EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 538 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 326,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 176 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 538 名订阅者。
根据 04 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 26,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.64%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.41% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 139 次浏览,首日通常累积 2 395 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 05 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 538
订阅者
-724 小时
-77 天
+2630 天
帖子存档
15 538
የኢትዮ - ኬንያ የኢነርጂ ሚኒስትሮች የሁለትዮሽ ውይይት ተካሄደ
.......///......
የኢትዮ - ኬንያ የኢነርጂ ሚኒስትሮች የሁለትዮሽ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።
የኢፌዲሪ የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ስለሺ በቀለ እና የኬንያ ኢነርጂና ነዳጅ ሚኒስትር ሚስተር ቻርለስ ኬተር ከልዑካን ቡድኖቻቸው ጋር በመሆን ውይይት አድርገዋል።
ሚኒስትሮቹ በውይይቱ ላይ እንደገለፁት ሁለቱ ሀገራት ለኃይል መሰረተ ልማት ዝርጋታ ግዙፍ መዋዕለ ንዋይ አፍሰዋል።
ከ አንድ ሺህ በላይ ኪሎ ሜትሮች የሚረዝመው የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር ሊያስተሳስር የሚችል ግዙፍ ፕሮጀክት በመሆኑ መጠናቀቁ ለሁለቱ ሀገራት ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ሚኒስትሮቹ ገልፀዋል።
በኢትዮጵያ በኩል የተዘረጋው የ412 ኪሎ ሜትር የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ መስመርና የዲሲ ኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ የሙከራና ፍተሻ ስራ የተከናወነ ሲሆን በኬንያ በኩል መዘርጋት ካለበት 633 ኪሎ ሜትር ውስጥ 30 ኪሎ ሜትር ብቻ መቅረቱ በውይይቱ ላይ ተጠቅሷል።
በመሆኑም ቀሪ ስራውን በቀጣይ አንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የኬንያ ኢነርጂና ነዳጅ ሚኒስትር ቻርለስ ኬተር አስታውቀዋል።
ዛሬ የተጀመረው የሁለትዮሽ ውይይት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ሲጠናቀቅ የሙከራ ስራ በሚጀመርበት ሁኔታ ላይ ለመምከርና ቀደም ሲል የተፈረመው የኃይል ሽያጭ ስምምነት ላይ ያልተጠናቀቁ ጉዳዮችን ለማጠናቀቅ ነው።
ስምምነቱንም በቀጣዮቹ ሁለት ሳምንታት ውስጥ እንዲያጠናቅቁ ሚኒስትሮቹ ለባለሙያዎች ቡድን አቅጣጫ ሰጥተዋል።
የሁለቱ ሀገራት የባለሙያዎች ቡድን ዝርዝር በሆኑ የስምምነትና የቴክኒክ ጉዳዮች ላይ ለቀጣዮ ሶስት ቀናት የሚመክሩ ይሆናል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 03 ቀን 2014
15 538
እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሰን! አደረሳችሁ!
አዲሱ ዓመት የሠላም፤ የጤናና የደስታ እንዲያደርግልን ምኞታችን የፀና ነው፡፡
15 538
የሃይማኖት አባቶች የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎበኙ
............/////...........
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባቶች የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎበኙ።
የሃይማኖት አባቶቹ አዲሱን ዓመት አስመልክቶ ቡራኬ ለመስጠትና በሁለተኛው ዙር የግድቡ የውሃ ሙሌት ላይ ስሜታቸውንና አጋርነታቸው ለመግለፅ ወደሥፍራው ጉብኝት አድርገዋል።
ጉብኝቱ በሠላም ሚኒስቴርና በሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አስተባባሪነት የተከናወነ ሲሆን የሃይማኖቶቹ የበላይ ጠባቂ አባቶችና ተወካዮቻቸውን ያሳተፈ ነበር።
በጉብኝቱ ወቅት የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ባደረጉት ማብራሪያ በቀጣዩ ጥቅምት ወር 2014 ዓ.ም ግድቡ ኃይል የማመንጨት ሂደቱን የሚጀምር መሆኑን ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጳጉሜ 04 ቀን 2013
15 538
የተቋም ሀብት ዕቅድ ስርዓት - ERP ሥርዓት በይፋ መተግበር ጀመረ
........./////......
በተቋሙ በተመረጡ አምስት ዘርፎች የተዘረጋው የተቋም ሀብት ዕቅድ ሥርዓት - ERP ሥርዓት የመጀመሪያው ምዕራፍ ተጠናቆ በይፋ መተግበር ጀመረ፡፡
የተዘረጋውን ሥርዓት የያስጀመሩት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ ተቋሙ ግዙፍ ሀብትን የሚያንቀሳቅስ ቢሆንም አሰራሮቹ በሲስተም ያልተደገፉ እና መረጃዎች ወረቀት ተኮር እንደነበሩ ገልፀዋል፡፡
ስለሆነም ተቋሙን ከቴክኖሎጂ ጋር በማስተሳሰር ወደተሻለ ደረጃ ማሸጋገር አስፈላጊ በመሆኑ የተቋም ሀብት ዕቅድ ሥርዓት (Enterprise resource planning) ትግበራ መጀመሩን ተናግረዋል፡፡
በጥቅምት ወር 2013 ዓ.ም ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በተደረገ ሥምምነት የተጀመረው የSAP_ERP ሲስተም ዝርጋታ የመጀመሪያው ምዕራፍ ተጠናቆ ሥራ መጀመሩን ያበሰሩት ዋና ሥራ አስፈጻሚው በሥራው ላይ የተሳተፉትን አመራሮችና ባለሙያዎችን አመስግነዋል።
በቀጣይም ተቋሙ ሌሎች ቴክኖሎጅዎችን ተግባራዊ በማድረግ ዛሬ ከተዘረጋው ሲስተም ጋር አስተሳስሮ ለመስራት ጥረት ይደረጋል ብለዋል፡፡
የተቋሙ የሞደርናዜሽን ቢሮ ዳይሬክተር አቶ ገነቱ ደሳለኝ በበኩላቸው ተቋሙ ከኢትዮጰያ አየር መንገድ እና ሳፕ (SAP) ከተባለ ዓለም አቀፍ ኩባንያ ጋር በመተባበር በሦስት ደረጃዎች የተቋም ሀብት ዕቅድ ሥርዓት ለመዘርጋት ሲሰራ መቆየቱን ጠቅሰዋል፡፡
የተቋም ሀብት ዕቅድ ሥርዓት (Enterprise resource planning) ተግባራዊ መደረጉ ተጠያቂነት ያለው ሥርዓትን ለመዘርጋት፣ በተቋሙ ያሉ የሥራ ክፍሎችን ለማስተሳሰር እና ወጥነት ያለው ሥራ ለማከናወን የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ሲስተሙን ለመዘርጋትና ለሥልጠና 143 ሚሊዮን ብር SAP የተባለውን ሲስተም ከነፍቃዱ ለመግዛት 1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ዩሮ ወጭ መደረጉን አቶ ገነቱ አስታውሰዋል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኮሜሪሻል ቺፍ ኦፊሰር አቶ ኢሳያስ ወ/ማርያም በበኩላቸው ሲስተሙ ዘመናዊ ከሚባሉት መካከል ቀዳሚው መሆኑን ጠቅሰው ድርጅታቸው ቀሪ ሥራዎችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጳጉሜ 02 ቀን 2013
15 538
የህልውና ዘመቻውን ለሚቀላቀሉ የተቋሙ ሠራተኞች ሽኝት ተደረገ
……..///………..
በሀገራችን እየተካሄደ የሚገኘውን የህልውና ዘመቻ ለሚቀላቀሉ ሁለተኛ ዙር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች ሽኝት ተደረገላቸው፡፡
በሽኝት ፕሮግራሙ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ በአሸባሪው የህወሓት ጁንታ ቡድን እየተሰነዘረ ያለውን ሀገር የማፍረስ አደጋ ለመቀልበስ ተቋሙን ወክለው ለሚዘምቱ ሠራተኞች ምስጋና አቅርበዋል፡፡
ሥራ አስፈጻሚው ሠራተኞች ዘመቻውን በፅናትና በአሸናፊነት ተወጥተው ወደ መደበኛ ሥራቸው እንደሚመለሱም እምነታቸውን ገልፀዋል፡፡
የዋና ሥራ አስፈጻሚ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በበኩላቸው ጀግኖች አባቶቻችን ከውጭ ወራሪ ጠብቀው ያቆዩዋትን ሀገር በመካድ ጥቃት እያደረሰ የሚገኘውን የህወሓት ከሃዲ ቡድን ለመደምሰስ ተቋሙ የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱን አንስተዋል፡፡
ከድጋፉ በተጨማሪ ዘመቻውን በአካል ተቀላቅሎ አሸባሪ ቡድኑን ለመፋለም ፍላጎት ላላቸው 6 የተቋሙ ሠራተኞች ሽኝት መደረጉን የተናገሩት አቶ ሙላት 3 ሠራተኞች ቀደም ብለው ዘመቻውን መቀላቀላቸውን ገልፀዋል፡፡
ሰራተኞቹ በተቋሙ የነበራቸውን ተሳትፎ በህልውና ዘመቻው በመድገም ተቋማቸውን እና ሀገራቸውን እንደሚያኮሩ እምነት አለኝ ብለዋል፡፡
ሽኝት የተደረገላቸው ሠራተኞች አሸባሪውን ቡድን ለመከላከልና ለመጨረሻ ጊዜ ለማጥፋት በሚደረገው ዘመቻ ለመሳተፍ ያነሱት ጥያቄ በተቋሙ ተቀባይነት አግኝቶ በክብር ሽኝት መደረጉ እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል፡፡
ዘማቾቹ ሀገር ከሁሉም በላይ መሆኗን በማንሳት ሥራም ሆነ ህይወት ሊቀጥሉ የሚችሉት ሀገር ሲኖርና ሰላም ሲሆን ብቻ ነው ብለዋል፡፡
በዘመቻው እነሱ ብቻ ሳይሆኑ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለሀገሩ ወታደር መሆኑን ተገንዝቦ ለሚደረግለት ማንኛውም ጥሪ መዘጋጀት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጳጉሜ 01 ቀን 2013
15 538
የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች የኢትዮጵያዊነት ቀንን አክብረዋል
………////………..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የስራ መሪዎችና ሠራተኞች የኢትዮጵያዊነት ቀንን በተቋሙ ዋና መሥሪያ ቤት ውስጥ አክብረዋል
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2013 ዓ.ም የጳጉሜ ቀናቶች በተለያዩ ስያሜዎች እንዲከበሩ በወሰነው መሰረት የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞችም የኢትዮጵያዊነት ቀን የሚል ስያሜ የተሠጠውን ጳጉሜ 1 ቀንን አክብረዋል፡፡
የኢትዮጵያን አንድነትና ሉአላዊነት ለማስጠበቅ ጀግኖች አባቶቻችን ደማቸውን ያፈሰሱላትንና አጥንታቸውን የከሰከሱላትን ኢትዮጵያን እንደሀገር ለማስቀጠል፤ ሉዓላዊነቷን ለማስከበርና ሰንደቅ ዓላማዋን ከፍ ለማድረግ በተለያየ መልኩ በቁርጠኝነት በመሰለፍ በኢትዮጵያዊነት መንፈስ መንቀሳቀስ እንደሚገባ መልዕክት ተላልፏል፡፡
ኢትዮጵያዊ ሁሉ በኢትዮጵያዊነቱ እንደሚኮራው ሁሉ ሀገርም ከእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ትልቅ ኃላፊነት ስለምትጠብቅ ሁሉም በተመደበበት የስራ መስክ ላይ በትጋትና በቅንነት በማገልገል ኃላፊነቱን በአግባቡ እንዲወጣም ጥሪ ቀርቧል፡፡
የ2013 ዓ.ም የጳጉሜ ቀናቶች የኢትዮጵያን ባህልና ትውፊት በሚያሳድጉ መልኩ በተለያዩ ስያሜዎች የሚከበሩ ሲሆን ቀናቶቹ ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ በአገር አቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያዊነትንና የተለያዩ የበጎ አድራጎት ሥራዎችን በሚያጠናክር መልኩ ሲከበሩ እንደነበር ይታወሳል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጳጉሜ 1 ቀን 2013 ዓ.ም
15 538
ከደብረታቦር እስከ ነፋስ መውጫ የሚገኘው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ
.......////.........
በአሸባሪው የህወኃት ቡድን ጥቃት የደረሰበት ከደብረታቦር እስከ ነፋስ መውጫ የሚገኘው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተጠግኖ ከትናንት ምሽት ጀምሮ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።
ከደብረታቦር ነፋስ መወወጫ ድረስ ባለው መስመር ላይ በተፈፀመ ጥቃት የኃይል ማስተላለፊያ ሽቦ(ኮንዳክተር) በተለያዩ 13 አካባቢዎች ላይ በመበጣጠሱ ኃይል ተቋርጦ ቆይቷል።
መስመሩን እንደአዲስ በመቀየርና እና መገናኘት የሚችሉትን የተለያዩ መገናኛዎችን በመጠቀም ለመጠገን ከፍተኛ ርብርብ ተደርጓል።
የደረሱትን ጉዳቶች በመጠገን በትናንትናው ዕለት ነሐሴ 28 ቀን 2013 ዓ.ም ከምሽት 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ንፋስ መውጫና ደብረታቦር ከተሞችና አካባቢያቸው ኃይል እንዲያገኙ ማድረግ ተችሏል፡፡
የንፋስ መውጫ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በሽብርተኛው ቡድን ዘረፋና የንብረት ማውደም ቢፈፀምበትም ዳግም በማደስ ለአገልግሎት ማብቃት ተችሏል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ነሐሴ 29 ቀን 2013 ዓ.ም
15 538
የተቋም ሀብት ዕቅድ ስርዓት - SAP-ERP System ትግበራ ተጠናቆ ማክሰኞ ጳጉሜ 2 ቀን 2013 ዓ.ም በይፋ ሥራ ይጀምራል፡፡ የ ERP -Enterprise resource planning መተግበር ወጪ ቆጣቢ በሆነ መልኩ ፈጣን ፣ትክክለኛና ቀልጣፋ የመረጃ፣ የማህደር፣ የፕሮጀክት አስተዳደር፣ የፋይናስ፣ የግዢ እና የንብረት አያያዝ እና አስተዳደር እንዲኖር በማድረግ በተቋሙ ያለውን የመረጃና የዶክመንት አያያዝ ችግር ይቀርፋል ተብሎ ይታመናል፡፡ የመጀመሪያው ምዕራፍ ተጠናቆ ለትግበራ ዝግጁ በመሆኑ የተቋማችን ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ የእንኳን ደስ አለን መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
15 538
ሙስናን የሚጠየፍ ትውልድ ለመቅረፅ ከቤተሠብ ጀምሮ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ ሰልጣኞች ገለፁ
……..///…….
ሙስናን የሚጠየፍ ሀገር ወዳድ ትውልድ ለመቅረፅ ከቤተሠብ ጀምሮ የትምህርት እና የሃይማኖት ተቋማት እንዲሁም ሌሎች ማህበራዊ ተቋማት በጋራ ሊሰሩ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮች ተናገሩ፡፡
በሥነ ምግባር እሴቶችና በሙስና መከላከል ላይ በማተኮር በተዘጋጀው ሥልጠና ላይ የተቋሙ የህግ አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር አቶ መርክነህ ይገዙ እንደገለፁት የሙስናና ብልሹ አሰራር አስተሳሰብና ተግባር በትምህርት ቤት እና በሃይማኖት ተቋማት ከተስፋፋ ሙስናን ለመከላከል እጅግ አዳጋች ስለሚያደርገው አስቀድሞ መከላከል ይገባል፡፡
በመንግስት ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች ላይ የተተገበረው የሀብት ምዝገባ ሥርዓት በግል ባለሀብቱም ላይ ሊተገበር ይገባል ብለዋል፡፡
የሰው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ አቶ አታላይ አበበ በበኩላቸው የሙስና ወንጀል በሚጣራበት ወቅት ሰነድ ላይ ከሚፈርሙ አካላት በተጨማሪ ከጀርባ ሆነው የሚያማክሩና ትዕዛዝ የሚሰጡ ከፍተኛ ባለስልጣናት የሚጠየቁበት የህግ ስርዓት ሊበጅ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡
የመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ ደግሞ ከዚህ ቀደም የሙስና ወንጀል የሚፈፅሙ ባለስልጣናት በፖለቲካዊ ውሳኔ ምክንያት ተገቢውን ቅጣት ባለማግኘታቸው ለሙስና መስፋፋት በር መክፈቱን ተናግረዋል፡፡
ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ የሰጡት የፌደራል የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ተስፋዬ ከፋለ በተቋሙ የሚስተዋሉ የአሰራር ግድፈቶችና የሙስና አዝማሚያዎችን ቀድሞ ለመከላከል ማስተማር፣ መምከር፣ ከዚያ ያለፈን ደግሞ በህግ አግባብ መጠየቅ ይገባል ብለዋል፡፡
አቶ ተስፋዬ እንደገለፁት በሙስና ወንጀል የማጣራት ሂደት ሰነድ ላይ የፈረሙ ብቻ ሳይሆን ከጀርባ ሆነው አሉታዊ ተፅእኖ የሚያሳድሩ ባለስልጣናት የሚጠየቁበት የህግ አግባብ ተቀምጧል፡፡
የተቋሙ ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ለሙስና ተጋላጭ የሆኑ የስራ ዘርፎችን በመለየት የተለየ ድጋፍ፣ ክትትልና ቁጥጥር ማድረግ ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡
ሥልጠናው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት የተዘጋጀ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ነሐሴ 28 ቀን 2013 ዓ.ም
15 538
ዋና ሥራ አስፈፃሚው ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳደድር ጋር ተወያዩ
……./////………..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳደድር አሻድሊ ሀሰን በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ትናንት ተወያዩ፡፡
ውይይቱ የግድቡ ውሃ ከሚተኛበት አካባቢ የተነሱ ሰዎችን መልሶ በማስፈር፣ በካሳ ክፍያ፣ መሰረተ ልማት ለማሟላት የተሰሩት ሥራዎች ያሉበትን ደረጃና በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተከናወነውን የምንጣሮ ሥራ በመገምገም ላይ ያተኮረ ነበር፡፡
እስካሁን በሂደቱ የተገኙ ልምዶችን በመቀመርና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በመለየት በቀጣይ የተሻለ አፈፃፀም እንዲኖር ለማድረግ በመስማማት አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡
በተጨማሪም ክልሉ ከዚህ ቀደም ባቀረበው የኤሌክትሪክ መሰረተልማት ጥያቄ ላይ ገለፃ ተደርጓል፡፡
ሁለቱም ወገኖች በቀጣይ በሚሰሩ ጉዳዮች ላይ በዕቅድ ማከናወን ያለባቸውን ተግባራት ለይተው በቅንጅት ለመስራት ተስማምተዋል፡፡
ውይይቱ ውጤታማ እንደነበርና በስምምነት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ገልፀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ነሐሴ 28 ቀን 2013 ዓ.ም
15 538
ሙስናን እና ሌብነትን በተደራጀ መልኩ መከላከል እንደሚገባ ተገለፀ
......///........
ሙስና የሀገርን ዕድገት በማቀጨጭ ህዝቦችን ለድህነት የሚዳርግ በመሆኑ በፅኑ መታገል እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ስራ አስፈፃሚ ተናገሩ።
ለተቋሙ አመራሮች በስነምግባር እሴቶች ላይ የተዘጋጀው ስልጠና በንግግር ሲከፍቱ የጽ/ቤቱ ሥራ አስፈፃሚ አቶ መርጋ ተረፈ እንደተናገሩት በአሁኑ ጊዜ በዓለም ላይ በዓመት ከአንድ ትሪሊዮን ዶላር በላይ በሙስና ይባክናል።
ይህንንም በጊዜ መከላከል ካልተቻለ በሀገር ላይ ከፍተኛ ቀውስ ያስከትላል ብለዋል፡፡
ሥራ አስፈፃሚው እንደገለፁት ሙስና የፍትህ ስርዓትን በማዛባት፣የፖለቲካ ስርዓትን በማበላሸት ሀገርን ለሁለንተናዊ አደጋ የሚያጋልጥ ካንሰር ነው፡፡
ሥልጠናውን የሰጡት የፌደራል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ተስፋዬ ከፋለ በበኩላቸው ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የተቋሙ አመራሮች አርአያ በመሆን ሊሰሩ ይገባል ብለዋል፡፡
የስካንዲቪያን አገሮች የሆኑት እንደ ስዊድን እና ኖርዌይ ዜጎችን በስነ ምግባር በማነፅ አመርቂ ውጤት ያስመዘገቡ መሆኑን የገለፁት አቶ ተስፋዬ የአፍሪካ ሀገራት ደግሞ ከአመራር ጀምሮ በሙስና ስር የሰደደ ችግር ያለባቸው ናቸው ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ባለፉት 25 ዓመታት በኢትዮጵያ የተደራጀ ሌብነትና ብልሹ አሰራር ተስፋፍቶ እንደነበርና ይህም ሔዶ ሔዶ ሀገራዊ ትርምስ መፍጠሩንና የመንግስት ለውጥ ማስከተሉን ከፍተኛ ባለሙያው እንደማሳያ አስታውሰዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ የሚፈስበት ተቋም እንደመሆኑ አደረጃጀቱን በማዘመንና የሙስና በሮችን በመዝጋት የተጣለበትን የህዝብ አደራ በአግባቡ ሊወጣ ይገባል ብለዋል፡፡
እንደ ተቋም የሚታይን ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለማክሰም አሳሪ የሆኑ መመሪያዎችን ማስተካከል፤ግልፅነትና ተጠያቂነት ያለበት አሰራር ስርዓት ማጎልበት ይገባልም ነው ያሉት፡፡
አቶ ተስፋዬ እንዳሉት የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ሀብታቸውን እንዲያስመዘገቡ ማድረግ አንዱ የሙስናና ብልሹ አሰራር መቆጣጠሪያ መንገድ ነው፡፡
በተቋሙ ለሙስና ተጋላጭ የሆኑ የስራ ክፍሎችን በመለየት በትኩረት በመደገፍና በመከታተል በግዥ ስርዓት፣ በቅጥር እና በአገልግሎት አሰጣጥ ከአድሎ የፀዳ፣ እኩልነትንና ፍትሐዊነትን ያማከለ አገልግሎት ሊሰጥ እንደሚገባ ከፍተኛ ባለሙያው አስገንዝበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ነሐሴ 27 ቀን 2013 ዓ.ም
15 538
ተቋሙ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ከ7 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አድርጓል
……….////……….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሰጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ ለማሳካት ከሚያከናውናቸው ስራዎች ጎን ለጎን በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በመሳተፍ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ላይ ይገኛል፡፡
ተቋሙ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ባጋጠሙ የተፈጥሮ አደጋዎች ችግር ለደረሰባቸው ወገኖች እንዲሁም መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች ከ7 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ተወጥቷል፡፡
በበጀት ዓመቱ በጣና ሀይቅ የተከሰተውን የእምቦጭ አረም ለመከላከል ሲሰራ ለነበረው የዘመቻ ስራ፣ በኦሞ እና በአዋሽ ወንዞች ሙላት ምክንያት ከቀያቸው ለተፈናቀሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ማቋቋሚያ እንዲሁም በተቋሙ የሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ አማካኝነት ለተመረጠ የህጻናት ማሳደጊያ ተቋም የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡
በኦሞ ወንዝ ሙላት ምክንያት የተነሳ አካባቢው በጎርፍ ሲጥለቀለቅ ለችግር ለተጋለጡት ወገኖች የገንዘብ ድጋፍ ከማድረግ ባለፈ ነዋሪዎቹ በጎርፍ እንዳይጎዱ ጀልባ በመከራየት የህይወት አድን ስራም አከናውኗል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም የታላቁ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ማስተባበሪያ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽ/ቤት በሀገሪቱ እያከናወነ ለነበረው የገቢ ማሰባሰቢያ የንቅናቄ ስራ የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ ተችሏል፡፡ ተቋሙ በአዲስ አበባ ከተማ እየተደረገ ላለው የቤት ዕድሳትና ምገባ ፕሮግራም ላይ የበኩሉን አስተዋፅኦ አድርጓል፡፡
በሀገሪቱ የሚከሰቱ የተለያዩ ማህበራዊ ችግሮችን ለመፍታት እና በልማት ስራዎች ላይ የራሱን ኃላፊነት ለመወጣት የሚያከናውነውን ስራ በተያዘው የ2014 በጀት ዓመት አጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል፡፡
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ማህበራዊ ኃላፊነትን ለመወጣት ሲከናወን የነበረው የድጋፍ ስራ ወጥነት ያልነበረው በመሆኑ በተያዘው የበጀት ዓመት ማህበራዊ ኃላፊነትን ለመወጣት የሚከናወኑ ስራዎችን ወጥነት ባለው መልኩ እንዲከናወኑ ለማድረግ የስፖንሰርሽፕ መመሪያ በመዘጋጀት ላይ ይገኛል፡፡
መመሪያው የሚመለከታቸው የስራ ክፍሎች አስተያየት ከሰጡበት በኋላ ለተቋሙ ከፍተኛ አመራር ቀርቦ ሲጸድቅ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል፡፡
በተጠናቀቀዉ የ2013 በጀት ዓመት ከገንዘብ ድጋፍ በተጨማሪ ሠራተኞችን በማስተባበር በጤና ተቋማት እየተስተዋለ ያለውን የደም እጥረት ለመቅረፍ የሚያግዝ የደም ልገሳ ፕሮግራም ተካሂዷል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ነሐሴ 25 ቀን 2013 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
