል 51) በውጭ ቆመህ አትፈልገው ማቴ12:46-50 እውነተኛ ቤተሰብ መንፈሳዊ ኦንጂ የስጋ ዝምድና አይደለም። ወደ እግዚአብሔር ቤተሰብ በመቀላቀል የእግዚአብሔር ልጅ የሚኮነውም በሰጋ ከክርስቲያን ከሆኑ ቤተሰብ በመወለድ ሳይሆን ከመንፈስ በመወለድ ብቻ ነው ስለዚህ ነው ዮሐንስ "እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም" ዮሐ1:13 ከኢየሱስ ጋር አንድ ቤት ቢኖሩ፣ እርሱ በተኛበት መኝታ ላይ ቢተኙ፣ እርሱ የተጠቀመባቸውን እቃዎች የመጠቀም እድል ቢያገኙ፣ እርሱ የለበሰው ልብስ በእጅህ ቢገባ፣ በስጋ የእርሱ ወንድም ወይም እህት ብትሆን ወዘተ… ነገር ግን በእርሱ አዳኝነት ሰው ካላመነ በቀር በውጭ መቅረቱ ግድ ነው፡፡ ሚስጥሩ እዚህ ጋር ነው፣ የክርስቶስን በረከት መካፈልና በውጭ ከመቅረት የሚያድነው ቃሉን በማመን ብቻ ነው፡፡ 1. በውጭ የቆሙ "ገናም ለሕዝቡ ሲናገር፥ እነሆ፥ እናቱና ወንድሞቹ ሊነጋገሩት ፈልገው በውጭ ቆመው ነበር" ማቴ12:46 ጌታ ብዙ ሰዎች ከበውት እያስተማረ፣ በአገልግሎት ላይ ሳለ እናቱና ወንድሞቹ የተለየ ስፍራ የሚሰጣቸው መስሎአቸው ይመስላል!! በመልዕክተኛ እንደሚፈልጉት ላኩ፡፡ እነዚህ ሰዎች ለምን በውጭ ቆሙ? እንደሌሎቹ በእግሮቹ ስር ተቀምጠው ለምን አይማሩም? ምክንያቱም ከማርያም በቀር “ወንድሞቹ ስንኳ አላመኑበትም ነበር” ዮሐ7፡5 ምንም እንኳ ግማሽ የሥጋ ወንድሞቹ ቢሆኑም ያሉት ውጪ ነው፡፡ ሰው ከክርስቶስ ጋር እድል ፈንታ የሚኖረው በእርሱ በማመን ዳግመኛ ሲወለድ ብቻ ነው፡፡ ዳግም ሳይወለዱ አገልግሎት፣ ኃይማኖታዊ ተግባራትን ሲፈጽሙ መኖር በውጪ ከመጣል አያድንም፡፡ ጌታ ለእንደዚህ ዓይነት ሰዎችን ሲናገር “በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም። በዚያ ቀን ብዙዎች፦ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን፥ በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን፥ በስምህስ ብዙ ተአምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል። የዚያን ጊዜም፦ ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ ዓመፀኞች፥ ከእኔ ራቁ ብዬ እመሰክርባቸዋለሁ” ማቴ7፡21-23 በእርግጥ ከትንሳኤ በኋላ ወንድሞቹ ራሳቸው በእርሱ በማመን ከውጭ ወደ ውስጥ ገብተዋል፡፡ 2. የሥጋ ዘመዶቹ "አንዱም፡— “እነሆ፥ እናትህና ወንድሞችህ ሊነጋገሩህ ፈልገው በውጭ ቆመዋል” አለው" ማቴ12:47 ማርያም ኢየሱስን ከወለደች በኋላ ከዮሴፍ ጋር በጋብቻ ቀጥለው ልጆችን ወልዳለች ማቴዎስም ዮሴፍ በንጽህና ጠብቋት የቆየችው እስክትወልድ ድረስ ብቻ መሆኑን ሲናገር “የበኩር ልጅዋንም እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም …” ማቴ1፡25 ማለቱ ነው ነገር ግን ከዚያ በኋላ በጋብቻ ስለመኖራቸውና ልጆችንም ስለመውለዳቸው ማስረጃዎች አሉ የመጀመሪያው ባደገበት አካባቢው የነበሩ ሰዎች ምስክርነት ነው ሲናገሩም “ይህስ ጸራቢው የማርያም ልጅ የያቆብም የዮሳም የይሁዳም የስምዖንም ወንድም አይደለምን? እኅቶቹስ በዚህ በእኛ ዘንድ አይደሉምን? አሉ፤ ይሰናከሉበትም ነበር” ማር6፡3 ሁለተኛው ምስክር ማርያም ራስዋ የተናገረችው ነው፡፡ ኢየሱስ አስራ ሁለት ዓመት በሆነው ጊዜ እንደ ህጉ ሥርዓት ወደ ቤተመቅደስ ይዘውት ከመጡና ስርአቱን ጨርሰው ሲመለሱ አጠገባቸው መሆኑን አላስዋሉም ነበርና ከአንድ ቀን ጉዞ በኋላ አብሮአቸው አለመሆኑን ሲያውቁ እየፈለጉት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፡፡ በቤተመቅደስ ሲያገኙት “… እናቱም፦ ልጄ ሆይ፥ ለምን እንዲህ አደረግህብን? እነሆ፥ አባትህና እኔ እየተጨነቅን ስንፈልግህ ነበርን አለችው” ሉቃ2፡48 ከአስራ ሁለት ዓመት በኋላ አብረው ናቸው፣ ዮሴፍ ኢየሱስን ስላሳደገው አባትህና እኔ አለችው፣ ባልዋ ባይሆን አባትህ ትለዋለች? በእርግጥ ዮሴፍ አሳዳጊው እንጂ አባቱ ስላልሆነ “ስለ ምን ፈለጋችሁኝ? በአባቴ ቤት እሆን ዘንድ እንዲገባኝ አላወቃችሁምን? አላቸው” ሉቃ2፡49 ባጠቃላይ የሥጋ ዝምድናን አስበው ኢየሱስን ፈለጉት ነገር ግን የሥጋ ዘመዶቹም ይሁኑ ማንኛውም ሰው ከክርስቶስ ጋር እድል ፈንታ የሚኖረው ሰው ከመንፈስ ሲወለድ ብቻ ነው፡፡ ይህ ካልሆ ግን ውጪ መቅረት ይሆናል፡፡ 3. የአባቱን ፈቃድ የሚያደርግ "እጁንም ወደ ደቀ መዛሙርቱ ዘርግቶ እንዲህ አለ፡— “እነሆ እናቴና ወንድሞቼ፤ በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ ሁሉ፥ እርሱ ወንድሜ እኅቴም እናቴም ነውና" ማቴ12:49,50 ጌታ በሥጋ ቤተሰቦቹ በውጭ መፈለጉን ሲሰማ የሚያገለግለውን ህዝብ ይቅርታ አንድ ጊዜ እናቴ ወንድሞቼ መጥተዋልና አናግሬአቸው ልምጣ አላለም፣ የተለየም ነገር አላደረገም፡፡ ይልቁንም ለእርሱ ጥብቅ ቤተሰብ በሰማያት ያለውን የአባቱን ፈቃድ የሚያደርግ እንደሆነ በፊቱ የተቀመጡትን ደቀ መዛሙርቱን በእጁ እየጠቆመ ተናገረ፡፡ የአባት ፈቃድ ምንድነው? ጌታ ራሱ ሲናገር “ልጅንም አይቶ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወትን እንዲያገኝ የአባቴ ፈቃድ ይህ ነው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ” ዮሐ6፡40 ብሎአል ስለዚህ በክርስቶስ የሚያምኑ ሁሉ አንድ ቤተሰብ ናቸው ኤፌ2፡19፡፡ ከቃሉ ርቀው ያሉ የሥጋ ቤተሰቦቻችንም ቢሆኑም እንኳ ከእኛ ወገን አይደሉም፡፡ ማንም እርቆ ያለ በክርስቶስ በማመን የመቅረብ እድል አለው ኤፌ2፡13፡፡ ጸጋ ይብዛላችሁ Telegram:- @mentesnotkebede2020 👍 Join በማድረግ እየተቀላቀሉን ሌሎችም እንዲሳተፉ ሼር በማድረግ ይሳተፉ Email:- mentesnot_kebede@yahoo.com ስልክ:- 0911693190
191
13
ዓርብ 15/12/18 የማቴዎስ ወንጌል መልዕክት (ክፍል 50) አርነትን ያለማጽናት አደጋው ማቴ12:43-45 ጌታ ኢየሱስ ለፈሪሳውያንና ለሚቃወሙት ሁሉ እጅግ ትልቅ ማስጠንቀቂያ እየሰጠ ይገኛል፡፡ እርሱ ወደ ምድር የመጣው የሰውን ልጅ ነፍሰ ገዳይ ከሆነው ከሰይጣን አገዛዝ ነጻ ሊያወጣ ነው ስለዚህ ነው ዮሐንስ “የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ …” 1ዮሐ3፡9 የሚለው፡፡ ክርስቶስን የገፋና የተቃወመ ሰው ማምለጫ የለውም፡፡ በክርስቶስ ያመነ ሰው ደግሞ በህጋዊ መንገድ ከሰይጣን አገዛዝ ነጻ ወጥቶአል “እርሱ ከጨለማ ሥልጣን አዳነን፥ ቤዛነቱንም እርሱንም የኃጢአትን ስርየት ወዳገኘንበት ወደ ፍቅሩ ልጅ መንግሥት አፈለሰን” ቆላ1፡13,14 ስለዚህ በክርስቶስ ያመነው ሰው ከዚህ በኋላ ሰይጣን በህይወቱ ምንም ዓይነነት ህጋዊ መብት የለውም ነገር ግን ሰይጣን ህጋዊ መብት ባይኖረውም በዚያ ሰው ህይወት ውስጥ አንዳች እድል ለማግኘት ዘወትር በዙሪያው ይዞራል “በመጠን ኑሩ ንቁም፥ ባላጋራችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አንበሳ ይዞራልና፤ በዓለም ያሉት ወንድሞቻችሁ ያን መከራ በሙሉ እንዲቀበሉ እያወቃችሁ በእምነት ጸንታችሁ ተቃወሙት” 1ጴጥ5፡8,9 ሰው በክርስቶስ ባለው ማንነት እያደገ ካልሄደ በብዙ መንገድ እድል ስለሚያገኝ ሊያሰቃየው ይችላል ስለዚህ ራስን ከክፉ ለማዳን አማኝ በክርስቶስ ምን እንደተደረገለትና እርሱ በክርስቶስ ማን እንደሆነ እየተረዳ መሄድ ያስፈልገዋል፡፡ በዚህ ክፍል መብት ያጣው ሰይጣን ምን እንደሚያደርግ እንመለከታለን፡- 1. የመናፍስቱ ስቃይ "ርኩስ መንፈስ ግን ከሰው በወጣ ጊዜ፥ ዕረፍት እየፈለገ ውኃ በሌለበት ቦታ ያልፋል፥ አያገኝምም" ማቴ12:43 ሰይጣንና ጭፍሮቹ በዚህ በምድር እየሰሩ ይገኛሉ፣ ይህንን የፈቀደላቸው እግዚአብሔር ሳይሆን ራሱ የሰው ልጅ ነው፡፡ ኃጢአት ምንግዜም ለሰይጣን ህጋዊ መብት ይሰጠዋል ኤፌ2፡1,2፡፡ አዳም የእግዚአብሔርን ቃል በመተላለፉ በምድር ላይ የነበረውን የመግዛት ሥልጣን ሰጥቶታል፡፡ ምንም እንኳ እግዚአብሔር የሁሉ ገዢ ቢሆንም ሰው አሳልፎ በፈቃዱ የሰጠውን ሥልጣን መንጠቅና መከልከል አይችልም ምክንያቱም ሰው ፈቃዱን በነጻነት ይጠቀም ዘንድ እንዲችል አስቀድሞ ስለሰጠው ነው፡፡ ስለዚህ ነው ክርስቶስ ራሱን በሰው ዘር ውስጥ አስገብቶ በምድር ላይ ህጋዊ መብት ያለው ሰው ሆኖ በመምጣትና ያንን ሁሉ መከራ በመቀበል የሰይጣንን ስልጣን የገፈፈው፡፡ በዚህም በመስቀሉ ስራ “አለቅነትንና ሥልጣናትን ገፎ፥ ድል በመንሣት በእርሱ እያዞራቸው በግልጥ አሳያቸው” ቆላ2፡15 ሰይጣን በምድር ላይ እንደ ሰው የሚመቸው ማደሪያ የለውም፡፡ ከሰው ከወጣ በኋላ በምድር ላይ እየተንከራተተ ይሰቃያል፡፡ ሰይጣን የግድ ማደሪያ ስለሚያስፈልገው በአንድ ወቅት ጌታ ሲያስወጣው ወደ እሪያዎች ውስጥ እንዲገቡ የለመኑት ለዚህ ነው ማር5፡12፡፡ ሰይጣን በብዙ ቁጥር ሆነውም እንኳ አብረው በአንድ ሰው ውስጥ ማደር ይፈልጋሉ፡፡ ሰይጣን ያደረበት ሰው ስቃዩ ብዙ ነው በክርስቶስ ነጻ ካልወጣ በስተቀር በሌላ በማንም ነጻ ሊወጣ አይችልም፡፡ በኃይማኖት ሰዎች የሚደረግ መናፍስትን የማስወጣት ስራ ውጤት አልባና የቀልድ ጨዋታ ብቻ ነው፡፡ ሰይጣን ድል የተነሳው በክርስቶስ ብቻ ነው፡፡ 2. የመናፍስቱ ጉብኝት "በዚያን ጊዜም፡— ‘ወደ ወጣሁበት ቤቴ እመለሳለሁ፡’ ይላል፤ ቢመጣም ባዶ ሆኖ ተጠርጎና አጊጦ ያገኘዋል" ማቴ12:44 ሰይጣን በክርስቶስ ከሰው ህይወት ከተባረረ በኋላ ስለሚሰቃይ ደጋግሞ ወደዚያ ወደ ቀድሞው ሰው እየመጣ ያየዋል ነገር ግን ያ ሰው ከዳነና ነጻ ከወጣ በኋላ ከክርስቶስ ጋር ጉዞውን ካልቀጠለ፣ በቀድሞ ድርጊቱ ከቀጠለ መንፈሱ ያንን በመጠቀም እንደገና በዚያ ሰው ህይወት ውስጥ ገብቶ የማደር መብት ያገኛል፡፡ ለአንድ ሰው ነጻ መውጣት ብቻውን ዋስትና አይደለም፡፡ አስቀድሞ የሰይጣን ተገዢ የነበረ ሰው አሁን ደግሞ የክርስቶስ ተገዢ ሆኖ ጉዞውን መቀጠል አለበት፣ የሰው ልጅ ያለ ሰይጣን ወይም ያለ እግዚአብሔር ነጻ ሆኖ መኖር አይችልም የግድ ከሁለት ለአንዱ መሆን አለበት ስለዚህ ነው ጌታ እናንተ ሸክም የከበደባችሁ ወደ እኔ ኑ አሳርፋችኋለሁ ካለ በኋላ ቀንበሬን ተሸከሙ በማለት ያዘዘው ሰው ያለ ሸክም መሆን አይችልም፡፡ የጌታን ቀሊልና ልዝብ ቀንበር እንቢ ካለ ክፉውን የሰይጣን የስቃይ ሸክም ለመሸከም ይገደዳል፡፡ አስቀድሞ ሰይጣን የገነባውን አስተሳሰብ በክርስቶስ እውቀት ካልተተካ በቀር ሰው በክርስቶስ ድኖ እንኳን ሰይጣን በነዚያ አሳቦች ይጫወትበታል ስለዚህ ነው ጌታ "... በትምህርቴ ብትጸኑ እናንተ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ፤ እውነትንም ታውቃላችሁ፤ እውነትም ነጻ ያወጣችኋል" ዮሐ8:31-32 ያለው፡፡ ስለዚህ ሰይጣን ደግሞ እድል እንዳያገኝ ሰው በክርስቶስ እውቀት መሞላት አለበት፡፤ 3. የመናፍስቱ አስከፊ ድርጊት "ከዚያ ወዲያ ይሄድና ከእርሱ የከፉትን ሰባት ሌሎችን አጋንንት ከእርሱ ጋር ይወስዳል፥ ገብተውም በዚያ ይኖራሉ፤ ለዚያም ሰው ከፊተኛው ይልቅ የኋለኛው ይብስበታል። ለዚህ ክፉ ትውልድ ደግሞ እንዲሁ ይሆንበታል" ማቴ12:45 መናፍስት በግል ብቻ ሳይሆን በጋራ ተናበው ይሰራሉ፡፡ አንድ መንፈስ ከሰው ህይወት ከወጣ በኋላ ያ ሰው ዳግመኛ እድል ከሰጠው ያ መንፈስ ብቻውን አይመጣም፡፡ ሌሎች ቢያንስ በትንሹ ሰባት ከእርሱ የከፉ መናፍስትን ጋብዞ ወደዚያ ሰው ህይወት ይመጣሉ ይገቡታል የዚያም ሰው ህይወት ከቀድሞው ይልቅ የከፋ ይሆንበታል፡፡ ሰው ዳንኩ፣ አመንኩ ካለ በኋላ በጌታ ቃል መኖር ካልቀጠለ ድነቱ የጸና አይደለም፡፡ ይህንን እውነት በዮሐ8፡30-52 ባለው ክፍል ላይ አመኑ የተባሉ ሰዎች በኋላ ግን ጌታን ጋኔል አለብህ በማለት የሰደቡ እነርሱ ናቸው፡፡ አንድ ሰው ለመዳኑ ማረጋገጫ የሚሆነው ጌታን አግኝቶ ነጻ ከወጣ በኋላ ምንም ፈተናና ስደት ቢነሳበት እንኳ በክርስቶስ እውነትና ፍቅር መቀጠል ሲችል ብቻ ነው፡፡ ብዙ ጊዜ ካመነ ሰው ውስጥ መናፍስት እንዴት ይወጣል የሚል ጥያቄ ይነሳል፡፡ ሰው የማያውቀው ያ ሰው አመንኩ አለ እንጂ ህይወቱን ለሰይጣን አጋልጦ የሚሰጥበት የኃጢአት ወይም የሌላ አምልኮ ልምምድ ይኖረዋል እንዲሁም በጉባኤ ይታይ ይሆናል እንጂ ቃሉ በእርሱ ውስጥ የለም፡፡ ሌላው ጉዳይ ዳነ በተባለበት ወቅት ቀድሞ ከያዘው መንፈስ ነጻ አልወጣ ሊሆን ይችላል፡፡ ጌታ በነበረበት ዘመን ያለው ትውልድ ኢየሱስን በመግፋቱ የከፋ ዘመን ውስጥ ወድቋል፡፡ ጸጋ ይብዛላችሁ Telegram:- @mentesnotkebede2020 👍 Join በማድረግ እየተቀላቀሉን ሌሎችም እንዲሳተፉ ሼር በማድረግ ይሳተፉ Email:- mentesnot_kebede@yahoo.com ስልክ:- 0911693190
810
14
ረብዕ 13/12/18 የማቴዎስ ወንጌል መልዕክት (ክፍል 49) ለክፉ ልብ ምልክት አይጠቅምም ማቴ12:38-42 ጌታ ኢየሱስ ከመወለዱ ጀምሮ የመጽሐፍትን ተስፋ በሚገባ እየፈጸመ በእስራኤል ልጆችና በኃይማኖት መሪዎቻቸው ፊት ብዙና ከበቂ በላይ ምልክቶችን አሳይቶአቸዋል፡፡ ከህዝቡም መካከል ማንም ከቁጥር የማያስገባቸው ተራ አሳ አጥማጆችና ቀራጮች ግን “… ሙሴ በሕግ ነቢያትም ስለ እርሱ የጻፉትን የዮሴፍን ልጅ የናዝሬቱን ኢየሱስን አግኝተነዋል …” ዮሐ1፡46 እያሉ ከአባት ባገኙት መገለጥ ተከትለውታል፡፡ ጌታም ለነዚህ ህጻናት ላላቸው ተከታዮቹ ይህ ታላቅ እውነት ስለተገለጠላቸው አባቱን ሲያመሰግን ታይቶአል “በዚያን ሰዓት ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ ሐሤት አደረገና፦ የሰማይና የምድር ጌታ አባት ሆይ፥ ይህን ከጥበበኞችና ከአስተዋዮች ሰውረህ ለሕፃናት ስለ ገለጥህላቸው አመሰግናለሁ፤ አዎን አባት ሆይ፥ ፈቃድህ በፊትህ እንዲህ ሆኖአልና” ሉቃ10፡21 ነገር ግን ራሳቸውን የኃይማኖት መሪ አድርው የሾሙ ሰወች በልብ ድንዳኔ ውስጥ ወድቀው መሲሁን ጋኔል እያስወጣ ጋኔል አለበት እያሉ ተቃወሙት፡፡ በዚህ ልብ ሆነው አሁንም ምልክትን ይጠይቁታል ነገር ግን የጌታ ምላሽ እንዲህ ነበር፡- 1. ክፉ ልብ "እርሱ ግን መልሶ እንዲህ አላቸው፡— “ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል፥ ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም" ማቴ12:39 ዓይኑን ላጨፈነ፣ ልቡን አውቆ ለዘጋ ሰው ምንም ተአምር ቢደረግለት ለውጥ አይኖረውም፡፡ የተአምራት ዓላማ የመሲሁን መምጣት ማመላከት ነው ነገር ግን የእውቀትን መክፈቻ በእጃቸው የያዙ እነዚህ የኃይማኖት መሪዎች ልባቸው ክፉ በመሆኑ የኪዳኑን አምላክ አስትተው ትውልዱን ለሌላ ወይም አመንዝራ አድርገውታል ጌታም እነዚህን ሰዎች “እናንተ ሕግ አዋቂዎች፥ የእውቀትን መክፈቻ ስለ ወሰዳችሁ፥ ወዮላችሁ ራሳችሁ አልገባችሁም የሚገቡትንም ከለከላችሁ” ሉቃ11፡52 አለ፡፡ ጌታም ለዚህ ትውልድ ከነብዩ ዮናስ በቀር ሌላ ምልክት እንደማይሰጠው ተናገረ፡፡ ይህ ምን ዓይነት ምልክት ነው? ይህ ህዝብ በሰላምና በክብር መሲሁ እጁን ዘርግቶ በርህራሄ የህዝቡን ቁስቁልና እየፈወሰ ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ ቢጠራቸውም እንቢ ስላሉና ስላመጹ ከዚህ በኋላ ሁለት ነገር ከፊታቸው አለ አንዱ ሌላ እድል የሚያገኙት በመከራ ብቻ እንደሆነ እያሳያቸው ነው ምክንያቱም ዮናስ የእግዚአብሔርን ጥሪ እንቢ በማለት በገዛ አሳቡ ተይዞ ወደ ተርሴስ በመርከብ በመሸሹ በአሳ ነባሪ ሆድ ውስጥ ለሶስት ቀንና ሌሊት መከራውን አየ ነገር ግን እግዚብሔር እንደገና እድል ስለሰጠውና ለጥሪው እሺ በማለቱ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ታዝዋል፡፡ ይህም ትውልድ ከዚህ በኋላ ያለው እድል በመከራ መመለስ ብቻ ነው፡፡ ጌታም እንደተናገረው የእስራኤል ህዝብ በብዙ መከራ ውስጥ እያለፉ ብዙዎች በዘመናት መካከል ወደ ጌታ መጥተዋል፡፡ ሁለተኛው መሲሁን ስለሚገድሉ እርሱ በፍጹም ታዛዥነት በሲኦል ሆድ ለሶስ ቀንና ሌሊት እንደሚያድር ተናገረ፡፡ ይህ በአይሁድ የቀን አቆጣጠር አንድ ሰው በአንድ ቀን ውስጥ ለስድስት ሰዓታት ከቆየ እንደ እንድ ቀን ይቆጠራል፣ ቀንን የሚቆጥሩት ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት በመሆኑ ስለዚህ ነው ጌታ ከዓርብ ስድስት ሰዓት እስከ እሁድ አስራ ሁለት ሰዓት በሲኦል ቆይቶ ከዮናስ ጋር ቆይታውን ያነጻጸረው፡፡ በዚህም ምልክቱ መሲሁ እንደተጻፈለት ተገድሎ በትንሳኤ ለአህዛብ ሁሉ የመመለሳቸው ተስፋ ሆኖ ማየት ነው፡፡ 2. የነነዌ ሰዎች "የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፤ በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና፥ እነሆም፥ ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ" ማቴ12:41 ከዚህ በኋላ ያለው ምልክት ግን ተስፋ ሳይሆን ኩነኔና ፍርድ ነው፡፡ የነነዌ ሰዎች አህዛብ ወይም የኪዳን ህዝብ ያልሆኑ ሲሆኑ በአመጻቸው እግዚአብሔር እንደሚፈርድባቸው በነብዩ ዮናስ በኩል አስጠነቀቃቸው ህዝቡ ግን የእግዚአብሔርን ቃል አምነው ከንጉሱ እስከ ወፍጮ እስከምትፈጨው ሰራተኛ ድረስ ትልቅ ትንሽ ሳይሉ ራሳቸውን አዋርደው ለሶስ ቀን በጸሎት በመቆየት ንስሃ ገቡ፣ ተመለሱ በዚህም እግዚአብሔርን አከበሩ እግዚአብሔርም ሊያደርግባቸው ከተናገረው ፍርድ ተመለሰ፡፡ ይህ የኪዳን ህዝብ የሆነው እስራኤል ግን ከነብዩ ዮናስ የሚበልጠው ህግና ነብያት የመሰከሩለት ክርስቶስ በመካከላቸው በፍርድ መንፈስ ሳይሆን በፍቅርና በርህራሄ ድንቆችንና ተአምራቶችን እያደረገ የእግዚአብሔር መንግሥት መቅረብዋን ቢያበስራቸውም እነርሱ ግን ራሳቸውን ዝቅ ልባቸውንም ክፍት ሊያደርጉ አልቻሉም፡፡ ስለዚህ ከዚህ በኋላ ክርስቶስ ፊቱ ወደ አህዛብ እንደሚዞር የሚያመላክት መልእክት እየተናገረ ነበር፡፡ 3. ንግሥት አዜብ "ንግሥተ ዓዜብ በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥታ ትፈርድበታለች፤ የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለችና፥ እነሆም፥ ከሰሎሞን የሚበልጥ ከዚህ አለ" ማቴ:42 ለእስራኤል ወርቃማውን ዘመን ያመጣ የንጉስ ዳዊት ልጅ ሰለሞን እግዚአብሔር በሰጠው ጥበብ፣ ሃብትና ገናናነት በዓለም ያነበሩ ነገሥታት ሁሉ ጥበቡን ለማየት ከዓለም ጫፍ ድረስ ወደ እርሱ ይመጡ ነበር፡፡ ከነዚህ ነገስታት መካከል አንድዋ ኢትዮጵያዊቱ ንግሥት አዜብ አንድዋ ስትሆን እርስዋም በብዙ ስጦታ ወደ ንጉሡ በመምጣት እንቆቅልሽዋን ሁሉ ለንጉሡ አቅርባ ሁሉን ፈታላት፡፡ አሁን ግን ከሰለሞን የሚበልጠው ክርስቶስ ከሩቅ አገር ሳይሆን ከመካከላቸው ተነስቶ እያለ ከጥበቡ ሊቋደሱ፣ በመልእክቱ ሊደነቁ ፈጽሞ አለመፈለጋቸው ምን ያህል አሳዛኝ ክስተት ነው፡፡ ይህች ሴት ግን ለዚህ ክፉ ትውልድ በፍርድ ቀን ከሳሻቸው ሆና ትቆማለች፡፡ ጸጋ ይብዛላችሁ Telegram:- @mentesnotkebede2020 👍 Join በማድረግ እየተቀላቀሉን ሌሎችም እንዲሳተፉ ሼር በማድረግ ይሳተፉ Email:- mentesnot_kebede@yahoo.com ስልክ:- 0911693190
717
15
没有文字...
205
16
ማክሰኞ 12/12/18 የማቴዎስ ወንጌል መልዕክት (ክፍል 48) ዛፍ ከፍሬዋ ትታወቃለች ማቴ12፡33-37 ጌታ ኢየሱስ ፈሪሳውያን በመንፈስ ቅዱስ ላይ የሰነዘሩት የስድብ ቃል በምን ምክንያትና ውጤቱም ምን ሊያስከትል እንደሚችል አሁንም በቀጣዮቹ ቁጥሮች ውስጥ ይናገራል፡፡ ሰዎች የሚናገርዋቸው ቃሎች ማንነታቸውንና ልባቸውን ቁልጭ አድርገው የሚገልጡ እውነተኛ ማስረጃዎች ስለመሆናቸው በሚገባ ይናገራል፡፡ እንዲሁም የመንፈስ ቅዱስን ማንነት ከተግባሩ ወይም ከፍሬው መለየት አይቻልም። የመንፈስ ቅዱስን ሥራ የሚያጣጥል ማንኛውም ሰው የመንፈስ ቅዱስንም ዋጋ እያጣ ብቻ ሳይሆን ሊወጣው ወደማይችል አደገኛ መንገድ ራሱን እየመራ ነው። በሰው ልብ የተሰወረውን መልካም ይሁን ክፉ ጠባይ ገላጭና አጋላጭ የሰው አንደበት ነው፡፡ ጌታ ኢየሱስ በዚህ ክፍል ዛፍንና ፍሬውን በማነጻጸር ይህንን ትልቅ እውነት ይናገራል፡- 1. ውስጥና ተግባር “ዛፍ ከፍሬዋ ትታወቃለችና ዛፍዋን መልካም፥ ፍሬዋንም መልካም አድርጉ፥ ወይም ዛፍዋን ክፉ ፍሬዋንም ክፉ አድርጉ” ማቴ12፡33 መልካም ዛፍ መልካም ፍሬ፣ ክፉ ዛፍ ደግሞ ክፉ ፍሬ ማፍራታቸው የማይለወጥ ተፈጥሮአዊ እውነታ ነው፡፡ ውስጣዊ ዘር ወይም ማንነት በፍሬ ይገለጣል ነገር ግን ወደ ሰው ስንመጣ መልካም የነበረ ሰው ማንነቱን የመለወጥና ፍሬውን የማበላሸት ምርጫ አለው፡፡ እግዚአብሔር ስለ እስራኤል ሲናገር “አሁን ስለ ወዳጄና ስለ ወይን ቦታው ለወዳጄ ቅኔ እቀኛለሁ። ለወዳጄ በፍሬያማው ኮረብታ ላይ የወይን ቦታ ነበረው። በዙሪያው ቈፈረ፥ ድንጋዮችንም ለቅሞ አወጣ፥ ምርጥ የሆነውንም አረግ ተከለበት፥ በመካከሉም ግንብ ሠራ፥ ደግሞም የመጥመቂያ ጕድጓድ ማሰበት፤ ወይንንም ያፈራ ዘንድ ተማመነ፥ ዳሩ ግን ሆምጣጣ ፍሬ አፈራ” ኢሳ5፡1,2 ሰዎች ክፉ ስለመሆናቸው እግዚአብሔር ተጠያቂ አይደለም እርሱ የሰራው ሁሉ መልካም ነው ነገር ግን ሰው ክፉ ማንነትን ፈቅዶ ስለተቀበለ ውጤቱም የማይቀለበስ ክፉ ሆነበት፡፡ ስዚህ ነው ጌታ ዛፍዋን መልካም፥ ፍሬዋንም መልካም አድርጉ በማለት ውስጥን በመቀየር ባህሪን መቀየር እንደሚቻል እየተናገረ ያለው፡፡ 2. የማን መሆን ፍሬው “እናንተ የእፉኝት ልጆች፥ ክፉዎች ስትሆኑ መልካም ለመናገር እንዴት ትችላላችሁ? በልብ ሞልቶ ከተረፈው አፍ ይናገራልና” ማቴ12፡34 እስራኤላውያን በኪዳን የእግዚአብሔር ልጆች ነበሩ ነገር ግን ወላጅ ቀይረዋል ራሳቸውን የእፉኝት ወይም የሰይጣን ልጆች አድርገዋል፡፡ ለዚህ የማንነት ቅየራ ምክንያት የሆነው አጣመው የተማሩት ትምህርት ነው፡፡ ክፉ ትምህርት ራስን ለጠላት አሳልፎ ይሰጣል፣ ትምህርት ባህርይን ይቀርጻል፡፡ ውስጣዊ ማንነት መገለጫው ደግሞ የሰው አንደበት ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች መጽሐፍት የመሰከሩለትን ጌታ መሳደባቸው እነዚያን መጽሐፍትን ለገዛ ፈቃዳቸው አጣመው በመረዳታቸው ነው፡፡ ስለዚህ ነው ልባቸውን የሞላው ክፉ ትምህርት ክፉ እንዲያፈሩ አደረጋቸው ጌታ የልብንና የአንደበትን ቁርኝት አንዱ የሌላው መገለጫ ስለመሆኑና ህይወቱን እንዴት እንደሚመርዘው ሲናገር “በልብ ሞልቶ ከተረፈው አፉ ይናገራልና መልካም ሰው ከልብ መልካም መዝገብ መልካሙን ያወጣል፥ ክፉ ሰውም ከልብ ክፉ መዝገብ ክፉውን ያወጣል” ሉቃ6፡45 3. ቃልና ፍርድ “እኔ እላችኋለሁ፥ ሰዎች ስለሚናገሩት ስለ ከንቱ ነገር ሁሉ በፍርድ ቀን መልስ ይሰጡበታል፤ ከቃልህ የተነሣ ትጸድቃለህና ከቃልህም የተነሣ ትኰነናለህ” ማቴ12፡36,37 ከአፍ የወጣ ነገር ውጤት ይዞ ይመለሳል እንጂ እንዲሁ አየር ላይ አይቀርም፡፡ የአንደበት ቃል ህይወትን ወይም ሞትን የማፍራት ኃይል አለው ጠቢቡ ሲናገር “የሰው ሆድ ከአፉ ፍሬ ይሞላል፥ ከንፈሩም ከሚያፈራው ይጠግባል። ሞትና ሕይወት በምላስ እጅ ናቸው፤ የሚወድዱአትም ፍሬዋን ይበላሉ” ምሳ18፡20,21 እንዲሁ በአንደበት ምክንያት ሰው ጽድቅን ወይም ኩነኔን ወደ ህይወቱ ይጠራል፡፡ በፍርድ ቀን የሚታየው የሰው ልብ ሳይሆን የአንደበቱ ቃል መሆኑን ጌታ ሲናገር “እኔ እላችኋለሁ፥ ሰዎች ስለሚናገሩት ስለ ከንቱ ነገር ሁሉ በፍርድ ቀን መልስ ይሰጡበታል …” አንደበት ትልቅ ጥንቃቄ የሚፈልግ በመሆኑ ያዕቆብ ሲናገር “ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ሰው ሁሉ ለመስማት የፈጠነ ለመናገርም የዘገየ ለቍጣም የዘገየ ይሁን” ያዕ1፡19 ይላል፡፡ ያለ ጥንቃቄ እንደ ልብ መናገር አደጋው እጅግ ብዙ በመሆኑ አንደበትን መጠበቅ አስፈላጊ ነገር ነው፡፡ ያዕቆብ ሲናገር አንደበቱን መግዛት የቻለ ሰው በኃጢአት ላይ ድልን ያገኘ ሰው ስለመሆኑ ይናገራል “ሁላችን በብዙ ነገር እንሰናከላለንና፤ በቃል የማይሰናከል ማንም ቢኖር እርሱ ሥጋውን ሁሉ ደግሞ ሊገታ የሚችል ፍጹም ሰው ነው” ያዕ3፡2 ጸጋ ይብዛላችሁ Telegram:- @mentesnotkebede2020 👍 Join በማድረግ እየተቀላቀሉን ሌሎችም እንዲሳተፉ ሼር በማድረግ ይሳተፉ Email:- mentesnot_kebede@yahoo.com ስልክ:- 0911693190
238
17
ሰኞ 11/12/18 የማቴዎስ ወንጌል መልዕክት (ክፍል49) እውርና ዲዳ መንፈስ /02/ ማቴ12፡22-32 5. የእግዚአብሔር መንግሥት ቀርባለች “እኔ ግን በእግዚአብሔር መንፈስ አጋንንትን የማወጣ ከሆንሁ፥ እንግዲህ የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ እናንተ ደርሳለች” ማቴ12፡28 አጋንንት የሰይጣን ጭፍሮች፣ የወደቁ መላእክት ናቸው፡፡ ይህ የመናፍስቱ ዓለም በሥልጣን ተዋረድ የተደራጀ፣ መዋቅር ያለው እርስ በእርሱ አንዱ ሌላውን ሳይቃወም የሚሰራ፣ የጨለማ ኃይላት ናቸው፡፡ እነዚህ መናፍስቶች በዓየር ላይ ሥልጣን ያላቸው ሲሆን ያለ ክርስቶስ የሆነውንና ከኃጢአት በታች የወደቀውን ዓለም በሙሉ በማስጨነቅ የሚገዙ ናቸው “በበደላችሁና በኃጢአታችሁ ሙታን ነበራችሁ፤ በእነርሱም፥ በዚህ ዓለም እንዳለው ኑሮ፥ በማይታዘዙትም ልጆች ላይ አሁን ለሚሠራው መንፈስ አለቃ እንደ ሆነው በአየር ላይ ሥልጣን እንዳለው አለቃ ፈቃድ፥ በፊት ተመላለሳችሁባቸው” ኤፌ6፡1,2 ይኸው መንፈስ በተደራጀ መንገድ የሚሰራ ስለመሆኑ ጳውሎስ ሲናገር “መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ” ኤፌ6፡12 ከዚህም የተነሳ ጌታ በዚህ ስፍራ እንዳደረገው ሰውን በማጥቃት፣ ዲዳና ደንቆሮ በማድረግ የሚሰራውን ይህን ኃይል ድል በመንሳት ሰውን ነጻ አወጣ፣ ይህ የሚያሳየው ሌላ ከመናፍስቱ ኃይል በላይ የሚልቅ የእግዚአብሔር ኃይል በመካከላቸው እንደመጣ የሚያለመክት ነው፡፡ ስለዚህ ነው “በእግዚአብሔር መንፈስ አጋንንትን የማወጣ ከሆንሁ፥ እንግዲህ የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ እናንተ ደርሳለች” በማለት የሚሟገታቸው፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ሥልጣን በብሉይ ኪዳን በነበሩ አገልጋዮች ዘንድ አልነበረም፡፡ 6. ኃይለኛውን የማሰር ውጤት “ወይስ ሰው አስቀድሞ ኃይለኛውን ሳያስር ወደ ኃይለኛው ቤት ገብቶ እቃውን ሊነጥቀው እንዴት ይችላል? ከዚያም ወዲያ ቤቱን ይበዘብዛል” ማቴ12፡29 መናፍስት ይህን ዓለም በይገባኛል፣ እንደራሱ ንብረት ይዞ ይሰራል፡፡ ሰዎችም በግልጽም እንዲሁም በተለያየ ኃይማኖታዊ ሽፋን እያመለኩ ይሰግዱለታል፡፡ ኃይለኛ በመሆኑ በሰው አቅም የሚደፈር አይደለም፡፡ ሰውን ሁሉ በሞት ፍርሃት አስረው ያኖራሉ “እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥ በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ …” ዕብ2፡15 ሰይጣን ድል ሊነሳው ያልቻለ ከሰው ልጆች መካከል አንድ ኃይለኛ ሰው ወደ ዓለም እንደገባ አውቋል ጌታ አርባ ቀን ከጸለየ በኋላ ሊፈትነው ቀረበ፣ ሰውን ሁሉ ያንበረከከበትን ፈተና አቀረበለት ጌታ ግን ፈተናዎቹን በሙሉ ከንቱ በማድረጉ ለጊዜው ሳይወድ በግዱ በሩን ከፍቶ አስገባው ለዚህም ነው ለሰዎች የእግዚአብሔር መንግስት መቅረቡን እያወጀ፣ ሰይጣን በልዩ ልዩ በሽታ ያሰቃያቸውን እየፈወሰ ሲዞር አንዳች ሊያደርገው ያልቻለው፡፡ ጴጥሮስ ሲናገር “እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበረና” ሐዋ10፡38 ኢየሱስ በመጨረሻ በመስቀል ስራው ለዘላለም አለቅነቱንና ሥልጣኑን በመግፈፍ ድል ነሳው ቆላ2፡15 አሁን ሥልጣን በሰማይና በምድር የክርስቶስ በመሆኑ በእርሱ የሚያምኑ በሙሉ የዚህ ስልጣን ተካፋይ ሆኑ በዚህም ቤተክርስቲያን የኃይለኛውን ቤት እየበዘበዘች ትገኛለች፡፡ ጉዳዩ የኃይል ነው፡፡ የጌታ ልጆች ይህን ስልጣን ጸልየው ወይም ተቀድሰው የሚያገኙት ሳይሆን በክርስቶስ የተሰጣቸው በመሆኑ በእምነት ሊጠቀሙበት ይገባል፡፡ 7. የመሳደብ ኃጢአት አይሰረይም “ስለዚህ እላችኋለሁ፥ ኃጢአትና ስድብ ሁሉ ለሰዎች ይሰረይላቸዋል፥ ነገር ግን መንፈስ ቅዱስን ለሰደበ አይሰረይለትም” ማቴ12፡31 ፈሪሳውያን ዲዳና ደንቆሮ መንፈስ የነበረበትን ሰው ጌታ መንፈሱን አስወጥቶ ነጻ እንዳወጣው፣ እንደፈወሰው በሰሙ ጊዜ በአጋንንት አለቃ ነው አጋንንትን የሚያወጣው በማለት ክፉ ንግግር ተናገሩ፡፡ ይህንን ሲናገሩ እየሰደቡ የነበረው በክርስቶስ አድሮ ይሰራ የነበረውን መንፈስ ቅዱስን ነበር፡፡ ስለዚህም ጌታ በአዲስ ኪዳን ይቅር ስለማይባል አንድ አስከፊ ኃጢአት ተናገረ እርሱም መንፈስ ቅዱስን መሳደብ ወይም እርሱን መቃወም ነው፡፡ ይህ ኃጢአት አብዛኛውን ጊዜ በአማኝ የሚሰራ ሳይሆን በማያምኑ ሰዎች የሚሰራ ኃጢአት ነው፡፡ ማንም በመንፈስ ቅዱስ እየተሰራ ያለን የጌታን ሥራ መቃወም የለበትም፣ ለምሳሌ የጌታ ልጅ ሆኖ አንዳንድ ጊዜ ከእርሱ አስተምህሮ ውጪ የሆኑ ናቸው ብሎ የሚላቸውን ሰዎች የሰይጣን ናቸው ከማለት በፊት በቃሉ መመርመር፣ ሰዎች ስላሉ ብቻ ከእነርሱ ጋር አብሮ ክፉ ነገር አለመናገር፣ የጌታን መንፈስ ማዳመጥ፣ ጊዜ በመውሰድ ጉዳዩን በሚገባ ማጤን ያስፈልገዋል፡፡ መንፈስ ቅዱስን መሳደብ የመንፈስ ቅዱስን ስራ ለሰይጣን መስጠት ነው፡፡ እንዲህ አይነት ተቃውሞ የሚያሰሙ ሰዎች ከዚህ ተግባራቸው ከተመለሱና በዚያ አቋማቸው ጸንተው የህይወት ዘመናቸውን ካልጨረሱ ልክ እንደ ጳውሎስ ባለማወቅ እያደረጉት በመሆኑ ምህረትን ያገኛሉ፡፡ 1ጢሞ1፡13 አንዳንዶች መንፈስ ቅዱስን ሰድቤ ይሆናል ብለው የሚጨነቁ ሰዎች ጭንቀታቸው በራሱ በዚህ ኃጢያት አለመያዛቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ ነገር ግን ይህን ኃጢአት ሰርቶ ይቅር ወደማይባል ደረጃ የደረሰ ሰው ልቡ ስለሚደነድን አይጨነቅም ደግሞም ምንም ዓይነት የጸጸት መንፈስ አይታይበትም፡፡ ጸጋ ይብዛላችሁ Telegram:- @mentesnotkebede2020 👍 Join በማድረግ እየተቀላቀሉን ሌሎችም እንዲሳተፉ ሼር በማድረግ ይሳተፉ Email:- mentesnot_kebede@yahoo.com ስልክ:- 0911693190
223
18
ዓርብ 08/12/18 የማቴዎስ ወንጌል መልዕክት (ክፍል48) የተዓምራት ኃይልና ተቃውሞው /01/ ማቴ12፡22-32 የእግዚአብሔር ኃይል በተገለጠበት ስፍራ ሁሉ ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ አለ፡፡ ለዚህም ደግሞ ሰይጣንና ክፉ ልብ ያላቸው ሰዎች ተቀናጅተው የሚሰሩት ስራ ነው፡፡ ጌታ ኢየሱስ የሰው ልጅ ያለበትን ትልቅ ቀውስ ስለሚያውቅ የእርሱን እርዳታ ፈልገው ወደ እርሱ ለሚመጡና ለሚቀርቡ ሁሉ በብዙ ርህራሄ በፈቃደኝነት መፍትሄ ይሰጣቸው ነበር፡፡ ጴጥሮስ ሲናገር “እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበረና” ሐዋ10፡38 በዚህ ክፍል እውርም ዲዳም የሆነን ሰው ወደ ጌታ አምጥተው ጌታ ኢየሱስ ፈወሰው ስለዚህ ሰውዬው አየ፣ ደግሞም ተናገረ፡፡ ማቴዎስ ተፈወሰ ይላል ሌሎች ወንጌላት ግን ፈውሱ የተከናወነበት ዋንኛ ምክንያት፣ እርሱም አጋንንት ከዚህ ሰው ህይወት በመውጣቱ እንሆነ ይነግሩናል፡፡ ከብዙ ክፉ ነገሮች በስተጀርባ ያለው ዲያቢሎስ መሆኑን እናያለን፡፡ እንደዚህ የዲያቢሎስን መንግሥት ኪሳራ ውስጥ እየከተተ ያለ አገልግሎት መነቀፉ፣ ተቃውሞን ማስተናገዱ የማይቀር እውነታ ነው፣ ለዚህም ተቃውሞ የሚያስከትለውን ውጤትና የጌታን መልስ እናያለን፡- 1. አትጠራጠር “ሕዝቡም ሁሉ ተገረሙና፦ እንጃ ይህ ሰው የዳዊት ልጅ ይሆንን? አሉ” ማቴ12፡23 ትችት፣ ተቃውሞ፣ ጥርጣሬና አለማመን ባለበት ስፍራ ሁሉ በሌሎች ህይወት የሚያሳድረው ተጽዕኖ ቀላል የሚባል አይደለም፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ፈውስ ካላስደነቀን ምን ሌላ ነገር ሊኖር ነው፡፡ መቼም ይህ ሰዎችን የሚያስደምም ትሪክ አይደለም፣ ተጨንቆና ታስሮ ለነበረ ሰው መፍትሄ የሰጠ እውነታ እንጂ፡፡ ለዚህ ዓይነት ክፉ ትችትና ነቀፋ ጆሮን የሚሰጥ ሰው እምነቱን ሽባ ያደርግበታል፡፡ ይህንን ታላቅ ነገር ሰዎች እያዩ እንጃ ይህ ሰው የዳዊት ልጅ ይሆንን? አሉ ለምን ጥርጣሬ? ምክንያቱም በዙሪያቸው ያለው ተጽዕኖ ነው ይህንን የፈጠረው፡፡ ስለዚህ ትችትንና፣ ተቃውሞን ከሚያሰሙ ሰዎች በመራቅ የትኛውንም ነገር በቃሉ ወደ መመዘን መምጣት ይገባል ጳውሎስ ሲናገር “ሁሉን ፈትኑ መልካሙንም ያዙ፤ ከማናቸውም ዓይነት ክፉ ነገር ራቁ” 1ተሰ5፡21,22 ይህ ነው እምነታችንን የሚገነባው፡፡ 2. መልካም ምላሽ የላቸውም “ፈሪሳውያን ግን ሰምተው፦ ይህ በብዔል ዜቡል በአጋንንት አለቃ ካልሆነ በቀር አጋንንትን አያወጣም አሉ” ማቴ12፡24 በዓላማ ዓይናቸውን የጨፈኑ፣ በፈቃደኝነት ልባቸውን የዘጉ ሰዎች በምንም መንገድ መልካም ነገር ሊያስቡም ሊናገሩም አይችሉም፡፡ ፈሪሳውያን ይህንን አስገራሚ የፈውስ ምስክርነት ሲሰሙ በአጋንንት አለቃ ነው አጋንንትን የሚያወጣው አሉ፡፡ ለሁሉ ነገር ትችት፣ ለሁሉ ነገር ተቃውሞ የሚያሰሙ ሰዎች ፈጽሞ ጤና የሆነ መንፈስ እንደሌላቸው አመላካች ነው፡፡ ይህ ስድብ ነው፣ ስድብ ደግሞ አንዱ የሰይጣን መለያው ነው፡፡ ዮሐንስ በራዕዩ ያየውን ሲናገር “ታላቅንም ነገርና ስድብን የሚናገርበት አፍ ተሰጠው፥ በአርባ ሁለት ወርም እንዲሠራ ሥልጣን ተሰጠው። እግዚአብሔርንም ለመሳደብ ስሙንና ማደሪያውንም በሰማይም የሚያድሩትን ሊሳደብ አፉን ከፈተ” ራዕ13፡5,6 ዛሬም እንዲህ አይነት ድፍረት የተሞሉና እውነተኛ የጌታ ስራ እየተሰራ፣ ሰዎች ነጻ እየወጡና ሰላም እየሆኑ እያዩ በልብ ድንዳኔና ሌሎች ስለነቀፉአቸው ያለምንም ማስረጃ ከአጋንንት ነው ለማለት የሚደፍሩ ሰዎች አሉ፡፡ ይህ አደገኛ ድርጊት ነው፣ ሰይጣን ሰውን የሚጠቅም አንዳች ስራ የለውም፡፡ ጌታም ለተከታዮቹ ሲያስጠነቅቅ “ደቀ መዝሙር እንደ መምህሩ፥ ባሪያም እንደ ጌታው መሆኑ ይበቃዋል። ባለቤቱን ብዔል ዜቡል ካሉት፥ ቤተሰዎቹንማ እንዴት አብዝተው አይሉአቸው!” ማቴ10፡15 3. መንግሥት ተለያይቶ አይቆምም “ኢየሱስ ግን አሳባቸውን አውቆ እንዲህ አላቸው፦ እርስ በርስዋ የምትለያይ መንግሥት ሁላ ትጠፋለች፥ እርስ በርሱ የሚለያይ ከተማም ሁሉ ወይም ቤት አይቆምም” ማቴ12፡25 ጠቢቡ “አንተ ደግሞ እርሱን እንዳትመስል ለሰነፍ እንደ ስንፍናው አትመልስለት” ምሳ26፡4 እንደሚል ጌታ ለስድባቸው ስድብ አልመለሰም ነገር ግን ጨዋነት በተሞላ መንገድ ትልቅ ትምህርት ለዓለም የሰጠ ምላሽ ሰጠ፡፡ አንድነት ኃይል የመሆኑ ጉዳይ አይደለም በቤተክርስቲያን፣ በቤተሰብና በመንግሥት በሰይጣንም መንግሥት ውስጥ እንኳ የሚሰራ የማይለወጥ ዓለማቀፋዊ መርህ መሆኑን ተናገረ፡፡ አንድ ህብረት እርስ በእርሱ ከተለያየ ሊቆም ፈጽሞ አይችልም፡፡ ጳውሎስ በቅዱሳን መካከልም እንኳ ያለ መከፋፈል ጥፋትን ሊያመጣ ችንደሚችል ሲናገር “ነገር ግን እርስ በርሳችሁ ብትነካከሱና ብትበላሉ እርስ በርሳችሁ እንዳትጠፋፉ ተጠንቀቁ” ገላ5፡15 ስለዚህ አጋንንት አጋንንትን ካወጣ መንግሥቱ ልትቆም አትችልም፡፡ የአመጽ ሰራተኞችም የአመጽ ስራቸውን ለመፈጸም ምን ያህል እርስ በእርሳቸው መናበብና መቀባበል ሊኖራቸው እንደሚችል ተናገረ፡፡ 4. ልጆቻቸው ምስክር ይሆኑባቸዋል “እኔስ በብዔል ዜቡል አጋንንትን የማወጣ ከሆንሁ፥ ልጆቻችሁ በማን ያወጡአቸዋል? ስለዚህ እነርሱ ፈራጆች ይሆኑባችኋል” ማቴ12፡27 አንዳንድ የአይሁድ የታልሙድ ጽሁፎች እንደሚያሳዩት አይሁዳውያኑ በክፉ መንፈስ የተያዙ ሰዎችን ነጻ ለማውጣት የሚያደርጉአቸው ልምምዶች አሉ፡፡ ሉቃስም በሐዋርያት ሥራ ላይ የዚህን የአጋንንት ማስወጣት ልምምድ በአይሁድ መካከል እንዳለ የጠቆመ አንድ አሳብ ሰንዝሮአል “አጋንንትንም እያወጡ ይዞሩ ከነበሩት አይሁድ አንዳንዶች፦ ጳውሎስ በሚሰብከው በኢየሱስ እናምላችኋለን እያሉ ክፉዎች መናፍስት ባሉባቸው ላይ የጌታን የኢየሱስን ስም ይጠሩባቸው ዘንድ ሞከሩ” ሐዋ19፡13 ስለዚህ ጌታ እንደ ሎጂክ ያነሳላቸው ነገር ቢኖር እኔ አጋንንትን በአጋንንት አለቃ የማስወጣ ከሆነ የናንተን ልጆች ምን ያስወጣሉ ልትሉአቸው ነው? የሚል ሞጋች ጥያቄ አቀረበላቸው፡፡ ይህ ዓይነቱ ልምምድ በኛም አገር በአንዳንድ ኃይማኖቶች ውስጥ አለ፣ አጋንንትን ውጣ እያሉ ሲያስጮሁ፣ አጋንንቱ ይሁን ሰውዬው ባይታወቅም ወጣን እያለ ሲጮህ እናያለን፡፡ መታወቅ ያለበት አጋንንት ሥራውን ባፈረሰ፣ በመናፍስቱ ዓለም ላይ ሥልጣን ባለው በክርስቶስ ስም ካልሆነ በቀር መናፍስት ታዘው አይወጡም፡፡ ጸጋ ይብዛላችሁ Telegram:- @mentesnotkebede2020 👍 Join በማድረግ እየተቀላቀሉን ሌሎችም እንዲሳተፉ ሼር በማድረግ ይሳተፉ Email:- mentesnot_kebede@yahoo.com ስልክ:- 0911693190
218
19
ሐሙስ 07/12/18 የማቴዎስ ወንጌል መልዕክት (ክፍል47) የእግዚአብሔር ምርጡ አገልጋይ ማቴ12፡15-21 ፈሪሳውያን ኢየሱስን ከመቃወማቸውና ከመጥላታቸው የተነሳ ሊገሉት ተማከሩ፡፡ ይህ አገልጋይ ግን ለላከው፣ እነርሱ አምላካችን ለሚሉት አባቱ ደግፎ የያዘው ምርጡ አገልጋይ ነው ነብዩ ኢሳይያስ በትንቢቱ “እነሆ ደግፌ የያዝሁት ባሪያዬ፤ ነፍሴ ደስ የተሰኘችበት ምርጤ፤ በእርሱ ላይ መንፈሴን አድርጌአለሁ፥ እርሱም ለአሕዛብ ፍርድን ያወጣል” ኢሳ42፡1 ይላል፡፡ አገልግሎት ከኢየሱስም ጀምሮ ጦርነት በመሆኑ ሰዎች፣ ሁኔታዎች ስለኛ የሚሉትን እያየን ተስፋ መቁረጥ የለብንም ይልቁንም ቃሉና የላከን ስለእኛ የሚለውን በመስማትና በማወቅ ሩጫችንንና አገልግሎታችንን ለመፈጸም መጽናት ያስፈልገናል፡፡ በእውነት እየሄድን ሰዎች ሲገፉንና ሲጠሉን ይህ እንግዳ ነገር አይደለም ጌታም እንዲህ ብሎአል “ባርያ ከጌታው አይበልጥም ብዬ የነገርኋችሁን ቃል አስቡ። እኔን አሳደውኝ እንደ ሆኑ እናንተን ደግሞ ያሳድዱአችኋል …” ዮሐ15፡20 በዚህ ክፍል ፈሪሳውያን ኢየሱስ ላይ ሲያደቡ ማቴዎስ ስለ አገልጋዩ ከትንቢተ ኢሳይያስ ጠቅሶ አስቀድሞ ስለ እርሱ የተባለውን ይነግረናል፡፡ እነዚህን አሳቦች እንመልከት፡- 1. ለሁሉ መልስ አለው “ኢየሱስም አውቆ ከዚያ ፈቀቅ አለ። ብዙ ሰዎችም ተከተሉት፥ ሁሉንም ፈወሳቸው፥ እንዳይገልጡትም አዘዛቸው” ማቴ12፡15 ኢየሱስ ፈሪሳውያን ምን እየተማከሩ እንዳለ ሲረዳ እነሱን ለመመከትና ለመቋቋም ስጋዊ ጦርነት አልከፈተም ነገር ግን ከእነርሱ ፈቀቅ በማለት እርሱ በተላከበት ስራ ላይ ራሱን ጠምዶአል፡፡ ክፉዎች ምንም ያድርጉ የእግዚአብሔር አገልጋይ ራሱን እንዲህ በሚመስል ነገር ሊጠምድ አይገባም ጳውሎስ ሲናገር “ነገር ግን ጠብን እንዲያመጣ አውቀህ ከሰነፎችና ካልተማሩ ምርመራ ራቅ፤ የጌታም ባሪያ ለሰው ሁሉ ገር ለማስተማርም የሚበቃ ለትዕግሥትም የሚጸና ሊሆን እንጂ ሊጣላ አይገባውም” 2ጢሞ2፡23,24 በዚህ ሁኔታ ውስጥ እያለ ብዙ በሽተኞች ወደ እርሱ ሲመጡ ሲያይ ሁሉንም ፈወሳቸው፡፡ ይህ አስደናቂና ግልጽ ነገር ነው ወደ እርሱ ለመጡ በሽተኞች ሁሉ ያለው ፈቃዱ አንድ ነው እርሱም ፈውስ፣ ደህና መሆን ነው፣ ዛሬም የመይለወጥ ፈቃዱ ይኸው ነው፡፡ በአዲስ ኪዳን በወንጌላት ውስጥ ወደ አስራ ሰባት የሚሆኑ ሁሉንም ፈወሳቸው የሚሉ ጥቅሶች እናገኛለን (ማቴዎስ 4:23-24፣ 8:16-17፣ 9:35፣ 12:15፣ 14:14፣ 34-36፣ 15:30-31፣ 19:2፣ 21:14፤ ማርቆስ 1:32-34፣ 39፣ 6:56፤ ሉቃስ 4:40፣ 6:17-19፣ 7:21፣ 9:11፤ እና 17:12-17) እርሱ ግን ህዝቡ እንዳይገልጡትና የተደረገላቸውን እየተናገሩ ይበልጥ የጠላቶቹን ቁጣና ቅንዓት እንዳያባብሱ ለማንም እንዳይናገሩ ያዛቸው ነበር፡- 2. ፍርድን ያወጣል “እነሆ የመረጥሁት ብላቴናዬ፥ ነፍሴ ደስ የተሰኘችበት ወዳጄ፤ መንፈሴን በእርሱ ላይ አኖራለሁ፥ ፍርድንም ለአሕዛብ ያወራል። አይከራከርም አይጮህምም፥ ድምፁንም በአደባባይ የሚሰማ የለም” ማቴ12፡18,19 እግዚአብሔር በነብዩ ሲሳይያስ በኩል ስለ አገልጋዩ ሲናገር የመረጠው፣ ነፍሱ ደስ የምትሰኝበት እንደሆነ ተናገረ ይህንኑ አሳብ በመገለጥ ተራራ ላይ ለጆሮ በሚሰማ መልኩ “… በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ” ማቴ17፡5 እርሱ በመንፈስ ቅዱስ የተቀባ ለሰው ልጆች፣ ለአህዛብ ሁሉ ፍርድን የሚያወጣ ማለትም በብዙ ለተጨቆኑት፣ ለተጠቁት መፍትሄ የሚሰጥ፣ የመፍትሄ ቃል ያለው ነው፡፡ ስለዚህም ነው ወደ እርሱ የሚመጡትን ሁሉ በብዙ ርህራሄ ይፈውሳቸው፣ ከመከራቸውና ከአበሳቸው ነጻ በማውጣት ለህዝቡ እረፍትን እየሰጠ ያለው፡፡ እርሱ ከማንም ጋር አይሟገትም አይከራከርም፣ ምንም እንኳ እርሱ የአደባባይ አገልጋይ ቢሆንም እርሱ ከተላከበት ስራ ውጪ በአደባባይ በሌላ ጉዳይ ድምጹ አልተሰማም፡፡ 3. አህዛብ ተስፋ ያደርጉታል “ፍርድን ድል ለመንሣት እስኪያወጣ፥ የተቀጠቀጠን ሸምበቆ አይሰብርም የሚጤስን የጥዋፍ ክርም አያጠፋም። አሕዛብም በስሙ ተስፋ ያደርጋሉ” ማቴ12፡20,21 አይሁዳውያን እንደሚያስቡት የሚመጣው መሲህ የእነርሱ ብቻ ሳይሆን አህዛብ ሁሉ ተስፋ የሚያደርጉት በመንፈስ ነጻ አውጪ ነው፡፡ አስቀድሞ እግዚአብሔር ለአብርሃም ተስፋ ሲሰጠው “… የምድር ነገዶችም ሁሉ በአንተ ይባረካሉ” ዘፍ12፡3 ብሎታል፡፡ እርሱ የተቀጠቀጠን ሸንበቆ አይሰብርም፣ ሸንበቆ ከተቀጠቀጠ ቀጥ ብሎ ስለማይቆም ይቆርጡታል እንዲሁም የሚጤስ የጥዋፍን ክር አያጠፋም፣ ዘይቱ ያለቀበት የጧፉ ክር ዝም ብሎ ስለሚጨስ ያደርጉ የነበረው ያንን የሚጤስ ክር እፍ በማለት ያጠፉታል፡፡ ጌታ ግን እጅግ ተስፋ የቆረጡትን፣ የመኖር ተስፋ የሌላቸውን፣ የተረሱትን፣ ቀምበር የተሸከሙትን ነጻ እያወጣ ተስፋቸውን በማደስ የህዝብን ተስፋ ያለመልማል፡፡ ስለዚህ አህዛብ በስሙ ተስፋ ያደርጋሉ፡፡ ጸጋ ይብዛላችሁ Telegram:- @mentesnotkebede2020 👍 Join በማድረግ እየተቀላቀሉን ሌሎችም እንዲሳተፉ ሼር በማድረግ ይሳተፉ Email:- mentesnot_kebede@yahoo.com ስልክ:- 0911693190
216
20
ረብዕ 06/12/18 የማቴዎስ ወንጌል መልዕክት (ክፍል 47) ግብዝ የሆነ ተቃውሞ ማቴ12:9- ሰው ባለማወቅ ብቻ ሳይሆን በራስ ወዳድነት ሲመላለስ ሌላውን ሲኮንን፣ ሲቃወም ይገኛል፡፡ አለማወቅም ሆነ ራስ ወዳድነት ዓይንን ማጨለማቸው ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሔር ሥራ እንቅፋቶችም ናቸው፡፡ ጌታ ኢየሱስ በማቴ7 ላይ በዓይኑ ግንድ ተሸክሞ ከሌላው ሰው ዓይን ጉድፍ ላውጣ ስለሚል ግብዝ ሰው ምሳሌ ሲሰጥ “እንዳይፈረድባችሁ አትፍረዱ፤ በምትፈርዱበት ፍርድ ይፈረድባችኋልና፥ በምትሰፍሩበትም መስፈሪያ ይሰፈርባችኋል። በወንድምህም ዓይን ያለውን ጉድፍ ስለምን ታያለህ፥ በዓይንህ ግን ያለውን ምሰሶ ስለ ምን አትመለከትም? ወይም ወንድምህን፦ ከዓይንህ ጉድፍ ላውጣ ፍቀድልኝ እንዴትስ ትለዋለህ? እነሆም፥ በዓይንህ ምሰሶ አለ። አንተ ግብዝ፥ አስቀድመህ ከዓይንህ ምሰሶውን አውጣ፥ ከዚያም በኋላ ከወንድምህ ዓይን ጉድፉን ታወጣ ዘንድ አጥርተህ ታያለህ” ማቴ7፡1-5 ፈሪሳውያን ሰንበትን ስለማክበርና በሰንበት ሥራ እንዳይሰራ በመከላከል ወገባቸውን ታጥቀው የሟገታሉ ነገር ግን በቀዳሚነት ሰንበትን የሚጥሱትና የማያከብሩት ራሳቸው ሆነው መገኘታቸውን ጌታ አጋለጠ፡፡ እውነትን በመያዝ የሰዎችን ስውርና ክፉ ገበና መግለጥ እንዲህ ቀላል ነገር አይሆንም ስለዚህም ነው ፈሪሳውያን ኢየሱስን እንዴት እንዲያጠፉት ሲማከሩ የተገኙት “ፈሪሳውያን ግን ወጥተው እንዴት አድርገው እንዲያጠፉት ተማከሩበት” ማቴ12፡14 እውነትን በአመጻ መከልከል ማለት ይህ ነው ሮሜ1፡18 እንዲህ አይነት ሰው፡- 1. ወጥመድ ያዘጋጃል "እነሆም፥ እጁ የሰለለች ሰው ነበረ፤ ይከሱትም ዘንድ፡— “በሰንበት መፈወስ ተፈቅዶአልን?” ብለው ጠየቁት" ማቴ12:10 ከኢየሱስ ፈውሳቸውን ለመቀበል የተለያየ ዓይነት ችግርና በሽታ ያለባቸው ሰዎች እርሱ በተገኘበት ሁሉ ይገኙ ነበርና አንድ እጁ የሰለለች በሽተኛ ሰው በአንዱ ጉባኤ ተገኝቶአል፡፡ ይህንን ተገን በማድረግ እለቱ ሰንበት ስለ ነበር ሰውዬውን በመፈወስ ሰንበትን ይሽር እንደሆነ ቁጭ ብለው በማስረጃ ለማየትና ለመክሰስ በሰንበት መፈወስ ተፈቅዶአልን? ብለው ጠየቁት፡፡ ሰንበትን የሰጠ እርሱ ነው “የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ” ዘጸ20፡8 የሚለው ከአስርቱ ትዕዛዛት አንዱ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ህግን ፈጽሞ በእግዚአብሔር ፊት የጸደቀና ወደ እረፍቱ የገባ አንድም ሰው ስላልተገኘ እግዚአብሔር የራሱን ጽድቅ ለሚያምኑ ሁሉ በመስጠት ወደ እረፍቱ ሊያስገባ አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታአል፡፡ አሁን ቀንን በማክበር የሚመጣ እረፍት ስለሌለ እግዚአብሔር ራሱ በስራ ላይ ነው ስለዚህ ነው ጌታ “አባቴ እስከ ዛሬ ይሠራል እኔም ደግሞ እሠራለሁ ብሎ መለሰላቸው” ዮሐ5፡17 ይህንንም በተግባር በማሳየት እረፍትን የማያውቃትን ይህንን ሽባ ሰው በሰንበት ቀን በመፈወስ እረፍት ሰጠው፡፡ የኃይማኖት ሰው ዋና ትኩረቱ ሥርዓት ማስከበር እንጂ ስለ ሰው ግድ የለውም ስለዚህም ነው ሰውዬውን ለመክሰሻ ለመጠቀም ያሰቡት፡፡ 2. ራሱ ያንን ያደርጋል "እርሱ ግን፡— “ከእናንተ አንድ በግ ያለው በሰንበት በጉድጓድ ቢወድቅበት፥ ይዞ የማያወጣው ሰው ማን ነው?" ማቴ12:11 እነዚህ ሰዎች ግብዝ በመሆናቸው የለበሱትን ሽፋን ጌታ ገፈፈባቸው እነርሱ በሰዎች ፊት ጻድቅ ናቸው በጓዳቸው ግን በአደባባይ የሚያወግዙትን የንኑ ነገር በቀዳሚነት የሚያፈርሱና የሚፈጽሙ እነርሱ ናቸው፡፡ ስለዚህ ጌታ ከእናንተ በጉ ጉድጓድ ቢገባበት ማለትም በጉ ችግር ላይ ቢወድቅበት የሰንበትን ህግ ሽሮ በጉን ከጉድጓድ የማያወጣ ማን ነው? እንግዲህ ሰው ከበግ እንዴት አይበልጥ በማለት ሲናገር ጥርሳቸውን ከመንከስ ውጪ ምላሽ አልነበራቸውም፡፡ እነርሱ ጋር ሲሆን ችግር የሌለው ሥርዓት ለሌላው ሲሆን ግን ለእግዚአብሔር ተርቋሪ በመምሰል ይቃወማሉ ስለ እንደነዚህ ያሉ ሰዎች ጳውሎስ ሲናገር “አንተ የምትፈርድ ሰው ሁሉ ሆይ፥ የምታመካኘው የለህም፤ በሌላው በምትፈርድበት ነገር ራስህን ትኰንናለህና፤ አንተው ፈራጁ እነዚያን ታደርጋለህና” ሮሜ2፡1 3. ክፉ ያስባል "ፈሪሳውያን ግን ወጥተው እንዴት አድርገው እንዲያጠፉት ተማከሩበት" ማቴ12:14 ምን ቢሰበክላቸው፣ ምን ያህል ገበናቸው ቢገለጥ ልባቸው የደነደነ በመሆኑ ወደ ንስሀ አይመጡም፣ መንገዳቸውን ለማስተካከል ፈጽመው አይፈልጉም፡፡ ነገር ግን ክፉ ለማድረግ በልባቸው ቢለዋ ይስላሉ፡፡ የሚመልሱት ስለሌላቸው ከእርሱ ዘወር ብለው እርሱን እንዴት እንደሚገሉት ይመክራሉ፡፡ በእርግጥ እውነት አሸንፋ ትወጣ ዘንድ ዋጋ ታስከፍላለች፣ የማሸነፍ ኃይል ያለው ግን ለእውነት ከቆመው ጋር ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች ያሰቡትን አሁን ሊፈጽሙት ያልቻሉት ሰዎችን በመፍራት ነው፡፡ በፈሪሳውያኑና በጌታ መካከል ውጥረቱ እየጨመረ እየሄደ ይገኛል፡፡ ጸጋ ይብዛላችሁ Telegram:- @mentesnotkebede2020 👍 Join በማድረግ እየተቀላቀሉን ሌሎችም እንዲሳተፉ ሼር በማድረግ ይሳተፉ Email:- mentesnot_kebede@yahoo.com ስልክ:- 0911693190
214