EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 544 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 357,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 176 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 544 名订阅者。
根据 01 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 22,过去 24 小时变化为 4,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.24%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.50% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 921 次浏览,首日通常累积 2 563 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 02 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 544
订阅者
+424 小时
-357 天
+2230 天
帖子存档
15 544
ተቋሙ የማስተላለፊያ መስመርና የማከፋፈያ ጣቢያ ኦፕሬሽን ሪጅኖችን ቁጥር ወደ 13 አሳደገ
……..///…….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል አደረጃጀት በመዘርጋት የማስተላለፊያ መስመርና የማከፋፈያ ጣቢያ ኦፕሬሽን ሪጅኖችን ቁጥር ከዘጠኝ ወደ 13 አሳደገ፡፡
በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ አቶ ዳዊት ገ/እግዝአብሔር እንደገለፁት ግሪዱ እየሰፋና የማስተላለፊያ መስመሮች የሚሸፍኑት ርቀት እየጨመረ በመምጣቱ ለአስተዳደርና ቁጥጥር የሚመች አዲስ አደረጃጀት ተፈጥሯል፡፡
በሪጅኖች ያሉ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚሸከሙት ሜጋ ዋት ኃይል፣ የሚሸፍኑት ኪሎ ሜትርና ተጋላጭነትን (senesetivity) እንደ መስፈርት በመውሰድ አዲሱ አደረጃጀት መፈጠሩን ተወካዩ ገልፀዋል፡፡
አዲሱ አደረጃጀትም መደበኛ የጥገና ሥራዎችንና ችግሮች ሲከሰቱ በቅርበት ሆኖ አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ዘላቂና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አቅርቦትን ተደራሽ ለማድረግ ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው አብራርተዋል፡፡
ቀደም ሲል ከነበሩት ከዘጠኙ ሪጅኖች መካከል አዲስ አበባና ማዕከላዊ ሪጅን እንደገና ተዋቅረው ማዕከላዊ ሪጅን 1፣ ማዕከላዊ ሪጅን 2 እና ማዕከላዊ ሪጅን 3 በሚል ተደራጅተዋል፡፡
ንዑስ ሪጅን የነበሩትም ወደ ሪጅን በማደግ በአዲስ ስያሜ መዋቀራቸው ተገልጿል፡፡
የምስራቅ ሪጅን እና በሥሩ የነበረው የጅግጅጋ ንዑስ ሪጅን ምስራቅ ሪጅን 1 እና ምስራቅ ሪጅን 2 ሪጅን ተብለው ሲዋቀሩ የሰሜን ምስራቅ ሪጅን እና በሥሩ የነበረው የሰመራ ንዑስ ሪጅን ደግሞ ሰሜን ምስራቅ ሪጅን 1 እና ሰሜን ምስራቅ ሪጅን 2 በሚል ስያሜ ተዋቅረዋል፡፡
የደቡብ ሪጅን እና በሥሩ የነበረው የወላይታ ሶዶ ንዑስ ሪጅን ደግሞ ደቡብ ሪጅን 1 እና ደቡብ ሪጅን 2 በሚል ስያሜ እንደገና እንደተዋቀሩ ተብራርቷል፡፡
በአዲስ የተዋቀሩት ሪጅኖች በነበራቸው የሰው ኃይል ሥራቸውን እያከናወኑ ሲሆን ክፍተት ካጋጠመም እንደ አስፈላጊነቱ በዕድገትና ዝውውር እንዲሁም በአዲስ ቅጥር የሚሟላ ይሆናል ተብሏል፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 03 ቀን 2015 ዓ.ም
15 544
ክፍት የስራ መደብ ማስታወቂያ
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከታች በተገለፀው ክፍት የስራ መደብ ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ በኮንትራት መቅጠር በማስፈለጉ መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት አምስት /5/ ተከታታይ የስራ ቀናት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
1. የስራ መደብ ፡- ጂኦሎጂስት 1ኛ
የትምህርት ደረጃ እና የስራ ልምድ ፡- ከታወቀ ዩንቨርሲቲ/ኮሌጅ/ በጂኦሎጂ እና ተዛማጅነት ባለው የትምህርት መስክ የመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቀ/ች፤የስራ ልምድ አይጠይቅም፡፡
የስራ ደረጃ ፡- ዲ1
ደመወዝ ፡- 8,417.00 (ስምንት ሺ አራት መቶ አስራ ሰባት ብር)
ብዛት ፡- ሶስት (3)
የቅጥር ሁኔታ ፡- በኮንትራት
የስራ ቦታ፡- ኮይሻ ውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሳይት
ጥቅማጥቅም፡ ፕሮጀክት ሳይት ለስራ በሚቆዩበት ጊዜ የውሎ አበል እና መኖሪያ ቤት የሚሰጥ ይሆናል፡፡
ማሳሰቢያ
የመመዝገቢያ ቦታ፡- ሜክሲኮ፣ ኬኬር ህንፃ፤ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መ/ቤት በአካል በመቅረብ ዋናው በር ላይ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ የማይመለስ የትምህርት እና የስራ ልምድ ማስረጃ ኮፒ ማስገባት ይችላሉ፡፡
ትምህርት ያጠናቀቁበት ዓ.ም፡- የሚወዳደሩ አመልካቾች ትምህርታቸውን በ2012 ዓ.ም እና ከዚያ ወዲህ ያጠናቀቁ መሆን አለባቸው፡፡
15 544
ተቋሙ ለጥናትና ምርምር በለያቸው ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሠራተኞች እንዲሳተፉ ጥሪ ቀረበ
……..///……..
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚያጋጥሙ ችግሮችን በጥናት ላይ ተመስርቶ ለመፍታት የፈጠራ ሀሳብ እና ጥናት የማድረግ ችሎታ ያላቸውና የተቋሙ ሠራተኞች እንዲሳተፉ ጥሪ ቀረበ፡፡
በተቋሙ የምርምርና ሥርፀት ዳይሬክተር አቶ ሚራጅ ፈረጃ እንደገለፁት ተቋሙ በተለያዩ ዘርፎች የሚያጋጥሙትን ችግሮች በጥናት ላይ ተመስርቶ ብቃት ባላቸው የተቋሙ ባለሞያዎች ለማካሄድ ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል፡፡
ቀደም ሲል የጥናት ሂደቱን የሚከታተሉ ኮሚቴዎችን አዋቅሮ ወደ ሥራ በመግባት በታዳሽ የኃይል ምንጮች፣ በኢነርጂ ውጤታማነት እና የኃይል ጥራት፣ በኢነርጂ ሀብቶች ስርጭት፣ በፕሮጀክት አስተዳደር እና በሌሎች ዘርፎች ላይ 58 የሚሆኑ የጥናት መስኮች መለየታቸውን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡
ከተሰበሰቡት የጥናት መስኮች መካከል አንገብጋቢ የሆኑና አፋጣኝ ምላሽ ያሻቸዋል የተባሉ አምስት ጉዳዮችን በመለየት ወደ ጥናት ለመግባት እንቅስቃሴ መጀመሩን የገለፁት ዳይሬክተሩ የቀሩትና ተጨማሪ የጥናት መስኮች እንደ አስፈላጊነታቸው እየተለዩ ጥናት እንደሚካሄድባቸው ተናግረዋል፡፡
ችሎታው ያላቸው የተቋሙ ሠራተኞች በተለዩት የጥናት መስኮችና ድርጅቱን ሊያሳድግና የፋይናንስ አቅሙንም ሊያሻሽል ይችላል ባሉት ማንኛውም የቢዝነስ ሀሳብ ላይ እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በተቋሙ የሚስተዋሉ ችግሮችን በጥናት ታግዞ በዘላቂነት ለመፍታት በሥራ ክፍሎች፣ በተቋሙ ባለሙያ፣ በዘርፉ የጥናትና ምርምር ልምድ ካላቸው ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመሆን ለመሥራት መታቀዱን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡
እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ ከአዲስ አበባ፣ ከባህርዳርና ከጅማ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በትብብር ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት የተደረገ ሲሆን ስምምነቱ ከጥናቶች በተጨማሪ የማማከር ሥራዎችን፣ የልምድ ልውውጦችን እና ሥልጠናዎችን የሚያካትት ነው ብለዋል፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 02 ቀን 2015 ዓ.ም
15 544
ለገና በዓል እስከ 3 ሺህ አምስት መቶ ሜጋ ዋት ኃይል ለማቅረብ ዝግጅት ተጠናቋል
……..///……..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለገና በዓል በቂ ኃይል ለማቅረብ ዝግጅት ማጠናቀቁን የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ዳይሬክተር አስታወቁ፡፡
ዳይሩክተሩ አቶ የማነ ኢሳያስ እንደገለፁት ተቋሙ በዋናነት ኃይል አመንጭቶ የሚያቀርብ እንደመሆኑ መጠን ለገና በዓል የኃይል አቅርቦት ችግር እንዳያጋጥም አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል፡፡
የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ሁሉም ዩኒቶች ፍተሻ ተደርጎላቸው ዝግጁ የተደረጉ ሲሆን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎችም ፍተሻ መጠናቀቁን ገልፃዋል፡፡
ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እና ከኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያ ኦፕሬሽን ዘርፍ ሁሉም ሪጅኖች ጋር ውይይት መደረጉን የተናገሩት ዳይሬክተሩ ከኃይል መሰረተልማቶች ጋር የሚያጋጥም ችግር ቢኖር በአስቸኳይ ለመጠገን የሚያስችል የባለሙያዎች ቡድን በየደረጃው ተዋቅሯል ብለዋል፡፡
ዳይሬክተሩ እንደገለፁት ላለፉት ሁለት ዓመታት ኃይል ተቋርጦባቸው የነበሩት አካባቢዎች ዳግም ኃይል ኃይል እንዲያገኙ በመደረጉ ባለፉት ሳምንታት የኃይል ፍላጎት እያደገ የመጣ ቢሆንም ፍላጎቱን ለማሟላት የሚያስችል ዝግጅት ተጠናቋል፡፡
አምና በተመሳሳይ ወቅት የሰሜን ሪጅንና ሌሎች ኃይል የተቋረጠባቸውን አካባቢዎች ሳይጨምር የኃይል አጠቃቀሙ 2ሺህ አምስት መቶ ሜጋ ዋት ብቻ ነበር፡፡
ዘንድሮ ግን በዓሉ ሳይደርስም የኃይል አጠቃቀሙ 3 ሺህ ሃምሳ አምስት ሜጋ ዋት በመድረስ በተቋሙ የኃይል አቅርቦት ታሪክ ሪከርድ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡
በመሆኑም ለገና በዓል እስከ 3 ሺህ 5 መቶ ሜጋ ዋት የሚደርስ ኃይል ዝግጁ ተደርጓል፡፡
እንደ አቶ የማነ ገለፃ ኃይል ተቋርጦ የቆየባቸው አካባቢዎች ዳግም ኃይል እንዲያገኙ መደረጉና የገና በዓል የኃይል አጠቃቀም ከሌሎች በዓላት ከፍ የማለት አዝማሚያ ስለሚያሳይ የኃይል መዋዠቅ እንዳያጋጥም ከኤክስፖርት ኢንዱስትሪዎች በስተቀር ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች በበዓሉ ዋዜማና በበዓሉ ዕለት ኃይል እንዳይጠቀሙ አሳስበዋል፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 28 ቀን 2015 ዓ.ም
15 544
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
15 544
ባለፉት ስድስት ወራት የተቋሙ ክሊኒክ ከ4 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ሠራተኞች አገልግሎት ሰጥቷል
……..///…….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት 6 ወራት ከ4 ሺህ ለሚበልጡ ሠራተኞች የህክምና አገልግሎት መስጠቱን በተቋሙ የሰው ሀብት አስተዳደር መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ተማም አፍደል እንደገለፁት ተቋሙ የህክምና አገልግሎቱን በራሱ ክሊኒክ መስጠት ከጀመረ ከሐምሌ 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ለህክምና አገልግሎት ከመጡ 4 ሺህ 32 ሠራተኞች ውስጥ በክሊኒኩ አቅም 1 ሺህ 383 ሠራተኞች የህክምና አገልግሎት አግኝተዋል፡፡
ሁለት ሺህ 649 ታካሚ ሠራተኞች ደግሞ እንደሚፈልጉት የህክምና ዓይነት ወደተለያዩ የህክምና ተቋማት ለተጨማሪ ህክምና መላካቸውን አስታውቀዋል፡፡
በሥራ ላይ ጉዳት ደርሶባቸው የመጡ 32 ሠራተኞችም ውል ወደተያዘባቸው ህክምና ተቋማት ተልከው ተስተናገዳዋል ብለዋል፡፡
በተቋሙ መድሃኒት ቤት 2 ሺህ 5 መቶ ሠራተኞች መስተናገዳቸውንና 2 ሺህ ስድስት ሠራተኞች ደግሞ የጠየቁት መድሃኒት በተቋሙ መድሃኒት ቤት ባለመገኘቱ ወደ ከነማ ፋርማሲዎች ተልከው አገልግሎት ማግኘታቸውን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡
እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ 447 ሠራተኞች በመርፌ ክፍል እንዲሁም 81 ሠራተኞች ደግሞ ቀላል አደጋ ደርሶባቸው በድንገተኛ ክፍል አገልግሎቱን አግኝተዋል፡፡
በክሊኒኩ ላቦራቶሪ 944 ሴት እና 1 ሺህ 922 ወንድ ታካሚዎች አገልግሎት ማግኘታቸውን አቶ ተማም አስታውቀዋል፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 27 ቀን 2015 ዓ.ም
15 544
ተቋሙ የገቢ አማራጮችን በማስፋትና ወጪ በመቀነስ በኩል ውጤታማ ሥራዎችን እያከናወነ ነው
..........///……...
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የገቢ አማራጮችን በማስፋትና ወጪ በመቀነስ በኩል ውጤታማ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ በተቋሙ የፋይናንስ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ።
ሥራ አስፈፃሚው አቶ ደመረ አሰፋ እንደገለፁት የተቋሙ ገቢ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣው የገበያ አማራጮችን እያሰፋ በመምጣቱ ነው።
ለጎረቤት ሀገራት እያቀረበ ያለውን የኃይል ሽያጭ በማሳደግ የተቋሙን ገቢ ከፍ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት ሥራ አስፈፃሚው ከሱዳን እና ጅቡቲ በተጨማሪ በቅርቡ ከኬንያ ጋር የተጀመረው የኃይል ሽያጭ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የኃይል ሽያጭ ለተቋሙ ዋነኛ ገቢ ከመሆኑም ባሻገር ለሀገሪቱም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት በኩል ፋይዳው የጎላ እንደሆነም ነው የገለፁት።
ተቋሙ ለሌሎች የጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ዕቅድ ነድፎ በመንቀሳቀስ ላይ እንደሚገኝም ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል።
ለሀገር ውስጥ ከፍተኛ የኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች አስተማማኝ የሆነ የኤሌክትሪክ ለማቅረብ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ከኃይል ሽያጭ በተጨማሪ ከኢትዮ - ቴሌኮም እና ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ጋር ተቋሙ ባለው የሊዝ ስምምነት ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ ማቀዱንም ገልፀዋል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሁለት ዩኒቶች ወደ ሥራ መግባት በተቋሙ የገቢ አሰባሰብ ሂደት ላይ አወንታዊ ሚና ይጫወታል ያሉት አቶ ደመረ የመነጨውን ኃይል ወደ ተጠቃሚ ደንበኞች ለማድረስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመሮች አቅምን ማሳደግ ቀዳሚ ተግባር ሊሆን እንደሚገባም ተናግረዋል።
የተቋሙ ገቢ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ በመምጣቱ ምክንያት በርካታ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክቶችን በራስ የፋይናንስ አቅም መገንባት እንደጀመረ ገልፀዋል።
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 26 ቀን 2015 ዓ.ም
15 544
ተቋሙ የሚሰጠው የማማከር አገልግሎት መልካም ስሙን እያሳደገ ነው
………///……..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግ ዘርፍ የሚሰጠው የምህንድስና የማማከር አገልግሎት የተቋሙን ገፅታ እየገነባ መምጣቱን የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ፡፡
ሥራ አስፈፃሚው አቶ ውድነህ የማነ እንደገለፁት የማማከር አገልግሎቱ ተቋሙ የሚያከናውነውን ተግባር ደንበኞች እንዲረዱ ያደረገ፣ የመፈፀም ብቃቱን ያሳየ፣ በእውቀት የሚሰራ እና ከፍተኛ አቅም ያዳበረ መሆኑን ያሳየ ነው፡፡
ለዚህም ዘርፉ በሥራው ላይ ያሳየነው ጥራትና ፍጥነት፣ የሚያዘጋጀው የፍላጎት መግለጫ ሰነድ (Employer Requirement) ጥልቀት፤ የፕሮጀክት ክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የኮንትራት አስተዳደር ሥራዎች ተጠቃሾች መሆናቸውን አንስተዋል።
የማማከር አገልግሎት ያገኙ የሥራ ባለቤቶችም በተለያየ አጋጣሚ አድናቆታቸውንና ምስጋናቸውን ማቅረባቸው ለተቋሙ መልካም ስም ማደግ ማሳያ እንደሆኑ ሥራ አስፈጻሚው ገልፀዋል ።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግ ዘርፍ ከተለያዩ የመንግስትና የግል ተቋማት ጋር ባለው የማማከር ግንኙነት መልካም የስራ ግንኙነት ከመፍጠር ባለፈ በዘርፉ ያለውን እውቀት እና የዳበረ አቅም በተግባር ለማሳየት እንዳስቻለው አቶ ውድነህ ተናግረዋል፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 25 ቀን 2015 ዓ.ም
15 544
በኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መስመር ላይ የሚስተዋለውን የኃይል ብክነት እና ጥራት ለማሻሻል እየተሰራ ነው
..........///……....
በኢትዮ - ጅቡቲ የባቡር መስመር ላይ የሚስተዋለውን የኃይል ብክነት እና ጥራት ለማሻሻል እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል የኢነርጂ አካውንቲንግና ኳሊቲ አሹራንስ ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ሚኪያስ ወንድሙ እንደገለፁት ከዚህ ቀደም በባቡር መስመሩ ላይ ያጋጥም የነበረውን የኃይል መቆራረጥ እና ብክነት ለመቀነስ የተለያዩ ሥራዎች ተሰርተዋል።
በትራክሽን ጣቢያዎች ላይ በሚከሰት ጤናማ ያልሆነ የኃይል ሥርጭት ለኃይል ብክነቱ መከሰት አስተዋጽኦ አድርጓል ያሉት ሥራ አስኪያጁ ችግሩን ለመቅረፍም ስታትኮም እና ኤስ ቪ ሲ የሚባሉ መሣሪያዎችን በመጠቀም ለመከላከል መታቀዱንም ተናግረዋል።
በኢትዮ - ጅቡቲ ምድር ባቡር መስመር ላይ የኤሌክትሪክ ፍሰቱ እንዳይረበሽ ለማድረግ በአንዳንድ ጣቢያዎች ላይ የመከላከያ መሣሪያዎቹ ቢቀመጡም በቂ እንዳልሆኑ ነው አቶ ሚኪያስ ያስረዱት፡፡
በምስራቅ ሪጅን የሚገኙ አንዳንድ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ከኃይል ማመንጫ የራቁ በመሆናቸው ሳቢያ የቮልቴጅ መዋዠቅ ችግር እንደሚያጋጥማቸው ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል።
እንደ አቶ ሚኪያስ ገለፃ የኃይል ጭነት በሌለበት (off-peak) ወቅት የቮልቴጅ መዋዠቅ እንደሚያጋጥም ጠቅሰው ችግሩን ለመቅረፍ በቂ የኃይል ፍሰት መቆጣጠሪያ መሣሪያዎች ሊኖሩ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
የኃይል ብክነቱን እና ጥራቱን ለማሻሻል ከኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ጋር በትብብር እየተሰራ እንዳለም ነው አቶ ሚኪያስ የጠቀሱት።
ችግሩ በስፋት በሚስተዋልባቸው የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እና ጣቢያዎች ላይ ጥራታቸውን የጠበቁ መሣሪያዎች ማስቀመጥ እንደሚገባም ገልፀዋል።
በቮልቴጅ ችግር ምክንያት የሚስተዋለውን የኃይል ብክነት እና ጥራት ለማስተካከል የሚረዱ መሣሪያዎች ግዢ ለመፈፀም በሂደት ላይ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሚኪያስ እስከ መጋቢት 2015 ዓ.ም ድረስ በአዲጋላ ጣቢያ ላይ ሁለት የሪአክተር ዕቃዎች ለመትከል ዕቅድ እንደተያዘም ተናግረዋል፡፡
የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር የትራክሽን ጣቢያዎች የኮሙዩኒኬሽን መሰረተ ልማት ያልተሟላላቸው ከመሆናቸውም ባሻገር ከብሔራዊ የኃይል ቋት ጋር የተገናኙ እንዳልነበሩ አውስተዋል፡፡ ችግሩን ለመቅረፍም በጣቢያዎቹ የፋይበር ኦፕቲክስ ዝርጋታዎች እና የኮሙዩኒኬሽን ዕቃዎች የመትከልና የማገናኘት ሥራ እየተሰራ እንደሆነም ነው ጨምረው የገለፁት።
በአዋሽ - ወልዲያ - ሃራ ገበያ የባቡር መስመር ፕሮጀክት ከኢትዮ - ጅቡቲ ምድር ባቡር የኃይል መስመር ልምድ በመውሰድ በመገንባት ላይ በሚገኙ ጣቢያዎች የኃይል ፍሰቱን የሚቆጣጠሩና የሚያመጣጥኑ መሳሪያዎችን መግጠም እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡
በአሁኑ ሰዓት ፕሮጀክቱን ባልተመጣጠነ የኃይል ፍሰት ከሚከሰት የኃይል ብክነት ለመታደግ የተለያዩ የጥንቃቄ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆናቸውን ጨምረው ተናግረዋል፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 21 ቀን 2015 ዓ.ም
15 544
የማመንጫ ጣቢያዎችን በራስ ኃይል የመጠገን አቅም እያደገ መጥቷል
……..///………
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ በራስ አቅም እያካሄደ ያለው የጥገና ሥራ አቅም እያደገ መምጣቱን የጊቤ 2 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ኃላፊ እና የኃይል ማመንጫዎች ጥገና ቡድን የቴክኒክ አስተባባሪ ገለጹ፡፡
አስተባባሪው አቶ ሹመት በላቸው እንደገለጹት ተቋሙ የጥገና ቡድን በማቋቋም ከዚህ በፊት በውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ የጥገና ሥራዎችን በማከናወን ለዓመታት የቆሙ ዩኒቶችን ወደ ሥራ ማስገባት ተችሏል፡፡
የጥገና ቡድኑ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን በራስ ኃይል የመጠገን አቅሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ በመምጣቱ ከውሃ ማመንጫ ጣቢያዎች በተጨማሪ በሌሎች የኃይል ምንጮች ላይም የጥገና ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡
የማመንጫ ጣቢያዎችን የጥገና ሥራ በራስ አቅም ለማከናወን የባለሙያዎችን ክህሎት እና የትምህርት ዝግጅት መሰረት በማድረግ ቡድን በማዋቀር አዳዲስ መሐንዲሶችን ልምድ ካላቸው ጋር በማጣመር ወደ ሥራ እንደተገባ አቶ ሹመት ተናግረዋል፡፡
እንደ አስተባባሪው ገለጻ የጥገና ሥራው በተቋሙ የራስ አቅም መከናወኑ ክህሎት ያላቸው ባለሙያዎችን ከማፍራት ባለፈ ከውጭ ሀገር ለሚመጡ የሌሎች ሀገር ዜጎች የጥገና ባለሙያዎች የሚወጣውን ወጪ በመቀነስ በኩል ከፍተኛ ፋይዳ እየተጫወተ ይገኛል፡፡
ከዚህ በፊት በማመንጫ ጣቢያዎች ላይ የሚከናወነው የጥገና ሥራ በተቀናጀ መልኩ ሲመራ እንዳልነበር ያስታወሱት አቶ ሹመት በአሁኑ ወቅት ልምድ ያላቸውን መሐንዲሶች በየጣቢያው በማዘዋወር በቅንጅት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
የጥገና ቡድኑ በግድቦች ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን መፍትሄ ለመስጠትና የቆሙ ዩኒቶችን ወደ ኦፕሬሽን ለመመለስ የጥገና ሥራዎችን በቁርጠኝነትና በተነሳሽነት እያከናወነ እንደሚገኝም ኃላፊው አመልክተዋል፡፡
በዚህም በበጢስ አባይ 2፣ በጊቤ ሦስትና በሌሎች ማመንጫ ጣቢያዎች ስኬታማ ሥራዎች መከናወናቸውን አስታውሰዋል፡፡
ወደ ጥገና ሥራ ከመገባቱ በፊት የብልሽቱን መነሻ ምክንያት በመለየትና የመፍትሔ አቅጣጫዎች እንደሚቀመጡ የጠቆሙት አስተባባሪው ለጥገና ሥራው የሚያስፈልጉ የተለያዩ የመለዋወጫ ዕቃዎችን፣ የደህንነት መጠበቂያ መሳሪያዎችንና የሰው ኃይል በማሟላት ወደ ሥራ እንደሚገባ አስረድተዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በረጲ ከደረቅ ቆሻሻ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ እየተከናወነ ያለው የጥገና ሥራም ይህ መሰረት በማድረግ ወደ ሥራ እንደተገባ ነው ያስታወቁት፡፡
ማመንጫ ጣቢያው በዓይነቱ የተለየ በመሆኑ የጥገና ሥራውን ለማከናወን ያስቸግራል የሚል አስተሳሰብ እንደነበር የጠቆሙት ኃላፊው ወደ ሥራ ሲገባ ግን “በራሳችን አቅም መጠገን እንችላለን፤ ጥገናውን ለውጪ ዜጎች አሳልፎ መስጠት የለብንም” የሚል አስተሳሰብ የተፈጠረበት ነው ብለዋል፡፡
አቶ ሹመት እንዳሉት የጥገና ቡድኑ ከዚህ በፊት በተከናወኑ የጥገና ሥራዎች የተገኙ ልምዶችን በግብዐትነት በመውሰድ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅሞ የጥገና ሥራውን እያከናወነ ይገኛል፡፡
በአሁኑ ወቅት በረጲ ኃይል ማመንጫ እየተከናወነ ካለው የጥገና ሥራ በተጨማሪ በቀጣይ በጊቤ 2 ማመንጫ ጣቢያ ላይ የጥገና ሥራዎችን በራስ አቅም ለማከናወን ዕቅድ መያዙን አስተባባሪው ጠቁመዋል፡፡
የማመንጫ ጣቢያዎችን የጥገና ሥራ በራስ አቅም በመጠገን ወደ ኦፕሬሽን ከማስገባት ባለፈ ለጥገና ሥራው የሚያስፈልጉ አንዳንድ የመለዋወጫ ዕቃዎች ላይ ማሻሻያ በማድረግና የሞዲፊኬሽን ሥራ በመስራት ተቋሙን ከተጨማሪ ወጪ መታደግ እንደተቻለ የጥገና ቡድኑ የቴክኒክ አስተባባሪ አስታውቀዋል፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 20 ቀን 2015 ዓ.ም
15 544
አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አቅርቦት እንዲኖር የሚያስችሉ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች በመገንባት ላይ ይገኛሉ
……...///………
በሀገሪቱ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አቅርቦት እንዲኖር የሚያስችሉ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች በመገንባት ላይ መሆናቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ ገለፁ፡፡
የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ክብሮም ካህሳይ እንደተናገሩት በሀገሪቱ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት የተለያዩ ኪሎ ቮልት መጠን ያላቸው ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች በመገንባት ላይ ይገኛሉ፡፡
ዘርፉ የተለያየ አደረጃጀትና ስያሜዎችን በመያዝ በርካታ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችንና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ሲገነባ መምጣቱን ያወሱት ሥራ አስፈፃሚው ባለ 45፣ ባለ 66፣ ባለ 132 እና ባለ 230 ኪሎ ቮልት መጠን ያላቸውን ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን መገንባቱን ተናግረዋል፡፡
በአሁኑ ወቅትም የተለያየ ኪሎ ቮልት መጠን ያላቸው አዳዲስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የግንባታና የማስፋፊያ ሥራዎች ላይ እየተሳተፈ ይገኛል ብለዋል፡፡
እንዲሁም ከ1 ሺህ ስድስት መቶ ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ከፍተኛ የኃይል ማስተላፊያ መስመሮች በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እየተገነቡ መሆኑን ሥራ አስፈፃሚው አብራርተዋል፡፡
በቅርቡ አገልግሎት የጀመረው የኢትዮ ኬንያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተቋሙ ለጎረቤት ሀገራት አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ የውጪ ምንዛሪ እንዲያገኝና የተሻለ ኢኮኖሚያዊ ትስስር እንዲኖር እንደሚያደርገው ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል፡፡
የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ኃይል እንዳይቆራረጥ ለማድረግ ሦስት የኃይል ማስተላለፊያ አማራጭ ቴክኖሎጂን የያዘ በመሆኑ የተቋሙን ተፎካካሪነት እንደሚያሳድገው አቶ ክብሮም ገልፀዋል፡፡
የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ ከጊዜ ወደጊዜ የመገንባት አቅሙን እያሳደገ በመምጣቱ በአሁኑ ወቅትም ባለ 400 ኪሎ ቮልት መጠን ያላቸውን ከፍተኛ ኃይል መስተላለፊያ መስመሮችን መገንባት የሚያስችል አቅም የፈጠረ መሆኑን ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ታህሳስ 18 ቀን 2015 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
