2 485
订阅者
无数据24 小时
-157 天
-5230 天
帖子存档
2 485
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ነገ ከተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ጋር ሊወያዩ ነው
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በነገው ዕለት ከተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ጋር ሊወያዩ ነው። የነገው ውይይት ባለፈው ሐምሌ ወር ከተደረገው ተመሳሳይ ስብሰባ ወዲህ የነበሩ ሂደቶች የሚገመገሙበት ነው ተብሏል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ነገ ማክሰኞ መስከረም 5፤ 2013 ረፋዱን ይካሄዳል ተብሎ ለሚጠበቀው ለዚሁ ስብሰባ፤ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ዛሬ ጥሪ ተደርጎላቸዋል። ጥሪው የደረሳቸው አንድ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር፤ ስብሰባው በወቅታዊ ጉዳዩች ላይ ለመወያየት መጠራቱን እንደተገለጸላቸው ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ ሌላ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር በበኩላቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ስብሰባ እንዳለ ቢነገራቸውም፤ አጀንዳው በግልጽ እንዳልተነገራቸው ገልጸዋል።
እኚህ አመራር ስብሰባው ላለፉት ሁለት ወራት ሲካሄድ የቆየው እና በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ያሳተፈው ውይይት ማጠቃለያ ሳይሆን እንደማይቀር ግምታቸውን አስቀምጠዋል። በብሔራዊ መግባባት ላይ ያተኮሩትን ሁለት ውይይቶች ያዘጋጀው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ግን የነገው ስብሰባ ማጠቃለያ ሳይሆን ሂደቱ የደረሰበትን ደረጃ የመገምገሚያ መድረክ እንደሆነ አስታውቋል።
ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦
https://ethiopiainsider.com/2020/1901/
2 485
የትግራይ ምርጫ ኮምሽን የ2012 ዓ/ም የትግራይ ምርጫ የመጨረሻ ውጤት ይፋ አደረገ።
በውጤቱ መሰረት ህወሓት 152 መቀመጫዎችን በቀጥታ ኣብላጫ ድምፅ ያገኘ ሲሆን በቅይጥ ትይዩ የምርጫ ሰርዓት መሰረት ደግሞ 37 መቀመጫዎችን አግኝተዋል።
በአጠቃላይ ከ190 የምክርቤቱ መቀመጫዎች ህወሓት 189 መቀመጫዎች አግኝተዋል፡፡
ብሄራዊ ባይቶ ዓባይ ትግራይ/ባይቶና/ አንድ መቀመጫ አግኝተዋል፡፡
@ethiocheck
2 485
ችሎት!!
ተማሪ ሃይማኖት በዳዳን በመግደል ወንጀል ምርመራ ሲደረግበት የነበረው ደግነት ወርቁና 2ኛ ተከሳሽ ምህረቱ ሚጣ ላይ ክስ ተመሰረተ!
ግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ.ም በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በቤተ ሙከራ ክፍል ውስጥ ተማሪ ሃይማኖት በዳዳን በመግደል የወንጀል ምርመራ ሲደረግበት የነበረው ደግነት ወርቁ በውንብድና ወንጀል እንዲሁም 2ኛ ተከሳሽ ምህረቱ ሚጣ ላይ ደግሞ በከባድ የመሸሸግ ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸዋል።ክሱ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የከባድ የውንብድና ወንጀል ችሎት የተመሰረተ ሲሆን፥ በተረኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት መዝገቡ ታይቷል።
ተከሳሾቹ ክሱ የደረሳቸው እና ያቀረቡትን ዋስትና ጥያቄ ውድቅ ያደረገው ፍርድ ቤቱ ጠበቃ ለማቆም አቅም የለንም ማለታቸውን ተከትሎ የመንግስት ተከላካይ ጠበቃ እንዲመደብላቸው እና ተማክረው እንዲቀርቡ ክሱን ለማንበብ ለመስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰቷል።እስከዚያው በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ፍርድ ቤቱ አዟል።
@ethiocheck
2 485
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶ/ር ሳሙኤል ኡርቃቶ መልእክት!!
"ተማሪዎች በኮቪድ 19 ምክንያት በቤታችሁ መሆናችሁ ከባድ ጊዜ እንደሆነ እገነዘባለሁ። ነገር ግን ኮቪድ 19 የብዙዎችን ነፍስ የነጠቀ እንደመሆኑ ጥንቃቄና ትዕግስት ከእናንተ ይጠበቃል። አዲሱ ዓመት 2013 መልካም ነገር ላይ የምትደርሱበት ያለማችሁበት የሚፈጸምበት እንዲሆን ሁሌም ራሳችሁን ለመጠበቅ አትዘናጉ።
በምናደርገው ጥንቃቄና በምንወስደው እርምጃ የቫይረሱን ስርጭት መግታትና አደጋውን መቀነስ እንችላለን፡፡ በቅርቡ ለምትመለሱበት መማር ማስተማር ይሔው ጥንቃቄ ወሳኝ በመሆኑ በዚህ ረገድ የተሻለ ስራ እንድንሰራ አደራ እላለሁ! የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ተቋማትም ተማሪዎችን መልሶ ለመቀበል የሚደረገውን ዝግጅት አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ አሳስባለሁ!"
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር
@ethiocheck
2 485
የትግራይ ክልላዊ ምርጫ ነገ ይካሄዳል!
ነገ በትግራይ ይደረጋል ለተባለው ምርጫ 2672 ድምፅ መስጫ ጣብያዎች መዘጋጀታቸው የትግራይ ምርጫ ኮምሽን ማስታውቁን ዶቼ ቨለ (DW) ዘግቧል።
በነገው ድምፅ የመስጠት ስነ ስርዓት 2 ነጥብ 7 ሚልዮን ህዝብ ድምፅ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ከዛሬ ምሽት ጀምሮ የብስክሌቶች ፣ የሞተር ሳይክሎች ፣ ባለሶስት እግር ተሽከርካሪዎች (ባጃጆች) እንቅስቃሴ በጊዜያዊነት መከልከሉ የትግራይ ፀጥታና አስተዳደር ቢሮ አስታውቋል፡፡
ነገ ጳጉሜ 4/2012 ዓ/ም ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ ማታ 12 ሰዓት መራጮች ድምፅ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
@ethiocheck
2 485
የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን የጋዜጠኞች የጉዞ ክልከላን በተመለከተ “መረጃ አልነበረኝም” አለ
ከነገ በስቲያ በትግራይ የሚካሄደውን ምርጫን ለመዘገብ፤ ዛሬ ወደ መቀሌ ሊጓዙ የነበሩ ጋዜጠኞች ከአውሮፕላን ጣቢያ እንዲመለሱ መደረጉን በተመለከተ ቅድሚያ መረጃ እንዳልነበረው እና ጉዳዩን እንደሚያጣራ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገለጸ። የጉዞ እገዳ የተደረገባቸው ጋዜጠኞች መታወቂያቸው፣ የተንቀሳቃሽ ስልኮቻቸው፣ ላፕቶፖቻቸው፣ ካሜራዎች እና ሌሎች የስራ ዕቃዎቻቸው መወሰዳቸውን በጸጥታ ኃይሎች እንደተወሰዱባቸው ተናግረዋል።
ጋዜጠኞቹ እና ሌሎች መንገደኞች ወደ መቀሌ ሊጓዙ የነበረው ዛሬ ከቀኑ አምስት ሰዓት ላይ ነበር። ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ አንድ መንገደኛ እንደተናገሩት የአየር ማረፊያ የጸጥታ ሰዎች ከወትሮው በተለየ ለውጭ ሀገር ዜጎች ጥያቄ ሲያቀርቡ ነበር። በኢትዮጵያ የኒው ዮርክ ታይምስ ዘጋቢ የሆነው ሳይመን ማርክስ በተለይ በርካታ ጥያቄዎች ሲቀርቡለት እንደነበር ማየታቸውን ተናግረዋል።
ዝርዝሩን ለማንበብ ይህን ሊንክ (ማገናኛ) ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2020/1828/
@ethiocheck
2 485
የአሥራት ጋዜጠኞች በዋስትና እንዲፈቱ ፍርድ ቤቱ ወሰነ
አራዳ የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት የአሥራት ጋዜጠኞች እያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ውሳኔ ማስተላለፉን አስራት ሚዲያ በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል።
ፖሊስ በተደጋጋሚ መረጃ አቀርባለሁ በሚል ቀጠሮ እንዲሰጠው ቢጠይቅም በተሰጠው ቆጠሮ አለኝ ያለውን መረጃ ማቅረብ አልቻለም።
በመሆኑም ፍርድ ቤቱ በላይ ማናዬ፣ ሙሉጌታ አንበርብር፣ ምስጋናው ከፈለኝ እና ዮናታን ሙሉጌታ በእያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር ዋስ ከእስር እንዲለቀቁ ወስኗል። @ethiocheck
2 485
የዘንድሮ (2012ዓ.ም.) የበጎ ሰው ልዩ ሽልማት አሸናፊዎች ስምንት ሲሆኑ
አራቱን እነሆ
1) አቶ ካሊድ ናስር
ባለፉት አምስት ወራት በኮቪድ 19 ኮሮና ቫይረስ ምክንያት የገዛ መኖሪያ
ግቢያቸውን ሳይቀር በመስጠት፣ መጠለያ የሌላቸውን በመደገፍ የበጎ አድራጎት
ሥራ የሠሩ፤
2) አቶ ኪሮስ አስፋው ፡
ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት ያለማቋረጥ መቶ ጊዜ የሕዳሴ ግድብ ቦንድ የገዙ፤
3) ቢኒያም ከበደ ፡
የንባብ ለሕይወት መሥራች አዘጋጆች አንዱ እንዲሁም የኢትዮጵያ ልጆች
ቴሌቭዥን መሥራች፤
4) መሀመድ አል አሩሲ
የህዳሴው ግድብ ተሟጋች ፡ በተለይም በአረብኛ ቋንቋ ከግብፆች ጋር በሚዲያ
እየተናነቀ የሚገኝ ወጣት
@ethiocheck
2 485
የትግራይ ክልል አካሂደዋለሁ ካለው ምርጫ ጋር ተያይዞ የፌደሬሽን ምክር ቤት በጠራው አስቸኳይ ስብሰባ ውሳኔ አሳለፈ
የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ያወጣው የምርጫ አዋጅ ቁጥር 351/2012 እና የምርጫ ኮሚሽን ማቋቋሙ ከሕገ መንግስቱ የሚቃረን መሆኑን የፌደሬሽን ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ አስታውቋል፡፡
ምክር ቤቱ በዛሬው ዕለት ያካሄደውን አስቸኳይ ስብሰባን ተከትሎ ያወጣው ሙሉ መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
የፌዴሬሽን ምክር ቤት ዛሬ ነሐሴ 30 ቀን 2012 ዓ.ም ባካሄደው 5ኛ ዙር የፓርላማ ዘመን 5ኛ አመት 1ኛ አስቸኳይ ስብሰባ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔን ወደ ጎን በመተው የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ያወጣው የምርጫ አዋጅ ቁጥር 351/2012 እና አዋጁን መሰረት አድርጎ ያቋቋመው የምርጫ ኮሚሽን፣ ያሳለፋቸው ውሳኔዎች እና የፈፃማቸው ተግባራት የሕገ መንግስት ትርጉም ውሳኔ እንዲሰጥበት በሕገ መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ተጣርቶ ለመጨረሻ ውሳኔ ለምክር ቤቱ በሕገ መንግስት ትርጉምና የማንነት ጉዳዮች በኩል በቀረበው የውሳኔ ሀሳብ ላይ ውይይት አድርጓል፡፡
በውይይቱም ላይ በእስከ አሁኑ ሂደት የፌዴሬሽን ምክር ቤት ለትግራይ ሕዝብ ትልቅ ክብር ያለው መሆኑንና ህገወጥ አካላት በሚፈፅሙት ድርጊት ምክንያት በሕዝቡ ላይ ጉዳት ሊደርስበት አይገባም ብሎ የሚያምን መሆኑ እና በቀጣይም ችግሮችን በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ ለመፍታት እየተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡
በሌላ በኩል የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የራያ ራዩማ ዴሞክራሲዊ ፓርቲ እና የወልቃይት ጠገዴ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ለምክር ቤቱ ያቀረቧቸውን ቅሬታዎች በመጥቀስ የትግራይ ክልል እያካሄደ ካለው ህገወጥ ምርጫ ጋር ተያይዞ በዜጎች ላይ እየደረሰ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት እና በሕገ መንግስቱ የተረጋገጡ የፖለቲካ ፓርቲዎች መብት አለማክበር ተቀባይነት የሌለውና ሊታረም የሚገባው መሆኑ ከማስቀመጡም ባሻገር የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሰኔ 3 ቀን 2012 ዓ.ም የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት 6ኛውን አገራዊ ምርጫ በተመለከተ ያስተላለፈውን ውሳኔ እና የምክር ቤቱ አፈ-ጉባኤ በደብዳቤ ሕገ መንግስቱና የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ እንዲከበር የሰጡትን ማሳሰቢያ አለመቀበሉ ኢ-ሕገ መንግስታዊ ነው ብሏል ምክር ቤቱ፡፡
በተጨማሪም ምክር ቤቱ የሚከተሉትን የሕገ መንግስት ትርጉም ውሳኔዎች በሙሉ አፅድቋል፡፡
1) የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ያወጣው የምርጫ አዋጅ ቁጥር 351/2012 ከሕገ መንግስቱ አንቀጽ 55(15) እና አንቀጽ 55(2)(መ) ጋር ይቃረናል፤
2) የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የምርጫ አዋጅ ቁጥር 351/2012ን መሰረት አድርጎ የምርጫ ኮሚሽን ማቋቋሙ በሕገ መንግስቱ አንቀጽ 102 ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠውን ስልጣን ይጥሳል፤
3) የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት፣ አስፈፃሚ አካላት እና የምርጫ ኮሚሽን ምርጫን በሚመለከት ያወጣው የምርጫ አዋጅ ቁጥር 351/2012 ያሳለፏቸው ውሳኔዎች እና የፈፀሟቸው ተግባራት ከሕገ መንግስቱ ጋር የሚቃረኑ በመሆናቸው በሕገ መንግስቱ አንቀጽ 9(1) መሰረት እንዳልተደረጉ የሚቆጠሩ፣ የማይፀኑ እና ተፈፃሚነት የሌላቸው ናቸው በማለት የፌዴሬሽን ምክር ቤት በሙሉ ድምጽ የመጨረሻ ውሳኔ አስተላልፏል፡ @ethiocheck
2 485
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተቋረጠውን ትምህርት ለማስቀጠል ማስታወቂያ አውጥቷል!
በሁሉም ደረጃ ያሉ ተማሪዎች ሳይሆን 'የድህረ ምረቃ ተማሪዎች' ብቻ በ2012 ዓ/ም ያቋረጡትን ትምህርታቸውን ለመቀጠል እንዲመዘገቡ ጥሪ ተደርጎላቸዋል።
1. የመደበኛ ፕሮግራም (Regular) ተማሪዎች መስከረም 4-6/2012 ዓ/ም
2. የእረፍት ቀን ፕሮግራም (Weekend) ተማሪዎች መስከረም 7-8/2012 ዓ/ም
ምዝገባ የሚከናወን ሲሆን የመደበኛ ፕሮግራም ተማሪዎች መስከረም 7 እንዲሁም የእረፍት ቀን ተማሪዎች መስከረም 9/2013 ዓ/ም ትምህርት ይጀምራል።
@ethiocheck
2 485
አቶ ጃዋር መሀመድን ጨምሮ በ14 ተጠርጣሪዎች ላይ ዐቃቤህግ ዘጠኝ የቅድመ ምርመራ ምስክሮችን አሰምቷል።
ዐቃቤ ህግ 15 የቅድመ ምርመራ ምስክሮች ማዘጋጀቱን የገለፀ ሲሆን፥ ከ15 ምስክሮች ውስጥ 4ቱ በተለያዩ ምክንያቶች እና የምስክር ጊዜ ላለማራዘም ማሰማት አልፈልግም ሲል ለችሎቱ ገልጿል።ዐቃቤ ህግ በ11ኛ እና 14ኛ ተራ ቁጥር ያስመዘገባቸው ቀሪ ሁለት ምስክሮች ስልካቸው ባለመስራቱ ለነሃሴ 29 ቀን 2012 ዓ.ም ከመጋረጃ በስተጀርባ ምስክርነት ይሰማልኝ በማለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት በልደታ አዳራሽ የተገኙት አቶ ጃዋር መሀመድን ጨምሮ 14 ተጠርጣሪዎች ላይ የዐቃቤ ህግ ቀሪ ሁለት ምስክሮች ዛሬ ተሰምተዋል።
በዚህም ሂደትም ዐቃቤ ህግ የሚያሰማቸው እና የማያሰማቸው ቀሪ ምስክሮች ዝርዝር ይገለፅልን ሲሉ የተጠርጣሪ ጠበቆች ጠይቀዋል።ዐቃቤ ህግም ለደህንነታቸው ሲባል ዝርዝራቸውን አልገልፅም፤ ከዚህ በፊት ምስክር የነበሩ ግለሰብ በተተኮሰባቸው ሽጉጥ ጉዳት ደርሶባቸው ፓሊስ ጣቢያ ማደራቸውን ጠቅሶ በተለያዩ ጊዜ ምስክሮች ላይ ዛቻ እና ማስፈራሪያ እየደረሰ በመሆኑ ለደህንነታቸው ሲል ዝርዝራቸውን መግለፅ እንደማይፈልግ አብራርቷል።ተጠርጣሪዎችም የተለያዩ አቤቱታዎቻቸውን ለፍርድ ቤት አስመዝግበዋል።
አቶ በቀለ ገርባ የባንክ ሂሳባቸው መታገዱን እና የግል ተሽከርካሪያቸው እንዳልተመለሰላቸው አቤቱታ አቅርበዋል። እንዲሁም የማረሚያ ቤት አያያዛቸው እንዲስተካከል ጠይቀዋል።አቶ ሃምዛ አዳነ በአንድ መፅሄት እንዲሁም በሌሎች ጋዜጦች ስሜ እየጠፋ ነው ሲሉ አመልክተዋል።አቶ ሸምሰዲን ጠሃ የተባሉ ተጠርጣሪም የጆሮአቸውን ህመም በሚፈልጉት የህክምና ተቋም እንዲታከሙ ፍርድ ቤቱ ያዘዘው ትዕዛዝ አልተፈፀመም ሲሉ በድጋሜ ለፍርድ ቤት አቤቱታ አቅርበዋል።ጉዳዩን የተከታተለው ፍርድ ቤትም በተነሱ አቤቱታዎች ላይ ትዕዛዝ ለመስጠት እና ሁለት የዐቃቤ ህግ ከመጋረጃ ጀርባ የቅድመ ምርመራ ምስክሮችን ለመስማት ለነሃሴ 29 ቀን 2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
@ethiocheck
2 485
የእነ አቶ ደጀኔ ጣፋ ክስ ዝርዝር ምን ይዟል?
የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ምክትል ዋና ጸሀፊ የሆኑት አቶ ደጀኔ ጣፋ በሕገ መንግስት እና ሕገ መንግስታዊ ስርዓት ላይ በሚፈጸም ወንጀል ተከሰሱ። የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ በአቶ ደጀኔ እና አቶ መስተዋርድ ተማም በተባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ ባቀረበው ክስ፤ ተከሳሾቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈጸሙት በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው ከሚገኙ እና ካልተያዙ ግብረ አበሮቻቸው ጋር በመሆን እንደነበር ጠቅሷል።
አቶ ደጀኔ እና አቶ መስተዋርድ በተከሰሱበት ወንጀል “በህዝብ ደህንነት ላይ ከፍተኛ ቀውስ የደረሰ በመሆኑ ተከሳሾቹ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈጸሙት በሕገ መንግስትና በሕገ መንግስት ስርዓት ላይ በሚደረግ ወንጀል ተከሰዋል” ሲል አቃቤ ህግ በክስ ሰነዱ አስፍሯል። ተከሳሾቹ በክስ ሰነዱ የተጠቀሰባቸው የወንጀል ህግ አንቀጽ 238 (2) “ወንጀሉ ሲፈጸም በሕዝብ ደህንነት ወይም ኑሮ ላይ ከፍተኛ ቀውስ ደርሶ እንደሆነ፤ አድራጊው በዕድሜ ልክ እስራት ወይም ሞት ይቀጣል” በማለት ይደነግጋል።
ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ይህን ማገናኛ (ሊንክ) ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2020/1812/
@ethiocheck
2 485
ለአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የእስረኛ አስተዳደር ኃላፊ በፍርድ ቤት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው
የእነ ጃዋር መሐመድን የቀዳሚ ምርመራ መዝገብ የሚመለከተው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት፤ ለአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የእስረኛ አስተዳደር ኃላፊ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጠ። ፍርድ ቤቱ ማስጠንቀቂያውን የሰጠው በፖሊስ ኮሚሽኑ ቁጥጥር ስር ላሉ ሶስት ተጠርጣሪዎች የኮሮና ምርመራ ተደርጎ፣ ውጤት እንዲቀርብ የሰጠው ተደጋጋሚ ትዕዛዝ ባለመፈጸሙ ነው።
ፍርድ ቤቱ ባለፈው አርብ ባስቻለው ችሎት፤ የፖሊስ ኮሚሽኑ የእስረኛ አስተዳደር ኃላፊ ለዛሬ ታስረው እንዲቀርቡ አዝዞ ነበር። ዛሬ ማክሰኞ ነሐሴ 26፤ 2012 ችሎት ፊት የቀረቡት ዋና ኢንስፔክተር አራጌ እሸቴ "በቴሌቪዥን በተላለፈው መሰረት መቅረብ ስላለብኝ ቀርቤያለሁ። ማንም አስሮ ያስገደደኝ አካል የለም" ሲሉ ለፍርድ ቤቱ ተናግረዋል።
በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ቁጥጥር ስር ላሉ ሁሉም ተጠርጣሪዎች በነሐሴ ወር ውስጥ ለሶስት ጊዜያት ያህል ምርመራ እንደተደርገላቸው የተናገሩት የእስረኛ አስተዳደር ኃላፊው፤ ሆኖም የምርመራ ውጤታቸውን ለፍርድ ቤት እንዲቀርብ "ማንም የነገረኝ ወይም የጠየቀኝ የለም" ብለዋል። "እኛ ማቅረብ የምንችለው የራሳችንን እስረኞች ውጤት ነው" ያሉት ዋና ኢንስፔክተር አራጌ "የእነርሱን ማቅረብ ያለባቸው የፌደራል እስረኛ አስተዳደር ኃላፊዎች ነው" ሲሉ ለፍርድ ቤቱ ምላሽ ሰጥተዋል።
ምርመራ ይደረግላቸው ከተባሉት ሶስት ተጠርጣሪዎች አንዱ የሆኑት የOMN ጋዜጠኛ መለሰ ድሪብሳ፤ የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ቀደም ሲል ማድረጋቸውን ሆኖም ውጤቱ እንዳልተነገራቸው ለፍርድ ቤቱ ገልጸዋል። ከእነርሱ ጋር አብረው ሲበሉ እና ሲጠጡ የነበሩ ሌሎች ተጠርጣሪዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጠቆመው በእነርሱ ላይም አንዳንድ ምልክቶች በመታየታቸው ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ ማቅረባቸውን አስታውሷል። ፍርድ ቤቱ እንዲመረመሩ ትዕዛዝ ካስተላለፈ በኋላ ግን የእነርሱን ናሙና የወሰደ እንደሌለ አብራርቷል።
ጉዳዩን የሚመለከቱት ዳኛ ፍርድ ቤቱ በሶስት የተለያዩ የችሎት ውሎዎች ለሶስቱ ተጠርጣሪዎች ምርመራ እንዲደረግ ትዕዛዝ ቢሰጥም አለመፈጸሙን ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የእስረኞች አስተዳደር ኃላፊ በቀጣይ ቀጠሮ ትዕዛዙን ፈጽመው እንዲቀርቡ "የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ" የሰጡት ዳኛው "በቀጣይ ቀጠሮ ተመርመረው የማይቀርቡ ከሆነ በእርስዎ ላይ እርምጃ ይወሰዳል" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ፍርድ ቤቱ በአሁኑ ወቅት አቃቤ ህግ በእነ ጃዋር መሐመድ መዝገብ በተካተቱ 14 ተጠርጣሪዎች ላይ ያቀረበው ምስክር በመስማት ላይ ነው። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
[ይህ ዘገባ ተጨማሪ መረጃ ታክሎበታል]
@ethiocheck
2 485
ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ዛምቢያ ዉስጥ ተገደለ
(50 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ባረፉበት ቦታ ነበር ጥቃት የደረሰባቸው)
ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ዛምቢያ ካቴቴ አውራጃ ውስጥ ቺቦላያ በተባሉ ነዋሪዎች በተፈጸመ ጥቃት መገደሉን ዛምቢያ ሪፖርትስ ትናንት በድረ-ገጹ ዘግቧል። በዘገባዉ መሠረት ወደ ደቡብ አፍሪቃ ለመጓዝ የፈለጉ 50 ኢትዮጵያዉን ስደተኞች ምዋሚ በተሰኘው ድንበር በኩል በሕገወጥ መንገድ ዛምቢያ ገብተዉ ካቴቴ ውስጥ መቆየታቸዉን የአካባቢው ፖሊስ አስታዉቋል።
የአካባቢው ነዋሪዎች ኢትዮጵያውያኑ ስደተኞች ባረፉበት ቦታ በሌሊት በድንገት ባደረሱት ጥቃት ከግድያው ባሻገር ዘጠኝ ኢትዮጵያውያን መጠነኛ የመቊሰል አደጋ እንደደረሰባቸው የአካባቢው ፖሊስ ኮሚሽነር ሉክሰን ሳካላ ገልጠዋል።ከስደተኞቹ መካከል 38ቱ በፖሊስ ሲያዙ ኹለት ስደተኞች ግን ማምለጣቸውን የፖሊስ ኃላፊው አክለው ተናግረዋል።
የፖሊስ አዛዡ የአካባቢው ነዋሪ በሰፈራቸው ስለመጡ ሰዎች ጥርጣሬ ቢያድርበትም ጥቃት መፈጸሙ ግን ስህተት ነው፤ ማድረግ የነበረባቸው ለፖሊስ ማሳወቅ ነው ብለዋል። ግድያ እና ጥቃት ፈጻሚ ዛምቢያውያን ላይ ፖሊስ የወሰደው ርምጃ ስለመኖሩ ግን ዘገባው አይጠቅስም።
ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በተደጋጋሚ ወደ ደቡብ አፍሪቃ በሚያደርጉት ሐገወጥ ስደት ዛምቢያን ጨምሮ በሚያቋርጧቸዉ ሃገራት ተደጋጋሚ ጥቃትና አደጋ ይደርስባቸዋል።
@ethiocheck
2 485
ኢ/ር ታከለ ኡማ በህገ ወጥ መንገድ የተሰጠ ምንም አይነት ቤት የለም አሉ።
ታከለ ኡማ(ኢ/ር) የመሬት ወረራን በተመለከተ ከመጀመሪያዋ ቀን ጀምሮ እስከ መጨረሻዋ እለት ድረስ ጠንካራ የሆነ እርምጃ ስንወስድበት የቆየንበት ጉዳይ ነው ሲሉ ምላሻቸውን በማሕበራዊ ገጻቸው ላይ አስፍረዋል። ለ20ሺህ አርሶአደሮች የተሰጡ የኮንዶሚኒየም ቤቶች ከአንድ ዓመት ተኩል በፊት በካቢኔ የተወሰነና የተተገበረ ነው። በድብቅ የተተገበረም ሳይሆን በመንግስት ሚዲያም በይፋ የተገለፀ ነበር በማለትም ገልጸዋል።
ከመሬታቸው ተፈናቅለው ሜዳ ላይ ከወደቁ በራሳቸው መሬት ላይ በተሰራ ህንጻ ዘበኛ እና ተሸካሚ ሆነው ከቀሩ 67 ሺህ አባወራዎች መሃል የከፋ ችግር ላይ ለወደቁት 20 ሺህ ኮንዶሚንየም ቢያንስ እንጂ የሚበዛ አይደለምም ብለዋል። ከዚህ ውጭ በህገወጥ መንገድ የተሰጠ ምንም አይነት ቤት የለም፤ ይህ ሥራችን በተደጋጋሚ በይፋ ስንናገር እንደነበረው የምናፍርበት ሳይሆን የምንኮራበት ነው ሲሉም አስታውቀዋል።
ኢ/ር ታከለ ኡማ
@ethiocheck
2 485
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በአዲስ አበባ መሬት ወረራ እና የጋራ መኖሪያ ቤቶች ኢፍትሃዊ ዕደላ ላያ ያደረገው ጥናት ውጤት ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡
@ethiocheck
2 485
💥የቢሾፍቱ ከተማ ፍርድ ቤት የአቶ ልደቱ አያሌውን ፋይል ዝግቶ በነፃ አሰናበታቸው፡፡
የቢፍሾቱ ከተማ አንደኛ ደረጃ ፍርድ ቤት የኢዴፓ መስራችና የስራ አስፈፃሚ አባል የሆኑት አቶ ልደቱ አያሌው በተከሰሱበት ጉዳይ ምንም የሚያስጠይቃቸው ነገር እንዳላገኘ በመግለፅ በነፃ እንዳሰናበታቸው ተሰማ፡፡
ሸገር የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሊቀ መንበር የሆኑትን አቶ አዳነ ታደሰን በስልክ አነጋግሮ አቶ ልደቱ ተጠርጥረው ለእስር የተዳረጉበት የፍርድ ቤት መዝገብ መዘጋቱን አረጋግጧል፡፡
ፍርድ ቤቱ አቶ ልደቱ ከፖሊስ ጋር ያላቸውን የዋስትና ጉዳይ ጨርሰው እንዲለቀቁ ማዘዙን ሸገር ከአቶ አዳነ ሰምቷል፡፡
አቶ ልደቱ አያሌው የድምፃዊ ሀጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ በቢሾፍቱ በተፈጠረው ረብሻ አመፅ በማነሳሳትና በገንዘብ በመርዳት በሚል ጠርጥሬአቸዋለሁ ባለው የቢሾፍቱ ከተማ ፖሊስ አዲስ አበባ ውስጥ በቁጥጥር ስር ውለው በፍርድ ቤት ጉዳያቸውን ሲከታተሉ መክረማቸው ይታወቃል፡፡
ሸገር ኤፍ ኤም
@ethiocheck
