ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 533 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 368,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 174

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 533 名订阅者。

根据 30 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 10,过去 24 小时变化为 -6,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 24.86%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.87% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 862 次浏览,首日通常累积 2 620 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 01 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 533
订阅者
-624 小时
-207
+1030
帖子存档
ጳጕሜን 03 ቀን 2015 ዓ.ም. - የበጎነት ቀን
ጳጕሜን 03 ቀን 2015 ዓ.ም. - የበጎነት ቀን

ጳጉሜን 2 ቀን 2015 ዓ.ም. - የመስዋዕትነት ቀን መስዋዕትነት በሚጠይቁ ፈታኝ ሥራዎች ላይ በመሰማራት የተቋማችን ተልዕኮ እንዲሳካ ያልተቋረጠ ጥረት የምታደርጉ የተቋማችን ሠራተኞች እና የሥራ መሪ
ጳጉሜን 2 ቀን 2015 ዓ.ም. - የመስዋዕትነት ቀን መስዋዕትነት በሚጠይቁ ፈታኝ ሥራዎች ላይ በመሰማራት የተቋማችን ተልዕኮ እንዲሳካ ያልተቋረጠ ጥረት የምታደርጉ የተቋማችን ሠራተኞች እና የሥራ መሪዎችን ዛሬ በሀገርአቀፍ ደረጃ የሚከበረውን የመስዋዕትነት ቀን ምክንያት አድርጌ በራሴና በከፍተኛ ሥራ አስፈፃሚ ቡድኑ ስም ማመስገን እፈልጋለሁ። የኃይል ማመንጨትና የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ የግንባታ፣ ኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች በአብዛኛው በአስቸጋሪ መልክዐምድር እና በፈታኝ የአየር ንብረት ውስጥ የሚከናወኑ ከመሆናቸው ባለፈ የአካል እና የህይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ መሆኑ ይታወቃል። በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት በትግራይ፣ በአማራ እና በአፋር ክልሎች የተጎዱ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን መልሶ ለመጠገን የተቋማችን ሠራተኞች የፀጥታ ኃይሉን ተከትለው ከፍተኛ መስዋዕትነት በመክፈል ለወራት የተቋረጠውን ኃይል መልሶ በማገናኘት ህብረተሰቡ ኤሌክትሪክ እንዲያገኝ ከማድረግ ባለፈ የተቋሙን ገፅታ በመገንባት አመርቂ ውጤት አስመዝገበዋል። በታሪክ ሲታወስ ለሚኖረው ለዚህ ተግባር ተቋማችን በድጋሚ ምስጋናውን ያቀርባል። ስለኢትዮጵያ አስፈላጊውን መስዋዕትነት እንከፍላለን! አሸብር ባልቻ(ኢንጂነር) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ

photo content
+7

ለመላዉ የተቋማችን ሠራተኞች እና የሥራ መሪዎች በሙሉ ዛሬ ጳጉሜን 1 ቀን 2015 ዓ.ም. በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሚከበረው የአገልጋይነት ቀን እንኳን በሰላም አደረሳችሁ፡፡ የዛሬዋ ዕለት “ኢትዮጵያን እናገልግል” በሚል መሪ ቃል ተሰይማለች፡፡ ይህች ዕለት በቀን 24 ሰዓት፣ ሳምንቱን ሙሉ ሰባቱንም ቀናት፣ እንዲሁም ዓመቱን ሙሉ የኃይል አቅርቦት ሳይስተጓጎል ለማቅረብ ለሚተጋው ለተቋማን ትልቅ ትርጉም አላት፡፡ ኃይል የማመንጨት እንዲሁም የመነጨውን ኃይል በማስተላለፊያ መስመሮች የማጓጓዝና ወደሚፈለገው ቦታ የማድረስ ሥራ ለአፍታ እንዳይስተጓጎል ለማድረግ የሚሰራው ሥራ ቀን ከሌሊት በአስቸጋሪ መልክዓምድር እና የአየር ሁኔታ ውስጥ በማለፍ የሚሰራ ሥራ መሆኑን አብዛኛው ሰው እንደሚረዳው እምነት አለኝ፡፡ ይህን አስቸጋሪ እና ፈታኝ በሆነ ሁኔታ ውስጥ የከናወን አገልግሎት በዓመት አንድ ቀንም ቢሆን እንዲታሰብ መደረጉ መልካም ጅምር ቢሆንም አንዷን ቀን እንደ ዓመት አንዱን ዓመት እንደ አንድ ቀን በማድረግ ያልተቋረጠ የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራ የምስትሰሩ ሠራተኞችን በተቋማችን ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን ስም ለማመስገን እወዳለሁ፡፡ እያንዳንዱ ዜጋ በቤቱ ውስጥ የዕለት ተዕለት ተግባሩን በብቃት እንዲከውን፣ እያንዳንዱ ተቋም የተሰጠውን ተልዕኮ ማሳካት እንዲችል፣ ማህበራዊ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት ለህብረተሰቡ የሚፈለገውን አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ዓመቱን በሙሉ ያለማቋረጥ ኤሌክትሪክ ለማቅረብ የምትተጉት ለእውነተኛ የህዝብ አገልጋይ የተቋማችን ሠራተኞች እና የሥራ መሪዎች እንኳን አደረሳችሁ ስል በታላቅ ኩራት ነው፡፡ የሰው ልጆች በዚህ ዓለም የመኖር ተልዕኮና ምስጢር ለሀገር እና ለህዝብ ፋይዳ ያለው አስተዋጽኦ አበርክቶ ማለፍ ነው፡፡ ስለሆነም ራሳችንን በዕድሜያችን ምን ሰርተናል? ለማህበረሰባችን ምን አበርክተናል ብለን ልንጠይቅ ይገባል፡፡ የዚህን ጊዜ የምናገኘው መልስ ድርሻችን የተለያየ ቢሆንም ለተቋማችን፣ ለህዝባችንና ለሀገራችን አንዳች ፋይዳ ያለው አስተዋጽኦ እንዳበረከትን ያለጥርጥር መናገር እንችላለን፡፡ እውነት ነው - የእያንዳንዳችን አስተዋጽኦ ነው ተቋማችን የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ እንዲወጣ የሚያደርገው፤ የእያንዳንዳችን ሥራ ነው የህዝብን ጥያቄ የሚፈታው፡፡ በመሆኑም የጀመርነውን ህዝባዊ አገልግሎት ከደመወዝ ባሻገር እያሰብን ለህዝባችንና ለሀገራችን የበለጠ የምንሰራበት እንዲሆን የተሰጠንን ኃላፊነት በትጋት እንድንወጣ አሳስባለሁ፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ እኛ አለን፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ቤተሰቦቻችን አሉ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ያስተማረንና ያሳደገን ማህበረሰብ አለ፡፡ “ኢትዮጵያን እናገልግል” በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን የአገልጋይነት ቀን የተለየ ትኩረት የሰጠነው በዚህ ምክንያት ነው፡፡ ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ! አሸብር ባልቻ(ኢንጂነር) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ

photo content
+5

የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች በሀገሪቱ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ተወያዩ .......///........ በአማራ ክልል የተከሰተውን አለመረጋጋት ለመፍታት ሁሉም የመፍትሄው አካል ሊሆን እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ተናገሩ። የሥራ መሪዎቹና ሠራተኞቹ በአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ውይይት አካሂደዋል። በውይይቱ ላይ የተገኙት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት ውይይቱ ለሠራተኛው በክልሉ ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ መረጃ በመስጠት የጋራ መግባባት ላይ ለመድረስ ያለመ ነው። በክልሉ የተፈጠረውን አለመረጋጋት ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑን የጠቀሱት ዋና ሥራ አስፈፃሚው ችግሩን ለመፍታት ሁሉም የመፍትሄው አካል ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በክልሉ የሚነሱ ጥያቄዎች መልስ እንዲያገኙ ከኃይል ይልቅ የሠላም አማራጭን መከተል እንደሚገባ  ተናግረዋል። ሠላም በአንድ አካል ብቻ ሊመጣ ስለማይችል የክልሉን ብሎም የሀገሪቱን ሰላም ለማስፈን በሚሰራው ሥራ ላይ ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”          የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ነሐሴ 25 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

photo content
+9

ተቋሙ ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ወጪ የትምህርት ግብዐቶች ድጋፍ አደረገ ..........///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የም ዞን ለሚገኘው ፎፋ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተለያዩ የትምህርት ግብዐቶችን ድጋፍ አድርጓል። ድጋፉን የተቋሙ የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽ ዘርፍ የክላስተር 1 ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጌትነት በቀለ ለዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ገ /ሚካኤል አስረክበዋል። የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ገ/ ሚካኤል በርክክብ ሥነ ሥርዓቱ ወቅት እንደተናገሩት ትምህርት የድህነት ተራራን ለመናድ የሚያግዝ መሳሪያ በመሆኑ በዕውቀት ግንባታ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይገባል። ተቋሙ ያደረገው ድጋፍ "ጥራት ያለው ትምህርት ለትውልድ " በሚል መሪ ቃል የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻልና በግብዐት እንዲሟሉ ለማድረግ የተጀመረው ሀገር አቀፍ ንቅናቄ አንድ አካል መሆኑን ጠቅሰው ለተደረገው ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል። ተቋሙ ያደረገው ድጋፍ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና ሀገር በቀል ዕውቀቶችን ለማዳበር እየተከናወነ ያለውን ሥራ እንደሚደግፍም አመልክተዋል። የትምህርት ጥራትን ለማረጋጋጥ እና በትምህርት ቤቶች ላይ የተጓደሉ የትምህርት መሳሪያዎችን ለማሟላት ሁሉም ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል። የተቋሙ የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽ ዘርፍ የክላስተር 1 ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጌትነት በቀለ በበኩላቸው እንደተናገሩት ተቋሙ ከተሰጠው ተልዕኮ በተጨማሪ በተለያዩ ምክንያቶች ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የሰብዓዊ ዕርዳታ እና በሀገሪቱ ለሚከናወኑ የልማት ሥራዎች የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ ይገኛል። ተቋሙ የማህበረሰብ አቀፍ ድጋፎችን ከማድረጉም ባሻገር በማመንጫ ጣቢያዎች አካባቢ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ኃይል እንዲያገኙ የማድረግና የሥራ ዕድሎችን እንዲፈጠርላቸው በማድረግ በኩል በርካታ ሥራዎች ማከናወኑን ጠቁመዋል። ለፎፋ 2ኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤቱ የተደረገው ድጋፍ ለተለያዩ አገልግሎት የሚውሉ ጠረጴዛዎች፣ የጥቁር ሰሌዳ፣  የቤተ መጻህፍት መደርደሪያዎች፣ የላብራቶሪ ዕቃዎች፣ ቁም ሳጥን፣ ወንበሮች፣ ለተማሪዎች መተኛ የሚያገለግሉ አልጋዎች እና ሌሎች የትምህርት ግብዐቶችን ያካተተ ሲሆን ለዚህም ተቋሙ ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማድረጉን ተናግረዋል። ተቋሙ በትውልድ ልማት ሥራዎች ላይ አሻራውን በማሳረፉ ደስተኛ መሆኑንም አመላክተዋል። ከዚህ በፊት ዞኑ ከጊቤ II የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ጋር በመተባበር ጣቢያውን ከሰው ሰራሽ  አደጋዎች ለመጠበቅ  ህብረተሰቡ ላደረገው ድጋፍ አመስግነው በቀጣይ የዞኑ ነዋሪ በአካባቢው የሚገኙ የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ብረቶችን ከስርቆትና መሰል ወንጀሎች መጠበቅ እንዳለበትም አሳስበዋል። በርክክብ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የዞኑና የወረዳው የሥራ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተወካዮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም የፎፋ ከተማና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”          የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ነሐሴ 24 ቀን 2015 ዓ.ም

ለዛሬ ምን ቀጠሮ ይዘዋል? ተቋማችን የሚሳተፍበት የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ አውደርዕይ በኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በይፋ መከፈቱ ይታወሳል። አውደርዕዩ ከሰኞ እስከ እሁድ ከጠዋቱ 2:30 እስ
ለዛሬ ምን ቀጠሮ ይዘዋል? ተቋማችን የሚሳተፍበት የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ አውደርዕይ በኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በይፋ መከፈቱ ይታወሳል። አውደርዕዩ ከሰኞ እስከ እሁድ ከጠዋቱ 2:30 እስከ ምሽት 1:00 ሰዓት ድረስ ለዕይታ ክፍት ሆኗል።ዛሬ ነሐሴ 22 ቀን 2015 ዓ/ም በኢነርጂ ዘርፍ የተሰማሩ ተቋማት ሠራተኞች የሚጎበኙበት ቀን እንዲሆን ስለተመቻቸ በአዲስ አበባና በዙሪያዋ የምትገኙ የተቋማችን ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች አውደርዕዩን እንድትመለከቱ እንጋብዛለን። የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ

photo content
+3

እንኳን ደስ አለን!! እንኳን ደስ አላችሁ !!! ......////....... በሀንጋሪ ቡዳፔስት እየተካሔደ ባለው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶች ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች አንደኛ፣ ሁለተኛ እና አምስተኛ በመውጣት አሸናፊ ሆነዋል።                   አትሌት አማኔ በሪሶ 1ኛ በመሆን ለሃገሯ የወርቅ ሜዳሊያ ስታስገኝ፣ የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ አትሌት እና የአምናው ሻምፒዮና የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት አትሌት ጎይተቶም ገ/ስላሴ 2ኛ በመሆን የብር ሜዳሊያ አግኝታለች። ሌላኛዋ የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ አትሌት ያለምዘርፍ የኋላው 5ኛ በመውጣት የዲፕሎማ ተሸላሚ ሆናለች።                                    እንደሀገር በተገኘው ውጤት እና የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ አትሌቶች ባመጡት ውጤት በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”          የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ነሐሴ 20 ቀን 2015 ዓ.ም

ለመላው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች እና የሥራ መሪዎች ተቋማችን የሚሳተፍበት የውና ኢነርጂ ዘርፍ አውደርዕይ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በይፋ መከፈቱ
ለመላው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች እና የሥራ መሪዎች ተቋማችን የሚሳተፍበት የውና ኢነርጂ ዘርፍ አውደርዕይ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በይፋ መከፈቱ ይታወሳል። በመሆኑም አውደርዕዩ ከሰኞ እስከ እሁድ ከጠዋቱ 2:30 እስከ ምሽት 11:00 ሰዓት ድረስ ለዕይታ ክፍት መሆኑን እየገለፅን የፊታችን ሰኞ ነሐሴ 22 ቀን 2015 ዓ/ም ደግሞ በኢነርጂ ዘርፍ የተሰማሩ ተቋማት ሠራተኞች ብቻ የሚጎበኙበት ቀን እንዲሆን ስለተመቻቸ በአዲስ አበባና በዙሪያዋ የምትገኙ የተቋማችን ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች በተጠቀሰው ቀን የጉብኝት መርሃግብሩ ላይ እንድትሳተፉ እንጋብዛለን። የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ

photo content

photo content
+5

photo content
+9

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚሳተፍበት የውሃና ኢነርጂ አውደርዕይ ተከፈተ .........///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚሳተፍበት የውሃና ኢነርጂ አውደርዕይ በኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና በተባበሩት አረብ ኢመሬቶች ፕሬዝዳንት ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ተከፍቷል። በኢትዮጵያ ሳይንስ ሙዚየም ትናንት በይፋ የተከፈተው የውሃ እና ኢነርጂ አውደ ርዕይ ለቀጣዮቹ አራት ሳምንታት እንደሚቆይ የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ገልፀዋል። አውደርዕዩ በውሃ፣ ሳኒቴሽና ኢነርጂ ዘርፍ የተሰማሩ የግልና የመንግስት ተቋማት የተሳተፉበት ሲሆን በእያንዳንዱ የአውደርዕይ ቡዝ ላይ የተቋማቱን ሥራ የሚያሳዩ ሳቢና አስተማሪ መረጃዎችን ለዕይታ ቀርበዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልም የታላቁ ህዳሴ ግድብን ሞዴልን ጨምሮ በግንባታ እና በኦፕሬሽን ላይ ያሉ የውሃ እና የንፋስ ሞዴሎች እንዲሁም ተቋሙ የሚሰራቸውን ሥራዎችና የወደፊት ዕቅዶች የሚያሳዩ መረጃዎች ለዕይታ አቅርቧል። አውደ ርዕዩ የኢትዮጵያን የውሃ እና የኢነርጂ ሀብቶች እንዲሁም እምቅ አቅምን ለማሳየት ያለመ ሲሆን ለቀጣዮቹ 30 ቀናት ለህዝብ ክፍት ይሆናል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”          የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ነሐሴ 13 ቀን 2015 ዓ.ም

የፈተና ውጤት ማስታወቂያ
የፈተና ውጤት ማስታወቂያ

ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሰጠ ማሳሰቢያ ቅዳሜ ሐምሌ 29 እና እሁድ ሐምሌ 30 ቀን 2015 ዓ/ም የቦሌ ዓለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ጂ አይ ኤስ ማከፋፈያ ጣቢያን ከቃሊቲ ኮተቤ ከተዘረጋው ባለ132 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር ጋር የማገናኘት ሥራ ይሰራል። በመሆኑም ለሥራው ሲባል ቅዳሜ ከማለዳው 11:30 ሰዓት እስከ 12:30 ሰዓት ድረስ መስመሩን የማለያየት እንዲሁም ከምሽቱ 12:00 እስከ 1:00 ሰዓት ድረስ መስመሩን የማገናኘት ሥራ ስለሚሰራ ከዚህ በታቸ በተዘረዘሩት አካባቢዎች ኃይል ተቋርጦ የሚቆይ መሆኑን እናስታውቃለን። ከወረገኑ ማከፋፈያ ጣቢያ ወደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ በተዘረጋው መስመር፣ በብሔራዊ ሜቲዮሮሎጂ፣ በስካይ ላይት ሆቴል እና በአካባቢው፣ በዩኒቲ ዩኒሸርሲቲ፣ በ24 ቀበሌ፣ በኮሪያ ሆስፒታል፣ በፓርላማ ተመራጮች መኖሪያ፣ በገርጂ፣ በቦሌ ክፍለከተማና በአካባቢው፣ በጆኒ ገራዥና በአካባቢው፣ በሰሚት ለስላሳ ፋብሪካ፣ በፍየል ቤት፣ በዋጄ ጊዮርጊስ፣ በፍሊንት ስቶን ሪል ስቴት እና በአካባቢው፣ በኢትዮ ፕላስቲክ ፋብሪካና በአካባቢው፣ በጃክሮስ ሪል ስቴት፣ በጎሮ እና በአካባቢው በተጠቀሱት ቀናትና ሰዓታት ኃይል ስለሚቋረጥ ተገቢውን ዝግጅት እንድታደርጉ ከወዲሁ እናሳስባለን። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

photo content
+4