EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 559 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 384,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 165 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 559 名订阅者。
根据 23 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 0,过去 24 小时变化为 -2,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.89%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.48% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 026 次浏览,首日通常累积 2 408 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 24 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 559
订阅者
-224 小时
-37 天
无数据30 天
帖子存档
15 559
በተቋሙ ለሁለተኛ ጊዜ እየተካሄደ ያለዉ "የመሀሉ ዘመን" ሀገራዊ መድረክ መካሄድ ጀመረ
........///........
በመዲናዋ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ማዕከላዊ ሪጂን 1፣ 2፣ 3 መምሪያዎች እና የብሄራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል የሚገኙ አመራሮችና ሠራተኞች "የመሀሉ ዘመን" በሚል መሪ ሀሳብ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ዉይይት ማካሄድ ጀምረዋል።
ሀገራዊ መድረኩ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፋይናንስና ኃብት አስተዳደር ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ የተከፈተ ሲሆን "የመሐሉ ዘመን" በሚል ርዕስ ስለ ለውጥ ወጥመዶች እና የመሻገር ሂደቶችን የሚዳስሰው ሰነድ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) ለውይይት ቀርቧዋል።
በውይይት መድረኩ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፋይናንስና ኃብት አስተዳደር ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ፣ የኢትዮጵያ ኢንሸስትመንት ሆልዲንግ የኢነርጂ ዘርፍ ዳይሬክተር ጌትነት መላክ (ዶ/ር)፣ የዋና ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝን ጨምሮ ከመምሪያዎቹ እና ከብሃራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል የተውጣጡ ሠራተኞች እና አመራሮች ተገኝተዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ግንቦት 13 ቀን 2017 ዓ.ም
15 559
ያለፉት ሰባት ዓመታት በርካታ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ስኬቶች የተመዘገቡበት ነው - ተስፋሁን ጎበዛይ
….....///……...
በኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት በርካታ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ስኬቶች መመዝገባቸውን የኢፌዲሪ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ ገለፁ።
ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች "መሀሉ ዘመን" በሚል መሪ ሀሳብ በመንግስት የተዘጋጀውን የመወያያ ሰነድ ያቀረቡት ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ እንደገለፁት መሀሉ ዘመን የኢትዮጵያን መነሻ፣ አሁን የደረሰችበትን ሁኔታ እና ቀጣይ መዳረሻ የሚያመላክት የሽግግር ዘመን ነው ብለዋል።
ከትላንት ውድቀቶቻችንና ከዛሬ ስኬቶቻችን ተምረን ነገን የተሻለ ለማድረግ እንደ ሀገር ጠንክረን መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በለውጥ ሂደት በርካታ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሠራሽ ፈተናዎችን መሻገሯን የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታው ድርቅ፣ ጎርፍ፣ የበረሃ አንበጣና የኮቪድ-19 ወረርሽኝ እንዲሁም የእርስ በርስ ግጭትና መፈናቀል ለውጡን የፈተኑ ጉዳዮች መሆናቸውን ለአብነት አንስተዋል።
በለውጡ ዋዜማና በለውጡ ወቅት ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን እንዲሁም ስኬቶችን አብራርተው በዓለም ሀገራት የኃይል አሰላለፍ ውስጥ የኢትዮጵያ አቅም እንዴት እንዳደገና ምን ውጤት እንደመጣም ገልፀዋል።
ያለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት በርካታ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ስኬቶች የታዩበትና መዋቅራዊ ለውጥ የተደረገበት መሆኑንም አስረድተዋል።
በአሁኑ ወቅት የሕዝቡ የለውጥ ፍላጎት፣ የአመራሩ ቁርጠኝነት እና ብስለት የተሞላበት ውሳኔ ለውጡን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገራቸውን ተናግረዋል።
የሕዝብ ጥያቄዎችን በመመለስ፣ የትርክት ለውጥ በማምጣት፣ አካታች ፖለቲካዊ አጀረጃጀት እና ኢኮኖሚያዊ ሪፎርም በመተግበር ስኬት ማስመዝገብ መቻሉንም ነው የገለፁት።
እንደ አቶ ተስፋሁን ገለፃ የተሳካ የህግ ማስከበር ዘመቻ፣ የፕሪቶሪያ ሥምምነት እና የህዳሴ ግድብ እያደገ ለመጣው የኢትዮጵያ አቅም አወንታዊ ሚና ተጫውተዋል።
የህዳሴ ግድብ ግንባታ የማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ መድረሱ ለኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ብርሃን የፈነጠቀና በቀጣናው ሀገራት ላይም ያላትን የኃይል ሚዛን ያስጠበቀ መሆኑን ገልፀዋል።
ተቋሙ በኃይል ልማት ዘርፉ ላይ እያከናወናቸው የሚገኙትን የለውጥ ሥራዎች ቀጣይነት ባለው መልኩ በማሳለጥ የኤሌክትሪክ አቅርቦቱን ለማሻሻል መስራት እንደሚገባው ጠቅሰዋል።
በቀረበው ሰነድ ላይ የውይይቱ ተሳታፊዎች ጥያቄዎችና አስተያየቶችን ያነሱ ሲሆን የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተውባቸዋል።
የባህር በር ጥያቄው ተቋሙ በኃይል ልማት ዘርፉ ለሚያከናውናቸው ፕሮጀክቶች የሚያገለግሉ ግብዓቶች በወቅቱ ወደ ሳይት እንዲደርሱ በማድረግ በአፈፃፀማቸው ላይ አወንታዊ አስተዋፅዖ እንደሚኖረው ኢንጂነር አሸብር ጠቅሰዋል።
በኦፕሬሽን እና ግንባታ ሥራዎች ላይ ውጤታማ ለመሆን እንደ ተቋም ያለውን አቅምና ግብ ታሳቢ ያደረገ ዕቅድ በማዘጋጀት ወደ ተግባር መግባት እንደሚያስፈልግ አፅዕኖት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡
የተቋሙ አመራር እና ሠራተኛ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ንቁ ተሳታፊ በመሆን የህዝብ መሰረታዊ ጥያቄ የሆነውን የኤሌክትሪክ አቅርቦት ለመመለስ መስራት እንደሚገባ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አሳስበዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥጌ/ግአ/ሙጉ/ሞመ
ግንቦት 11 ቀን 2017 ዓ.ም
15 559
የተቋሙ ሠራተኞች "የመሀል ዘመን" ወጥመድ እና መሻገር በሚል መሪ ሀሳብ ላይ እየተወያዩ ነው
........///........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች "የመሀል ዘመን" በሚል መሪ ሀሳብ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ዉይይት ማድረግ ጀምረዋል።
የለውጥ ወጥመዶች እና የመሻገር ሂደቶች ላይ ባተኮረው የዉይይት መድረክ ላይ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ በመንግስት የተዘጋጀውን የመወያያ ርዕሰ ጉዳይ አቅርበዋል።
በውይይት መድረኩ ላይ የኢትዮጵያ ኢንሸስትመንት ሆልዲንግ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር)፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ አክሊሉ ታደሰ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ፣ የኢትዮጵያ ኢንሸስትመንት ሆልዲንግ የኢነርጂ ዘርፍ ዳይሬክተር ጌትነት መላክ(ዶ/ር) ጨምሮ ከስምንት መቶ በላይ የዋና መስሪያ ቤት ሰራተኞች በመሳተፍ ላይ ናቸው።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሞመ
ግንቦት 11 ቀን 2017 ዓ.ም
15 559
#News Update
በጣቢያው ከሚተከሉት ሁለት ትራንስፎርመሮች መካከል የአንደኛው ሥራ ተጠናቋል
………///………
በወልቂጤ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እየተከናወነ የሚገኘው የትራንስፎርመር ቅየራ ሥራ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ የማዕከላዊ 3 ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ አስታወቀ።
በመምሪያው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ታደሰ ገብሬ እንዳስታወቁት በማከፋፈያ ጣቢያው ከሚተከሉት ሁለት ትራንስፎርመሮች መካከል 7 ነጥብ 5 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው አንደኛው ትራንስፎርመር ትናንት ምሽት ኃይል መስጠት ጀምሯል፡፡
ትራንስፎርመር ቅየራው በመጠናቀቁ በ33 ኪሎ ቮልት የአገና፣ ወሸርቤ እና ዋዩ እንዲሁም ዳልጌ ከተሞች የኤሌክትሪክ ኃይል ማግኘት መጀመራቸውን ገልፀዋል።
በጣቢያው የቴክኒክ ችግር የገጠመውንና ለወሊሶ፣ ቱሉቦሎና በዙሪያቸው ለሚገኙ ከተሞች አገልግሎት ሲሰጥ የቆየውን ትራንስፎርመር ከቦታው በማንሳት 63 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው ሌላኛውን ትራንስፎርመር የማስቀመጥ ሥራ መሰራቱንም ነው የገለፁት።
በአሁኑ ወቅት ትራንፎርመሩን የመገጣጠም ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝ የገለፁት አቶ ታደሰ በቀጣይ ቀናት ቀሪ ሥራዎችን በማከናወን የፍተሻና ሙከራ ሥራ እንደተጠናቀቀ ኃይል መስጠት ይጀምራል ብለዋል።
እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በጣቢያው እየተከናወነ በሚገኘው የትራንስፎርመር ቅየራ ሥራ የወሊሶ ከተማን የኤሌክትሪክ አቅርቦት በእጥፍ ያሳድጋል።
ሪጅኑ የትራንስፎርመር ቅየራ ሥራውን ከስምንት እስከ አስር ቀናት አጠናቆ ለህብረተሰቡ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ርብርብ እያደረገ እንደሚገኝም አቶ ታደሰ ተናግረዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሙጉ/ሞመ
ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም
15 559
መስተዳድሮቹ ለማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ መፋጠን የበኩላቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል
.........///.........
የደቡብ ወሎ ዞን ዞንና የደሴ ከተማ መስተዳድሮች በደሴ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ በተያዘለት መርሐ ግብር እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ አረጋገጡ።
የዞኑ ዋና አስተዳደሪ፣ የደሴ ከተማ ከንቲባና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ በተያዘለት መርሐ ግብር ለማጠናቀቅ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት አድርገዋል።
በውይይቱ ላይ አቶ ውድነህ እንደገለፁት ግንባታው የሚያስፈልጉ እንደ አሸዋ፣ ድንጋይና ጠጠር ያሉ ግብዐቶች የግንባታ የስራ በቅርበት የሚገኙበትን ሁኔታ በመቻቸት መስተዳድሮቹ ድጋፍ ሊያደርጉ ይገባል።
በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች እየተፈፀመ ያለውን ስርቆት ለመከላከል የመስተዳድር አካላት ትኩረት እንዲሰጡ ጠይቀዋል።
በውይይቱ ላይ የደሴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሳሙኤል ሞላልኝ እንደገለፁት በከተማው ለረጅም ዘመን አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው ባለ 66 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ በከተማዋ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት በበቂ ሁኔታ ማስተናገድ ባለመቻሉ የኃይል መቆራረጥና የፈረቃ አገልግሎት እንዲሰጥ ምክንያት ሆኗል።
ችግሩ እንዲፈታና በየጊዜው እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለመመለስ የማከፋፈያ ጣቢያ እንዲገነባ ለመንግስት ጥያቄ ሲቀርብ እንደነበር ያነሱት ከንቲባው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለጥያቄው ምላሽ በመስጠቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በመሆኑም በግንባታ ላይ የሚገኘው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ መጠናቀቅ የከተማው ህዝብ በጉጉት የሚጠብቀው ፕሮጀክት ነው ብለዋል።
ከንቲባው እንደገለፁት የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ እስከሚሆን ድረስ የግንባታው ተቋራጭ ለሚጠቀማቸው የነዳጅ፣ ድንጋይ፣ አሸዋና ጠጠር የመሳሰሉ ግብዓቶችን ቅድሚያ ማግኘት የሚችሉበትን ዕድል ይመቻቻል።
ፕሮጀክቱ በተያዘለት መርሐ ግብር እንዲጠናቀቅ የከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዓሊ መኮንን በበኩላቸው በዞኑ ውስጥ የሚገነቡ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ እንዲጠናቀቁ እና መሰረተ ልማቶቹ ስርቆት እንዳይፈፀምባቸው ዞኑ ጥብቅ ክትትል እንደሚያደርግ አስታውቀዋል።
ስርቆት የሚፈፅሙ አካላት በህግ እንዲጠየቁና የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች በነዋሪዎች እንዲጠበቁ እንደሚደርጉ ተናግረዋል።
በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ ሀሳብ የሰጡት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ መስተዳድሮቹ ተቋሙ ለሚያቀርባቸው ጥያቄዎች ድጋፍ ለማድረግ ያሳዩትን ዝግጁነት አድንቀዋል።
በደሴ ከተማ እየተገነባ ያለው የማከፋፈያ ጣቢያ ለከተማው ብቻ ሳይሆን በቅርብ ርቀት ለሚገኙ የዞኑ አካባቢዎች በቂ ኃይል የሚሰጥ በመሆኑ ተቋሙ በዞኑ ሲቀርቡ ለነበሩ የኃይል ፍላጎት ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ እየመለሰ መሆኑን የሚያሳይ ነው ብለዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ፍጌ/ሞመ
ግንቦት 9 ቀን 2017 ዓ.ም
15 559
ሪጅኑ በበጀት ዓመቱ የታቀዱ ሥራዎችን በዕቅዱ መሰረት ለማከናወን እየሰራሁ ነው አለ
……..///……
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ አንድ ሪጅን በ2017 በጀት ዓመት የያዛቸውን መደበኛ የኦፕሬሽን እና ጥገና ሥራዎች እንዲሁም ጣቢያዎችን የማዘመን እና ሌሎች መደበኛ ተግባራት በዕቅዱ መሰረት ለማከናወን እየሰራ መሆኑን የሪጅኑ ዳይሬክተር አስታወቁ።
ዳይሬክተሩ አቶ ወርዲ መሐመድ እንዳስታወቁት በዘጠኝ ወራት ውስጥ ያልተከናወኑ ሥራዎችን በቀሪ ጊዜያት በማጠናቀቅ የበጀት ዓመቱን ዕቅድ ለማሳካት ሪጅኑ የመቶ ቀን ዕቅድ አውጥቶ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል።
በመቶ ቀን ዕቅድ ከተያዙት ተግባራት መካከል በሀረር፣ ሁርሶ እና አዲጋላ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ በጋዝ የሚሰራ የመቆጣጠሪያ ቅየራ እንዲሁም በድሬዳዋ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ የመቆጣጠሪያ ክፍል ዕድሳት እና ከሁርሶ ድሬዳዋ ቁጥር 3 ባለ 132 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር የኮንዳክተር ቅየራ ሥራዎች ዋንኛዎቹ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በማከፋፈያ ጣቢያዎች አገልግሎት ላይ የማይውሉ ንብረቶችን በመለየት የጣቢያዎችን ንጽህና መጠበቅ እና ለሥራ ምቹ የማድረግ ሥራዎችም የዕቅዱ አካል መሆናቸውን አክለዋል።
እስከ በጀት ዓመቱ ማጠናቀቂያ ድረስ የተያዙትን ሥራዎች ብቅዱ መሰረት እንዲከናወን ከማድረግ ጎን ለጎን በቀጣይ በጀት ዓመት የሚከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎችን ዕቅድ እየተዘጋጀ መሆኑንም ገልጸዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
አወ/ሞመ
ግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ.ም
15 559
የትራንፎርመር ጥገና ሥራውን እስከ ነገ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው
……….///……….
በድሬዳዋ ቁጥር 3 ባለ 230/132/33/15 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ አጋጥሞ የነበረውን የትራንስፎርመር ብልሽት እስከ ነገ አጠናቆ ወደ ሥራ ለማስገባት እየተሠራ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ አበበው አበራ እንዳስታወቁት በቮልቴጅ አለመመጣጠን ምክንያት በጣቢያው የሚገኙ ሁለት ባለ 63 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች ላይ ብልሽት አጋጥሞ ነበር።
ጣቢያው ከቆቃ - ሁርሶ በ230 ኪሎ ቮልት ጥምር መስመር እና ከቆቃ - አዋሽ በ230 ኪሎ ቮልት ነጠላ መስመር እንዲሁም ከሁርሶ በ132 ኪሎ ቮልት ኃይል በመቀበል ለድሬዳዋ ከተማ፣ለድሬደዋ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ እና በዙሪያው ለሚገኙ ኢንዱስትሪዎች እንዲሁም በ132 ኪሎ ቮልት ወደ ሀረር እና አካባቢው ኃይል እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
ይሁን እንጂ ትራንፎርመሮቹ በመበላሸታቸው ጣቢያው በ230 ኪሎ ቮልት ያገኝ የነበረው ኃይል ስለተቋረጠ በኃይል አቅርቦቱ ላይ ጫና ማሳደሩን ኃላፊው ገልጸዋል።
እንደ ኃላፊው ገለጻ መጠነኛ ጉዳት የገጠመውን አንድ ትራንስፎርመር በአስቸኳይ ጠግኖ ወደ አገልግሎት እንዲመለስ ለማድረግ ከሪጅኑና ከዋና መስሪያ ቤት የተውጣጡ ባለሙያዎች እየሰሩ ነው።
የጣቢያው የኦፕሬሽንና ጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ከድር አብደላ በበኩላቸው ትራንስፎርመሩ ተጠግኖ ወደ አገልግሎት ሲገባ ድሬደዋ ከተማ እና በዙሪያው ያሉ ኢንዱስትሪዎች፣ ሀረር እና አካባቢው ኃይል የሚያገኙበትን አማራጭ እንደሚያሰፋ ተናግረዋል።
ሥራ አስኪያጁ እንዳሉት ጥገናው እስከ ነገ ተጠናቆ ወደ ሥራ ሲጀምር በጣቢያው ላይ የነበረውን ጫና በከፍተኛ ደረጃ ያቃልላል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
አወ/ሞመ
ግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ.ም
15 559
የመቆጣጠሪያ ክፍሉ ዕድሳት እየተደረገለት ነው
....///.....
በምሥራቅ 1 ሪጅን በመቶ ቀን ዕቅድ ከተያዙት ሥራዎች መካከል አንዱ የሆነው የድሬዳዋ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ የመቆጣጠሪያ ክፍል ዕድሳት እየተደረገለት መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ ገለጹ።
ኃላፊው አቶ ሚካኤል አልዬ እንደገለጹት የመቆጣጠሪያ ክፍሉ ጣሪያ በዕድሜ ብዛት የተነሳ በመሠነጣጠቁ ፍሳሽ ወደ መቆጣጠሪያዎች በማስረግ ጉዳት እንዳያደርስ ዕድሳት እየተከናወነለት ነው።
ዕድሳቱ በዋናነት በመቆጣጠሪያ ክፍሉ ጣሪያ ላይ እየተከናወነ መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው ይህም የዝናብ ውሃ በማስገባት መቆጣጠሪያዎቹን እንዳይጎዳ እና በጣቢያው የኦፕሬሽን ሥራ ላይ ጫና እንዳያሳድር ያደርጋል ብለዋል።
እንደ ኃላፊው ገለጻ የመቆጣጠሪያ ክፍሉ የአርማታ ንጣፍ ሙሊት እና የልሰና ሥራ ሲጠናቀቅ የውሃ መከላከያ ንጣፎችን ጨምሮ ሌሎች የማጠናቀቀያ ሥራዎች በጥቂት ቀናት ውስጥ ይጠናቀቃሉ።
የድሬዳዋ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ከ1952 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን በተለያዩ ጊዜያት በተደረገለት የማስፋፊያ እና የአቅም ማሳደግ ሥራ እስከ 56 ሜጋ ዋት ኃይል የመጫን አቅም አለው።
ጣቢያው በ15 ኪሎ ቮልት ባሉት ስድስት ወጪ መስመሮች ለድሬዳዋ ከተማ እና በዙሪያው ለሚገኙ ፋብሪካዎች እንዲሁም በ132 ኪሎ ቮልት ለናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ ይገኛል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ኑሀ/ሞመ
ግንቦት 7 ቀን 2017 ዓ.ም
15 559
የፕሮጀክቱን የሲቪል ሥራ አፈፃፀም 17 ከመቶ ለማድረስ እየተሰራ ነው
……….///……….
የደሴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የፕሮጀክት የሲቪል ሥራ አፈፃፀምን እስከ በጀት ዓመቱ መጨረሻ 17 ከመቶ ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ የተመራ ቡድን የፕሮጀክቱን ግንባታ ሲጎበኝ ሥራ አስኪያጁ አብዱ ኪያር እንደተናገሩት በ1 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ግንባታው የተጀመረው የማከፋፈያ ጣቢያ የፕሮጀክት አፈፃፀም 12 በመቶ ደርሷል፡፡
ፕሮጀክቱ ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ ሳይቱን ለግንባታ ዝግጁ በማድረግ የመሬት ቆረጣና የአፈር ማንሳት፣ የአፈር መንሸተት መከላከያ ግንብ ግንባታ፣ የመኖሪያ ቤት መሠረት ግንባታ እና ኮለን የማቆምና ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡
63 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮችን በቦታቸው የማስቀመጥ ሥራ መጠናቀቁን የሳይት ሥራ አስኪያጁ አስረድተዋል።
የተቋሙ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ በበኩላቸው የማከፋፈያ ጣቢያው መገንባት በደሴና አካባቢዋ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያስችል ገልፀዋል። ይህም ተቋሙ በሁሉም አካባቢዎች እያደረገ ያለውን የልማት ተደራሽነትን የሚያሳይ ነው ብለዋል።
ግንባታው የሚገነባበት ቦታ ጥቁር አፈር በመሆኑ ተጨማሪ የመሬት ቆረጣና አፈር የማንሳት ሥራ ማስፈለጉን የተናገሩት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ሥራው ቀድሞ ከታሰበው ውጭ ያጋጠመ በመሆኑ የተወሰነ መጓተት ማስከተሉን ጠቁመዋል፡፡
ሥራውን በተያዘለት ዕቅድ መሠረት ማጠናቀቅ የሚያስችሉ ሥራዎችን በቀሪ ጊዜያት ውስጥ ጠዋትና ማታ መስራት እንዳለባቸው አቅጣጫን አስቀምጠዋል።
በጉብኝቱ ላይ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚውን ጨምሮ የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት መምሪያ ዳይሬክተር ሰለሞን ኃይለጊዮርጊስ፣ የኢንጂነሪንግ ሱፐርቪዥንና ኮንትራት አስተዳደር መምሪያ ዳይሬክተር ግርማ ዘለቀ፣ በዘርፉ የግዥና ፋይናንስ መምሪያ ተወካይ ዳይሬክተር ሙሉቀን ዮሴፍ ተገኝተዋል፡፡
የደሴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የግንባታ ወጪ ሙሉ ለሙሉ በተቋሙ የሚሸፈን ሲሆን የግንባታ ሥራውን የተቋሙ የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት መምሪያ የአማካሪነትና የቁጥጥር ስራዎችን ደግሞ የተቋሙ የኢንጂነሪንግ ሱፐርቪዥንና ኮንትራት አስተዳደር መምሪያ በጋራ ይሰሩታል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ኑሀ/ሞመ
ግንቦት 6 ቀን 2017 ዓ.ም
15 559
በጣቢያው ሲከናወን የቆየዉ የመቆጣጠሪያዎች ቅየራ ተጠናቀቀ
…….///……….
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ 2 ሪጂን ሥር በሚገኘው የሠመራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሲከናወን የቆየው የመቆጣጠሪያ ወይም ስዊችጊር ቅየራ መጠናቀቁን የመምሪያው ዳይሬክተር አስታውቁ፡፡
ዳይሬክተሩ አቶ ሐሰን ሙሓመድ እንደገለፁት በተቋሙ በራስ አቅም የማከፋፈያ ጣቢያውን የመቆጣጠሪያ ክፍል የማሻሻልና የማዘመን ሥራዎች በመስራት የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝነት ለመጨመር ተችሏል፡፡
በማከፋፈያ ጣቢያው ለረጅም ጊዜ ያገለገለውን በአየር የሚሰራ መቆጣጠሪያ በጋዝ ወደሚሰራ መቆጣጠሪያ መቀየር መቻሉ የጣቢያውን የኦፕሬሽን አቅም በማሳደግ አስተማማኝ እና የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችል ጠቅሰዋል።
የተቀየሩት መቆጣጠሪያዎች ቀደም ሲል የሚያጋጥመውን የኃይል መቆራረጥን ለማስወገድ እና የቁጥጥር ሥርዓቱን ለማዘመን እንደሚያስችል አስረድተዋል፡፡
በ2003 ዓ.ም ተገንብቶ ለአፋር ክልል በዋነኝነት ኃይል እያቀረበ የሚገኘው የሰመራ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከኮምቦልቻ በ230 ኪሎ ቮልት የተቀበለውን ኃይል ወደ አፍዴራና ዲቾቶ ማከፋፈያ ጣቢያዎች በማስተላለፍ ከ80 በመቶ በላይ የሆነውን የአፋር ክልል ተደራሽ ያደርጋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ኑሀ/ሞመ
ግንቦት 5 ቀን 2017 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
