EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 537 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 329,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 179 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 537 名订阅者。
根据 03 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 31,过去 24 小时变化为 -1,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.36%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.21% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 097 次浏览,首日通常累积 2 520 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 10。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 04 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 537
订阅者
-124 小时
-167 天
+3130 天
帖子存档
15 542
የትራንስፖርት ስምሪትና ቁጥጥር መምሪያ ዘመናዊ የአሰራር ስርዓት መዘርጋቱን አስታወቀ
……..////…….
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስፖርት ስምሪትና ቁጥጥር መምሪያ ዘመናዊ የአሰራር ስርዓት ተግባራዊ ማድረጉን አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ኃይላይ ተስፋይ እንደገለፁት ቀደም ሲል የተቋሙ ተሸከርካሪዎች ወደ አንድ ማዕከል የተሰበሰቡ ባለመሆናቸው ምክንያት የተሽከርካሪ ስምሪት አገልግሎት አሰጣጡ አስቸጋሪ ነበር፡፡
ይሁንና ካለፈው በጀት ዓመት ጀምሮ የተቋሙ ተሽከርካሪዎች በመምሪያ ሥር እንዲሰባሰቡ መደረጉ አሰራሩን ቀልጣፋ ከማድረጉ በተጨማሪ አላስፈላጊ ወጭዎችን ማስቀረት እንዳስቻለ ኃላፊው አብራርተዋል፡፡
ለሥራ ክፍሉ ቀደም ሲል በወረቀት ይቀርብ የነበረውን የተሽከርካሪ ስምሪት ጥያቄ በኦንላይን ማስተናገድ መጀመሩንም ተናግረዋል፡፡
አዲስ የተዘረጋው የአሰራር ስርዓት የትራንስፖርት አገልግሎት ጠያቂዎች ፍላጎታቸውን በኦንላይን እንዳቀረቡ ወዲያው በእጅ ስልካቸው ላይ የተመደበውን ተሸከርካሪ የሠሌዳ ቁጥር፣ የአሽከርካሪውን ስምና ስልክ በአጭር የጽሁፍ መልክት አማካኝነት እንዲደርስ የሚያደርግ ነው፡፡
ይህም ስራ ክፍሉ ለውስጥ ደንበኞች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልገሎትን መስጠት ከማስቻሉ በተጨማሪ ለወረቀት ይወጣ የነበረ ወጪን ማስቀረት አስችሏል ብለዋል፡፡
እንደ ኃላፊው ገለፃ የሠራተኛውን እርካታ ከፍ ለማድረግ ከሦስት ዓመት በፊት በአዲስ አበባ ከተማ ለሚኖሩ የተቋሙ ሠራተኞች የትራንስፖርት አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑንና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ እስከ ሱሉልታ፣ ደብረዘይት እና ሰንዳፋ ከተሞች የትራንስፖርት አገልግሎት እየተሰጠ ነው፡፡
መምሪያው ዘመናዊ የቁጥጥር ስርዓት ለመዘርጋት በተሽከርካሪዎች ላይ የGPS ቴክኖሎጂን የመግጠም እና የተቋሙን ማሽነሪዎችና ተሸከርካሪዎች በቀላሉ እንዲለዩ ለማድረግ በንብረቶቹ ላይ የተቋሙን ሎጎ መለጠፍ የሚያስችሉ ስራዎች በማከናወን ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡
ይህም የተቋሙ ንብረቶች ከተቋሙ ስራ ውጭ አገልግሎት እንዳይሰጡ የሚያደርግ ዘመናዊ የአሰራር ስርዓት መሆኑን አቶ ኃይላይ አብራርተዋል፡፡
የትራንስፖርት ስምሪትና ቁጥጥር መምሪያው በፕሮጀክቶች አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ ተሽከርካሪዎችን በመለየት ወደ ተቋሙ ባለቤትነት የማዛወር ስራ እየተሰራ ነው፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ለረጅም ጊዜ በማገልገላቸው ምክንያት በቂ መለዋወጫ ያልተገኘላቸውን 38 ተሸከርካሪዎች ውስጥ በጨረታ እንዲሸጡ ማድረጉንና በቀጣይም 22 ተሽከርካሪዎችን በግልፅ ጨረታ ለመሸጥ በዝግጅት ላይ መሆኑን መምሪያው አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዚያ 10 ቀን 2014 ዓ/ም
15 542
የተቋሙ ሠራተኞች መንግስት የዋጋ ንረትን እንዲያረጋጋ ጠየቁ
.......///.........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች መንግስት የዋጋ ንረትን እንዲያረጋጋ ጠየቁ፡፡
ወራተኞቹ በተቋማዊና በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ባካሄዱት ውይይት በተቋሙ ከደመወዝ እና ጥቅማጥቅም፣ ከእውቅና አሰጣጥና የሥራ ላይ ደህንነት፣ ከሠራተኞች የስራ አፈጻጸም መመዘኛ መስፈርቶችና የአሰራር ሥርዓት፣ እንዲሁም ሌሎች በተቋሙ ሊስተካከሉ ይገባሉ ያሏቸውን ጥያቄዎች አንስተዋል፡፡
መንግስትም የዜጎችን ሠላምና ደህንነት እንዲያረጋግጥ፣ ሥርዓት አልበኝነትን እንዶቆጣጠርና እንዲሁም የዋጋ ንረትን እንዲያረጋጋ ሠራተኞቹ ጠይቀዋል፡፡
ሠራተኞቹ በሰጡት አስተያየት ተቋሙ በተለያዩ አካባቢዎች እየገነባቸው ባሉ እና አገልግሎት በሚሰጡ የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶች ላይ ተደጋጋሚ ዝርፊያዎች እየተፈጸመ በመሆኑ በየደረጃው ካሉ የክልል የመስተዳድር አካላት ጋር ተቀራርቦ መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡
ውይይቱን የመሩት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት ውይይቱ ከሠራተኛው የሚነሱ የተለያዩ ተቋማዊ ችግሮችን ለመፍታትና በተቋሙ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ለሰራተኛው ለማስተዋወቅ ፋይዳው የጎላ ነው፡፡
በሀገሪቱ እየተስተዋለ ያለው የሰላም መደፍረስ እና የኑሮ ውድነት በተቋሙ ዐበይት ተግባራት ላይ ተጽዕኖ ማሳደሩን ዋና ስራ አስፈጻሚው አስታውቀዋል፡፡
ይሁንና ህገ-ወጥነትን መከላከልና ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንዲሁም የኑሮ ውድነትን መግታት ለመንግስት ብቻ የሚተው ባለመሆኑ ሁሉም በተናጠል ኃላፊነቱን በአግባቡ እንዲወጣ አሳስበዋል፡፡
የተቋሙን ገቢ ለማሳደግ የተለያዩ አዳዲስ የገቢ ማስገኛ አማራጮችን ለመተግበር እየተሰራ መሆኑን ያነሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ከዚህ ጎን ለጎን ወጪ ቅነሳ ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
እየተሰሩ ያሉ የገቢ ማስገኛ መንገዶች ሲተገበሩ ለሀገሪቱ የውጭ ምንዛሪ በማስገኘት ተቋሙን የሀገሪቱ አስተማማኝ ኃይል አቅራቢ እንደሚያደርገው እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡
ዋና ሥራ አስፈፃሚው እንደገለፁት ተቋሙ የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማት በሚገነባባቸው አካባቢዎች የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ ሲሆን ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣትም በጀት ተመድቦ እየሰራ ይገኛል፡፡
በተቋሙ የኢንጅነሪንግ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ውድነህ የማነ በበኩላቸው በተቋሙ ያሉ ችግሮችን ለመፍታትና ሠራተኛው የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች ለመመለስ መሰል ውይይቶችን ማካሄድ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ጠቁመው ውይይቱ በቀጣይ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል፡፡
ተቋሙን ለከፍተኛ ወጭ እየዳረገ ያለውን የቢሮ ህንጻ ኪራይ ለማስቀረት እየተሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡
ተቋሙ የሚያከናውናቸውን የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች በወቅቱ፣ በጥራትን በተያዘለት ወጭ ለማከናወን የራስ ኃይል ቢሮን ማጠናከርና የሠራተኞችን አቅም ማሳደግ እንደሚገባም አንስተዋል፡፡
በውይይቱ ወቅት ከሠራተኞች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የዘርፍ ሥራ አስፈጻሚዎች ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተውባቸዋል፡፡
በቀጣይ በኃይል ማመንጫዎች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም በሪጅኖች ላይ ተመሳሳይ ውይይት እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዚያ 07 ቀን 2014 ዓ/ም
15 542
የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ አካባቢን የኤሌክትሪክ ችግር በአጭር ጊዜ ለመፍታት አልተቻለም
……../////……..
የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ አካባቢ ኤሌክትሪክ በአጭር ጊዜ እንዲያገኝ ለማድረግ መቸገሩን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንደገለፁት በሽብር ቡድኑ ምክንያት የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ኃይል ከተቋረጠ ከአንድ ዓመት በላይ ሆኖታል፡፡
የላሊበላ እና የዋግ ኽምራ ዞን በርካታ አካባቢዎችም ለወራት የኤሌክትሪክ ኃይል እያገኙ አይደለም ብለዋል፡፡
እንደ አቶ አሸብር ገለፃ የላሊበላ፣ ሰቆጣ፣ ወልቃይት፣ ጠገዴ እና ሰቲት ሑመራ አካባቢዎች ኃይል ያገኙ የነበሩት በሽብር ቡድኑ በተያዙ አካባቢዎች ከሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ከተዘረጉ መሥመሮች ነበር፡፡
በዚህ የተነሳ የተቋረጡትን መሥመሮች ለመጠገንና አካባቢዎቹ ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ ተቋሙ መቸገሩን ዋና ሥራ አስፈፃሚው አስታውቀዋል፡፡
ለላሊበላና አካባቢው ሌሎች አማራጮችን እየታዩ በመሆናቸው በአጭር ጊዜ ሊፈቱ እንደሚችሉ የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈፃሚው ለወልቃይት ጠገዴ አካባቢ መፍትሔ ለመስጠት ከጎንደር ወይም ከመተማ ኃይል መዘርጋት ግድ ስለሚል ረጅም ጊዜ እንደሚጠይቅ ጠቅሰዋል፡፡
በወልቃይት ጠገዴን ያለው ችግር ከሌሎች አካባቢዎች በተለየ ከዓመት በላይ የቆየው በአካባቢው አማራጭ መስመር ባለመኖሩና የአዲስ መስመር ዝርጋታው ትልቅ ኢንቨስትመንት የሚጠይቅና ረዘም ያለ ጊዜ የሚወስድ በመሆኑ ነው ብለዋል፡፡
ይሁንና በአጭር ጊዜ መፍትሔ ለመስጠት የክልሉ መንግስት፣ የፌደራል መንግስትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ሊሳተፉበት እንደሚገባ አቶ አሸብር ጠቁመዋል፡፡
የአጭር ጊዜ መፍትሔ ሊሆን የሚችለው ኦፍ ግሪድ የሆኑ አማራጮችን ተግባራዊ በማድረግ እንደሆነ አሳስበዋል፡፡
ላሊበላን በጄኔሬተር መብራት ለመስጠት የተደረገው ሙከራ በነዳጅ አቅርቦት ምክንያት መስተጓጎሉ አይዘነጋም፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዚያ 07 ቀን 2014 ዓ/ም
15 542
በሀገሪቱ ሙሉ የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ ከተከሰተ አንድ ዓመት አልፎታል
……///…..
በሀገሪቱ ሙሉ በሙሉ የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ ከተከሰተ አንድ ዓመት እንዳለፈው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ፡፡
የማዕከሉ ዳይሬክተር አቶ የማነ ኢሳያስ እንደገለፁት ባለፈው አንድ ዓመት በሀገሪቱ ሙሉ በሙሉ ኃይል እንዳይቋረጥ ማድረግ የተቻለው (Total black out) ከብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል፣ ከሪጅኖች እና ከኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ጋር በቅንጅት በመሰራቱ ነው፡፡
በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ በሚያጋጥሙ ችግሮች ሳቢያ ባለፉት ዓመታት አልፎ አልፎ ሙሉ የኃይል መቋረጥ ያጋጥም እንደነበር ያስታወሱት ዳይሬክተሩ የሥራ ክፍሎች በቅንጅት መስራታቸው በመላ ሃገሪቱ ኃይል ሳይቋረጥ አንድ ዓመት እንዲቆይ አድርጎታል ብለዋል፡፡
እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ባለፈው አንድ ዓመት ከሪጅኖች እና ከኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ጋር በጋራ በማመንጫ ዩኒቶች፣ በከፍተኛ የኃይል ማከፋፈያ እና ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የፍተሻ፣ የቁጥጥር እና የአስቸኳይ ጥገና ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡
በኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ውስጥ በኃይል ማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የሚደረገው ክትትል በሰው ኃይልና በቴክኖሎጂ በታገዘ ዘመናዊ የመከላከያ ሥርዓት እየተደገፈ መምጣቱ ችግሩን ለመቀነስ አስተዋፅኦ እንዳበረከተ ገልፀዋል፡፡
ከኃይል ማመንጫዎች እና ከሪጅን ቢሮዎች ጋር የሚደረገው የመረጃ ልውውጥ ሥርዓት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየዘመነ መሔዱ ችግሮችን በቀላሉ ለይቶ አፋጣኝ መፍትሔ ለማስቀመጥ ማስቻሉንም ተናግረዋል፡፡
በግሪድ ሥርዓት ውስጥ ያልገቡ የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች መኖራቸው በተደጋጋሚ የኃይል መቋረጥ እንዲከሰት ሲያደርጉ መቆየታቸውን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡
ተቋሙ ባለፈው አንድ ዓመት የጊቤ 3 - ገላን - ወላይታ ሶዶ ሁለተኛ ሰርኪዩት እና በለስ የሚገኙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት መግባታቸውና የመከላከያ ሥርዓታቸው ተቀናጅቶ እንዲሰራ መደረጉ በግሪድ ሥርዓቱ ላይ የነበረውን ጫና በመቀነስ ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ ማድረጉን አንስተዋል፡፡
በጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ ያሉት የግንኙነት መሳሪያዎች በነበረባቸው የእርስ በእርስ የመናበብ ችግር መቀረፉ የግሪድ ሥርዓቱ እንዳይረበሽ አድርጓል ብለዋል፡፡
በሁሉም የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ውስጥ የሚገኙ ዩኒቶች እና የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ችግር በሚገጥማቸው ወቅት የሚሰጠው ምላሽ የከፊልና የነጠላ መስመር የኃይል መቋረጥ ችግሩን በዘላቂነት ለመቀነስ ያስችላል ተብሏል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዚያ 06 ቀን 2014 ዓ/ም
15 542
ባለፉት ዘጠኝ ወራት ጊቤ 3 ከዕቅድ በላይ ኃይል ማመንጨት ችሏል
……..////……..
የጊቤ 3 የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ኃይል የማመንጨት አፈፃፀሙ ከዕቅድ በላይ መሆኑን አስታወቀ፡፡
የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ሰሙ እንደገለፁት በ2014 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት 4900 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ለማመንጨት አቅዶ 5230 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ በማምረት ከዕቅዱ በላይ የ4 በመቶ ብልጫ ያለው አፈፃፀም አስመዝግቧል፡፡
የኃይል ምርት አፈፃፀሙ ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀርም የ19 በመቶ ብልጫ እንዳለው አቶ ሀብታሙ ተናግረዋል፡፡
እንደ አቶ ሀብታሙ ገለፃ በመስከረም ወር የማመንጫ ዩኒቶችን ሊያስቆሙ የሚችሉ ችግሮችን መቅረፍ የሚያስችሉ የመለዋወጫ ዕቃዎች መገዛታቸው ጣቢያው ከዕቅዱ በላይ ኃይል እንዲያመነጭ አስችሏል፡፡
የጣቢያው የጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ንጉሴ ማሙሻ በበኩላቸው ለዩኒቶቹ ተከታታይነት ያላቸው የጥገና ሥራዎች በወቅቱ መከናወናቸው የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ከዕቅዱ በላይ ኃይል እንዲያመርት እገዛ አድርጓል ብለዋል፡፡
በዕቅድ ተይዘው እየተከናወኑ ካሉ የጥገና ሥራዎች ውጪ እስካሁን የማመንጫ ዩኒቶችን ሊያስቆም የሚችል ምንም ችግር እንዳልተከሰተም ነው ኃላፊው የተናገሩት፡፡
ተቋሙ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው የሚያቅዳቸውን ዕቅዶች ከግብ እንዲያደርስ የመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት ግዢ ሊፋጠንና የስታፍ ፕላኑን የሚመጥን የሰው ኃይል እንዲሟላ ኃላፊዎቹ ጠይቀዋል፡፡
የጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ፍላጎት ከ40 እስከ 50 በመቶ እየሸፈነ የሚገኝና ኢኮኖሚውን በመደገፍ በኩል አስተዋፅኦው የጎላ ያለው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዚያ 05 ቀን 2014 ዓ/ም
15 542
በባለፉት ዘጠኝ ወራት 8 የተለያዩ ጥቆማዎች ለጽ/ቤቱ ቀርበዋል
………///………
ባለፉት ዘጠኝ ወራት 8 የተለያዩ ጥቆማዎችን መቀበሉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥነ- ምግባርና ጸረ ሙስና መከታተያ ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡
የጽ/ቤቱ ሥራ አስፈጻሚ አቶ መርጋ ተረፈ እንዳስታወቁት ከቀረቡ ጥቆማዎች ውስጥ ሁለቱ የሙስና ወንጀል ባህሪ ያላቸው ሲሆኑ ስድስቱ ደግሞ አስተዳደራዊ እርምጃ የሚሹ ጥቆማዎች ናቸው።
እንደ አቶ መርጋ ገለጻ ሁለቱ የሙስና ወንጀል ጥቆማዎች በተጭበረበረ የኃላፊዎች ፊርማና ማህተም የተፈፀመ የጉዞ አበልና የቀን ሠራተኞች ክፍያ እና ያልተገባ ጥቅም በመፈለግ በሁለት የመንግስት መስሪያ ቤቶች ውስጥ በመስራት ላይ የነበረ በአንድ የተቋሙ ሠራተኛ ጉዳይ ላይ ያተኮሩ ናቸው፡፡
ጥቆማዎቹ ለፌደራል የሥነ- ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ከሚቀርብ የጥቆማና የመረጃ ስርዓት እንዲሁም በተቋሙ እየተስተዋሉ ያሉ የሙስና ወንጀሎችን የተቋሙ ሠራተኞች እና የውጭ ደንበኞች ጥቆማ እንዲሰጡ በተቀመጠው አሰራር መሰረት የቀረቡ መሆናቸውን አቶ መርጋ አስታውቀዋል፡፡
ለጽ/ቤቱ የሚቀርቡ ጥቆማዎች በአስቸኳይ የሙስና መከላከል ሥራ አፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 21/2013 ላይ በተደነገገው መሰረት በመመዘን ትክክለኝነቱን የማጣራት ስራ ሲከናወን እንደነበር ስራ አስፈጻሚው ጠቁመዋል፡፡
ለጽ/ቤቱ ከቀረቡ ጥቆማዎች ውስጥ ሁለቱ የሙስና ወንጀሎች ለፍትህ አካላት ተልከው የውሳኔ ሀሳብ እየተጠበቀ ሲሆን ሌሎች አስተዳደራዊ እርምጃ የሚሹ ጉዳዮች ደግሞ በተቋሙ ባለሙያዎች ክትትል እየተደረገባቸው መሆኑን አቶ መርጋ ተናግረዋል፡፡
ባለፉት ዘጠኝ ወራት በተቋሙ ባለሙያዎች ክትትል ሲደረግባቸው ከነበሩ ጉዳዮች መካከል በሁለት ሠራተኞች ላይ የስራ ስንብት፣ በአንድ ሠራተኛና በሁለት የስራ ኃላፊዎች ላይ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ እንዲሁም በአንድ ባለሙያና በአንድ የሥራ ኃላፊ ላይ ደግሞ የገንዘብ ቅጣት እርምጃ መወሰዱን ነው ስራ አስፈጻሚው የገለጹት፡፡
በቀረቡ የሙስና ወንጀል ጥቆማዎች ላይ ክትትል ከማድረግ በተጨማሪ ለአስተዳደራዊ ችግሮች በሚያጋልጡ የተለያዩ ጉዳዮች ላይ የአሰራር ስርዓት ማስተካከያዎች መደረጋቸውንም አቶ መርጋ ጠቁመዋል፡፡
እንደ አቶ መርጋ ገለጻ በዕቃ ግምጃ ቤት የንብረት አያያዝ እና ጥበቃ፤ በንብረት አወጋገድ የጨረታ ሂደት፣ በፕሮጀክትና ኦፕሬሽን መካከል የሚደረግ የንብረት ርክክብ፤ በፋይናንስ የክፍያ አፈፃፀም እና በውክልና አሰጣጥ ላይ፤ በትምህርትና ስልጠና የመረጣ ሂደት፤ በዓመት ፍቃድ አሰጣጥ እና በሰዓት መቆጣጠሪያ አያያዝ ፣ በማከፋፈያ ጣቢያ የጥበቃ ኃላፊዎች ምደባ የአሰራር ስርዓት ላይ ማስተካከያ ለማድረግ የተለያዩ ሥራዎች ተጀምረዋል፡፡
የሙስና ትግሉን በጥናትና በመረጃ ላይ በመመስረት እንዲከናወን ለማድረግ በሥራ ዘርፉ ውስጥ የአሰራር ጥናትና አስቸኳይ የሙስና መከላከል እና የስልጠና፣ ኮሙዩኒኬሽንና ሀብት ምዝገባ የሚሉ ሁለት የሥራ ክፍሎችን የማደራጀት ስራ መሰራቱንም ኃላፊው ተናግረዋል፡፡
በሥነ-ምግባር ግንባታ፣ በሙስና ተጋላጭነት ጥናትና መረጃ አገልግሎት ላይ የበለጠ በመስራት በቀጣይ ተቋሙን ከሙስናና ብልሹ አሰራር የፀዳ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶት እንደሚሰራም አቶ መርጋ አረጋግጠዋል፡፡
የሙስና ወንጀል ውስብስብና ረቂቅ በመሆኑ ድርጊቱን በሥራ ክፍሉ ባለሙያዎች ብቻ መግታት ስለማይቻል በባለሙያዎች በሚደረገው የሥነ-ምግባር ግንባታ፣ የሙስና ተጋላጭነት ስጋት ጥናትና የሙስና መረጃ አገልግሎት ሥራ ላይ የተቋሙ ሠራተኞችና የስራ መሪዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ አቶ መርጋ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዚያ 04 ቀን 2014 ዓ/ም
15 542
ኃይል የማመንጨት ሥራውን ለማዘመን እየተሰራ ነው
…….///……..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ የተለያዩ የማዘመን ሥራዎችን እየተከናወኑ መሆኑን በተቋሙ የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈጻሚ አስታወቁ፡፡
ሥራ አስፈፃሚው አቶ እያየሁ ሁንዴሳ እንደተናገሩት ኃይል የማመንጨት ሥራዉን በዘመናዊ መንገድ ለማከናወን በማመንጫ ጣቢያዎች ላይ የተለያዩ የማዘመን ስራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡
በአሁኑ ሰዓትም በግልገል ጊቤ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የዕለት ተዕለት ስራዎችን፣ የቁጥጥር ሥርዓቱን እና ቴክኒካል የሆኑ የድጋፍ ስራዎችን ዘመናዊ በሆን መልኩ እንዲከናወኑ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎች በመከናወን ላይ ናቸው ብለዋል፡፡
እንደ ሀገር የኤሌክትሪክ ኃይል በሚቋረጥበት ጊዜ ከጊቤ 3 እስከ ገላን ድረስ የተዘረጉትን መስመሮች እና የጣቢያው ዩኒቶች በማኑዋል ሲፈተሹ እንደነበር ያነሱት ሥራ አስፈፃሚው በአሁኑ ሰዓት ስራውን አውቶማቲክ በሆነ መልኩ ለማከናወን የማዘመን ስራ ለማከናወን እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ይህንንም ሥራ ለማከናወን 420 ሺህ ዶላር በጀት ተይዞ ዶንግ ፋንግ ከተሰኘ የቻይና ኩባንያ ጋር የውል ስምምነት መፈረሙንም ሥራ አስፈፃሚው ገልጸዋል፡፡
አቶ እያየሁ አክለውም በጊቤ 1 እና በበለስ የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ የስካዳ ማሻሻያ ስራዎችን ለማከናወን የስምምነት ድርድር በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡
በአሁኑ ሰዓት የተለያዩ የማዘመን ስራዎች እየተከናወነላቸው ከሚገኙ ማመንጫ ጣቢያዎች በተጨማሪ በቀጣይ በሌሎች ጣቢያዎች ላይ የማመንጨት ሥራውን ሊያዘምኑ የሚችሉ የተለያዩ ሥራዎችን ለማከናወን እየተሰራ እንደሚገኝ ሥራ አስፈጻሚው አስታውቀዋል፡፡
የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን የቴክኒክ ድጋፍ ሥራ አስኪያጁ አቶ አብዱ ይማም በበኩላቸው እንደገለፁት በጣቢያው ላይ ከዕቅድ ጀምሮ የመለዋወጫ እቃ አቅርቦቱን፣ የዕቃ ግምጃ ቤት አስተዳደርን፣ የመረጃ አያያዝ እና ሪፖርት የማድረግ ስራዎችን (on care asset management system) በዘመናዊ መልኩ እንዲከናወን ለማድረግ የሚያግዙ የተለያዩ ስራዎች በመከናወን ላይ ናቸው፡፡
እንደ አቶ አብዱ ገለጻ በጣቢያው ላይ ትክክለኛ ያልሆነ ድምጽ ሲሰማ ያለውን ችግር በቀላሉ መለየት እንዲቻልና የጣቢያውን የቁጥጥር ስርዓት ማዘምን የሚያስችል "On care acoustics" ስራ እየተከናወነ ይከኛል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ቴክኒካል የሆኑ የድጋፍ ስራዎችን በምስል በተደገፈ መልኩ (On call video) ከሌላ አካባቢ ከርቀት ሆኖ እንዲከናወኑ ለማድረግ የሚያግዝ የማዘመን ስራ እየተከናወነ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡
በጊቤ 2 ማመንጫ ጣቢያ ላይ እየተከናወነ ያለው የማዘመን ሥራ ከጀርመን መንግስት በድጋፍ የተገኘ ከ677 ሺህ ዩሮ በላይ በጀት ቮይት (Voith) በተባለ የጀርመን ኩባንያ በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡
መጋቢት 2013 ዓ.ም አካባቢ የተጀመረው ይህ ፕሮጀክቱ በአሁኑ ወቅት በመጠናቀ ላይ ሲሆን የኮሚሽኒንግ ስራውን በቅርቡ ለማከናወን ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዚያ 03 ቀን 2014 ዓ/ም
15 542
በዝርፊያ የወደቀው የአዋሽ 2 - አሰላ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ ጥገና ተጠናቀቀ
………///……….
በዘራፊዎች ተቆርጦ የወደቀው ከአዋሽ 2 ወደ አሰላ የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን በእንጨት ምሰሶ የመተካት ሥራ ተጠናቀቀ።
መጋቢት 24 ቀን 2014 ዓ.ም በዶዶታ ወረዳ እና ጌራ ከተማ አቅራቢያ በተፈፀመው የምሰሶ አካላት ዝርፊያ ሁለት ምሰሶዎች የወደቁ ሲሆን በአካባቢው በከፊል ኤሌክትሪክ ተቋርጦ መቆየቱ ይታወሳል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጥገና ቡድን ለቀናት ሲያከናውን የቆየውን ጥገና ዛሬ በማጠናቀቁ ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ ኤሌክትሪክ መልሶ የማገናኘት ሥራ ይከናወናል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዚያ 2 ቀን 2014 ዓ/ም
15 542
ጣቢያው የምርምርና ልማት ማዕከል በማቋቋም ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል
…….///…….
የጊቤ 3 የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የምርምርና ልማት ማዕከል በማቋቋም የተለያዩ ሥራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ፡፡
የጣቢያው የጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ንጉሴ ማሙሻ እንደገለፁት ጣቢያው በተደጋጋሚ የሚያጋጥሙትን ችግሮች ለይቶ ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት የሚያስችል የምርምርና ልማት ማዕከል አቋቁሟል፡፡
ጣቢያው ግዙፍ እንደመሆኑ መጠን ውስብስብ የሆኑ የአሰራር ሥርዓቶችን ለማሻሻል ጥናትና ምርምሮችን ማከናወን መጀመሩን አቶ ንጉሴ ተናግረዋል፡፡
የማዕከሉ መቋቋም በራስ አቅም የሚሰሩ ስራዎችን ለማጠናከር፣ የሠራተኞችን አቅም ለማሳደግ እና ወጪ ለመቀነስ ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለው ኃላፊው አብራርተዋል፡፡
የጥገና ሥራዎች በጥናት ታግዘው መከናወናቸው የጣቢያውን የማመንጨት አቅም ከፍ እንደሚያደርግ የጠቀሱት ኃላፊው ማዕከሉ ከተቋቋመ በኋላ የተሠሩ ሥራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
ማዕከሉ የሠው ኃይል ልማት ሥራዎችን በማከናወን ብክነቶችን ከመቀነስ ባለፈ ጊዜ ይወስዱ የነበሩ ተግባራትን አሳጥሮ በመስራት ረገድ መሻሻሎችን አስገኝቷል ብለዋል፡፡
የጣቢያው ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ሰሙ በበኩላቸው ማዕከሉ በጣቢያው የኃይል ማመንጫ፣ የጥገና እና የአስተዳደር ክፍሎች ተናበው ዕቅዶቻቸውን እንዲያሳኩ በማድረግ መፍትሔ ሰጪ ሥራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡
እስካሁን በተሰራው ሥራም በጣቢያው የሚገኙ የሥራ ክፍሎች የመረጃ ልውውጥ ሥርዓት እንዲዘምን መደረጉን ጠቅሰዋል፡፡
በምርምርና ልማት ማዕከሉ ውስጥ ሥራ እየሠሩ የሚገኙት አቶ አማኑኤል ዳንኤል በበኩላቸው የማዕከሉ መቋቋም ዋና ዓላማ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው በጥናታዊ ምርምሮች እንዲታገዝ በማድረግ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ሥርዓት እንዲኖረው ማስቻል ነው ብለዋል፡፡
ማዕከሉ የተለያዩ ሥልጠናዎችን በማዘጋጀት ባለሙያዎችን የማብቃት ሥራዎች ለመስራት እየተዘጋጀ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡
አቶ አማኑኤል እንደገለፁት ማዕከሉ የምርምርና ልማት ሥራዎችን ለማከናወን የሚያግዘውን ድረ-ገፅ በመስራት የተለያዩ ፕሮጀክቶች መተግበር ጀምሯል፡፡
በጣቢያው በተደጋጋሚ ብልሽት እያጋጠማቸው ያሉ ዕቃዎችን በመለየት ዘላቂ የሆነ መፍትሔ ለመስጠት የሚያስችሉ የአጭርና የረጅም ጊዜ የምርምርና ልማት ዕቅዶችን ነድፈው በመንቀሳቀስ ላይ መሆናቸውን አቶ አማኑኤል ገልፀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መጋቢት 30 ቀን 2014 ዓ/ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
