ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 560 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 357,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 160

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 560 名订阅者。

根据 25 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 32,过去 24 小时变化为 -5,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.03%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.88% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 052 次浏览,首日通常累积 2 472 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 26 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 560
订阅者
-524 小时
+167
+3230
帖子存档
photo content
+5

የኢትዮ-ኤሌክትሪክ የሴቶች ቡድን ሊጉን በድል ጀምሯል ........///........ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያው ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ድል ቀንቶታል። ቡድኑ ዛሬ ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም ከቂርቆስ ክ/ከተማ ጋር ባከናወነው ጨዋታ አምስት ለባዶ አሸንፏል። የኢትዮ-ኤሌክትሪክ እንስቶች ሙሉ የጨዋታ የበላይነት ባሳዩበት መርሃግብር  ማህሌት ምትኩ ለቡድኗ ሁለት ጎል ስታስቆጥር ቀሪዎቹን ሶስት ጎሎች ህዳት ካሱ፣ ዙፋን ደፈርሻ እና ሳባ ኃ/ሚካኤል ከመረብ አሳርፈዋል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ኳስን ተቆጣጥሮ በመጫወት እና ቶሎ ቶሎ ወደ ግብ በመድረስ ከተጋጣሚያቸው የላቀ እንቅስቃሴ ማድረግ ችሏል። ቂርቆስ ክፍለ ከተማ በአንፃሩ በመከላከል ላይ የተመሰረተ አጨዋወት ቢከተልም ከሽንፈት አልዳነም። የኢትዮ-ኤሌክትሪክ የአማካይ ተጫዋች ሀና ሲሳይ ኮከብ ተጫዋች በመሆን ተመርጣለች። በሁለተኛ ሳምንት የጨዋታ መርሃ ግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከሐዋሳ ከተማ በመጪው ቅዳሜ ጥቅምት 30 ቀን 2017 ዓ.ም የሚካሄድ ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

ጣቢያው የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎችን እየሰራ ነው .......//...... የመልካ ዋከና የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎችን እየሰራ መሆኑን አስታወቀ። የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ በቀለ እንደገለጹት ጣቢያው ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች ተከናውነዋል። በጣቢያው ዙሪያ በሚገኙ አምስት ቀበሌዎች ላይ የውሃ ጉድጓዶችን በማስቆፈር ማህበረሰቡን የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ከማድረግ ባሻገር የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ኢብሳ ጤና ጣቢያን ሰርቶ ማስረከቡን ገልጸዋል። በኃይል ማመንጫ ጣቢያው ዙሪያ የሚገኙ 12 ቀበሌዎችን ከ65 ሚሊዮን ብር በላይ በማውጣት የመብራት ተጠቃሚ መደረጋቸውን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ ቀሪ አካባቢዎችን ተጨማሪ 330 ሚሊዮን ብር በመመደብ የመብራት ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል። እንደ አቶ ቴዎድሮስ ገለፃ ሮቤ ጌርጀዳን ከጌዴዶ ከተማ የሚያገናኝ 10 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ ጣቢያው መስራቱንም ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅትም ከጣቢያው እስከ በቆጂ መገንጠያ ያለውን 26 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ እና ከጣቢያው እስከ አዳባ ያለውን 30 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ የጥገና ሥራ ለመስራት በሂደት ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል። በጣቢያው ግቢ የሠራተኞችና የአካባቢው ማህበረሰብ ልጆች የሚማሩባቸው ከኬጂ እስከ 8ኛ ክፍል የሚያስተምሩ ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን የተናገሩት አቶ ቴዎድሮስ 250 ለሚሆኑ የቅድመ መደበኛ የአካባቢው ተማሪዎችም የትራንስፖርት አገልግሎት እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል። የዋቤ ኢብሳ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር የሆኑት አማና ፈቶ እንደገለጹት ጣቢያው ውሃ፣ መብራት እና የትምህርት ቁሳቁስ ለትምህርት ቤቱ እያቀረበ ነው። ይህም ልጆቹ ርቀው ሳይሄዱ ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል። የአካባቢው አባገዳ የሆኑት ሐጂ እንድሪስ ሐጂ ጉራሪ በበኩላቸው ጣቢያው ለአካባቢው ማህበረሰብ ትምህርት ቤት፣ ጤና ጣቢያና መንገድ ከመስራት ባለፈ የውሃና የመብራት ተጠቃሚ እያደረገ ነው ብለዋል። በዚህም የአካባቢው ማህበረሰብ ርቆ ሳይሄድ ንጹህ የመጠጥ ውኃ እንዲያገኝ፣ ልጆቹን እንዲያስተምርና የሕክምና አገልግሎት እንዲያገኝ ማድረጉን ጠቁመዋል። የኃይል ማመንጫ ጣቢያው እያከናወነ ላለው የልማት ስራ ምስጋናቸውን ያቀረቡት አስተያየት ሰጪዎቹ በዚህም ማህበረሰቡ በጣቢያው ላይ ያለው የእኔነት ስሜት እያደገ እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል። በቀጣይም ከጣቢያው የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን የጣቢያውን ደህንነት ለመጠበቅ እንደሚሰሩ ተናግረዋል። የመልካ ዋከና ውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሥራ የጀመረው በ1980 ዓ.ም ሚያዚያ 15 ቀን ነው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

ቡድኑ የመጀመሪያ ጨዋታውን ነገ ያከናውናል .......///........ የ2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ጥቅምት 24 ቀን ቦሌ ክ/ከተማ ከአዳማ ከተማ ጋር በሚያደርጉት ጨዋታ ይጀመራል። የኢትዮ-ኤሌክትሪክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን ደግሞ ነገ ጥቅምት 25 ቀን 2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ጨዋታውን ከቂርቆስ ክፍለ ከተማ ጋር በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም የሚያከናውን ይሆናል። ቡድኑ በፕሪሚየር ሊጉ ብርቱ ተፎካካሪ ለመሆን እንዲረዳው ከአንድ ወር በላይ የጨዋታ ቅድመ ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቷል። በርካታ አዳዲስ ተጫዋቾችን ወደ ቡድኑ  ያካተተው ኢትዮ - ኤሌክትሪክ በዚህ የውድድር ዘመን የዋንጫ ተፎካካሪ ለመሆን እየሰራ ነው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 24 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

በድሬዳዋና አካባቢው ምሽት ተቋርጦ የነበረው ኃይል ተመልሷል ……///……… በድሬዳዋ ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ትናንት ምሽት አራት ሰዓት አካባቢ በተከሰተ የእሳት አደጋ ምክንያት የተቋረጠው ኃይል እኩለ ለሊት ላይ መመለሱን በኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የምስራቅ አንድ ሪጅን አስታወቀ፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ወርዲ መሀመድ እንደገለፁት በማከፋፈያ ጣቢያው ትራንስፎርመር ላይ የገጠመው ችግር ለድሬዳዋ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል መቋረጥ ምክንያት ሆኗል፡፡ በተፈጠረው እሳት የተነሳ በድሬዳዋ ከተማና አካባቢው ከምሽት 4:20 እስከ 7:00 ድረስ ኃይል ተቋርጦ መቆየቱን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። ከማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል ያገኝ የነበረው ድሬዳዋ ማከፋፈያ ጣቢያ እንዲሁም ሀረር እና ጅግጅጋ ከሁርሶ በቀጥታ ኃይል እንዲያገኙ በመደረጉ ከድሬዳዋ ናሽናል ሲሚንቶ በስተቀር በአካባቢው ኃይል ሙሉ በሙሉ መመለሱን አስታውቀዋል። የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ችግሩ እንዳይሰፋ ሁለት የእሳት ማጥፊያ ተሽከርካሪዎች በመመደቡ እና የአስተዳደሩ ከፍተኛ ኃላፊዎችም በቦታው በመገኘት ላደረጉት እገዛ ዳይሬክተሩ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የችግሩን መንስዔ ለማወቅ ከዋና መስሪያ ቤት ባለሙያዎች መላካቸውንም ጠቁመዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 24 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሁለተኛ ድሉን አስመዘገበ .......///..... በ6ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሜርሊግ ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ፡ ሐዋሳ ከተማን 2 ለ 1 በማሸነፍ ሁለተኛ ድሉን ማስመዝገብ ችሏል። ትናንት ምሽት አንድ ሰዓት በተከናወነው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ በ11ኛው ደቂቃ ዓሊ ሱለይማን ባስቆጠራት ጎል ሐዋሳ ከተማ ቀዳሚ መሆን ችሏል። የሐዋሳው በረከት ሳሙኤል በ43ኛው ደቂቃ በራሱ ግብ ላይ ባስቆጠራት ጎል አቻ መሆን የቻለው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ኢዮብ ገ/ማርያም በ89ኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ሁለተኛ ጎል ድል ተቀዳጅቷል። ተመጣጣኝ የጨዋታ ፉክክር በታየበት የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ በርካታ ግብ የሚሆኑ ኳሶች መክነዋል። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በፕሪሜርሊጉ አምስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 23 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

የሀገርን ሀብት መጠበቅ ለነገ የሚተው ጉዳይ አይደለም .........///......... የሀገርን ሀብት መጠበቅ ለነገ የሚተው ጉዳይ አለመሆኑን የምዕራብ አርሲ ዞን ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ገለፁ። ከምዕራብ አርሲ ዞን እና ከዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች እንዲሁም ከሻሸመኔ ከተማ አስተዳደር የተውጣጡ አመራሮች፣ የፀጥታ እና ደህንነት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎችን ለመከላከል በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ አዛዡ ኮማንደር ቶሎሳ መልካ እንደገለፁት ህብረሰቡን በማሳተፍ መሰረተ ልማቱን በባለቤትነት ስሜት እንዲጠብቅ ማድረግ ይገባል። በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የተጋረጠው የስርቆት ወንጀል ከዞኑ የፀጥታ አቅም በላይ እንዳልሆነ አዛዡ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከዞኑ የፀጥታ መዋቅር ጋር ተቀራርቦ በመስራት ችግሩን ለመፍታት መስራት እንደሚገባ ኮማንደር ቶሎሳ ጠቁመዋል። የፖሊስ አዛዡ እንደገለፁት ህብረተሰቡን በማስተባበር ወንጀልን ለመከላከል ከሚደረገው ጥረት በተጓዳኝ ዝርፊያ በሚፈፅሙ አካላት ላይ አስተማሪ ህጋዊ እርምጃ ይወሰዳል። በሻሸመኔ ከተማ የቢሻን ጉራቻ ክፍለ ከተማ አስተዳዳሪ አቶ አየለ ዲካሞ እንደተናገሩት የልማት አውታሮች ላይ ዝርፊያ የሚፈፅሙ አካላት በሀገር ኢኮኖሚ ላይ እንቅፋት እየፈጠሩ በመሆኑ ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ የሚያደርግ የተጠናከረ ርምጃ መውሰድ ይገባል። በኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የሚፈፀሙ ዝርፊያዎች በሀገር ዕድገት ላይ ያላቸውን አሉታዊ ተፅዕኖዎች ለህብረተሰቡ በማስገንዘብ ችግሩን መከላከል ይቻላል። የስርቆት ወንጀሉ ከተማና ገጠርን በኃይል አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት መፍጠሩን ከውይይቱ መገንዘባቸውን አቶ አየለ ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በመሰረተ ልማት ስርቆት ዙሪያ ወጥነት ያለው የመረጃ ልውውጥ ሥርዓት እንዲዘረጋና ተቀራርቦ የመስራት ባህልን እንዲያዳብርም ነው ያሳሰቡት። የሻላ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ተሾመ ደገፋ በበኩላቸው በወረዳው ባለፉት ዓመታት ለኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆት ተጋላጭ የሆኑ ቦታዎችን በመለየት ለህብረተሰቡ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል። በወረዳው በብረት ማቅለጥና ተያያዥ የጋራዥ ሥራዎች ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች ላይ ጥብቅ ክትትል በማድረግ ስርቆቱን መቀነስ መቻሉን ተናግረዋል። የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን ከስርቆት ለመታደግ ያለመ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ በወረዳው ስር ባሉ የመንግሥት መዋቅሮች እየተሰራ እንደሚገኝም ነው ኮማንደር ተሾመ ያብራሩት።       💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

ፕሮጀክቱ በግብዓት አቅርቦት ችግር ምክንያት እንዳይጓተት እየተሰራ ነው ........///......... የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የግብዓት አቅርቦቱ የተቀላጠፈ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፍያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ የግዥና ፋይናንስ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙሉቀን ዮሴፍ እንደተናገሩት ለፕሮጀክቱ አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶች ወቅቱን ጠብቀው እንዲሟሉ እየተደረገ ነው። የፕሮጀክቱ የግብዓት አቅርቦት እንዲፋጠን የሥራ ክፍሉ ለፕሮጀክቱ የሚያስፈልጉ ብረቶችን በጨረታ ገዝቶ አስቀድሞ ማስገባቱን ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም በግዥ ሥርዓቱ ላይ የሚያጋጥመውን መጓተት ለመቅረፍ እንዲሁም ጊዜንና ወጪን ለመቆጠብ በሳይቱ ላይ ጥራት ያለው ብሎኬት በራስ ኃይል መመረቱን ገልጸዋል። በዚህም ከ50 ሺ በላይ ብሎኬት በማምረት ከሦስት ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማዳን ተችሏል ብለዋል፡፡ እንደ አቶ ሙሉቀን ገለፃ በራስ አቅም ከሚከናወነው ሥራ በተጓዳኝ ከመከላክያ ግንባታ ግብዓቶች ማምረቻ ድርጅት ጋር ስምምነት በመፈጸም የኮንክሪት ሙሌት ሥራ በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን አብራርተዋል። ይህም በራስ ኃይል መምሪያ በኩል እየመጣ ያለውን የአሰራር ለውጥ ብቻ ሳይሆን የሥራ ውጤትንም ያሳየ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ሥራ አስኪያጁ እንደሚሉት ለፕሮጀክቱ አስፈላጊ ግብዓቶችን በወቅቱ ለማቅረብ የሚያስችሉ ሥራዎች ቀድመው በመከናወናቸው እና ሳይት ላይ በመድረሳቸው የፕሮጀክቱ አፈጻጸም የተሻለ እንዲሆን አድርጎታል፡፡ ለግንባታ ሥራው የሚቀርቡ ግብዓቶች በጥራት ተቆጣጣሪ ሱፐርቫይዘሮች በአግባቡ ክትትል እንደሚደረግባቸውም አስረድተዋል፡፡ በግብዓት አቅርቦት ችግር ምክንያት የሚጓተት የፕሮጀክት ሥራ መኖር የለበትም በሚል ሲሰራ መቆየቱን ያወሱት አቶ ሙሉቀን በቀጣይ የግብዓት አቅርቦቱ እንደተሳለጠ እንዲቀጥል የግብዓት ፍላጎት ዕቅድ ከ15 ቀን በፊት እንዲቀርብ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ከፕሮጀክቱ ማጠናቀቂያ ሥራዎች ጋር በተያያዘ ከወር በኋላ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ግዢ ለመፈፀም በጨረታ ሂደት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

የዞኑ አስተዳዳሪ በየደረጃው የሚገኙ የመንግስት መዋቅሮች የመሰረተ ልማት ስርቆትን ለማስቀረት ተገቢውን የህግ ማስከበር ሥራ እንዲሰሩ አሳሰቡ .........///…….. በኦሮሚያ ክልል የምዕራብ አርሲ ዞን  ዋና አስተዳዳሪ የመሰረተ ልማት ስርቆትን ለማስቀረት በሚደረገው እንቅስቃሴ ላይ በየደረጃው የሚገኙ የመንግስት መዋቅሮች ተገቢውን የህግ እርምጃ  የማስወሰድ ሥራዎች እንዲሰሩ አሳሰቡ። ዋና አስተዳዳሪው አቶ አህመድ ሀጂ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከምዕራብ አርሲ ዞን እና ከተለያዩ ወረዳዎች የተውጣጡ አመራሮች፣ የፀጥታ እና ደህንነት የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ከሻሸመኔ ከተማ አስተዳደር አመራሮች ጋር በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ ስለሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎችና ተያያዥ ጉዳዮች ውይይት አድርገዋል፡፡ በውይይቱ ላይ በተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደገለፁት ተቋሙ ለህብረተሰቡ ኤሌክትሪክ ለማዳረስ በሚያደረገው ጥረት ውስጥ በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ እየተፈፀሙ ያሉ  የስርቆት ወንጀሎች ፈተና ሆነዋል። ተቋሙ በ2016 በጀት ዓመት በስርቆትና የተሰረቁ የኃይል መሰረተ ልማቶችን መልሶ ለመገንባት ከአንድ ቢሊየን ብር በላይ ወጪ ማውጣቱን የጠቀሱት ዳይሬክተሩ ከዚህ ውስጥ በኦሮሚያ ክልል ብቻ 450 ሚሊየን ብር ጉዳት እንደደረሰበት ተናግረዋል። እንደ አቶ ሞገስ ገለፃ ተቋሙ ባለፉት ሦስት ዓመታት በምዕራብ አርሲ ዞን በኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ በተፈፀመ ስርቆትና ጉዳት የደረሰባቸውን የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች መልሶ ለመገንባት ከ18 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ አውጥቷል። በዞኑ የተፈፀሙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት የስርቆት ወንጀሎች ያደረሱት ጉዳት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ በሲዳማ፣ ቤኒሻንጉል  ጉሙዝ፣ ሶማሌ እና ሐረሪ ክልሎች ከተፈፀመው ድምር ጉዳት ከፍ ያለ መሆኑንም ነው አቶ ሞገስ የገለፁት። በኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የወንጀል ድርጊት በሚፈፅሙ አካላት ላይ የፍትህና ፀጥታ ዘርፎች የሚያከናውኗቸው የምርመራና አስተማሪ ውሳኔ የመስጠት ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም ነው ያስገነዘቡት። የደቡብ አንድ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ  ጣቢያዎች መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ንጉሴ እንደገለፁት ባለፉት 3 ዓመታት በምዕራብ አርሲ ዞንና በሻሸመኔ ከተማ አስተዳደር ዙሪያ 11 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ወድቀዋል። በዞኑና በከተማ አስተዳደሩ በሚፈፀሙ ተደጋጋሚ የስርቆት ወንጀሎች ሳቢያ  ህብረተሰቡ ኃይል ተቋርጦ እንዳይቆይበት ለማድረግ የወደቀውን ምሰሶ በእንጨት ምሰሶ በመተካት ጊዚያዊ መፍትሔ ለመስጠት እየተሞከረ እንደሚገኝ ነው አቶ ምትኩ የጠቀሱት። እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ባለፉት ዓመታት ከዞን፣ ከወረዳና ከከተማ አስተዳደር የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆት ላይ ተሳትፎ የነበራቸውን ተጠርጣሪዎች ለህግ የማቅረብ ሥራ ተሰርቷል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ክትትልና ቁጥጥር ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንዳስታወቁት በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ እየተፈፀሙ የሚገኙ የስርቆት ወንጀሎች የኃይል መቆራረጥና የአገልግሎት ጥራት ችግር እንዲከሰት ምክንያት ሆነዋል። በዞንና በወረዳዎች የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማደራጀት መሰረተልማቶቹን የመጠበቅ፣ ዛፎችን የማስመንጠር እና ስርቆትን የመከላከል ሥራዎችን ለመስራት መታቀዱንም ነው የገለፁት። የፀጥታ እና የፍትህ አካላት በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ የስርቆት ወንጀል በሚፈፅሙ ህገ- ወጦች ላይ የማያዳግም እርምጃ እንዲወስዱም ነው አቶ ዋለ ያሳሰቡት። የምዕራብ አርሲ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ ሐጂ እንደተናገሩት በዞኑ በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ በተፈፀሙ  የስርቆት ወንጀሎች የደረሰው ጉዳት የችግሩን ጥልቀት ያሳያል። በዞኑ በህዝብ ጥቅም ላይ ጉዳት በሚያደርሱ አካላት ላይ በየደረጃው የሚገኙ የመንግስት መዋቅሮች ተገቢውን የህግ እርምጃ  የማስወሰድ ሥራዎች እንዲሰሩ አሳስበዋል። የሻሸመኔ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አዳነ ተ/ጊዮርጊስ በበኩላቸው በኃይል አቅርቦትና ተደራሽነትን ለማሳደግ ለሚሰራው  ሥራ የአመራሩ ሚና የጎላ ሊሆን ይገባል። በመሰረተ ልማቶቹ ላይ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎችን ከምንጩ ለማድረቅ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ የምዕራብ አርሲ ዞን እና የሻሸመኔ ከተማ አስተዳደር በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባም ነው ከንቲባው ያሳሰቡት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

photo content
+9

የፈተና ውጤት ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ መጋቢት 11 ቀን 2016 ዓ.ም በሲቪል መሀንዲስ 1ኛ የስራ መደብ በቋሚነት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ
+1
የፈተና ውጤት ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ መጋቢት 11 ቀን 2016 ዓ.ም በሲቪል መሀንዲስ 1ኛ የስራ መደብ በቋሚነት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል ከተ.ቁ 1 እስከ 11 ያላችሁ በተሰጠው የጽሁፍ ፈተና አብላጫ ውጤት ያመጣችሁ በመሆኑ ከጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ በዋናው መ/ቤት ኮተቤ ብረታብረት በሚገኘው የሰራተኛ ምደባ ቢሮ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ.ም