EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 537 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 357,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 176 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 537 名订阅者。
根据 01 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 22,过去 24 小时变化为 4,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.24%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.50% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 921 次浏览,首日通常累积 2 563 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 02 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 537
订阅者
+424 小时
-357 天
+2230 天
帖子存档
15 537
የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ በመጀመሩ መደሰታቸውን የከተማዋ ነዋሪዎች ገለፁ
...........///............ የደብረታቦር እና አካባቢው ነዋሪዎች የዘመናት ጥያቄያቸው የነበረው የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ በማግኘቱ መደሰታቸውን ተናገሩ።
በደብረታቦር ከተማ አስተዳደር የፀጉር አዲኮ ቀበሌ የሃይማኖት አባት የሆኑት መምህር ገ/ እግዚአብሔር መርሻ እንደተናገሩት የኃይል ማከፋፈያ ግንባታው መጀመሩ የብርሃን ደብር የሚል ትርጓሜ ላላት ለደብረታቦር ከተማ ተጨማሪ የተስፋ ብርሃን ያጎናጽፋታል።
ፕሮጀክቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ማንኛውንም ዓይነት ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውንም መምህር ገ/ እግዚአብሔር አረጋግጠዋል።
የፀጉር አዲኮ ቀበሌ ሊቀ መንበር አቶ መንግሥቱ ሞላ በበኩላቸው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው መጀመር ለታሪካዊቷ ደብረታቦር ከተማ እና አካባቢው የኢንቨስትመንት ለመሳብ እንደሚያግዝ ገልፀዋል።
እንደሊቀመንበሩ ገለፃ የፕሮጀክቱ ግንባታ ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ስራ ሁሉ ይከናወናል።
የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ያለው ዘለቀ በበኩላቸው የፕሮጀክቱ ግንባታ ያለአንዳች የፀጥታ ችግር እንዲከናወን ፕሮጀክቱን የሚከታተሉ የፀጥታ አስከባሪዎች እንደሚመደቡ አስታውቀዋል።
ማከፋፈያ ጣቢያው የሚገነባበት ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ወጣት አማረ ብርቁ በበኩሉ ከዚህ በፊት ሥራ እንዳልነበረው ገልፆ ፕሮጀክቱ በፈጠረለት የሥራ ዕድል ራሱንና ቤተሰቡን በመደገፍ ላይ መሆኑን ተናግሯል።
ወጣት አማረ ሁሉም ወጣት ራሱን ከአልባሌ ቦታዎች በማራቅ ራሱንና ቤተሰቡን ለመቀየር በሚያስችል ስራ መሠማራት ይኖርበታል ብሏል።
የደብረታቦር ባለ 230 ኪ.ቮ. የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ በደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ ደሳለኝ በላቸው ግንቦት 19 ቀን 2015 ዓ.ም በይፋ መጀመሩ ተበስሯል።
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ግንቦት 20 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
የደብረታቦር ባለ 230 ኪ.ቮ የኃይል ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ በይፋ ተጀመረ
……….///……….
ለደብረታቦር እና አካባቢው አገልግሎት እንዲሰጥ የታቀደው የደብረታቦር ባለ 230 ኪ.ቮ የኃይል ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ግንቦት 19 ቀን 2015 ዓ.ም. በይፋ ተጀምሯል፡፡
ግንባታውን በይፋ ያስጀመሩት የከተማዋ ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ ደሳለኝ በላቸው እንደተናገሩት ፕሮጀክቱ የደብረታቦር እና አካባቢውን ህዝብ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ ለኢንዱስትሪ መስፋፋትም ጉልህ ሚና ይኖረዋል።
የደብረታቦር እና አካባቢው የዘመናት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ጥያቄ ምላሽ በማግኘቱ መደሰታቸውንም ተናግረዋል።
ፕሮጀክቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ የከተማ አስተዳደሩ እና የአካባቢው ህብረተሰብ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል መምሪያ የፕሮጀክት ማኔጅመንት 2 ሥራ አስኪያጅ አቶ ተድላ ሰይፉ በበኩላቸው የሚገነባው የማከፋፈያ ጣቢያ ሁለት ፓወር ትራንስፈርመሮች ፣ ሁለት ገቢና ሃያ ወጪ መስመሮች እንደሚኖሩት ገልፀዋል።
የግንባታ ወጭው ከዓለም ባንክ በተገኘ ብድር እንደሚሸፈን የገለፁት አቶ ተድላ ግንባታውን በተያዘለት ጊዜና ጥራት ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ አስታውቀዋል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ፕሮጀክቱ ከጅማሬው ከ70 በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ጠቅሰው ፕሮጀከቱ በስኬት እንዲጠናቀቅ የአካባቢው ማህበረሰብ ድጋፍ እንዲያደርግም ጠይቀዋል።
የዋና ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ተወካይ አቶ ዋለ ታምሬ በበኩላቸው የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ ስርቆቱን ለማስቀረት የሃይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች ህዝቡን እንዲያስተምሩ አሳስበዋል።
በዘጠኝ ሔክታር መሬት ላይ የሚያርፈውን ፕሮጀክት በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ መታቀዱን እና ለግንባታው 250 ሚሊዮን ብር መመደቡን የገለፁት ደግሞ የፕሮጀክቱ የሳይት ስራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ ከፈለኝ ናቸው።
በግንባታ ማስጀመሪያ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ከንቲባን ጨምሮ ምክትል ከንቲባው አቶ ኃይለኢየሱስ ሰሎሞን፣ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊዋ ወ/ሮ አዲስ መብራቴ፣ ሌሎች የከተማዋ የሥራ ኃላፊዎች፣ የአካባቢው ነዋሪዎችና የሃይማኖት አባቶች ተገኝተዋል።
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ግንቦት 20 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
የወሰን ማስከበር ችግር ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና በጀት እንዳይጠናቀቁ እያደረገ ይገኛል
………///………..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እያከናወናቸው ያሉ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ግንባታ በተያዘላቸው መርሐግብር እና በጀት ለማጠናቀቅ የወሰን ማስከበር ችግር ፈተና እንደሆነ በተቋሙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ ገለጹ፡፡
ሥራ አስፈጻሚው አቶ ክብሮም ካህሳይ እንደገለጹት ተቋሙ በመላ ሀገሪቱ ከሚያከናወናቸው የተለያዩ ፕሮጀክቶች አብዛኛዎቹ የወሰን ማስከበር ችግር ያለባቸው በመሆኑ በተያዘላቸው መርሃ ግብር እና በጀት እንዳይጠናቀቁ እያደረጋቸው ይገኛል፡፡
ከቋሚ ንብረቶች በተጨማሪ ጥቅም ለማግኘት በመፈለግ እየተከናወኑ ያሉ የአዳዲስ ቤቶች ግንባታ እና የችግኝ ተከላዎች በፕሮጀክቶቹ የግንባታ ሂደት ላይ ፈተና መሆናቸውንም አቶ ክብሮም አስታውቀዋል፡፡
የካሳ ግምቱ በከተማና ወረዳ መስተዳድሮች የሚከናወን በመሆኑ አንዳንድ የወረዳ አስተዳደሮች የካሳ ግምት ሥራውን በወቅቱ እንደማያቀርቡ እና ለሥራው ትኩረት ያለመስጠት ሁኔታ እንደሚስተዋልባቸው ሥራ አስፈፃሚው ገልፀዋል፡፡
ተቋሙ የወሰን ማስከበር ችግሮችን ለመፍታት ፕሮጀክቶች ከሚገኙባቸው የወረዳ መስተዳደሮች ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ እና በመስተዳድሮቹ ከሚቋቋሙ ኮሚቴዎች ጋር ውይይቶች እንደሚደረጉ ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሥራውን ከመታዘብና ተሰርተው የሚቀርቡ የካሳ ግምት ክፍያዎችን በማረጋገጥ ክፍያውን ከመፈጸም የዘለለ ሚና እንደሌለው ሥራ አስፈፃሚው አመልክተዋል፡፡
እንደ አቶ ክብሮም ገለጻ ፕሮጀክቶች በመዘግየታቸው የተነሳ በውጭ ሥራ ተቋራጮች በሚከናወኑ ፕሮጀክቶች ላይ ተጨማሪ የማካካሻ እና የይገባኛል ጥያቄ እንዲነሳ በማድረግ ተቋሙን ለተጨማሪ ወጭ እየደረገው ይገኛል፡፡
የፕሮጀክቶች ግንባታ ቢጠናቀቅም የወሰን ማስከበር ችግሮች ካልተፈቱ ፕሮጀክቱን ኢነርጃይዝ ማድረግ ስለማይቻል ህብረተሰቡን የኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ ከፍተኛ ተግዳሮት ይኖራቸዋል ብለዋል፡፡
በመሆኑም ህብረተሰቡ ፕሮጀክቶች በወቅቱ ተጠናቀው ወደ አገልግሎት ሲገቡ ተጠቃሚ የሚያደርጉት ራሳቸውን መሆኑን ተገንዝበው ተባባሪ እንዲሆኑና የመስተዳድር አካላቱም ካሳ የተከፈላቸውን ግለሰቦች በማስነሳት የሚታዩትን ክፍተቶች በማረም ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና በጀት እንዲጠናቀቁ ለማድረግ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ አሳስበዋል፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
ማህበሩ የፋይናንስ አቅሙ ከ14 ሚሊዮን ብር በላይ መድረሱን አስታወቀ
…….///……..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ባከናወናቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት የፋይናንስ አቅሙ ከዕለት ወደ ዕለት እያደገ መምጣቱን የማህበሩ ሊቀመንበር አስታወቁ፡፡
ሊቀመንበሩ አቶ መኮንን ክፍሌ እንደገለፁት የአባላት ወርሃዊ ክፍያ በአግባቡና በወቅቱ በመሰብሰቡ በአሁኑ ጊዜ የማህበሩ ተቀማጭ ገንዘብ ከ14 ሚሊዮን ብር በላይ ደርሷል፡፡
በተጨማሪም ማህበሩ ያፈራውን ገንዘብ ባንኮችን በጨረታ አወዳድሮ በማስቀመጥ ከአራት ሚሊዮን ብር በላይ ወለድ ማግኘቱንም ነው ሊቀመንበሩ ያስታወቁት፡፡
ማህበሩ ባለፉት ሶስት ዓመታት ገቢውን ለማሳደግ አዳዲስ አባላትን በማፍራት በየወሩ የደመወዛቸውን አንድ በመቶ በመሰብሰብ የፋይናንስ አቅሙን ማጠናከሩን ተናግረዋል፡፡
እንደ ሊቀመንበሩ ገለፃ የቀድሞው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ወደሁለት የተለያዩ ተቋማት ሲከፈል ማህበሩ አንድ ሚሊዮን ብር ድርሻ ያገኘ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ 14 እጥፍ በማሳደግ በጥሬ ገንዘብ 14 ሚሊዮን ብር አድርሶታል፡፡
የማህበሩ የኦዲት ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ተሾመ በላይ በበኩላቸው የማህበሩ የፋይናንስ አጠቃቀም እና የአሰራር ስርዓት በየዓመቱ ኦዲት እየተደረገ እንደሚገኝ ገልፀው የ2013 እና የ2014 በጀት ዓመት የማህበሩ የፋይናንስ አጠቃቀም ህግና መመሪያን የተከተለ መሆኑ በኦዲት መረጋገጡን ተናግረዋል፡፡
የ2015 በጀት ዓመት የፋይናንስ አፈፃፀም የኦዲት ሥራ መጀመሩን የተናገሩት አቶ ተሾመ የኦዲት ግኝቶችን በማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ መሠረት ለማህበሩ ጠቅላላ ጉባኤ ይቀርባል ብለዋል፡፡
እንደ አዲስ ከተቋቋመ ስምንት ዓመታትን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር አምስት የሥራ አስፈፃሚ አባላት ያሉት ሲሆን ለጠቅላላ ጉባኤ ተጠሪ የሆኑ ሶስት የኦዲት ኮሚቴ እና 49 የምክር ቤት አባላትን ያቀፈ ነው፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
የሪጅኑ የጤና ስፖርት ቡድን በድሬዳዋ እየተካሄደ ባለው የተቋማት ስፖርት ውድድር ላይ እየተሳተፈ ይገኛል
………///……….
በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር አዘጋጅነት እየተካሄደ ባለው የተቋማት ስፖርት ውድድር ላይ የምስራቅ ሪጅን 1 የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ የሠራተኞች የጤና ስፖርት ቡድን በተለያዩ የውድድር ዓይነቶች እየተሳተፈ እንደሚገኝ የጤና ቡድኑ አስተባባሪ ገለፁ።
አስተባባሪው አቶ ማትያስ ብዙነህ እንደገለፁት የሪጅኑ ሠራተኞች የጤና ስፖርት ቡድን በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር አዘጋጅነት እየተካሄደ ባለው የተቋማት የስፖርት ውድድር ላይ በጠረጴዛ ቴኒስ፣ በሩጫ እና በእግር ኳስ የስፖርት ዓይነቶች ተቋሙን በመወከል እየተሳተፈ ይገኛል።
የቡድኑ ሂሳብ ሹም አቶ ሰለሞን ደምሴ በበኩላቸው በድሬዳዋ እየተካሄደ ያለው ውድድር በተያዘው ዓመት በሀገር አቀፍ ደረጃ በደሴ ከተማ አስተዳደር ለሚካሄደው የተቋማት የስፖርት ውድድር የሚሳተፉ ቡድኖችን ለመለየት ነው።
እስከ አሁን ከተካሄዱ ውድድሮች በሴቶች 100 እና 200 ሜትር ሩጫ ልዩወርቅ አበበ ሪጅኑንና ተቋሙን በመወከል ደሴ ለሚካሄደው ውድድር ማለፍ መቻሏን ነው የተናገሩት።
የጤና ቡድኑ የሚሳተፍበት የወንዶች እግር ኳስ ውድድር ከግንቦት 19 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚካሄድ ያነሱት አቶ ሰለሞን ቡድኑ በደሴ ለሚካሄደው ውድድር ለማለፍ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅትና ልምምድ እያደረገ ይገኛል ብለዋል።
የጤና ስፖርት ቡድኑ ጤንነቱ የተጠበቀ ሠራተኛ ለመፍጠር እና በሠራተኛው መካከል ያለውን የእርስ በርስ መረዳዳትና ግንኑነት እንዲጠናከር እያደረገ እንደሚገኝም ገልፀዋል።
ቡድኑ በተመሳሳይ ውድድሮች መሳተፉ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በአገልግሎቱ መካከል ያለውን ልዩነት ለህብረተሰቡ በማሳወቅና ግንዛቤ በመፍጠር ተቋሙን ለማስተዋወቅ ያግዛል ብለዋል።
የጤና ስፖርት ቡድኑ ተቋሙን ለማስተዋወቅ እየሰራ በመሆኑ የተቋሙ ሥራ አመራር አስፈላጊ ድጋፍ እንዲያደርግለት ጠይቀዋል።
የጤና ስፖርት ቡድኑ መስከረም 2015 ዓ.ም መጀመሪያ ላይ ተቋቁሞ ከከተማ አስተዳደሩ ስፖርት ኮሚሽን እውቅና ያገኘ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ግንቦት 17 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
በኢትዮ ኬንያ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የሚፈፀመው ስርቆት በከፍተኛ ደረጃ ቀንሷል
……...///……....
የኢትዮ ኬንያ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በሚያልፍባቸው አካባቢዎች የመስተዳድር አካላት ለፕሮጀክቱ ትኩረት በመስጠታቸው የስርቆት ወንጀሎች እየቀነሱ መምጣታቸውን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ቴዎድሮስ አያሌው እንደገለፁት በደቡብ ክልል በወላይታ፣ በኮንሶ፣ እና በጋሞ ዞኖች እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል በቦረና ዞን የስርቆት ወንጀሎች በተደጋጋሚ ይከሰቱ ነበር።
እንደገለፁት ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ ፕሮጀክቱ በይፋ ሥራ እስከሚጀምር ድረስ ከ100 ቶን በላይ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ የብረት አካላት እና የኮንዳክተር ስርቆት እንዲሁም 12 ኪ.ሜ. የኮሙኒኬሽን ኬብል በመዘረፉ ተቋሙ 140 ሚሊየን ብር ተጨማሪ ወጪ ማውጣቱን ሥራ አስኪያጁ አስታውሰዋል።
ወንጀለኞችን በቁጥጥር ስር በማዋል ረገድ በሁሉም ዞኖች የተለያዩ ጥረቶች ቢደረጉም ተጠርጣሪዎች ላይ ውሳኔ ለመስጠት የሚታየው መዘግየት እና በአነስተኛ የገንዘብ ዋስ ተጠርጣሪዎች መለቀቃቸው ስርቆቱን ለማስቆም ፈታኝ እንደነበር ጠቅሰዋል፡፡
ይሁንና ከአካባቢዎቹ መስተዳደር አከላት ጋር ጠንካራ ግንኙነትን በመፍጠርና በትብብር በመሰራቱ ፕሮጀክቱ ሥራ ከጀመረ በኋላ ምንም ስርቆት አልተፈፀመም ብለዋል።
ለዚህ ተስፋ ሰጪ ውጤት መምጣት ለአካባቢ መስተዳድሮች ምስጋናቸውን ያቀረቡት አቶ ቴዎድሮስ በከፍተኛ ወጪ የተገነባውና ለኢትዮጵያና ኬንያ የሁለትዮሽ ግንኙነት ከፍተኛ ፋይዳ ላለው ለኢትዮ - ኬንያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ደህንነት መጠበቅ በአካባቢው መስተዳድሮችና በህዝቡ የተጀመሩ የጥበቃ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የኢትዮ - ኬንያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በኢትዮጵያ በኩል ከወላይታ ሶዶ እስከ ኢትዮ ኬንያ ድንበር ድረስ 443 ኪ.ሜ. ርቀት ያለውና 994 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች አሉት፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ግንቦት 17 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
የጊቤ 1 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ9 ወራት ውስጥ ከሰባት መቶ ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል
……..///……..
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጊቤ 1 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ውስጥ 701 ነጥብ 6 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ማመንጨቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ደሳለኝ ንጉሴ እንደገለፁት ማመንጫ ጣቢያው በዘጠኝ ወራት ውስጥ ለማመንጨት ካቀደው 776 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓት ውስጥ 701 ነጥብ 6 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ በማመንጨት የዕቅዱን 90 ነጥብ 3 በመቶ አሳክቷል።
በዘጠኝ ወራት የመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ40 ጊጋ ዋት ወይም የ2 ነጥብ 8 በመቶ ብልጫ መኖሩን ሥራ አአስኪያጁ ገልጸዋል።
ጣቢያው በበጀት ዓመቱ ቀሪ ወራት የሚፈለገውን ኃይል ለማቅረብ ዝግጁ መሆኑንም ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።
የጊቤ 1 የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ1996 ዓ.ም በይፋ ሥራ የጀመረ ሲሆን በወቅቱ 184 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ በማመንጨት ቀዳሚው ጣቢያ ነበር።
የጣቢያውን የሲቪል ሥራ ሳሊኒ ኢምፒሪጊሎ የአሁኑ ዊ ቢውልድ እና የኤሌክትሮ መካኒካል ሥራውን ደግሞ ኤሊን የተባለ የአውስትራሊያ ኩባንያ ያከናወኑ ሲሆን ለግንባታውም 256 ሚሊዮን ዩሮ ወጭ ተደርጎበታል።
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ግንቦት 16 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
ተቋሙ ተሽከርካሪዎችን በራስ አቅም በመጠገን ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ አድኗል
………///………
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተሽከርካሪዎቹን በራሱ አቅም በመጠገን ባለፉት 9 ወራት ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ ማዳኑን የተሸከርካሪ ጥገና አስተዳደር ቢሮ ገለፀ፡፡
የቢሮው ሥራ አስኪያጅ ተወካይ አቶ ብሩክ እንዳለ እንደገለፁት በጋራዡ እየተከናወኑ ያሉት ሥራዎች ተቋሙን ከብዙ ወጭ አድነውታል፡፡
እንደተወካዩ ገለጻ በአሁኑ ወቅት ጋራዡ የተቋሙን ተሽከርካሪ እና ማሽነሪዎች የሞተር ዕድሳት፣ ከባድና ቀላል ጥገና፣ ሙሉ የቦዲና ቀለም ቅብ እንዲሁም ሰርቪስ የማድረግ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡
የሥራ ክፍሉ አዲስ ለሚገዙ ተሽከርካሪዎችም የድርጅቱን የሥራ ባህሪ ግምት ውስጥ ያስገባ የቴክኒክ ዝርዝር የፍላጎት መግለጫ ማዘጋጀትና በወጣው መስፈርት መሰረት መገዛታቸውን የማረጋጥ ሥራ እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡
በተጨማሪም ከፕሮጀክቶች ወደ ተቋሙ ለሚዘዋወሩ ተሸከርካሪዎችና ማሽነሪዎች ሙሉ የቴክኒክ ምርመራ ማድረግ እና በኢንሹራንስ ለሚጠገኑ ተሸከርካሪዎች ደግሞ የክትትል ሥራዎችን እንደሚያከናውን ነው አቶ ብሩክ የተናገሩት፡፡
በተቋሙ ደረጃውን የጠበቀ የጥገና ማዕከል ለመገንባት በጀት መያዙንና የሰው ኃይል ለማሟላት ጥያቄ መቅረቡን አቶ ብሩክ ጠቁመዋል፡፡
የጋራዡ ባለሙያዎች በተለያዩ ድርጅቶች የልምድ ልውውጥ እንዲያካሂዱና በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ሥልጠና እንዲያገኙ በማድረግ ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት ጥረት እየተደረገ ሲሆን አሁን ላለው አቅም የጥገና መስሪያ ቁሳቁሶች በተገቢው መንገድ የተሟሉ መሆናቸው ተገልጿል፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ግንቦት 15 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
ተቋሙ ከኃይል መሠረተ ልማት ግንባታ ጎን ለጎን ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ነው
………///…….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከመሠረተ ልማት ግንባታ ጎን ለጎን ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን የጊቤ 1 የውኃ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ደሳለኝ ንጉሴ እንደገለፁት በኃይል ማመንጫ ግድቡ ዙሪያ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የትምህርት፣ የንፁህ የመጠጥ ውሃ እና የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡
በተቋሙ ወጪ የተገነባው የንፁህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ከጣቢያው ሠራተኞች ባሻገር ለአካባቢው ነዋሪ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል።
በጅማ ዞን ሰኮሩ ወረዳ ዳካ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ ሂንዲያ አባጀበል እንደተናገሩት በአካባቢው ንፁህ የመጠጥ ውሃ ባለመኖሩ ረጅም መንገድ ተጉዘው የወንዝ ውሃ ይጠቀሙ ነበር፡፡
የጊቤ 1 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የመጠጥ ውሃ ጉድጓድ ካስቆፈረ በኋላ ግን በቅርብ ርቀት የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።
አቶ ተማም አህመድ የተባሉ የአካባቢው ነዋሪ በበኩላቸው ተቋሙ ከውሃ አቅርቦት በተጨማሪ ትምህርት ቤት ሠርቶ ለነዋሪው ማስረከቡን እና የአካባቢው ማህበረሰብ ድንገተኛ ችግር ሲያጋጥመው ትራንስፖርት በማመቻቸት ሁልጊዜ በሀዘንና ደስታ ከጎናቸው መሆኑን ተናግረዋል።
በተቋሙ የጊቤ 1 የሰው ሀይል አስተዳደርና ጠቅላላ ንብረት አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ ተወካይ አቶ ጌቱ ጋሻሁን እንደገለፁት የማህበረሰቡ ፍላጎት እያደገ በመምጣቱ ተጨማሪ የውሃ አገልግሎት መስጫ ጣቢያ ግንባታ እየተከናወነ ነው።
በ3 አዋሳኝ ቀበሌዎች የሚኖሩ አራት መቶ አባወራዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የንፁህ መጠጥ ውሃ የቁፋሮ ሥራ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁንና የቧንቧ መስመር ዝርጋታ ሥራ ለማከናወን የግዥ ሂደቱ መጀመሩን ተወካዩ አብራርተዋል።
ለጉድጓድ ቁፋሮው ብቻ 10 ሚሊዮን ብር መመደቡን የጠቆሙት አቶ ጌቱ ለቧንቧ መስመር ዝርጋታ የሚያስፈልገው ወጪ የሚታወቀው ከጨረታው በኋላ ነው ብለዋል።
በተያያዘ ዜና ከስደት የተመለሱ ወጣቶች የግድቡን ደህንነት ለመጠበቅ በለማው አረንጓዴ አካባቢ የሠርግና መዝናኛ፣ የጀልባ ትራንስፖርት እና የዓሳ ምግብ አገልግሎት በመስጠት ገቢያቸውን እያሳደጉ መሆናቸውን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ንጉሳ ገልጸዋል፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ግንቦት 14 ቀን 2015 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
