ch
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

前往频道在 Telegram
2 485
订阅者
无数据24 小时
-157 天
-5230 天
帖子存档
በባህር ዳር ከተማ ዛሬ ሰኞ ንጋት ላይ ሁለት ሮኬቶች መተኮሳቸውን የከተማይቱ ነዋሪዎች ለ “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። ሮኬቶቹ በከተማይቱ አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ መውደቃቸውንም ገልጸዋል።

የባንክ ሂሳብ የታገደባቸው 34 የኤፈርት ድርጅቶች የወንጀል ምርመራ እየተደረገባቸው ነው የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የባንክ ሂሳባቸው እንዲታገድ ያደረገባቸው 34 የትግራይ የመልሶ ማቋቋም ኢንዶውመንት ፈንድ (ኤፈርት) ድርጅቶች ላይ የወንጀል ምርመራ እየተደረገባቸው ነው። ጠቅላይ አቃቤ ህግ የድርጅቶቹን የባንክ ሂሳብ ያሳገደው ትላንት ሰኞ ህዳር 7፤ 2013 ለባንኮች በጻፈው ደብዳቤ መሆኑን “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የተመለከተችው ሰነድ ያሳያል። ሰላሳ አራቱ ድርጅቶች የባንክ ሂሳባቸው እንዲታገድ የተደረገው ከተጠረጠሩባቸው ሶስት ወንጀሎች ምርመራ ጋር በተያያዘ መሆኑን መስሪያ ቤቱ በደብዳቤው አስታውቋል። ድርጅቶቹ ከተጠረጠሩባቸው ወንጀሎች መካከል “በኢትዮጵያ የተለያዩ ክፍሎች የሚፈጸሙ የዘር ተኮር ጥቃቶችን፣ የሽብር ተግባራትን እና ሕገ መንግስታዊ ስርዓትን በኃይል ለመናድ ከሚሰሩ አካላት ጋር በመመሳጠርና ግንኙነት በመፍጠር በገንዘብ መደገፍ” የሚል ይገኝበታል። ድርጅቶቹ "በሙስና እና በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብን ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ" ወንጀሎችም ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን የጠቅላይ አቃቤ ህግ ደብዳቤ ያስረዳል። የፈደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ለምርመራው ይረዳው ዘንድ የድርጅቶቹን የባንክ ሂሳብ እንቅስቃሴ የሚያመለክቱ ማስረጃዎች በአስቸኳይ እንዲላክለትም ባንኮችን ጠይቋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) ለዝርዝር ዘገባ፦ https://ethiopiainsider.com/2020/2281/ * የ34ቱን ድርጅቶች ሙሉ ዝርዝር ከታች ከተያያዘው ምስላዊ መረጃ ይመልከቱ

photo content

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ድባጤ ወረዳ ባገረሸው ጥቃት ሶስት ሰዎች ቆሰሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመተከል ወረዳ ድባጤ ከተማ ዛሬ ረፋዱን በታጣቂዎች በተከፈተ ተኩስ ሶስት ሰዎች መቁሰላቸውን የወረዳው የመንግስት ኮሙዩኔኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በጽህፈት ቤቱ የሚዲያ ልማት ባለሙያ የሆኑት አቶ ጥላሁን ወየሳ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንደተናገሩት፤ በከተማይቱ አንግቶክ በተባለ ቀበሌ የተኩስ እሩምታ መሰማት የጀመረው ዛሬ ሰኞ ከቀኑ አምስት ሰዓት ገደማ ጀምሮ ነው። በተኩሱ የቆሰሉ ሶስት ሰዎች ወደ ድባጤ ከተማ ጤና ጣቢያ መወሰዳቸውን የሚገልጹት ባለሙያው፤ “የመሳሪያ ድምጽ አለ። አሁንም ቢሆን በህዝቡ ውስጥ የተረጋጋ መንፈስ አይታይም” ሲሉ በአካባቢው ስላለው ሁኔታ አስረድተዋል። ባለሙያው ተኩሱን የከፈቱት “ታጥቀው የገቡ ጸረ -ሰላም ኃይሎች ናቸው” ብለዋል። ዝርዝሩን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2020/2276/

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) በትግራይ ክልል በተለያዩ መስሪያ ቤቶቹ ተመድበው ይሰሩ የነበሩ የተወሰኑ ሰራተኞቹን ማስወጣቱን ምንጮች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። የውጭ ሀገር ዜግነት ያላቸው እና ኢትዮጵያውያን የድርጅቱ ሰራተኞች፤ በተመድ ተሽከርካሪዎች ተጭነው ክልሉን የለቀቁት ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ መሆኑንም ገልጸዋል። አዳራቸውን ትላንት በአማራ ክልል ያደረጉት እኚሁ ሰራተኞች፤ በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ እነዚሁ ምንጮች ጠቁመዋል። በአዲስ አበባ ከሚገኙ የተመድ መስሪያ ቤቶች በአንዱ የሚሰሩ የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ምንጭ፤ ድርጅቱ ሰራተኞቹን የማስወጣት የአስቸኳይ ጊዜ እንቅስቃሴ የጀመረው ባለፈው ማክሰኞ መሆኑን አስረድተዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

በኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ በትላንትናው ምሽት 1 ሰዓት ከ50 ገደማ “ከፍተኛ ተከታታይ ድምጾች” መሰማታቸውን በኤርትራ የአሜሪካ ኤምባሲ አስታወቀ። ኤምባሲው በአስመራ ለሚገኙ ዜጎቹ ዛሬ እሁድ ባሰራጨው የማስጠንቀቂያ መልዕክት፤ ያልተረጋገጡ ሪፖርቶች በአስመራ አውሮፕላን ማረፊያ ጣቢያ ቅጽር የሚፈነዱ መሳሪያዎች ሳይኖሩ እንዳልቀሩ አመላክተዋል ብሏል። ሆኖም ኤምባሲው “የአስመራ አውሮፕላን ማረፊያ ጣቢያ ስለመጠቃቱ ምንም ዓይነት ማመላከቻ የለም” ሲል ቀደም ሲል ከተሰራጩ ዘገባዎች ጋር የሚቃረን መልዕክት አስፍሯል። ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን የዲፕሎማቲክ ምንጮቻቸውን ጠቅሰው እንደዘገቡት፤ በትላንትናው ምሽት በትንሹ ሶስት ሮኬቶች ወደ አስመራ ከተማ መተኮሳቸውን ገልጸው ነበር። ሁለቱ ሮኬቶች የአስመራ አየር ማረፊያን መምታቸውን “ሮይተርስ” ዲፕሎማቶችን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል። ትላንት ምሽት በአስመራ ከተማ የተሰማውን ፍንዳታ ተከትሎ የመብራት እና የቴሌኮሚዩኒኬሽን ግንኙነቶች በመቋረጣቸው፤ ስለ ክስተቱ ከከተማይቱ ነዋሪዎች ዝርዝር መረጃ ማግኘት አልተቻለም። ፍንዳታው እንዴት እንደተከሰተ በኤርትራ መንግስት በኩል እስካሁን በይፋ የወጣ መረጃ የለም። የአስመራው የቅዳሜ ምሽት ፍንዳታ እንደተሰማ በርካቶች ጉዳዩን ከህወሓት የሚሳኤል ጥቃት ዛቻ ጋር አያይዘውታል። የህወሓት ስራ አስፈጻሚ አባል የሆኑት ጌታቸው ረዳ ቅዳሜ እኩለ ቀን ገደማ “ለድምጺ ወያኔ” ቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃለ ምልልስ፤ የትግራይ ኃይል “በምጽዋ እና አስመራ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን ለማምከን የሚያስችሉ የሚሳኤል ጥቃቶችን እንደሚያደርግ” አስጠንቅቀው ነበር። የትግራይ ሴንትራል ኮማንድ ቃል አቃባይ መሆናቸው የተነገረላቸው አቶ ጌታቸው፤ “ከኤርትራም ወገን ሆነ ከሌላው የኢትዮጵያ ክፍል የሚደረጉ ጥቃቶችን ለማምከን የሚያስችሉ የሚሳኤል የአጸፋ እርምጃዎችን መውሰድ የምንቀጥል መሆናችንን በዚህ አጋጣሚ መግለጽ እፈልጋለሁ” ሲሉ ለቴሌቪዥን ጣቢያው ተናግረዋል። በኢትዮጵያ መንግስት ዕውቅና የተነፈገውን የትግራይ ክልል መንግስትን በፕሬዝዳንትነት የሚመሩት ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በአስመራ ላይ ጥቃት የፈጸሙት የክልሉ ኃይሎች መሆናቸውን ዛሬ እሁድ ለ“ሮይተርስ” የዜና አገልግሎት አረጋግጠዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በቦሌ አየር ማረፊያ ተጨማሪ መታወቂያ መጠየቁን በተመለከተ ማብራሪያ ጠየቀ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በቦሌ አየር ማረፊያ የሚጓዙ ኢትዮጵያውያን መንገደኞች ከፓስፖርት በተጨማሪ የቀበሌ መታወቂያ ወረቀት እንዲያቀርቡ መገደዳቸውን በተመለከተ ማብራሪያ ጠየቀ። አዲሱ አሰራር “ዜጎችን በብሔራቸው በመለየት ለጥርጣሬ እና መድልዎ እንዲጋለጡ የሚያደርግ ነው” ብሏል። መንግስታዊው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋም ጥያቄውን ያቀረበው ለኢትዮጵያ ሲቪል አሺዬሽን ባለስልጣን እና ለአዲስ አበባ ቦሌ ኤርፖርት ደህንነት ቢሮ ትላንት ማክሰኞ ህዳር 1፤ 2013 በጻፈው ደብዳቤ ነው። የኮሚሽኑ ደብዳቤ እንደደረሳቸው ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ያረጋገጡት የኢትዮጵያ ሲቪል አሺዬሽን ባለስልጣን ዳይሬክተር ጄነራል ኮሎኔል ወሰንየለህ ሁነኛው፤ ጉዳዩ እርሳቸው የሚመሩትን መስሪያ ቤት የሚመለከት እንዳልሆነ ተናግረዋል። https://ethiopiainsider.com/2020/2231/

የፎቶ ዘገባ፦ በአዲስ አበባ አድዋ ድልድይ ስር ዛሬ ጠዋት ከፍተኛ የፍንዳታ ድምጽ መስማታቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች እና የዓይን እማኞች ለ"ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ገለጹ። ፍንዳታው እንዴት እንደደረሰ
የፎቶ ዘገባ፦ በአዲስ አበባ አድዋ ድልድይ ስር ዛሬ ጠዋት ከፍተኛ የፍንዳታ ድምጽ መስማታቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች እና የዓይን እማኞች ለ"ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ገለጹ። ፍንዳታው እንዴት እንደደረሰ እንደማያውቁ የሚናገሩት የዓይን እማኞች ሆኖም በፍንዳታው የተጎዳ ሳይሆን አይቀርም የተባለ አንድ ሰው ከድልድይ ስር ወጥቶ ወደ ሆስፒታል ሲወሰድ መመልከታቸውን አስረድተዋል። የፌደራል እና የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት፤ ፍንዳታው ተሰማበት የተባለበትን የድልድዩን ክፍል እግረኞች እንዳይተላለፉበት አጥረው ምርመራ ሲያደርጉ የ"ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ዘጋቢ ተመልክቷል ። የፌደራል ፖሊስ የፎረንሲክ እና ፈንጂዎች ምርምራ ቡድን ተሽከርካሪዎች እስከ ረፋዱ አምስት ሰዓት ድረስ በአካባቢው ቆመው ነበር። የአድዋ ድልድይም ሆነ ሌሎች መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ባይደረጉም በርከት ያሉ ፖሊሶች በአካባቢው የጸጥታ ቁጥጥር በማድረግ ላይ ናቸው። ፍንዳታው ደረሰበት በተባለበት የአድዋ ድልድይ ጎን ከሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ደጃፍም የፖሊሶች እንቅስቅሴ ከወትሮው በዛ ብሎ ታይቷል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) [ከጸጥታ አካላትም ሆነ ከዓይን እማኞች የምናገኛቸውን ተጨማሪ መረጃዎች እናክላለን።]

ከጥቅምት 25 ቀን 2013 ዓ.መ ጀምሮ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተሰጡ ሹመቶች፡ - አቶ ደመቀ መኮንን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር - ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም - ሌ/ጄኔራል አበባው ታደሰ የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም - አቶ ተመስገን ጥሩነህ የብሔራዊ መርጃና ድህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር - ኮሚሽነር ደመላሽ ገ/ሚካኤል የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር #PMOEthiopia @ethiocheck

"ወታደራዊው ተልዕኮ ውስን ነው" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ የፌደራል መንግሥቱ ትግራይ ክልል ላይ የሚያደርገው ወታደራዊ ዘመቻ "ግልፅ፣ ውስንና ተጨባጭ ውጤቶችን ማግኘት" ላይ ያነጣጠረ ነው ብለዋል። የትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል (ዶ/ር) በበኩላቸው ከዚህ ቀደም የፌደራል አስተዳደሩ ክልሉን ለመውረር እያሴረ ነው በማለት ሲወነጅሉ ተሰምተዋል። በፌደራል መንግሥቱና በክልሉ ያለው ወታደራዊ ግጭት ወደ እርስ በርስ ጦርነትም እንዳያመራም ስጋቶች አሉ። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በአስቸኳይ ጦርነቱን እንዲያረግቡትም ጥሪ አድርጓል። ግጭቱ በምን ሁኔታ ነው ያለው? የፌደራል መከላከያ ሰራዊት ወደ ትግራይ ክልል ተጨማሪ ወታደሮችን እንደሚልክና በአገሪቷም የሚገኙ የሰራዊቱ አባላትንም እየተሰበሰሰቡ መሆኑንም የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት ምክትል ኤታማዦር ሹም እና የኦፕሬሽን ዘርፍ ሐላፊ ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ ከሰሞኑ አስታውቀዋል። ጄኔራል ብርሃኑ እንዳሉት የሰራዊት አባላቱ በክልሉ ለሚገኘው የመከላከያ ሰሜን ዕዝ ድጋፍ ለመስጠት እንደሆነ ገልፀዋል። የሰሜን እዝ በክልሉ አስተዳዳሪ ህወሃት ቁጥጥር ስር እንዳለ ክልሉ ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ በትግራይ ላይ የሚደረገው የጦር ተልዕኮ "ውስን" እንደሆነና "የፌደራል መንግሥት ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ለወራት ያህል በትእግስት ተሞክሮ ባለመሳካቱ ጦርነቱም የመጨረሻ አማራጭ ሆኗል" በማለት በትዊተር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል። የክልሉ ፕሬዚዳንት ደብረፅዮን በበኩላቸው የትግራይ ኃይል በክልሉ የሚገኙትን የመከላከያ ሰሜን ዕዝ ጦር መሳሪያም ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር አውሏል ብለዋል። ቀውሱ እየተቀጣጠለና ምንም አይነት የመቀዛቀዝ ሁኔታም እንደሌለም እየተነገረ ነው። በውጊያው ስለተገደሉም ሆነ ስለተጎዱ ሰዎች ምንም አይነት መረጃ ባለመገኘቱ ግጭቱ ምን ያህል ከባድ እንደሆነ ማወቁን ፈታኝ አድርጎታል። ይህም በተወሰነ መንገድ ግጭቱን ተከትሎ የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎት በትግራይ ክልል ከመቋረጡ ጋር ተያያይዞ ነው። በክልሉ ተቋርጦ የነበረው የመብራት አገልግሎት በአሁኑ ወቅት ተመልሷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ስለ ግጭቱ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት የተቆጠቡ ሲሆን በምትኩ የጦርነት ተልዕኮው ሲጠናቀቅ መረጃዎች ይፋ እንደሚሆኑ ቃል ገብተዋል። @ethiocheck

አሜሪካ በትግራይ ክልል ያለው ወቅታዊ ውጥረት እንዲረግብ አሳሰበች። ሀገሪቱ በአዲስ አበባ ባለው ኤምባሲዋ በኩል ከደቂቃዎች በፊት ባወጣችው አጭር መግለጫ፤ ሁለቱም ወገኖች “የተመጠኑ እርምጃዎች” እን
አሜሪካ በትግራይ ክልል ያለው ወቅታዊ ውጥረት እንዲረግብ አሳሰበች። ሀገሪቱ በአዲስ አበባ ባለው ኤምባሲዋ በኩል ከደቂቃዎች በፊት ባወጣችው አጭር መግለጫ፤ ሁለቱም ወገኖች “የተመጠኑ እርምጃዎች” እንዲወስዱ ጠይቃለች። ኤምባሲው “ሁለቱም ወገኖች የሰላማዊ ህዝብን ደህነንነት እና ጸጥታ ቅድሚያ እንዲሰጡ አበክረናል እናበረታተለን” ብሏል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

መረጃ፦ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በወቅታዊ ጉዳዩች ላይ ከደቂቃዎች በኋላ ለጋዜጠኞች መግለጫ ይሰጣሉ ተብሏል።

በአማራ ክልል በዳንሻ በኩል ጥቃት ተፈጽሟል- ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በአማራ ክልል በዳንሻ በኩል “ተፈጽሟል” ያሉትን ጥቃት፤ የክልሉ የጸጥታ ኃይሎች “መመከታቸውን” ተናግረዋል። በትግራይ ክልል መቀሌን ጨምሮ በበርካታ ስፍራዎች በመከላከያ ሰራዊት ላይ ትላንት ማክሰኞ ምሽት “ያልተጠበቀ ጥቃት” መሰንዘሩን በመግለጫቸው የጠቀሱት አብይ፤ በኢትዮጵያ እስካሁን ከደረሱት ጥቃቶች “እጅግ አስነዋሪ ያደርገዋል” ያሉበትንም ምክንያት አብራርተዋል። “ሰላም ለማስከበር በተለያየ ሀገር የተሰማራው የሀገር መከላከያ ሰራዊት እንኳ፤ በውጭ ኃይሎች ያልደረሰበትን ጥቃት በገዛ ወገኖቹ ከጀርባው እንዲመታ ብዙዎች እንዲሰዉ፣ ብዙዎች እንዲቆስሉ፣ ንብረቶች እንዲወድሙ ተደርገዋል” ብለዋል። የመከላከያ ሰራዊት አባላት በሚሰጣቸው ግዳጅ፤ ከዚህ በኋላም መስዋዕትነቶች ሊከፍሉ እንደሚችሉም ጠቁመዋል። ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https:// ethiopiainsider.com/2020/2191/

የሕወሓት ተወካይ በምርጫ ቦርድ መድረክ በኢዜማ ተቃውሞ ገጠማቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መጪውን ጠቅላላ ምርጫ በተመለከተ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በሁለት ዙር ከሚያደርገው ውይይት፤ የመጀመሪያውን ዛሬ ቅዳሜ ጥቅምት 21፤ 2013 በአዲስ አበባው ሃያት ሬጀንሲ ሆቴል አካሂዷል። በመድረኩ ላይ የተሳተፉ በርከት ያሉ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፤ ከምርጫ በፊት የብሔራዊ መግባባት ውይይት መደረግ እንደሚኖርበት በተደጋጋሚ አንስተዋል። ይህንን ጉዳይ ካስተጋቡት መካከል የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓትን) ወክለው በውይይቱ የተሳተፉት አቶ ዳኘው በለጠ ይገኙበታል። አቶ ዳኘው ምርጫውን “ሙሽራ የሌለው ሰርግ እንደማካሄድ ነው የምቆጥረው” በማለት ከምርጫው በፊት መቅደም ሰላለባቸው ጉዳዮች ተናግረዋል። “መጀመሪያ ምርጫውን እንዴት ነው መካሄድ ያለበት?” በሚለው ላይ መግባባት ላይ መደረስ አለበት ብለዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲን የወከሉት ዶ/ር ጫኔ ከበደ፤ የሕወሓቱን ተወካይ ንግግር የስነ ስርዓት ጥያቄ በማንሳት አቋርጠዋል። ዶ/ር ጫኔ ሕወሓት ለዚህ ውይይት መጋበዙን ተቃውመው ከፓርቲው ጋር ለመነጋጋር “ፍቃደኛ” አለመሆናቸውንም አስታውቀዋል። የምርጫ ቦርድ ሃላፊዎችንም “ምርጫን በጨበራ ያደረገ ፓርቲ፤ ምርጫ ከሚያደርግ ጋር አዳብላችሁ መጋበዛችሁ ምን እንድናድምጥ ነው?” ሲሉ ጠይቀዋል። በምርጫ ቦርድ አመራሮች ፍቃድ በድጋሚ የመናገር ዕድል የተሰጣቸው የሕወሓቱ ተወካይ፤ በግንቦት መጨረሻ አሊያም በሰኔ ይካሄዳል የተባለው መጪው ምርጫ፤ የተሰጠው ጊዜ “የተንዛዛ ነው” ሲሉ ተችተዋል። የኮሮና ወረርሽኝ አነስተኛ በነበረበት ወቅት ተራዝሞ የነበረው ምርጫ፤ አሁን ስፋቱ በጨመረበት ወቅት ለመካሄድ መወሰኑንም ተወካዩ አንስተዋል። በዚህ ጉዳይ ላይ ምላሽ የሰጡት የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ፤ በወቅቱ ባለው ነባራዊ ሁኔታ ምርጫ ለማካሄድ መነሳት “ኃላፊነት የጎደለው ነው” ብለዋል። “ያንን ውሳኔ በመወሰናችን አንዳችንም ለህሊናችን ቅር የሚለን ነገር የለም” ሲሉም አጽንኦት ሰጥተዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) ውይይቱን በቪዲዮ ለመመልከት ይህን ሊንክ ተጭነው ወደ ዩቲዩብ ቻናላችን ጎራ ይበሉ፦ https://youtu.be/Pbi-hyTfPWc

ከ tiktok መንደር ያገኘነውን አስገራሚ ልብ የሚነካ vedio ልናጋራቹ ወደድን https://vm.tiktok.com/ZSQ6D61f/

የምስራቅ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ የቢሾፍቱ ከተማ ፖሊስ አቶ ልደቱ አያሌውን በአንድ መዝገብ ፈትቶ፣ በሌላ ማሰሩን የሚያሳይ ማስረጃ እንዲያቀርብ ዛሬ ትዕዛዝ ሰጠ። ፍርድ ቤቱ ትዕዛዙን የሰጠው
የምስራቅ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ የቢሾፍቱ ከተማ ፖሊስ አቶ ልደቱ አያሌውን በአንድ መዝገብ ፈትቶ፣ በሌላ ማሰሩን የሚያሳይ ማስረጃ እንዲያቀርብ ዛሬ ትዕዛዝ ሰጠ። ፍርድ ቤቱ ትዕዛዙን የሰጠው አቶ ልደቱ በትላንትናው ዕለት በታሰሩበት ፖሊስ ጣቢያ በዚህ አኳኋን እንደታሰሩ እንደተነገራቸው ለችሎት ካስረዱ በኋላ ነው። “ትላንት 10 ሰዓት ከ25 ላይ አንድ ፖሊስ የታሰርኩበት ፖሊስ ጣቢያ መጥቶ 'መዝገብ ላይ ፈትተንህ እንደገና ያሰርንህ መሆኑን እንድታውቀው ነው' ብሎኛል። እኔ ለአንድም ሰከንድ ከእስር ቤት አልተፈታሁም” ሲሉ አቶ ልደቱ ዛሬ ረፋዱን በአዳማ ከተማ ላስቻለው ፍርድ ቤት ተናግረዋል። እንዲህ አይነት ምክንያት ተቀባይነት እንደሌለው የገለጸው ፍርድ ቤቱ፤ የቢሾፍቱ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ አቶ ልደቱን 'ፈትቼበታለሁ' ያለበትን የመዝገብ ማስረጃ በነገው ዕለት ይዞ እንዲቀርብ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

የችሎት ውሎ፦ “አሁን እየተሰራ ያለው የአማተሮች ትያትር ነው”- አቶ ልደቱ አያሌው ላለፉት ሶስት ወራት በእስር ላይ የሚገኙት አቶ ልደቱ አያሌው፤ ፖሊስ ሊፈታቸው ባለመፍቀዱ በፍርድ ቤት በዋስትና ጉዳይ ላይ ያለው ክርክር ቀርቶ ሌላው የፍርድ ሂደት እንዲቀጠል ጠየቁ። ሕገ መንግስቱን በጣሱ መልኩ የፍርድ ቤት ውሳኔን ሳያስፈጽሙ የቀሩ አካላትን በተመለከተ “አሁን እየተሰራ ያለው የአማተሮች ትያትር ነው” ሲሉ እርምጃቸውን አጣጥለዋል። ያስያዙት የ100 ሺህ ብር ዋስትና ተከብሮላቸው ከእስር ሳይለቀቁ የቀሩት አቶ ልደቱ፤ በዛሬው የችሎት ውሎ ጠንከር ባለ ጽምጸት በጉዳዩ ላይ ያላቸውን አቋም አንጸባርቀዋል። የዞኑ ፍርድ ቤት የህግ የበላይነትን ለማስከበር አቅሙ የፈቀደውን ያህል ላደረገው ጥረት አክብሮታቸውን የገለጹት ዕውቁ ፖለቲከኛ፤ የፍርድ ቤቱን “ውድ ጊዜ”፣ እርሳቸው “ትያትር” ሲሉ በጠሩት ድርጊት ማባከን እንደማይፈልጉ አስታውቀዋል። “ከዚህ በኋላ ለታሪክ፤ ፖሊስ ሕገ መንግስቱን ጥሶ፣ የእኔንም መብት ጥሶ ያለከልካይ መሆኑ ይመዘገብልኝና ወደ ሌላው ክርክር እንቀጥል። ይሄ ጨዋታ ይቁም። እኔ የፍርድ ቤቱን ጊዜ በዚህ ማባከን አልፈልግም። እናንተ የምትችሉትን ሁሉ አድርጋችኋል። ከዚህ በላይ አልጠብቅም” ሲሉም ለፍርድ ቤቱ ተናግረዋል። ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2020/2176/

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለተወካዮች ምክር ቤት አባላት ከተናገሩት፦ (ለፓርላማ አባላት ሁለተኛ ዙር ጥያቄዎች የሰጧቸው መልሶች) * ስለ አንበጣ እና ጎርፍ - የበረሃ አንበጣ በተከሰተባቸው ቦታዎች አራት ሚሊዮን ሄክታር ታርሷል። ከዚህ ውስጥ ጥቃት የደረሰበት 420 ሺህ ሄክታር መሬት ነው። - የበረሃ አንበጣውን አሁን ባለበት ደረጃ ካስቆምነው ዘንድሮ ቢያንስ 35 ሚሊዮን ኩንታል ትርፍ ምርት እናመርታለን ብለን ነው የምንጠብቀው። - በጎርፍ 600 ሺህ ሰው ገደማ ተጠቅቷል። ከዚህ ውስጥ 220 ሺህ ሰው ተፈናቅሏል። ነገር ግን አንድም ሰው አልሞተብንም። * ስለ ፍትህ ስርዓቱ - የፍትህ ስርዓቱ ገለልተኛ ይሁን፣ ነጻ ይሁን ያለው [የለውጥ] ሃይል፣ የፍትህ ስርዓት ነጻነትን የሚቃረን መሆን የለበትም። አሁንም ያልተፈቱ ድክመቶች አሉ። - ፍርድ ቤት ለሚሰጣቸው ፍርዶች፣ ብያኔዎች፤ ምንም ሳናወላዳ መቀበል ያስፈልጋል። እኛ ያላከበርነውን ፍርድ ቤት፣ እኛ ያልታዘዝንለትን ፍርድ ቤት ነጻ እና ገለልተኛ ሁን ማለት ከንቱ ነገር ነው የሚሆነው። - የፍትህ ስርዓቱ የሚሰጣቸውን ውሳኔዎች አስፈጻሚ አካላት ማክበር ይጠበቅበናል። ከዚህ አንጻር ተጨማሪ ስራ ያስፈልጋል። አንዳንዱ ወንጀለኛ ይደብቃል። አንዳንዱ ሲታዘዝ አይፈጽምም። ይሄ ትክክል አይደለም። የራሳችንን ግብ፤ የእኛን ፍላጎት ነው የሚቃረነው። - የፍትህ ስርዓቱ የተሟላ የምናስበውን ነገር እንዲያሳካ መታለፍ ያለባቸው፣ አስፈጻሚው በጣም በጥንቃቄ ማየት የሚገባው ነገሮች አሉ። እኛ የመንግስት ቢሮ ስንይዝ እና ስንወጣ፤ የግል ስም፣ የግል ክብር፣ የግል ማንነት የሚባል ነገር መተው አለብን። ሰዎች መናገር፣ መጻፍ፣ መተቸት እንዲችሉ መፍቀድ አለብን። የማንፈቅደው ነገር ሰዎች ባላቸው ብዕር፣ ባላቸው ሚዲያ ‘ተነስ፣ ግደል፣ ተጋደል’ ማለት የለባቸውም እንጂ እኛን መተቸት እና ስለ እኛ መጻፍ መፍቀድ አለብን። - በእርግጥ አንዳንድ የሚጻፈው ነገር ስህተት ሊሆን ይችላል። መረጃ የሌለው ሊሆን ይችላል። በህግ ዓይን የሚያስጠይቅ ሊሆን ይችላል። ሆደ ሰፊ ሆነን የጀመርነውን የዲሞክራቲክ ኢትዮጵያን የመፍጠር ጉዳይ እያረጋገጥን ካልሄድን መልሰን የእኛኑ ትግል፣ ግብ መልሰን ነው የምንበላው። * ስለ ትግራይ እና የፌደራል መንግስት ግንኙነት መሻከር - የትግራይ ህዝብ ሀገር ወዳድ ህዝብ ነው። የትግራይ ህዝብ መለወጥ ይፈልጋል። ይሄን ታሳቢ ያደረገ ስራ የፌደራል መንግስት እየሰራ ያለው ህዝብ አለኝ ብሎ ነው። አስር፣ አስራ አምስት፣ ሃያ የማያስፈልጉ ግለሰቦች አሉ ሳይሆን ‘በሚሊዮን የሚቆጠር፤ አስፈላጊ፣ ባለመብት፣ የምንታገልለት ዜጋ አለን’ ብለን ነው እየሰራን ያለነው። ወደፊትም ይሄው ይቀጥላል። እዚያ ካለው ሃይል ጋር የሚያያዘው ጉዳይ ግን በህግ እና በህግ ብቻ የሚመለስ ይሆናል። - የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚወስነው ውሳኔ፣ [የተወካዮች] ምክር ቤት የሚወስነው ውሳኔ፣ የአስፈጻሚ አካል ይህንን ብቻ የሚያስፈጽም ይሆናል። በህግ እና በህግ እየሰራን እንቀጥላለን። በዚያ ውስጥ ሁሉ ነገሮች ፈር እየያዙ፣ መልክ እየያዙ መፍትሄ እያገኙ እንደሚሄዱ ተስፋ ይደረጋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) የዛሬውን የፓርላማ ውሎ የተመለከተ ዝርዝር ዘገባ ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2020/2157/

ብሄራዊ ባንክ የተቀየረውን ብር ምን ማድረግ እንዳለበት ሶስት አማራጮችን አስቀምጦ ለውሳኔ አቅርቧል፡፡ እነዚህም አንደኛው ማቃጠል ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ብሩን ፈጭቶ ለሸክላ መስሪያ ማዋል ነው፡፡ በሶስተኛነት የቀረበው ሀሳብ ብሩን የሚቆራርጥ ማሽን መግዛት መሆኑን ፎርቹን ጋዜጣ በዛሬ እትሙ ዘግቧል፡፡ የቀድሞው ብር ምን ሊሆን እንደሚገባው እንዲያጠና የተዋቀረው ቡድን እነዚህን አማራጮች ለባንኩ ገዢ ዶ/ር ይናገር ደሴ የዛሬ ሁለት ሳምንት ማቅረቡም ተገልጿል፡፡ ገዢው በመረጡት አማራጭ መሰረት ከሁለት ወር በኋላ ብሩ ሙሉ በሙሉ ተቀይሮ ሲጠናቀቅ የሚወገድ ይሆናል፡፡ ብሄራዊ ባንክ በወንጂ የብር ማቃጠያ ማእከል ያለው ሲሆን ካለፈው ስድስት አመት ወዲህ ግን ያረጁ ብሮችን ማስወገጃ ማሽን ገዝቷል፡፡ ጀርመን ሰራሽ የሆነው ይህ ማሽን ሁለት ሺህ አንድ መቶ(2,100) ኪሎ ግራም መጠን ያለውን ብር በግማሽ ሰአት ውስጥ ፈጭቶ በማቡካት የሚያስወግድ ነው፡፡ ይህ የተቦካው ብርም ለሸክላ ማምረቻ ግብአት ስለሚሆን ለባንኩ ተጨማሪ ገቢ የሚያስገኝለትን እድል ሲፈጥር ቆይቷል፡፡ ይህ ማሽን በአሁኑ ወቅት በቀድሞው አርቲስቲክ ማተሚያ ቤት ግቢ ውስጥ እንደሚገኝም ተዘግቧል፡፡ ይህ አማራጭ ከተወሰነ ማሽኑ ብቻውን ያንን ሁሉ ብር ማቡካት ስለማይችል ባንኩ ሌላ ማሽን ለመግዛት ይገደዳል፡፡ በሌላ በኩል ብሄራዊ ባንክ ብር መቅደጃ ማሽን ገዝቶ ብሩን ለመቆራረጥ ከፈለገ ጨረታ እንደሚያወጣ ታውቋል፡፡ የብሩ ማስወገጃ አማራጭ ከተወሰነ በኋላ ብሩን ከማስወገድ በፊት ሰፊ የቆጠራ ዘመቻ ስለሚከናወን ይህም ቀናትን እንደሚወስድ የቅርብ ምንጮች ለዜና ምንጩ አስረድተዋል፡፡ በበርካቶች ተመራጭ የሆነው አማራጭ ግን ብሩን ማቃጠል የሚለው ነው ተብሏል፡፡ @ethiocheck

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በፓርላማ ከተናገሩት፦ (በየጊዜው የሚጨመርበት) - ሃያ ገደማ ባንኮች ከብሔራዊ ባንክ ፍቃድ ለማግኘት በሂደት ላይ ናቸው። - በስራ ላይ ያሉ ባንኮች በዘንድሮ ዓመት ካፒታላቸውን ከፍ እንዲያደርጉ ይደረጋል። - እስካለፈው ሳምንት ድረስ 31 ቻርተር [አውሮፕላን] በላይ ገንዘብ ገብቷል። - የገንዘብ ኖት ለውጥ ከተደረገ ወዲህ እስካሁን ድረስ 1.3 ሚሊዮን ሰዎች የባንክ አካውንት ከፍተዋል። በዚህም 37 ቢሊዮን ብር ሴቭ ተደርጓል። - የኢትዮጵያ አብዛኛው ፕሮጀክት በአረም የተሞላ ነው። - የመንግስት ልማት ድርጅቶች፤ ኢትዮ ቴሌኮም እና አየር መንገድን ሳይጨምር፤ ከ600 ቢሊዮን ብር በላይ ዕዳ አለባቸው። ከዘንድሮ የኢትዮጵያ በጀት በላይ ዕዳ አለባቸው። - የንግድ ባንክ ህንጻን ከሚገነቡ ሰዎች መካከል ከ50 በላይ ሰዎች በኮሮና በመያዛቸው፤ ቁልፍ ቁልፍ ስራ የሚሰሩ የቻይና ባለሙያተኞች ስለፈሩ አንሰራም ብለው ወደ ሀገራቸው ሄደዋል። እስካለፈው ወር ድረስ ከፍተኛ ፍጥነት የነበረው የንግድ ባንክ ህንጻ ግንባታ በዚህ ሁለት ሶስት ሳምንት ቀንሷል። - እንጦጦ እና ሸገር [ፓርክን] በተመለከተ የሚነሱ አንዳንድ ድምጾች አሉ። አሁን ለእንጦጦ ምርቃት ያስፈልጋል ወይ ዳቦ ሳንበላ? ዳቦ አይቀድምም ወይ? የሚሉ ሆን ብለው የሚያስጮሁ ሰዎችም አሉ፤ በደንብ ካለመገንዘብም የሚከተሉ አሉ። ሰው ለዳቦ ብቻ አይኖርም። ሁልጊዜ ዳቦ ሳልበላ አይባልም። ዳቦ መብላት አለበት፤ ትክክል ነው። ለዚያ ዳቦ ፋብሪካ ሰርተናል። ስንዴ እያመረትን ነው፤ እርሱን አልተውነውም። - እንጦጦ እና የዳቦ ፋብሪካ ብቻ 10 ሺህ ገደማ ሰው አዲስ አበባ ውስጥ ስራ አስይዟል። “ስራ አጥነትን እንቀንስ” ይባላል፤ ፕሮጀክት ሲመጣ ደግሞ አቃቂር ለማውጣት ይሞከራል። የተከበረው ምክር ቤት እንጦጦን ብሰራም ባልሰራም ሊጠይቀኝ አይችልም። ምክንያቱም ምክር ቤቱ ለእንጦጦ አንድ ብር አልሰጠኝም። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)