ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 543 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 332,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 157

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 543 名订阅者。

根据 27 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 10,过去 24 小时变化为 -16,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.06%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.33% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 895 次浏览,首日通常累积 2 539 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 7

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 28 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 543
订阅者
-1624 小时
-97
+1030
帖子存档
photo content
+5

ተቋሙ የነደፈውን ስትራቴጂክ ዕቅድ ለማሳካት በትብብር መስራት ያስፈልጋል ..........///........... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ በአርባ ምንጭ ከተማ ሲያካሂድ የነበረውን የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ አጠናቋል። በግምገማው ወቅት ሠራተኞች የሥራ ላይ ደህንነት ህጎችን ተከትለው እንዲሠሩ ከማድረግ፣  ሥራዎችን በቴክኖሎጂ በመታገዝ ከመተግበር፣ ከዕቅድና ሪፖርት ዝግጅት፣ የቡድን ሥራን ከማጠናከር እና ብቃት ያለው ባለሙያ ከማፍራት አንፃር ክፍተቶች እንደነበሩ ተገምግሟል። የተቋረጡ መስመሮችን ወደ አገልግሎት በፍጥነት ለመመለስ ሲከናወን የነበረው የቁርጠኝነት ሥራ ደግሞ በጥንካሬ ተነስቷል። ከሠው ኃይል አስተዳደር፣ ከሲቪል ጥገና ሥራ፣ ከበጀት አመዳደብና አጠቃቀም፣ ከሥራ መሳሪያዎች አቅርቦት፣ የሠራተኞችን ደህንነት ከማረጋገጥ፣ ከንብረት አስተዳደር፣ ከኃይል መቋረጥ መከላከያ አሰራር ከአደረጃጀት እና ከሳፕ ሲስተም አተገባበር ጋር በተያያዘ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ በዘርፉ የቴክኒካል ድጋፍ መምሪያ  ዳይሬክተር አቶ አበባው ያለው በግምገማው ማጠቃለያ ወቅት እንደተናገሩት ሁሉም ሪጂኖች በክፍተት የተነሱ ሀሳቦችን መዝግቦ በመያዝ ወደ ለችግሮቹ መፍትሔ ሊሰጡ ይገባል። በዘርፉ የዲጂታላይዜሽንና አቅም ማሻሻል መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ዳዊት ገ/ እግዚአብሄር በበኩላቸው በሲሚንቶ እጥረት ምክንያት የአቅም ማሳደግ፣ የማሻሻያ እና የሲቪል ጥገና ሥራዎች ላይ ክፍተቶች እንደነበሩ ጠቅሰው ችግሩን ለመፍታት በትኩረት እንደሚሰራም ተናግረዋል። ችግሮች ሲከሰቱ ከመገፋፋት ይልቅ ተቋሙ የነደፈውን ስትራቴጂክ ዕቅድ ለማሳካት በዘርፉ ስር ያሉ ሁሉም ሪጂኖችና ሌሎች የሥራ ክፍሎች በቅንጅትና በትብብር መንፈስ መስራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። የተቋሙ መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ እንደገለፁት የዘርፉ ግምገማ ክፍተቶችን በማረም በቀጣይ የተሻለ ሥራ ለማከናወን እና በሪጅኖች መካከል መማማርና ልምድ ለመለዋወጥ ያግዛል። ማህበሩ ከተቋሙ ጋር በመቀናጀት ለሠራተኞች ምቹ የሥራ ቦታ እንዲፈጠር እና የሚስተዋሉ ክፍተቶች መፍትሄ እንዲሰጣቸው እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። ሌሎች የሥራ ዘርፎችም የዕቅድ አፈፃፀማቸውን ከሠራተኞቻቸው ጋር በመገምገም ለተሻለ ሥራ ራሳቸውን ዝግጁ እያደረጉ መሄድ እንዳለባቸው አሳስበዋል። ከዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ በተጨማሪ በአርባ ምንጭ እና በወላይታ ሶዶ ከተሞች በሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ጉብኝት በማድረግ ስለ ጣቢያዎቹ የሥራ እንቅስቃሴ ከሠራተኞች ጋር ተወያይተዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 27 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

የሦስት ተርባይኖችን የጥገና ሥራ ሙሉ በሙሉ በራስ አቅም ተከናውኗል ......///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ካሉት አራት ተርባይኖች የሦስቱን ጥገና ሥራ ሙሉ በሙሉ በራስ አቅም ማከናወን ጣቢያው አስታወቀ። በጣቢያው የጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ስዩም ኃይሉ እንደገለጹት ከ2013 ዓ.ም መጨረሻ ጀምሮ በአካባቢው በነበረው የጸጥታ ችግር ምክንያት ለተወሰኑ ወራት የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ከብሔራዊ የኃይል ቋት ውጪ ሆኖ ሲሰራ ቆይቷል። ይሁንና አካባቢው ወደ ሠላም ከተመለሰ በኋላ ጣቢያው ካሉት አራት ተርባይኖች ውስጥ የሦስቱን ተርባይኖች ጥገና ሙሉ በሙሉ በራስ አቅም መከናወኑን ኃላፊው ገልጸዋል። እንደ አቶ ስዩም ገለፃ ቀሪው ተርባይን ተፈቶ የጥገና ሥራ እየተከናወነ ነው። ጥገናቸው ከተጠናቀቁት ሦስት ተርባይኖች መካከል አንዱ በንዝረት ፍተሻ ላይ በመሆኑ በአሁን ወቅት ጣቢያው በሁለት ተርባይኖች ኤሌክትሪክ እያመነጨ ይገኛል ብለዋል። ጣቢያው በሙሉ አቅሙ ኃይል ወደ ማመንጨት እንዲገባ የሚያስችሉ የማስተካከያ፣ የቅድመ መከላከል የጥገና ሥራዎች እንዲሁም ሳምንታዊና ወርሃዊ የፍተሻ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል። የጣቢያው የጥገና ባለሙያ የሆኑት አቶ ሚካኤለ ገብረ ጻዲቅ በበኩላቸው የተርባይንን ጨምሮ ሌሎች የጥገና ሥራዎችን በራስ አቅም እያከናወኑ በመሆናቸው ጊዜንና ወጭን መቆጠብ እንዳስቻለ ተናግረዋል። የጣቢያውን የጥገና ሥራዎች በራስ አቅም ማከናወናቸው ሠራተኞች እርስ በእርስ ልምድ የሚለዋወጡበትና አቅማቸውን የሚያጎለብቱበትን እድል እንደፈጠረላቸውም ጠቁመዋል። ከመለዋወጫ ዕቃ ጋር የተያያዙ ችግሮች እንዲፈታላቸውም ጠይቀዋል። በ1994 ዓ.ም ግንባታው ተጀምሮ ጥቅምት 2002 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረው የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ 300 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አለው። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 26 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

photo content
+3

አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ትኩረት ተሰጥቶት ተሰርቷል ………///……. ባለፉት ዘጠኝ ወራት ያልተቆራረጠ እና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማድረግ በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የፍተሻና ጥገና ሥራዎች ላይ ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ መቆየቱን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የዕቅድና አፈፃፀም ክትትልና ትንተና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ታገል ደገፋ የዘርፉን የዘጠኝ ወራት ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማድረግ በ30 ሺህ 165 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የፍተሻ ሥራ ለማከናወን ታቅዶ በ23 ሺህ 710 ኪሎ ሜትር መስመር ላይ ፍተሻ ተከናውኗል፡፡ ከፍተሻ ሥራው በተጓዳኝ የ24 ሺህ 716 ኪሎ ሜት የማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የጥገና ሥራ ለማከናወን ታቅዶ በ17 ሺህ 282 ኪሎ ሜርት ላይ ጥገና ማከናወን መቻሉንም በሪፖርቱ አመልክተዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ከማስተላለፊያ መስመሮች በተጨማሪ በማከፋፈያ ጣቢያ ቤዮች ላይ የፍተሻና የቅድመ መከላከል ጥገና ሥራዎች ተከናውነዋል። በዚህም ባለፉት ዘጠኝ ወራት በ8 ሺ147 ቤዮች ላይ የፍተሻ ሥራ ለማከናወን ታቅዶ በ7 ሺ 351 ቤዮች ላይ ፍተሻ ሲከናወን በ8 ሺ 761 ቤዮች ላይ የቅድመ መከላከልና የጥገና ሥራዎች ለማከናወን ታቅዶ በ5 ሺ 774 ቤዮች ላይ መከናወኑን ነው የተናገሩት። አፈፃፀሙ ከዕቅዱ ልዩነት ያሳየው በአንዳንድ አካባቢዎች በተስተዋሉ የፀጥታ ችግሮች የተነሳ የፍተሻና የጥገና ሥራዎች በዕቅዱ መሠረት ለማከናወን ባለመቻሉ እንደሆነ አመልክተዋል። አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ የአቅም ውሱንነት ያለባቸውንና የቆዩ ማከፋፈያ ጣቢያዎች አቅም የማሳደግና የማሻሻል እንዲሁም ግሪዱንና አስተማማኝ ለማድረግና ብሬከሮችን ለማዘመን ትኩረት ተሰጥቶት በመከናወን ላይ ይገኛል። የአቅም ማሳደግና ማሻሻያ፣ በውጭ ስራ ተቋራጮች ሊከናወን የነበረ የስማርት ሜትር እና ዘመናዊ የመቆጣጣሪያ ብሬከሮች የተከላ ሥራዎችን በራስ አቅም ማከናወን መጀመሩ በዘጠኝ ወራት ከታዩ ጠንካራ ጎኖች መካከል ተጠቅሰዋል፡፡ በአንፃሩ የሥራ ላይ ደህንነት መሳሪያዎች አለመሟላት፣ በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሰራሮችን በተሟላ ሁኔታ መተግበር አለመቻል፣ ከካሳ ክፍያ ጋር የተያያዙ ችግሮች በወቅቱ መፍትሄ አለማግኘታቸው በድክመት የሚጠቀሱ መሆናቸውም በሪፖርቱ ላይ ተመልክቷል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም

በማከፋፊያ ጣቢያው የኃይል መቆራረጥ እንዳይኖር የሚያደርግ ሥራ ተሰርቷል .......///....... በአድዋ ማከፋፊያ ጣቢያ የኃይል መቆራረጥን ለማስወገድ የሚያስችል የአራት ብሬከሮች ቅየራ መከናወኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ሪጅን የአድዋ ማከፋፊያ ጣቢያ ኃላፊ ገለጹ። ኃላፊው አቶ አብርሃ ይስሃቅ እንደገለጹት በአድዋ ማከፋፊያ ጣቢያ የነበሩት አራት ብሬከሮች በተለያዩ ምክንያቶች ብልሽት ሲገጥማቸው ቆይቷል። በብሬከሮቹ ብልሽት ምክንያትም የማከፋፊያ ጣቢያው በሚሸፍነው የትግራይ ማዕከላዊ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች የኃይል መቆራረጥ ሲያጋጥም መቆየቱን ገልጸዋል። ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ በሰሜን ሪጅን የጥገናና የኦፕሬሽን መምሪያ አቅም አንድ ገቢና ሦስት ወጪ ብሬከሮች ተቀይረው ወደ ሥራ መግባታቸውን አስታውቀዋል። እንደ አቶ አብርሃ ገለጻ የብሬከሩ መቀየር የማከፋፊያ ጣቢያው በሚሸፍነው የትግራይ ማዕከላዊ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች ሲያጋጥም የነበረውን የኃይል መቆራረጥ በመቅረፍ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት አስችሏል። የሰሜን ሪጅን የማከፋፊያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን እና ጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ክፍሌ ተስፋዬ የአራቱ ብሬከሮች ቅየራ ሥራ ሙሉ በሙሉ በሪጅኑ ባለሙያዎች መከናወኑን ተናግረዋል። የብሬከር ቅየራው ላይ የተሳተፉ ሠራተኞች ሙያዊ አቅማቸውን የሚያጎለብቱበት አጋጣሚ መፍጠሩን አብራርተዋል። በ1989 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረው የአድዋ ማከፋፊያ ጣቢያ  64 ሜጋ ዋት ኃይል የመሸከም አቅም አለው። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ዛሬም ድል ቀንቶታል ........///........ በ18ኛው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማን ሶስት ለባዶ በማሸነፍ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዝግቧል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሙሉ በሙሉ የጨዋታ የበላይነት በወሰደበት በዚህ ጨዋታ የማሸነፊያ  ጎሎችን የአጥቂ መስመር ተጨዋቾቹ መሳይ ሰለሞን፣ አቤል ሀብታሙ እና ልዑልሰገድ አስፋው በ8ኛው፣ በ37ኛው እና በ92ኛው ደቂቃ አስቆጥርዋል። የኢትዮ-ኤሌክትሪክ የግራ መስመር ተመላላሽ ተጫዋች ያሬድ የማነ የጨዋታው ኮከብ በመሆን ተመርጧል። የዛሬውን ድል ተከትሎ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ42 ነጥብ እና በ21 ንፁህ ጎል የከፍተኛ ሊጉን በመምራት ላይ ሲሆን አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀረው ኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ በ29 ነጥብ ይከተላል። ወደነበረበት የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ለመመለስ በጥሩ ግስጋሴ ላይ የሚገኘው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመጪው  ሚያዝያ 01 ቀን 2016 ዓ.ም ከንብ ክለብ ጋር 19ኛ የሊግ ጨዋታውን የሚያከናውን ይሆናል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 24 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ 50 ቢሊየን ብር ያስፈልጋል .......///........ የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ የኮንክሪት ሙሌት ግንባታ 99 ነጥብ 2 በመቶ መድረሱን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጅነር ክፍሌ ሆሮ አስታወቁ። "በህብረት ችለናል" በሚል መሪ ቃል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመሰረት ድንጋይ የተጣለበትን 13ኛ ዓመት አስመልክቶ የፓናል ውይይት ተካሒዷል። በውይይቱ ላይ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ እንደገለፁት ከ10 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ የኮንክሪት ሙሌት ውስጥ የ10 ነጥብ 65 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ሙሌት ተጠናቋል። በአሁኑ ወቅት የግድቡ የሲቪል ሥራዎች 99 ነጥብ 2 በመቶ እንዲሁም የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች አፈፃፀም 79 በመቶ መድረሱንም ነው  ሥራ አስኪያጁ የጠቆሙት። እንደ ኢንጂነር ክፍሌ ገለፃ የውሃ ማስተላለፊያና መቆጣጠሪያ የብረታብረት ሥራዎች አጠቃላይ አፈፃፀም 90 በመቶ ተከናውኗል። እስከ የካቲት 2016 ዓ.ም ድረስ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ የፋይናንስ ወጪ 191 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር የደረሰ ሲሆን ቀሪ የግድቡን የግንባታ ሥራዎች ለማጠናቀቅም 50 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል። የኮንትራት ማሻሻያ መደረጉ፣ የተጣበበ የፕሮጀክት ጊዜ ሰሌዳና በግንባታ ወቅት በግድቡ መሠረት ላይ ያጋጠመ ልል ድንጋይ መኖሩ እንዲሁም የልምድ ማነስ እና የጥራትና ልኬት በሚፈለገው ደረጃ አለመሆን በፕሮጀክቱ ግንባታ ላይ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እንደነበሩ ጠቅሰዋል። በግድቡ ግንባታ ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታትም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የቦርድ አመራር እስከ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ድረስ የመዋቅር ለውጥ ተደርጓል ያሉት ሥራ አስኪያጁ በዘርፉ ልምድ ያላቸውን ሥራ ተቋራጮች ከመቅጠር ጀምሮ በቂ የፋይናንስ አቅርቦት እንዲመቻች መደረጉንም ተናግረዋል። በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዓለም አቀፍ ህግ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጀኔራል አምባሳደር ረታ አለሙ እንደገለፁት የፕሮጀክቱን ግንባታ ከማፋጠን በተጓዳኝ ግድቡ የህልውና ጉዳይ መሆኑን የሚሳይ የዲፕሎማሲ ስራ እየተሰራ ነው። የህዳሴ ግድቡን ጨምሮ ድንበር ተሻጋሪ ወንዞች ላይ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ስራ በመስራት ሀገራዊ ጥቅማችንን ማስጠበቅ አለብን ሲሉም ተናግረዋል። የታላቁ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ፍቅርተ ታምር በበኩላቸው ፕሮጀክቱ  በመላው ህዝባችን ተሳትፎና በመንግስት ክትትልና ድጋፍ እየተገነባ ይገኛል ብለዋል። ባለፉት 13 ዓመታት ለፕሮጀክቱ ግንባታ ከመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከ19 ቢሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን የገለፁት ዳይሬክተሯ በአሁኑ ወቅትም እስከ 300 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱን ገልፀዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 24 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+7

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 13ኛ ዓመት ክብረ በዓልን የሚዘክር አውደ ርዕይ ተከፈተ ...///... የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመሰረት ድንጋይ የተጣለበትን 13ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ "በህብረት ችለናል" በሚል መሪ ቃል የፎቶ እና የስዕል አውደ ርዕይ በአዲስ አበባ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት በይፋ ተከፍቷል። አውደ ርዕዩን የከፈቱት የኢፌዴሪ ምክትል ጠ/ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ባለፉት 13 ዓመታት የተጓዘባቸውን ሂደቶች የሚያስቃኙ የተለያዩ ፎቶዎችና ስዕሎችን ተዟዙረው ተመልክተዋል። ምክትል ጠ/ሚኒስትር አቶ ተመስገን አውደ ርዕዩን በከፈቱበት ወቅት እንደተናገሩት ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብቷ የታደለች ሀገር ናት። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ ህዝቦቿን አስተባብራ በራሷ አቅም ማልማት የምትችል ሀገር መሆኗን ያሳየ ትልቅ ፕሮጀክት ነው ብለዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እንደ አድዋ በዓል ሁሉ ለአፍሪካውያን ወንድም እህቶቻችን ከድህነት አቅም ለመውጣት የሚደረግ ትልቅ የብልፅግና ድልን የምናስተምርበት ይሆናል ሲሉ ገልፀዋል። እንደ ምክትል ጠ/ሚኒስትሩ ገለፃ የግድቡን ግንባታ የማይፈልጉ ኃይሎች የተለያዩ ችግሮችን ለመፍጠር ቢሞክሩም በዲፕሎማሲው ዘርፍ በተሰሩ ሥራዎች አሸናፊ ሆነናል። በአሁኑ ወቅት የአባይ ወንዝ ከዘፈንና ውዳሴ ተላቆ ታዳሽ የኤሌክትሪክ ኃይል እያመረተ እንደሚገኝም ነው የተናገሩት። አውደ ርዕዩ ዛሬን ጨምሮ እስከ መጋቢት 29 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ለጎብኝዎች ክፍት መደረጉም ታውቋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የግድቡ ግንባታ ከየት ተነስቶ የት እንደደረሰ እንዲሁም በተማሪዎች፣ ዲፕሎማቶችና የአገር ውስጥና የውጭ ጋዜጠኞች እና ሌሎችም አካላት መጎበኘቱን የሚያሳዩ ስራዎች ለዕይታ ቀርበዋል። በወቅቱም የኢትዮ-ፖስታ አገልግሎት ድርጅት በታላቁ የኢትዮጵያ  ህዳሴ ግድብ ሥም ያዘጋጀውን ቴምብር አስመርቋል። በአውደ ርዕይው መክፈቻ የኢፌዲሪ ምክትል ጠ/ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህን ጨምሮ፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጅነር ሀብታሙ ኢተፋ፤ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የሐይማኖት አባቶች፣ አምባሳደሮች እና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 24 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

የዘርፉ የ2016 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም መገምገም ጀመረ ........///..... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የ2016 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸሙን በአርባ ምንጭ ከተማ  መገምገም ጀምሯል። በዘርፉ የቴክኒክ ድጋፍ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አበባው ያለው ግምገማው ሲጀመር እንደተናገሩት በአፈፃፀም ግምገማው ላይ የሁሉም ሪጅኖች የዕቅድ አፈጻጸም ጠንካራና ደካማ ጎኖች፣ የተገኙ መልካም ተሞክሮዎች እና ያጋጠሙ ችግሮች በዝርዝር ቀርበው ውይይት ይካሄዳበታል። ከዚህ በተጨማሪም እየተከናወኑ ስላሉ የተቋማዊ ሪፎርም ሥራዎች፣ ለሪጅኖች እየተደረገ ስላለው የቴክኒካል ድጋፍና በሳፕ አተገባበር ላይ ስለሚስተዋሉ ጠንካራ ጎኖችና እያጋጠሙ ስላሉ ተግዳሮቶች ውይይት እንደሚካሄድ ጠቁመዋል። በግምገማው ላይ የሚሳተፉት የሪጅኖቹ  የሥራ ኃላፊዎችና ተወካዮች በትላንትናው ዕለት የሶዶ ኮንቨርተር ጣቢያ፣ የወላይታ ሶዶ ቁጥር አንድ እና ሁለት የማከፋፈያ ጣቢያዎችን የሥራ እንቅስቃሴ የጎበኙ ሲሆን በነገው ዕለት ደግሞ በአርባ ምንጭ ከተማ በሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ጉብኝት ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 24 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ መልዕክት

በሪጅኑ የሚፈጸመው ተደጋጋሚ የታወር ስርቆት በኦፕሬሽን ሥራዎች ላይ ስጋት ደቅኗል ......//........ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሰሜን ሪጅን የሚፈጸመው ተደጋጋሚ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ስርቆት በኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች ላይ ፈተና እየሆነ መምጣቱን ሪጅኑ አስታወቀ። በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመር እና የኦፕቲካል ፋይበር (OPGW) ጥገና ክፍል ሥራ አስኪያጅ አቶ ህንፃ ኣረጋዊ እንደገለጹት በሪጅኑ በሁሉም አካባቢዎችበመሰረተ ልማቱ ላይ ስርቆት እየተፈፀመ ቢሆንም በደቡባዊ ምስራቅ ዞን እንደርታ፣ ዋጅራትና አዲጉዶም ወረዳዎች ይበዛል። ከመቀሌ ማከፋፊያ ጣቢያ ተነስቶ ወደ በርኸሌ ዳሎል በተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ጥምር መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ በተፈጸመ ስርቆት ብቻ 5 ምሰሶዎች መውደቃቸውን አቶ ህንፃ ገልጸዋል። የተሰረቀውን የታወር ብረት የሚረከባቸው አካል በአቅራቢያቸው ስለሚያገኙ እና በከተሞች ዙሪያ የሚደረገውን ቁጥጥር የላላ በመሆኑ ስርቆቱ በሌሎች አካባቢዎችም ተባብሶ መቀጠሉን ኃላፊው አብራርተዋል። ይህም ተቋሙን ለአላስፈላጊ ወጪና ለከፍተኛ የሥራ ጫና ከመዳረጉም ባለፈ በአገልግሎት ተደራሽነትና ጥራት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደረ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። ከጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር አጥፊዎቹን እጅ ከፍንጅ በመያዝ ጭምር ለሕግ እንዲቀርቡ ቢደረግም አስተማሪ እርምጃ ስለማይወሰድ ችግሩ የመባባስ አዝማሚያ ማሳየቱ ጠቁመዋል። ችግሩን ለመፍታት ለሁሉም ወረዳዎችና ዞኖች በተደጋጋሚ በደብዳቤ ቢያሳውቁም አጥጋቢ መልስ አለማግኘታቸውን የገለጹት አቶ ህንፃ በችግሩ ላይ ለመወያየት ለክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ጥያቄ ቀርቦ ምላሽ እየተጠበቀ መሆኑንም አስታውቀዋል። የታወር ስርቆትን መከላከል ለአንድ አካል ብቻ የሚተው አይደለም ያሉት ሥራ አስኪያጁ የክልሉ የፖለቲካ አመራር፣ የፀጥታና የፍትህ አካላት እና መላው ሕብረተሰቡ የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል ብለዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2015 ዓ.ም ብቻ በኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማት ሥርቆት ከ100 ሚሊየን ብር በላይ ኪሳራ እንዳጋጠመው መዘገባችን ይታወሳል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 21 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+7