EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 525 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 336,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 179 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 525 名订阅者。
根据 07 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 5,过去 24 小时变化为 -2,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 28.59%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.03% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 440 次浏览,首日通常累积 2 489 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 10。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 08 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 525
订阅者
-224 小时
-57 天
+530 天
帖子存档
15 525
የቦርዱ ክትትል የግንባታውን አፈፃፀም የተሻለ አድርጎታል - አቶ አሸብር ባልቻ።
.................../////////................
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር አብርሃም በላይና ሌሎች የቦርዱ አባላት የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን አፈፃፀም በመከታተል የሚያደርጉት ድጋፍ ከፍተኛ መሆኑን ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ አሸብር ባልቻ ተናግረዋል።
አቶ አሸብር እንደገለፁት ቦርዱ በመደበኛነት በወር አንድ ጊዜ ግንባታው በሚካሄድበት ስፍራ በመገኘት አጠቃላይ አፈፃፀሙን በሳይት ምልከታና በሪፖርት በመገምገም ግብረመልስ እየሰጠ ነው።
በየሳምንቱ በሚያደርገው የቦርድ ስብሰባው አፈፃፀሙን የሚከታተል አጀንዳ በመቅረፅ ስራውን በቅርበት እየተከታተለና ለስራው የሚያስፈልጉ ውሳኔዎችን እያሳለፈ መሆኑን ገልፀዋል።
ይህም የግድቡን ግንባታ አፈፃፀም የተሻለ እንዳደረገው ዋና ስራ አስፈፃሚው ተናግረዋል።
ይህን መሰሉ ክትትልና ድጋፍ ግድቡ ውሃ መያዝ እስኪጀምር ብቻ ሳይሆን እስከፍፃሜው ድረስ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ሙሉ እምነት አለኝ ብለዋል።
ዛሬ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ያደረጉት ጉብኝት መንግስት ለግድቡ ግንባታ ተገቢውን ትኩረት እየሰጠ ለመሆኑ ማሳያ እንደሆነ ጠቅሰዋል።
ግንቦት 30 ቀን 2012 ዓ/ም
15 525
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ውኃ ለመያዝ የሚያስችሉ ሥራዎች ከሳምንታት በኋላ ይጠናቀቃሉ - ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ
********************
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ውኃ ለመያዝ የሚያስችሉ ሥራዎች ከሳምንታት በኋላ እንደሚጠናቀቁ የውኃ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ገለጹ።
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከአንድ ወር በኋላ ውኃ እንዲይዝ የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ መሆኑን ለኢቲቪ የገለጹት ሚኒስትሩ፣ በቀጣይ ሳምንታት የሚከናወኑ ቀሪ ተግባራት ከተከናወኑ በኋላ ግድቡ የመጀመሪያውን ዙር ውኃ መያዝ እንደሚችል ጠቁመዋል።
ይህም በሚቀጥለው ዓመት የቅድመ-ኃይል ማመንጫ ተግባሩን ለማከናወን ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ነው ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ የተናገሩት።
ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን እና ከሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች ጋር ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በጎበኙበት ወቅት ነው።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ከጉብኝታቸው በኋላ ግድቡ በሚከናወንበት ስፍራ ላይ ችግኞች መትከላቸውን ኢቢሲ ዘግቧል።
ግንቦት 30/2012 ዓ/ም
15 525
ም/ጠቅላይ ሚኒስትሩና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ጎበኙ
*********************
በኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የተመራ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ቡድን የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ጎብኝቷል፡፡
በጉብኝቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው፣ የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር አብርሀም በላይን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩና ሚኒስትሮቹ የግድቡን ግንባታ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
የግንባታውን ደረጃ በተመለከተ በባለሙያዎች ገለፃ የተደረገላቸው ሲሆን አጠቃላይ አፈፃፀሙ 74 በመቶ መድረሱም ተገልፃላቸዋል፡፡
ከጉብኝቱ በኋላ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንባታው በጥሩ ሂደት ላይ እንዳለ መመልከታቸውን በመግለፅ ውሃ ለመያዝ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።
በግንባታው የታሰበውን ውጤት በማስመዝገብ የሀገር ኩራት የሚሆን ፕሮጀክት መሆኑን እናረጋግጣለን ብለዋል።
ሌሎች ሚኒስትሮችም በተመለከቱት ነገር ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ግንቦት 30 /2012 ዓ/ም
15 525
ዋና ስራ አስፈፃሚው በኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በመገኘት ችግኝ ተከሉ፡
……………………////////……………………
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ በኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በመገኘት ችግኝ ተክለዋል፡፡
የ2012 የችግኝ ተከላ መርሃግብር በይፋ በተጀመረበት በዛሬው ዕለት ዋና ሥራ አስፈፃሚው ችግኝ ከተከሉ በኋላ እንደገለፁት ችግኞችን መትከል የአፈር መሸርሸርን በመከላከል የአየር መዛባትን ለመቆጣጠር ያግዛል፡፡
ይህም የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድቦችን ውሃ የመያዝ አቅም ከፍ በማድረግ የኃይል አቅርቦትን ለማሳደግ ያግዛል ብለዋል፡፡
በመሆኑም የኮቪድ ወረርሽኝን በመከላከልና አስፈላጊውን ርቀት በመጠበቅ ሁሉም የተቋሙ ሰራተኛ በሚኖርበት አካባቢና በሚሰራበት ቦታ ችግኞችን በመትከል በንቃት እንዲሳተፍ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ጥሪ አሳስበዋል፡፡
የ 2012 ዓመት የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃግብርን ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አሕመድ ከአረንጓዴ አሻራ ብሔራዊ አስተባባሪ ቡድን አባላት ጋር በሐዋሳ ከተማ ታቦር ተራራ ላይ ችግኞችን በመትከል ዛሬ በይፋ ማስጀመራቸው ይታወቃል፡፡
ግንቦት 28/2012 ዓ.ም.
15 525
የሐዘን መግለጫ
የምስራቅ ሪጅንም በሪጅኑ የትራንስሚሽን መስመር ጥገና ሠራተኛ እሸቱ ገዛኸኝ ህልፈት የተሰማውን ሐዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቹና ወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን ይመኛል።
ግንቦት 27 ቀን 2012 ዓ/ም
15 525
የሐዘን መግለጫ
የምስራቅ ሪጅን የትራንስሚሽን መስመር ጥገና ሠራተኛ የሆነው ባልደረባችን እሸቱ ገዛኸኝ የራይቱ ጎዴ 230ኪቮ መስመር የፍተሻ ስራ በተሰማራበት ህይወቱ አልፏል።
የኢትዮጲያ ኤሌክትሪክ ኃይል ማኔጅመንትና ሰራተኞች በሙሉ በደረሰው ህልፈት የተሰማቸውን ሐዘን እየገለፁ ለቤተሰቦቹና ወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን ይመኛሉ።
ግንቦት 27 ቀን 2012 ዓ/ም
15 525
የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የሶስትዮሽ ድርድር ለማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ስለሺ በቀለ ከሱዳን አቻቸው ፕሮፌሰር ያሲር አባስ ሞሐመድ ጋር በቪዲዮ ተወያይተዋል።
የውይይቱ ትኩረት የሶስትዮሽ ድርድሩ እንደገና ስለሚጀምርበት እና ግድቡን በተመለከተ ጉዳዮች እንዲሁም ሁለቱ ሀገራት ከድርድሩ ጋር የተያያዙና ያልተፈቱ ጉዳዮችን የተመለከተ ነበር።
ሁለቱ ወገኖች የሁለትዮሽ ስብሰባዎችን በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ የሶስትዮሽ ስብሰባው በቶሎ እንዲጀመር ለማድረግ መስማማታቸውን ሚኒስቴሩ በማህበራዊ ሚዲያ ገፁ ላይ አስፍሯል።
15 525
በኢትዮጵያ እስከትናንትና ድረስ(ዛሬን ሳይጨምር) በቫይረሱ ከተያዙት 365 ሰዎች መካከል 228 ሰዎች የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ናቸው፡፡
ዛሬ በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠው 24 ሰዎች ሲሆኑ 7 ከትግራይ 8 ከአማራ ክልል የተቀሩት ዘጠኙ ደግሞ ከአዲስ አበባ ናቸው፡፡
በቫይረሱ ከተያዙት ውስጥ 93 በመቶው በልደታና በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ይገኛሉ።
ከ228ቱ ሰዎች መካከል 40 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ በልደታ ክፍለ ከተማ የሚኖሩ ናቸው።
አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በመዲናዋ በሁለተኛ ደረጃ ከፍተኛ የቫይረሱ ስርጭት የሚታይበት ነው፡፡
በቫይረሱ ከተያዙት ሰዎች መካከል 56ቱ ወይም 16 በመቶዎቹ ምንም ዓይነት የጉዞ ታሪክ የሌላቸውና በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ጋር ንክኪ የሌላቸው ናቸው፡፡
በእነዚህና በሌሎችም የነዋሪዎች ጥግግት ከፍተኛ በሆነባቸው የከተማዋ ክፍሎች ከዚህ የሚልቅ ቁጥር ያለው ሰው በቫይረሱ ሳይጠቃ እንደማይቀር ይታመናል፡፡
ሰርግና ለቅሶ ለቫይረሱ ስርጭት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረጉ በመሆኑ ኅብረተሰቡ እንዲህ ያሉ ማኅበራዊ ክንውኖችን ማስቀረት እንዳለበት መልዕክት ተላልፏል።
15 525
ተቋሙ ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ ግብዓቶችን በስጦታ አገኘ
.....................///////.........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከቻይናው ኤን አር ኤሌክትሪክ ኃላፊነቱ የተወሰነ ኩባንያ (NR Electric Co.LTD) የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚያግዙ ግብዓቶችን በስጦታ አገኘ።
ኤን አር ኤሌክትሪክ ኃላፊነቱ የተወሰነ ኩባንያ ኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚያግዙ 700 የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብሎች (ማስኮች) እና ሁለት የሙቀት መለኪያ መሳሪያዎችን (ቴርሞሜትር) ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ድጋፍ አድርጓል፡፡
ግብዐቶቹን የተረከቡት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጀነሬሽን ኦፕሬሽን ግዥ ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ጀማል አህመድ እንደተናገሩት ድርጅቱ የኃይል ማመንጫ መለዋወጫ ዕቃዎችን በማቅረብ የሚታወቅና ከተቋማችን ጋር የረጅም ጊዜ ግንኙነት ያለው ነው።
አሁን የተላኩት የስጦታ ዕቃዎች በቁጥር አነስተኛ ቢሆኑም ኩባንያው በቀጣይ የተለያዩ የመከላከያ ግብዓቶችን ለመለገስ ቃል መግባቱን አቶ ጀማል ገልፀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከተለያዩ ድርጅቶች የኮሮና ቫይረስን መከላከል የሚያስችሉ ግብዓቶችን በስጦታ ማግኘቱ ወረርሽኙን ለመከላከል ለሚያደርገው ጥረት የጎላ ጠቀሜታ የሚኖራቸው መሆኑ ይታመናል፡፡
ግንቦት 07 ቀን 2012 ዓ.ም
15 525
የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሠራተኞች ከ386ሺህ ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ
…………….///////………...
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሠራተኞች ለጌርጌሴኖን የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ከ386ሺህ ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ ፡፡
የፕሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ አቶ መብራቱ ተሾመ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት እንደተናገሩት የኮይሻ የውሃ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሠራተኞች ያደረጉት ድጋፍ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ላቀረቡት የማእድ ማጋራት ጥሪ የተሰጠ ምላሽ ነው፡፡
የፕሮጀክቱ ሰራተኞች የወገን ደራሹ ወገን ነው በማለት በራሳቸው ተነሣሽነትና በበጎ ፈቃድ 386,810 ብር ገንዘብ በማሰባሰብ ለጌርጌሴኖን የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ድጋፍ ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡
የኮረና ቫይርስ በህብረተሰቡ ድጋፍ የሚቀሳቀሱ እንደ ጌርጌሴኖን የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ያሉ ተቋማትን እየጎዳ በመሆኑ ሌሎች ተቋማትና የህብረተሰብ ክፍሎችም ድጋፋቸውን አጠናክረው በመቀጠል ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባም አቶ መብራቱ ገልፀዋል፡፡
የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት መሰረታዊ የሰራተኞች ማህበር ሊቀ መንበር አቶ ተስፋዬ ጥላሁን በበኩላቸው ሁሉም የፕሮጀክቱ ሰራተኞች ሀገራዊ የመረዳዳት እሴቶችን በተግባር ለማሳየት በበጎ ፍቃድ እንደ አቅማቸው በማዋጣት ድጋፉ መሰብሰቡን ተናግረዋል፡፡ አቶ ተስፋዬ ገለፃ ሰራተኛው ይህን መሰል ድጋፎችንም በቀጣይም አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
የጌርጌሴኖን የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል መስራችና ስራ አስኪያጅ አቶ መለሰ አየለ ድጋፉን በተረከቡበት ወቅት እንደተናገሩት ህብረተሰቡ ወደ ማዕከሉ እየመጣ ያደርግ የነበረው ድጋፍ በአሁኑ ወቅት ቀንሷል፡፡
ይህን ተከትሎ ማእከሉ አንዳንድ ክፍተቶች እየገጠሙን በመሆኑ የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሰራተኞች ያደረጉት ድጋፍ ያጋጠሙንን ክፍተቶች ለመሙላት ያግዘናል ብለዋል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ https://www.facebook.com/Ethioelectric/posts/529697681038403
ግንቦት 01 ቀን 2012 ዓ.ም.
15 525
ለአዋሽ ወልዲያ ሀራ ገበያ የባቡር መስመር የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የአቅም ማሳደጊያ ግንባታ ስምምነት ተፈረመ
.............////////...............
ለአዋሽ- ወልዲያ ሀራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት የኃይል አቅርቦት የሚያገለግል የአራት የከፍተኛ የኤሌክትሪክ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፍያና አቅም ማሳደግያ ግንባታ ስራ ለማከናወን የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ፡፡
ስምምነቱ ለባቡር ፕሮጀክቱ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል ባለ 230/132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ማስፋፍያና የአቅም ማሳደግያ ግንባታ ነው።
ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የቻይናው ቲቢኢኤ ኩባንያ ተወካይ ሚስተር ሃኦ(Hao Dong) ዶንግ ተፈራርመዋል፡፡
የባቡር ፕሮጀክቱ ካለው ሃገራዊ ጠቀሜታ አኳያ የፕሮጀክቱ ግንባታ ስራ በተያዘለት የጊዜ መርሃ ግብር ጥራቱን ጠብቆ መጠናቀቅ እንዳለበት ዋና ስራ አስፈፃሚው አሳስበዋል፡፡
መንግስት የተጀመሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ለመጨረስ በሰጠው ትኩረት መሰረት የፕሮጀክቱ የኃይል አቅርቦት አጠቃላይ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት እንዲሸፈን መደረጉን ኢንጂነር አሸብር ተናግረዋል፡፡
የስራ ተቋራጩ ተወካይ ሚስተር ሃኦ በበኩላቸው የፕሮጀክቱን አስፈላጊነት ስለተገነዘብን ፕሮጀክቱን በተያዘለት የጊዜ ገደብ ፣ ጥራቱን ጠብቆ እንዲጠናቀቅ በትኩረት እንሰራለን ብለዋል፡፡
ፕሮጀክቱ በነባሮቹ የመተሃራ፣ የደብረ ብርሃን፣ የሸዋ ሮቢትና የከሚሴ ባለ 132 ኪ.ቮ. የከፍተኛ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የማስፋፊያና አቅም የማሳደግ ግንባታ ስራዎችን ያጠቃልላል፡፡
ለፕሮጀክቱ ግንባታ ስራዎችን ሰርቶ ለማጠናቀቅ 5 ነጥብ 3 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር እና 41 ሚሊየን ብር ተበጅቶለታል፡፡
አጠቃላይ ግንባታውም በ12 ወራት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ለአዋሽ- ወልዲያ ሀራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት የኃይል አቅርቦት የሚያገለግል ፋይናንስ አቅርቦት በማን ይሸፈን የሚለው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልንና የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽንን ሲያወዛግብ መቆየቱ የሚታወስ ነው።
በሌላ በኩል የባቡር ፕሮጀክቱ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ ግንባታ ስምምነት በጨረታው ካሸነፈው ተቋራጭ ጋር በቅርቡ እንደሚፈረምና ግንባታው እንደሚጀመር ይጠበቃል።
ሚያዚያ 30 ቀን 2012 ዓ/ም
15 525
የህዳሴ ግድብ በመጪው ክረምት ውሃ ለመያዝ የሚያስችለው ከፍታ ላይ እንዲደርስ እየተሰራ ነው - ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ
..................///////...................
በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የግንባታ ቦታ የሚመለከታቸው የመንግስት፣ የተቋራጮችና አማካሪዎች የስራ ሀላፊዎች ጋር የስራ ግምገማና ጉብኝት ማድረጋቸውን የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ገልፀዋል፡፡
ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በትዊተር ገፃቸው እንዳሰፈሩት የግድቡ ግንባታ እየተፋጠነ ይገኛል፡፡
በመጪው ክረምት ውሃ ለመያዝ እንዲያስችለው ከባህር ጠለል በላይ ከ525 ሜትር ከፍታ ወደ 534 ሜትር ማደጉን አስታውቀዋል።
እሰከ ሰኔ ወር መጨረሻ ሳምንት 572 ሜትር እንዲደርስ እየተሰራ ይገኛልም ብለዋል።
ላለፉት አምስት ዓመታት 525 ሜትር ላይ ከነበረበት ወደሚፈለገው ደረጃ የማሳደጉ ስራ በቅርቡ የውሃ መያዝ የመቻላችን ጉዳይ ብርቱ ማሳያ መሆኑንም ነው ያመለከቱት።
ከዚህም ውጤት ለመድረስ ወደ ኋላ የሚመልሰን ነገር አይኖርም ያሉት ሚኒስትሩ፥ የብረት ስራዎች፣ የትላልቅ ውሃ ማስተላለፊያ በሮች ተከላ፣ የተርባይንና ጀነሬተሮች ተከላ እና ሌሎች ስራዎች በእቅድ እየተከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል።
መፍጠን ያለባቸውን አስፈላጊ ስራዎች በመገምገም የማሻሻያ ውሳኔዎች መደረጋቸውን አመልክተዋል።
በግድቡ ግንባታ ስፍራም 24 ሰዓት እየተጉ ላሉ ባለሙያዎች ሚኒስትሩ ምስጋና አቅርበዋል።
ሚያዚያ 25 ቀን 2012 ዓ.ም
15 525
በገባነው ቃል መሰረት ፈተናዎችን አልፈን የቅድመ ማመንጨት ሂደቱን እውን እናደርጋለን - ዶ/ር አብርሃም በላይ።
የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በመጪው ክረምት ውሃ ለመያዝ በሚያስችለው ደረጃ ላይ ይገኛል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትርና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር አብርሃም በላይ፣ የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ስለሺ በቀለ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ አባል አምባሳደር ግርማ ብሩና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር በላይ በፕሮጀክቱ ስፍራ በመገኘት የግንባታውን ሂደት ገምግመዋል።።
ከግንባታው ተቋራጮች ጋር በግንባታው ሂደት ዙሪያ በዝርዝር ተወያይተው ግድቡን በመጎብኘት ግንባታው ውሃ ለመያዝ በሚያስችል ደረጃ ላይ እንደደረሰ አረጋግጠዋል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትርና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር አብርሃም በላይ ግንባታው በብዙ ፈተናዎች የታጀበ ቢሆንም ለህዝባችን በገባነው ቃል መሰረት ፈተናዎችን አልፈን የቅድመ ማመንጨት ሂደቱን እውን እናደርጋለን ብለዋል።
የተቋሙ የስራ አመራር ቦርድና ማኔጅመንት የግንባታ ሂደቱን በየወሩ በቦታው እየተገኘ የሚገመግም ሲሆን የኮሮና ቫይረስ በሀገራችን መከሰቱ ይፋ ከተደረገ በኋላ የአሁኑ የመጀመሪያው ነው።
ሚያዚያ 24 ቀን 2012 ዓ/ም
15 525
ተቋሙ የአፍና አፍንጫ መከላከያ ጭምብል በስጦታ አገኘ
...............////////..........
የቻይና ኤሌክትሪክ ዕቃዎች አቅራቢ (CET) ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሃያ ሺህ የአፍና አፍንጫ መከላከያ ጭምብል በስጦታ አበረከተ።
የአፍና አፍንጫ መከላከያ ጭምብሉ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል አስተዋጽኦ እንደሚኖረው በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ ተገልጿል።
ከዚህ ቀደም ሲል ከተቋማችን ጋር የተለያዩ ስራዎችን የሰሩ ሁለት ተቋማት የኮረና መከላከያ ግብዓቶች መለገሳቸውን መዘገባችን ይታወሳል።
ሚያዚያ 23 ቀን 2012 ዓ/ም
15 525
የከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ እና ማስተላለፊያ መስመር ለመገንባት ስምምነት ተፈረመ
……………….//////…………..
ለጊምቢ ቱሉ ካፒ የወርቅ ማዕድን የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል ባለ 132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያና ማስተላለፊያ መስመር ለመገንባት ስምምነት ተፈርሟል፡፡
ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የሲኖ ሃይድሮ ኩባንያ ተወካይ ሚስተር ቲያን ሆንጉአን ተፈራርመዋል፡፡
መንግስት ለዚህ ፕሮጀክት ልዩ ትኩረት በመስጠት የፕሮጀክቱን አጠቃላይ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት እንዲሸፈን ማድረጉን ኢንጂነር አሸብር ተናግረዋል፡፡
የወርቅ ማዕድኑ ከሚያስገኘው የውጭ ምንዛሬ አንፃር የፕሮጀክቱ ግንባታ በተያዘለት የጊዜ መርሃ ግብር ጥራቱን ጠብቆ መጠናቀቅ እንዳለበትም ዋና ስራ አስፈፃሚው አሳስበዋል፡፡
የስራ ተቋራጩ ተወካይ ሚስተር ቲያን በበኩላቸው የፕሮጀክቱን አስፈላጊነት ስለተገነዘብን ፕሮጀክቱን በተያዘለት የጊዜ ገደብ እና ጥራት ለማጠናቀቅ በትኩረት እንሰራለን ብለዋል፡፡
ለፕሮጀክቱ ግንባታ 5 ነጥብ 6 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር እና 121 ሚሊየን ብር ተበጅቶለታል፡፡
ፕሮጀክቱ አንድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና 40 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው ባለ 132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታን ያጠቃልላል፡፡
አጠቃላይ ግንባታውም በ13 ወራት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ሚያዚያ 22 ቀን 2012 ዓ.ም
15 525
የአሰላ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ለመገንባት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ
…………………………///////……………………
100 ሜጋ ዋት እንዲያመነጭ ታስቦ በአርሲ ዞን ሂጦሳ ወረዳ ኢተያ የሚገነባውን የአሰላ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ለማስጀመር የሚያስችል ስምምነት ተፈርሟል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ በስምምነት ሰነዱ ላይ ፊርማቸውን ካኖሩ በኋላ እንደገለፁት የአሰላ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ ከተገነቡት የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች መካከል አነስተኛ ቁጥር ያላቸው ተርባይኖችን በመጠቀም ከፍተኛ ኤነርጂ የሚያመርት መሆኑ የተለየ ያደርገዋል፡፡
እንደ አቶ አሸብር ገለፃ በፕሮጀክቱ እያንዳንዳቸው 3 ነጥብ 45 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው 29 ተርባይኖች ይተከላሉ፡፡
ለንፋስ ኃይል ማመንጫው የሚውለውን ገንዘብ የዴንማርክ መንግስት በስጦታና በብድር እንደሚሸፍን፣ ለ20 ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና እንደሚሰጥና ለአምስት ዓመት የኦፕሬሽንና የጥገና ስራ እንደሚሰራ ስምምነት ላይ መደረሱን ስራ አስፈፃሚው ተናግረዋል፡፡
ፕሮጀክቱን በተቋራጭነት የዴንማርክና ስፔን ጥምር ኩባንያ የሆነው ሲመንስ ጋሜሳ ሪኒውኤብል ኢነርጂ ሲገነባው የዴንማርኩ ኮዊ ደግሞ በአማካሪነት እንዲሰራ ተመርጧል፡፡
የፊርማ ስነስርዓቱ ተዋዋይ ወገኖች በአካል ሳይገናኙ በቨርቹዋል የተከናወነ ሲሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ከአዲስ አበባ ፤ የዴንማርክና ስፔን ጥምር ኩባንያ የሆነው ሲመንስ ጋሜሳ ሪኒውኤብል ኢነርጂ ደግሞ ከአውሮፓ በመሆን ስካን በተደረገው የስምምነት ሰነድ ላይ ፊርማቸውን አኑረዋል፡፡
በ145 ሚሊየን ዩሮ የሚገነባውን የአሰላ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ለማጠናቀቅ 25 ወራት ተይዘውለታል፡፡
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
